ሙዚቀኛ ኤልያስ መልካ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
የሙዚቃ አቀናባሪው፣ የግጥም እና ዜማ ደራሲው፣ ጊታሪስቱ፣ ፒያኒስቱ ኤልያስ መልካ ከ40 በላይ አልበሞችን እንዳቀናበረ ይነገርለታል፡፡በዘመናዊ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ላይ አይረሴ አሻራውን ያኖረው ኤልያስ መልካ የኩላሊት እና የስኳር ሕመም ገጥሞት ሕክምናውን ሲከታተል ነበር፤ትናንት ለሊት ባጋጠመው ድንገተኛ ሕመም ወደ ሆስፒታል ተወስዶ በዚያው ሕይወቱ ማለፉን ለመረዳት ችለናል።ሸገር በሙዚቀኛ ኤልያስ መልካ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን እየገለፀ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ፣ ለጥበብ ወዳጆቹ፣ ለአድናቂዎቹ መፅናናትን ይመኛል፡፡
Via Sheger
@YeneTube @FikerAssefa
የሙዚቃ አቀናባሪው፣ የግጥም እና ዜማ ደራሲው፣ ጊታሪስቱ፣ ፒያኒስቱ ኤልያስ መልካ ከ40 በላይ አልበሞችን እንዳቀናበረ ይነገርለታል፡፡በዘመናዊ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ላይ አይረሴ አሻራውን ያኖረው ኤልያስ መልካ የኩላሊት እና የስኳር ሕመም ገጥሞት ሕክምናውን ሲከታተል ነበር፤ትናንት ለሊት ባጋጠመው ድንገተኛ ሕመም ወደ ሆስፒታል ተወስዶ በዚያው ሕይወቱ ማለፉን ለመረዳት ችለናል።ሸገር በሙዚቀኛ ኤልያስ መልካ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን እየገለፀ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ፣ ለጥበብ ወዳጆቹ፣ ለአድናቂዎቹ መፅናናትን ይመኛል፡፡
Via Sheger
@YeneTube @FikerAssefa
በአፋር ክልል የቀድሞ ባለስልጣናት እና ግለሰቦች እየታሰሩ ነው!
ከስፍራው የደረሰኝ መረጃ እንደሚያመለክተው በአፋር ክልል በተለይ በአሳይታ እና ሎጊያ ከተሞች አንዳንድ የቀድሞ የክልሉ ባለስልጣናት፣ ነጋዴዎች እና ሌሎች ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው። የእስሩ ምክንያት በግልፅ ባይታወቅም በክልሉ ከሚወጣው የጨው ምርት ጋር ተያይዞም በርካታ እስር እንደተከናወነ ታውቋል። ባለፈው ሳምንት አንዳንድ የክልሉ መሪ ፓርቲ የቀድሞ ባለስልጣናትም ከአውሮፕላን ማረፊያ ጭምር እየተያዙ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
Via Elias Meseret
@YeneTube @FikerAssefa
ከስፍራው የደረሰኝ መረጃ እንደሚያመለክተው በአፋር ክልል በተለይ በአሳይታ እና ሎጊያ ከተሞች አንዳንድ የቀድሞ የክልሉ ባለስልጣናት፣ ነጋዴዎች እና ሌሎች ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው። የእስሩ ምክንያት በግልፅ ባይታወቅም በክልሉ ከሚወጣው የጨው ምርት ጋር ተያይዞም በርካታ እስር እንደተከናወነ ታውቋል። ባለፈው ሳምንት አንዳንድ የክልሉ መሪ ፓርቲ የቀድሞ ባለስልጣናትም ከአውሮፕላን ማረፊያ ጭምር እየተያዙ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
Via Elias Meseret
@YeneTube @FikerAssefa
“‘የቅማንት የራስ አስተዳደር ጥያቄ አልተመለሰም’ የሚሉ አካላት ትክክል አይድሉም ጥያቄዉ እንደተመለሰላቸዉ የፌዴሬሽን ም/ቤት ተቀብሎ አጽድቋል" አቶ ወርቁ አዳሙ በፌዴሬሽን ም/ቤት የሕገ መንግሥት ትርጉምና የማንነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጽ/ቤት ኃላፊ
"‘ሌሎች ተጨማሪ ሦስት ቀበሌዎች ወደ ቅማንት ይካለሉ’ የሚሉ ጥያቄዎችም ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ቀርበዋል፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤትም የጥናት ቡድን ልኮ ቀበሌዎቹ ኩታ-ገጠም አለመሆናቸዉን አረጋግጧል፤ ስለዚህ ጥያቄያቸው ተገቢ አይደለም ተብሏል”
Via Ethiopia Live Updates
@YeneTube @FikerAssefa
"‘ሌሎች ተጨማሪ ሦስት ቀበሌዎች ወደ ቅማንት ይካለሉ’ የሚሉ ጥያቄዎችም ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ቀርበዋል፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤትም የጥናት ቡድን ልኮ ቀበሌዎቹ ኩታ-ገጠም አለመሆናቸዉን አረጋግጧል፤ ስለዚህ ጥያቄያቸው ተገቢ አይደለም ተብሏል”
Via Ethiopia Live Updates
@YeneTube @FikerAssefa
ተማሪዎች ከተመደቡበት ዩኒቨርስቲ ወደሌላ ዩኒቨርስቲ መቀያየር እንደማይችሉ ተገለፀ።
ማንኛውም ተማሪ ከተመደበበት ዩኒቨርስቲ ወደሌላ ዩኒቨርስቲ መቀያየር እንደማይችል የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። ከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ድልድል ተጠናቆ ትናንት ይፋ መደረጉ አይዘነጋም፡፡
ምንጭ: ETV
@YeneTube @FikerAssefa
ማንኛውም ተማሪ ከተመደበበት ዩኒቨርስቲ ወደሌላ ዩኒቨርስቲ መቀያየር እንደማይችል የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። ከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ድልድል ተጠናቆ ትናንት ይፋ መደረጉ አይዘነጋም፡፡
ምንጭ: ETV
@YeneTube @FikerAssefa
የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች በመዋሃድ በሚመሰርቱት አዲስ ድርጅት ውስጥ ህወሃት እንደማይኖርበት የአዴፓ ም/ሊቀመንበር አቶ ዮሐንስ ቧያለው ተናገሩ።
አቶ ዮሀንስ በኢህአዴግ ውህደት ዙሪያ ከክልሉ የካቢኔ አባላት አባላትና የፀጥታ አመራሮች ጋር በተወያዩበት ወቅት ''ኢህአዴግን በምናፈርስበትንና ሌላ ውህድ ፓርቲ በምንመሰርትበት ሁኔታ ተግባብተናል። በውስጣችን ሆኖ ኢትዮጵያን ከሚያሸብረው ድርጅት ጋር እንደምንፋታም ተመሳሳይ አቋም ይዘናል ሲሉ ተደምጠዋል።አቶ ዮሃንስ አዴፓ ውህደቱ በፍጥነት እንዲፈጸም እንደሚፈልግም የገለጹ ሲሆን፣ ይህ የማይሆን ከሆነ ግን "በህዝቦች ደም በተጨማለቀው ኢህአዴግ ጥላ ስር ያውም 'ከትህነግ' ጋር አብሮ አይቀመጥም የጋራ ውሳኔም አያሳልፍም'' በማለት ከኢህአዴግ ራስን በማግለል ''ከሚመስሉን ጋር እንወሃዳለን'' ብለዋል።
ምንጭ:Ethiopia Live Updates
@YeneTube @FikerAssefa
አቶ ዮሀንስ በኢህአዴግ ውህደት ዙሪያ ከክልሉ የካቢኔ አባላት አባላትና የፀጥታ አመራሮች ጋር በተወያዩበት ወቅት ''ኢህአዴግን በምናፈርስበትንና ሌላ ውህድ ፓርቲ በምንመሰርትበት ሁኔታ ተግባብተናል። በውስጣችን ሆኖ ኢትዮጵያን ከሚያሸብረው ድርጅት ጋር እንደምንፋታም ተመሳሳይ አቋም ይዘናል ሲሉ ተደምጠዋል።አቶ ዮሃንስ አዴፓ ውህደቱ በፍጥነት እንዲፈጸም እንደሚፈልግም የገለጹ ሲሆን፣ ይህ የማይሆን ከሆነ ግን "በህዝቦች ደም በተጨማለቀው ኢህአዴግ ጥላ ስር ያውም 'ከትህነግ' ጋር አብሮ አይቀመጥም የጋራ ውሳኔም አያሳልፍም'' በማለት ከኢህአዴግ ራስን በማግለል ''ከሚመስሉን ጋር እንወሃዳለን'' ብለዋል።
ምንጭ:Ethiopia Live Updates
@YeneTube @FikerAssefa
የኢሬቻ በዓል በሰላም መከበሩን ፖሊስ አስታወቀ!
በርካታ ህዝብ የታደመበት እና በመስቀል አደባባይ የተከበረው የኢሬቻ በዓል በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ ለዚህም ህብረተሰቡ ላደረገው ቀና ትብብር ኮሚሽኑ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ ኮሚሽኑ በዓሉ በሰላም እንዲከበር ከሀገር መከላከለያ፣ ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ ከኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራቱን ገልጿል፡፡
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
በርካታ ህዝብ የታደመበት እና በመስቀል አደባባይ የተከበረው የኢሬቻ በዓል በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ ለዚህም ህብረተሰቡ ላደረገው ቀና ትብብር ኮሚሽኑ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ ኮሚሽኑ በዓሉ በሰላም እንዲከበር ከሀገር መከላከለያ፣ ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ ከኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራቱን ገልጿል፡፡
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
ኦሮምኛ፣ ሶማልኛና ትግርኛ የፌዴራል የስራ ቋንቋ ሊሆኑ ነው።
ሰሞኑን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከOBN ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ከአማርኛ ቋንቋ በተጨማሪ የፌዴራል የስራ ቋንቋዎችን ለመጨመር እንደታቀደ ከሚጨመሩትም መካከል ኦሮምኛ አንዱ እንደሆነ ቢናገሩም ሌሎቹ የሚጨመሩ ቋንቋዎች የትኞች እንደሆኑ አልተናገሩም ነበር።ነገር ግን አዲስ ማለዳ በዛሬ እትሙ ሶማሊኛና ትግርኛ ከሚጨመሩት ቋንቋዎች መካከል እንደሆኑ ይዞ ወጥቷል ።
@YeneTube @FikerAssefa
ሰሞኑን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከOBN ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ከአማርኛ ቋንቋ በተጨማሪ የፌዴራል የስራ ቋንቋዎችን ለመጨመር እንደታቀደ ከሚጨመሩትም መካከል ኦሮምኛ አንዱ እንደሆነ ቢናገሩም ሌሎቹ የሚጨመሩ ቋንቋዎች የትኞች እንደሆኑ አልተናገሩም ነበር።ነገር ግን አዲስ ማለዳ በዛሬ እትሙ ሶማሊኛና ትግርኛ ከሚጨመሩት ቋንቋዎች መካከል እንደሆኑ ይዞ ወጥቷል ።
@YeneTube @FikerAssefa
#NewsAlert
የታጠቁ አካላት በኤፍራታና ግድም ወረዳ ተኩስ ከፍተው አካባቢውን ለመረበሽ ያደረጉት ሙከራ መክሸፉን የወረዳው አስተዳድርና ፀጥታ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቁ የታጠቁ ኃይሎች በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ ከተራራ ሥፍራ በመሆን ወደ አጣዬ ከተማ በመተኮስ የአካባቢውን ሰላም እየረበሹ መሆኑን የወረዳው አስተዳድርና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው የሽጥላ ገልፀዋል።አቶ ጌታቸው እንዳስታወቁት ከተራራ ወደ ከተማዋው በተከፈተው ተኩስ ስጋት የአጣዬ ቅዳሜ ገበያ ተበትኗል፤ ነዋሪውም እየተረበሸ ነው።
የአማራ ክልል ልዩ ኃይልና የመከላከያ ሠራዊት ሕዝቡን ለማረጋጋት እየሠሩ እንደሆነም ኃላፊው አስታውቀዋል። የታጠቁ ኃይሎቹ በርከት ያሉ መሆናቸውንና በብዙ አቅጣጫ እንደሚተኩሱ ከመግለጻቸው ባለፈ ማንነታቸውና በሰው ላይ ያደረሱት ጉዳት ስለመኖሩ አልተገለጸም።
የሰሜን ሸዋ ዞን የሠላምና ደኅንነት ግንባታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ካሳሁን እምቢያለ ግን የታጠቁ ቡድኖቹ በልዩ ኃይል ላይ ጥቃት ሊፈጽሙ መሞከራቸውንና በአጸፋው ከጥፋት ኃይሎቹ አንዱ መገደሉን አስታውቀዋል። መምሪያው ሁኔታው ወደ መረጋጋት መመለሡንም አስታውቋል። አካባቢውን ልዩ ኃይል፣ ፌዴራል ፖሊስና መከላከያ ሠራዊት መቆጣጠሩም ተብራርቷል።በኤፍራታና ግድም የተከሰተው ሁኔታ ከሰሞኑ በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አጋጥሞ እንደነበር ከተገለጸው ክስተት ጋር የማይገናኝ ስለመሆኑም የመምሪያው ኃላፊ አስታውቀዋል።
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
የታጠቁ አካላት በኤፍራታና ግድም ወረዳ ተኩስ ከፍተው አካባቢውን ለመረበሽ ያደረጉት ሙከራ መክሸፉን የወረዳው አስተዳድርና ፀጥታ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቁ የታጠቁ ኃይሎች በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ ከተራራ ሥፍራ በመሆን ወደ አጣዬ ከተማ በመተኮስ የአካባቢውን ሰላም እየረበሹ መሆኑን የወረዳው አስተዳድርና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው የሽጥላ ገልፀዋል።አቶ ጌታቸው እንዳስታወቁት ከተራራ ወደ ከተማዋው በተከፈተው ተኩስ ስጋት የአጣዬ ቅዳሜ ገበያ ተበትኗል፤ ነዋሪውም እየተረበሸ ነው።
የአማራ ክልል ልዩ ኃይልና የመከላከያ ሠራዊት ሕዝቡን ለማረጋጋት እየሠሩ እንደሆነም ኃላፊው አስታውቀዋል። የታጠቁ ኃይሎቹ በርከት ያሉ መሆናቸውንና በብዙ አቅጣጫ እንደሚተኩሱ ከመግለጻቸው ባለፈ ማንነታቸውና በሰው ላይ ያደረሱት ጉዳት ስለመኖሩ አልተገለጸም።
የሰሜን ሸዋ ዞን የሠላምና ደኅንነት ግንባታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ካሳሁን እምቢያለ ግን የታጠቁ ቡድኖቹ በልዩ ኃይል ላይ ጥቃት ሊፈጽሙ መሞከራቸውንና በአጸፋው ከጥፋት ኃይሎቹ አንዱ መገደሉን አስታውቀዋል። መምሪያው ሁኔታው ወደ መረጋጋት መመለሡንም አስታውቋል። አካባቢውን ልዩ ኃይል፣ ፌዴራል ፖሊስና መከላከያ ሠራዊት መቆጣጠሩም ተብራርቷል።በኤፍራታና ግድም የተከሰተው ሁኔታ ከሰሞኑ በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አጋጥሞ እንደነበር ከተገለጸው ክስተት ጋር የማይገናኝ ስለመሆኑም የመምሪያው ኃላፊ አስታውቀዋል።
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 63 በነርሲንግና በህክምና ዶክትሬት ድግሪ ያሰለጠናቸውን ዕጩ ምሩቃንን በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
ሀዋሳ ዩንቨርስቲ አዲስ የተመደባቹ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ መስከረም 27-29 እንደሆነ ዩንቨርስቲው አሻሽሎ ባወጣው ማስታወቂያ አሳስቧል!
ከዚህም በተጨማሪ አምና 1ኛ አመት ተማሪ የነበራችሁና በተለያየ ምክንያት
ትምህርታቹን ያቋረጣችሁ ነገር ግን የመልሶ ቅበላውን መስፈርት የምታሟሉ በተጠቀሰው ቀን ቀርባችሁ እንድትመዘገቡ ተብላቿል።
@YeneTube @FikerAssefa
ከዚህም በተጨማሪ አምና 1ኛ አመት ተማሪ የነበራችሁና በተለያየ ምክንያት
ትምህርታቹን ያቋረጣችሁ ነገር ግን የመልሶ ቅበላውን መስፈርት የምታሟሉ በተጠቀሰው ቀን ቀርባችሁ እንድትመዘገቡ ተብላቿል።
@YeneTube @FikerAssefa
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በ2012 ትምህርት ዘመን ለመደበኛ አዲስ ገቢ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ለውጥ ማድረጉን አሳውቋል!
በዚህም መሰረት ከዚህ በፊት ከመስከረም 27 እና 28 የነበረው ወደ ጥቅምት 03 እና 04 2012 ዓ.ም መለወጡን ለማወቅ ችለናል።ለበለጠ መረጃ ከላይ የተለጠፈውን ያንብቡት።
@YeneTube @FikerAssefa
በዚህም መሰረት ከዚህ በፊት ከመስከረም 27 እና 28 የነበረው ወደ ጥቅምት 03 እና 04 2012 ዓ.ም መለወጡን ለማወቅ ችለናል።ለበለጠ መረጃ ከላይ የተለጠፈውን ያንብቡት።
@YeneTube @FikerAssefa
በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ የጦር መሣሪያ በቁጥጥር ሥር ዋለ።
በጎንደር ከተማ በሕገወጥ መንገድ በነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ውስጥ ሲጓጓዝ የነበረ የጦር መሣሪያ በቁጥጥር ሥር ውሏል። የመሣሪያዎቹ ዓይነት፣ ብዛት እና መሠል ዝርዝር መረጃ እንደደረሰን እናቀርባለን።
ምንጭ: አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
በጎንደር ከተማ በሕገወጥ መንገድ በነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ውስጥ ሲጓጓዝ የነበረ የጦር መሣሪያ በቁጥጥር ሥር ውሏል። የመሣሪያዎቹ ዓይነት፣ ብዛት እና መሠል ዝርዝር መረጃ እንደደረሰን እናቀርባለን።
ምንጭ: አብመድ
@YeneTube @FikerAssefa
"አከተመ በቃ" የኤልያስ መልካ የቀድሞ መምህር
መምህራኑ ጭምር «በልጅነቱ የነበረው ችሎታ የሚገርም ነበር» ሲሉ የሚመሰክሩለት ኤልያስ መልካ በ42 አመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ከ40 በላይ አልበሞች ከ400 በላይ ሙዚቃዎች እንደሰራ የሚነገርለት ኤልያስ ባለሙያዎች ፍትኃዊ ክፍያ ያገኙ ዘንድ እስከ ዕለተ ሞቱ ሲታገል ቆይቷል።
ሙሉውን ያንብቡ👇👇👇
https://telegra.ph/EliasMelka-10-05
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
መምህራኑ ጭምር «በልጅነቱ የነበረው ችሎታ የሚገርም ነበር» ሲሉ የሚመሰክሩለት ኤልያስ መልካ በ42 አመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ከ40 በላይ አልበሞች ከ400 በላይ ሙዚቃዎች እንደሰራ የሚነገርለት ኤልያስ ባለሙያዎች ፍትኃዊ ክፍያ ያገኙ ዘንድ እስከ ዕለተ ሞቱ ሲታገል ቆይቷል።
ሙሉውን ያንብቡ👇👇👇
https://telegra.ph/EliasMelka-10-05
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
[ Irreecha hora Finfinnee ]
የኢሬቻ በዓል አከባበር ልዩ ዝግጅት በቃላችን መሰረት የመጀመሪያ ቪዲዮ በየኔቲዩብ የዩቲዩብ ቻናል ላይ ለቀናል ተመልከቱት።
አዝናኝ እንዲሁም አስተማሪ የሆነ ቪዲዮ ነው
እንድትመለከቱት ጋብዘኖታል።
መልካም በዓል !!
ቪዲዮውን ለመመልከት ሊንኩን ⬇️⬇️⬇️
https://youtu.be/el-XLVO-ZGU
ከሆራ ፊንፊኔ ጋር የተያያዘ ቀጣይ ክፍል ሰኞ የሚለቀቅ ይሆናል።
💥እንዳይረሱ ሰብስክራይብ ማድረጎን!! 💥
@YeneTube @Fikerassefa
የኢሬቻ በዓል አከባበር ልዩ ዝግጅት በቃላችን መሰረት የመጀመሪያ ቪዲዮ በየኔቲዩብ የዩቲዩብ ቻናል ላይ ለቀናል ተመልከቱት።
አዝናኝ እንዲሁም አስተማሪ የሆነ ቪዲዮ ነው
እንድትመለከቱት ጋብዘኖታል።
መልካም በዓል !!
ቪዲዮውን ለመመልከት ሊንኩን ⬇️⬇️⬇️
https://youtu.be/el-XLVO-ZGU
ከሆራ ፊንፊኔ ጋር የተያያዘ ቀጣይ ክፍል ሰኞ የሚለቀቅ ይሆናል።
💥እንዳይረሱ ሰብስክራይብ ማድረጎን!! 💥
@YeneTube @Fikerassefa
ከወደ ካይሮ የደረሰኝ ሰበር መረጃ!
የግብፅ ፕረዚደንት ቢሮ ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው መግለጫ አሜሪካ በህዳሴ ግድብ ዙርያ የማደራደር ሚና እንድትጫወት እንደሚፈልግ ገልፁዋል!
ይህ መግለጫ የወጣው ለቀናት በካርቱም ሲካሄድ የነበረው የኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ የውሀ ሚኒስትሮች ውይይት ካለ ውጤት ዛሬ መጠናቀቁን ተከትሎ ነው። በዚህም ምክንያት ግብፅ አለም አቀፍ አደራዳሪዎች እንደሚያስፈልጉ ገልፃ ለዚህም አሜሪካንን እንዳጨች ተሰምቷል።
አሁን በደረሰኝ መረጃ ደግሞ የኢትዮጵያው ወሀ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ በካርቱም ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጡ ነው። ዝርዝሩ እንደደረሰኝ አቀርበዋለሁ።
Via :- Elias Meseret
@YeneTube @Fikerassefa
የግብፅ ፕረዚደንት ቢሮ ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው መግለጫ አሜሪካ በህዳሴ ግድብ ዙርያ የማደራደር ሚና እንድትጫወት እንደሚፈልግ ገልፁዋል!
ይህ መግለጫ የወጣው ለቀናት በካርቱም ሲካሄድ የነበረው የኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ የውሀ ሚኒስትሮች ውይይት ካለ ውጤት ዛሬ መጠናቀቁን ተከትሎ ነው። በዚህም ምክንያት ግብፅ አለም አቀፍ አደራዳሪዎች እንደሚያስፈልጉ ገልፃ ለዚህም አሜሪካንን እንዳጨች ተሰምቷል።
አሁን በደረሰኝ መረጃ ደግሞ የኢትዮጵያው ወሀ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ በካርቱም ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጡ ነው። ዝርዝሩ እንደደረሰኝ አቀርበዋለሁ።
Via :- Elias Meseret
@YeneTube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ መንግስት በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ አሞላል እና አለቃቀቅ ዙሪያ የተጀመረውን የሶስትዮሽ ቴክኒካዊ ምክክር ለማስቀጠል ቁርጠኛ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን የሶስተኛ ወገን ጣልቃ ገብነትን እንደማይደግፍ የኢትዮጵያው ውሃና ኢነርጂ ሚንስትር ተናግረዋል!
የግብጽ፣ ኢትዮጵያ እና ሱዳን የውሀ ጉዳይ ሚኒስትሮች መስከረም 5 እና 6 ቀን 2012 ዓ.ም በካይሮ ባካሄዱት ስብሰባ ባስቀመጡት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በካርቱም የሶስትዮሽ ስብሰባቸውን አካሂደዋል፡፡ ከሚኒስትሮቹ ስብሰባ አስቀድሞ የአገራቱ ገለልተኛ የሳይንሳዊ ጥናት ቡድን ከመስከረም 19 እስከ 22 ቀን 2012 ዓ.ም በካርቱም አምስተኛ ዙር ስብሰባውን አካሂዶ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክሯል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት በአገራቱ መካከል የሚደረገው ቴክኒካዊ ምክክር ብቸኛው የመፍትሄ አማራጭ በመሆኑ መቀጠል እንደሚኖርበት ያምናል፡፡የሳይንሳዊ ቡድኑ አራት ስብሰባዎችን አድርጎ አበረታች ውጤት እያሳየ ባለበት ወቅት ግብጽ በተናጠል ያቀረበችው የውሃ ሙሌት እና አለቃቀቅን የሚመለከተው ሰነድ ከትብብር ማዕቀፉ ውጪ የሆነ እና ሂደቱን ያናጠበ ሆኗል፡፡ ሆኖም የውሃ ሚኒስትሮች የኢትዮጵያ የውሃ ሙሌት እና አለቃቀቅ እቅድ፣ የግብጽ መንግስት የሚያቀርበው ሰነድ እንዲሁም ሱዳን በጉዳዩ ላይ የምታቀርበው ሰነድ ለሳይንሳዊ ቡድኑ ቀርቦ ዝርዝር ትንታኔ እንዲደረግበት እና ምክረ ሃሳብ እንዲቀርብለት በመስከረም ወር 2012 ዓ.ም በካይሮ በተደረገው ስብሰባ ወስነዋል፡፡
በካርቱም አራት ቀናትን ወስዶ በተካሄደው ስብሰባ የሳይንሳዊ ቡድኑ በመስከረም ወሩ የካይሮ ስብሰባ በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት የኢትዮጵያን የግድብ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ ዕቅድ፣ እንዲሁም ሱዳን እና ግብጽ ያቀረቡትን የሙሌት እና የውሃ አለቃቅ ቴክኒካዊ ጉዳዮችን የሚዳስሰውን ሃሳብ አዳምጦ ውይይቶችን አካሂዷል፡፡ ውይይቱ ሶስቱም ቡድኖች በተስማሙበት የርዕሰ ጉዳይ መዘርዝር ላይ የተመሰረተ ሲሆን በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ከመስማማት ተደርሶ በሌሎቹ ላይ የሃሳብ መለያየቶች ተመዝግበዋል፡፡
እነዚህ የሃሳብ #ልዩነቶች በሳይንሳዊ እና ጥናት ቡድኑ ውይይት እና ትንተና መግባባት ሊደረስባቸው የሚችሉ ናቸው፡፡ኢትዮጵያ ግድቡን እሰከ ሰባት አመት ድረስ በሚወስድ ሂደት ለመሙላት ያቀረበችው እቅድ የታችኛውን ተፋሰስ አገራት ጥቅም ለመጠበቅ ያላትን አቋም ያሳያል፡፡ ይህም በተጨማሪም ኢትዮጵያ እና ሱዳን ማናቸውም ቱክኒካዊ ጉዳዮች ለሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ ቀርበው ትንተና እንዲደረግባቸው ገንቢ እና አካታች የውይይት አካሄድ ቢከተሉም የግብጽ ወገን ያቀረብኳቸው ሃሳቦች በሙሉ ተቀባይነት ካላገኙ ውይይቱ ሊቀጥል አይችልም በሚለው የማያሰራ አቋሙ በመቀጠሉ የሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ ስራውን በተሟላ አኳኋን ማከናወን ሳይችል ቀርቷል፡፡ ይህ የግብጽ አቋም የሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ ስብሰባ እንዲሁም የሚኒስትሮች ስብሰባው ስምምነት በተደረሰባቸው ጉዳዮች ላይ ጭምር ሪፖርት እንዳያዘጋጁ አድርጓል፡፡
ይህ የግብጽ አካሄድ አዲስ ሳይሆን ከዚህ ቀደምም በግድቡ ላይ ሶስቱ አገራት ሊያከናውኑት የነበረውን የውሃ፣ የአካባቢያዊ እና ማህበራዊ ተጽእኖ ጥናት በግብጽ ወገን እንዲስተጓጎል በተደረገ ጊዜ የታየ የሳይንስ እና የምክክር የመፍትሄ አማራጭን የማፋለስ ዘዴ ነው፡፡
ኢትዮጵያ አለመግባባት መፍቻ ዘዴን የሚደነግገውን የመርህ መግለጫ ስምምነቱን አንቀጽ 10 ጠቅሶ መፍትሄ ለመፈለግ ጊዜው እንዳልሆነ እና ቴክኒካዊ ምክክሩ ሊቀጥል እንደሚገባ ታምናለች፡፡የውሃ ሚኒስትሮቹ በሁለት ቀናት ስብሰባቸው የሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ የደረሰበትን ተመልክተው አቅጣጫ ለማስቀመጥ ከፍተኛ ጥረት ቢያደርጉም የግብጽ ወገን ቀድሞውኑ የምክክር ሂደቱ #እንዲፋረስ አቋም ይዞ የመጣ በመሆኑ ጉባኤው የሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ በቀጣይነት ማከናወን ስላለበት ተግባር መመሪያ ሳያስተላልፍ ቀርቷል፡፡የግብጽ መንግስት ሶስተኛ ወገን በጉዳዩ ጣልቃ እንዲገባ እያቀረበ ያለው ሃሳብ በሶስቱ አገራት የትብብር መድረክ የታየውን አበረታች ሂደት የሚያጣጥል እና ሶስቱም አገራት በመጋቢት #2007 ዓ.ም. የፈረሙትን የመርሆዎች መግለጫ ስምምነት የሚጥስ ተግባር ነው፡፡ #የሶስተኛ_ወገን_ጣልቃ-ገብነት ኢትዮጵያ እና ሱዳን የማይቀበሉት እና ተገቢ ያልሆነ፤ በአገራቱ መካከል ያለውን ዘላቂ ትብብር የሚጎዳ፤ ለውይይት ያለውን በቂ እድል ወደጎን የሚያደርግ እና ገንቢ የሆነውን የውይይት መንፈስ የሚያደፈርስ ነው፡፡
ቴክኒካዊ ምክክር የሚጠይቀው የግድብ ሙሌት እና ውሃ አለቃቀቅ ጉዳይ ለፖለቲካ ምክክር እንዲቀርብ የሚጠይቀው ሃሳብም የጉዳዩን ጠባይ ያላገናዘበ፣ የሶስቱ አገራት መሪዎች የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉዳዩን ለመፍታት የሰጡትን መመሪያ የጣሰ እንዲሁም ተገቢ መፍትሄ ለመስጠት የማያስችልም ነው፡፡የኢትዮጵያ መንግስት ልዩነቶችን ለመፍታት እድል የሚፈጥረውን የምክክር ሂደት ለማጠናከር እንደሚሰራ እየገለጸ በጉዳዩ ላይ የሚሰራጨው የመገናኛ ብዙሃን እንዲሁም ሌላ አሉታዊ ዘመቻ የሶስቱን አገራት መተማመን ከመሸርሸር ያለፈ ውጤት እንደማይኖረው ይገልጻል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት በተደጋጋሚ እንደገለጸው የአባይን ውሃ የኢትዮጵያ ህዝቦችን የአሁን እና የወደፊት ፍላጎት ለማሟላት እና ብሄራዊ ጥቅምን ለማረጋገጥ ማልማቱን በመቀጠል ርትዕን የጠበቀ እና በማናቸውም የተፋሰሱ አገራት ላይ ጉልህ ጉዳት የማያደርስ አጠቃቀም እንዲኖር ይሰራል፡፡በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግስት በሕዳሴ ግድብ ላይ በሚደረገው ውይይት የሚከተለው አቅጣጫ የናይል ውሃን አስመልክቶ ለተደረጉት እና በኢትዮጵያ ላይ ምንም አይነት ተፈጻሚነት የሌላቸውን ስምምነቶች እውቅና የማይሰጥ እንዲሁም የላይኛውን የናይል ተፋሰስ አገራት መብት የማይጥስ እንዲሆን ነው፡፡
ምንጭ: የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa
የግብጽ፣ ኢትዮጵያ እና ሱዳን የውሀ ጉዳይ ሚኒስትሮች መስከረም 5 እና 6 ቀን 2012 ዓ.ም በካይሮ ባካሄዱት ስብሰባ ባስቀመጡት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በካርቱም የሶስትዮሽ ስብሰባቸውን አካሂደዋል፡፡ ከሚኒስትሮቹ ስብሰባ አስቀድሞ የአገራቱ ገለልተኛ የሳይንሳዊ ጥናት ቡድን ከመስከረም 19 እስከ 22 ቀን 2012 ዓ.ም በካርቱም አምስተኛ ዙር ስብሰባውን አካሂዶ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክሯል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት በአገራቱ መካከል የሚደረገው ቴክኒካዊ ምክክር ብቸኛው የመፍትሄ አማራጭ በመሆኑ መቀጠል እንደሚኖርበት ያምናል፡፡የሳይንሳዊ ቡድኑ አራት ስብሰባዎችን አድርጎ አበረታች ውጤት እያሳየ ባለበት ወቅት ግብጽ በተናጠል ያቀረበችው የውሃ ሙሌት እና አለቃቀቅን የሚመለከተው ሰነድ ከትብብር ማዕቀፉ ውጪ የሆነ እና ሂደቱን ያናጠበ ሆኗል፡፡ ሆኖም የውሃ ሚኒስትሮች የኢትዮጵያ የውሃ ሙሌት እና አለቃቀቅ እቅድ፣ የግብጽ መንግስት የሚያቀርበው ሰነድ እንዲሁም ሱዳን በጉዳዩ ላይ የምታቀርበው ሰነድ ለሳይንሳዊ ቡድኑ ቀርቦ ዝርዝር ትንታኔ እንዲደረግበት እና ምክረ ሃሳብ እንዲቀርብለት በመስከረም ወር 2012 ዓ.ም በካይሮ በተደረገው ስብሰባ ወስነዋል፡፡
በካርቱም አራት ቀናትን ወስዶ በተካሄደው ስብሰባ የሳይንሳዊ ቡድኑ በመስከረም ወሩ የካይሮ ስብሰባ በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት የኢትዮጵያን የግድብ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ ዕቅድ፣ እንዲሁም ሱዳን እና ግብጽ ያቀረቡትን የሙሌት እና የውሃ አለቃቅ ቴክኒካዊ ጉዳዮችን የሚዳስሰውን ሃሳብ አዳምጦ ውይይቶችን አካሂዷል፡፡ ውይይቱ ሶስቱም ቡድኖች በተስማሙበት የርዕሰ ጉዳይ መዘርዝር ላይ የተመሰረተ ሲሆን በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ከመስማማት ተደርሶ በሌሎቹ ላይ የሃሳብ መለያየቶች ተመዝግበዋል፡፡
እነዚህ የሃሳብ #ልዩነቶች በሳይንሳዊ እና ጥናት ቡድኑ ውይይት እና ትንተና መግባባት ሊደረስባቸው የሚችሉ ናቸው፡፡ኢትዮጵያ ግድቡን እሰከ ሰባት አመት ድረስ በሚወስድ ሂደት ለመሙላት ያቀረበችው እቅድ የታችኛውን ተፋሰስ አገራት ጥቅም ለመጠበቅ ያላትን አቋም ያሳያል፡፡ ይህም በተጨማሪም ኢትዮጵያ እና ሱዳን ማናቸውም ቱክኒካዊ ጉዳዮች ለሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ ቀርበው ትንተና እንዲደረግባቸው ገንቢ እና አካታች የውይይት አካሄድ ቢከተሉም የግብጽ ወገን ያቀረብኳቸው ሃሳቦች በሙሉ ተቀባይነት ካላገኙ ውይይቱ ሊቀጥል አይችልም በሚለው የማያሰራ አቋሙ በመቀጠሉ የሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ ስራውን በተሟላ አኳኋን ማከናወን ሳይችል ቀርቷል፡፡ ይህ የግብጽ አቋም የሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ ስብሰባ እንዲሁም የሚኒስትሮች ስብሰባው ስምምነት በተደረሰባቸው ጉዳዮች ላይ ጭምር ሪፖርት እንዳያዘጋጁ አድርጓል፡፡
ይህ የግብጽ አካሄድ አዲስ ሳይሆን ከዚህ ቀደምም በግድቡ ላይ ሶስቱ አገራት ሊያከናውኑት የነበረውን የውሃ፣ የአካባቢያዊ እና ማህበራዊ ተጽእኖ ጥናት በግብጽ ወገን እንዲስተጓጎል በተደረገ ጊዜ የታየ የሳይንስ እና የምክክር የመፍትሄ አማራጭን የማፋለስ ዘዴ ነው፡፡
ኢትዮጵያ አለመግባባት መፍቻ ዘዴን የሚደነግገውን የመርህ መግለጫ ስምምነቱን አንቀጽ 10 ጠቅሶ መፍትሄ ለመፈለግ ጊዜው እንዳልሆነ እና ቴክኒካዊ ምክክሩ ሊቀጥል እንደሚገባ ታምናለች፡፡የውሃ ሚኒስትሮቹ በሁለት ቀናት ስብሰባቸው የሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ የደረሰበትን ተመልክተው አቅጣጫ ለማስቀመጥ ከፍተኛ ጥረት ቢያደርጉም የግብጽ ወገን ቀድሞውኑ የምክክር ሂደቱ #እንዲፋረስ አቋም ይዞ የመጣ በመሆኑ ጉባኤው የሳይንሳዊ ጥናት ቡድኑ በቀጣይነት ማከናወን ስላለበት ተግባር መመሪያ ሳያስተላልፍ ቀርቷል፡፡የግብጽ መንግስት ሶስተኛ ወገን በጉዳዩ ጣልቃ እንዲገባ እያቀረበ ያለው ሃሳብ በሶስቱ አገራት የትብብር መድረክ የታየውን አበረታች ሂደት የሚያጣጥል እና ሶስቱም አገራት በመጋቢት #2007 ዓ.ም. የፈረሙትን የመርሆዎች መግለጫ ስምምነት የሚጥስ ተግባር ነው፡፡ #የሶስተኛ_ወገን_ጣልቃ-ገብነት ኢትዮጵያ እና ሱዳን የማይቀበሉት እና ተገቢ ያልሆነ፤ በአገራቱ መካከል ያለውን ዘላቂ ትብብር የሚጎዳ፤ ለውይይት ያለውን በቂ እድል ወደጎን የሚያደርግ እና ገንቢ የሆነውን የውይይት መንፈስ የሚያደፈርስ ነው፡፡
ቴክኒካዊ ምክክር የሚጠይቀው የግድብ ሙሌት እና ውሃ አለቃቀቅ ጉዳይ ለፖለቲካ ምክክር እንዲቀርብ የሚጠይቀው ሃሳብም የጉዳዩን ጠባይ ያላገናዘበ፣ የሶስቱ አገራት መሪዎች የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉዳዩን ለመፍታት የሰጡትን መመሪያ የጣሰ እንዲሁም ተገቢ መፍትሄ ለመስጠት የማያስችልም ነው፡፡የኢትዮጵያ መንግስት ልዩነቶችን ለመፍታት እድል የሚፈጥረውን የምክክር ሂደት ለማጠናከር እንደሚሰራ እየገለጸ በጉዳዩ ላይ የሚሰራጨው የመገናኛ ብዙሃን እንዲሁም ሌላ አሉታዊ ዘመቻ የሶስቱን አገራት መተማመን ከመሸርሸር ያለፈ ውጤት እንደማይኖረው ይገልጻል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት በተደጋጋሚ እንደገለጸው የአባይን ውሃ የኢትዮጵያ ህዝቦችን የአሁን እና የወደፊት ፍላጎት ለማሟላት እና ብሄራዊ ጥቅምን ለማረጋገጥ ማልማቱን በመቀጠል ርትዕን የጠበቀ እና በማናቸውም የተፋሰሱ አገራት ላይ ጉልህ ጉዳት የማያደርስ አጠቃቀም እንዲኖር ይሰራል፡፡በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግስት በሕዳሴ ግድብ ላይ በሚደረገው ውይይት የሚከተለው አቅጣጫ የናይል ውሃን አስመልክቶ ለተደረጉት እና በኢትዮጵያ ላይ ምንም አይነት ተፈጻሚነት የሌላቸውን ስምምነቶች እውቅና የማይሰጥ እንዲሁም የላይኛውን የናይል ተፋሰስ አገራት መብት የማይጥስ እንዲሆን ነው፡፡
ምንጭ: የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
🤩🤩🤩🤩የምስራች 🤩🤩🤩
በአ.አ በቀላሉ የማይገኙ ፤ ወደ12ሺ ሰዓቶች እና ቦርሣዎች ለትዛዝ ፤ ከ 1ሺ በላይ እቃዎች በ እጃችን መርጠው ይዘዙን ወደ ክልልም እንልካለን
ከታች ባለው ሊንክ ይጎብኙን
👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAENXyUTam6WMV6_hmg
በአ.አ በቀላሉ የማይገኙ ፤ ወደ12ሺ ሰዓቶች እና ቦርሣዎች ለትዛዝ ፤ ከ 1ሺ በላይ እቃዎች በ እጃችን መርጠው ይዘዙን ወደ ክልልም እንልካለን
ከታች ባለው ሊንክ ይጎብኙን
👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAENXyUTam6WMV6_hmg