YeneTube
118K subscribers
31.5K photos
485 videos
79 files
3.88K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
7 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ወርቅና በርካታ የዉጪ አገር ገንዘቦች ተያዙ!

በጉምሩክ ኮሚሽን የጅግጅጋ ቅ/ፅ/ቤት የቶጎ ጫሌ መቅርጫ ጣቢያ 7 ሚሊየን ብር የሚያወጣ 5ከ.ግ ወርቅና የዉጪ አገር ገኝዘቦችን ያዘ።በቀን 13/01/12 ከለሊቱ 9 ሰአት አካባቢ ከሰ/ቁጥር ኮድ3-05861 ድሬ አይሱዚ ኤክስፖርት የሚደረግ ጫት የጫነ ተሽከርካሪ የቶጎጫሌ ፈታሾች ባደረጉት ጥረትና ጠንካራ ፍተሻ 5 ኪ.ግ ጥፍጥፍ ወርቅ ፤ 175,584 የሳውዲ ሪያል እንዲሁም 7,155 ድርሀም በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
በጉምሩክ ኮሚሽንየ ጅግጅጋ ቅ/ፅ/ቤት የቶጎ ጫሌ መቅረጫ ጣቢያ ፈታሾች ቀን ከሌሊት ህገ ወጥ የገንዘብ ዝዉዉርና ኮንትሮባንድን ለመከላከል እያደረጉት ላለዉ ጠንካራ ስራ የገቢዎች ሚኒስቴር ያለዉን አድናቆት ያቀርባል፡፡ የተያዘዉ ወርቅና ገንዘብ እንደተለመደዉ ለብሄራዊ ባንክ ገቢ ይሆናል፡፡

ምንጭ: የገቢዎች ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa
ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በባህርዳርና በአዲስ አበባ የተፈፀሙትን ጥቃቶች የተመለከተው ምርመራ እንደቀጠለ መሆኑን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል እንደሻው ጣሰው ለአሜሪካ ድምፅ አስታውቀዋል፡፡

ምርመራው ዘግይቷል የሚባለው ነገርም ትክክል አይደለም ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፡፡ የተወሰ ጊዜም እንደሚወስድ ይታወቅ እንደነበርም አብራርተዋል፡ፖሊስ በጅምር ላይ የነበረውን ምርመራ አስመልክቶ መግለጫ መስጠቱን ያስታወሱት ኮሚሺነሩ፣ ሲጠናቀቅም ለሚመለከተው አካልና ለሕዝቡ ይፋ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ኮሚሺነሩ አክለው እንዳሉትም ከሰኔ 15ቱ ጥቃት ጋር በተያያዘ ከታሰሩ ተጠርጣሪዎች አብዛኛዎቹ ተለቀዋል፡፡ አሁን በቁጥጥር ሥር የሚገኙት ቁጥርም ከመቶ እንደማይበልጥ አስረድተዋል፡፡ አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከዚሁ ከሰኔ 15ቱ ጥቃት ጋር በተያያዘ የታሰሩ ሰዎች ቁጥር፣ በመንግሥት ከሚገልፀው የበለጠ መሆኑን እንደሚናገሩ ይታወቃል፡፡

ምንጭ:VOA
@YeneTube @FikerAssefa
የባህር ዳር ፈለገ ሕይወት ሆስፒታል ተገቢውን አገልግሎት እየሰጠ አይደለም ተባለ።

አዳዲስ የላቦራቶሪ መሣሪያዎችም መጥፋታቸው ተነግሯል።የባህርዳር ፈለገ ሕይወት ሆስፒታል ታካሚዎች ለተጨማሪ ወጪ እንዲዳረጉ በማድረግና በቂ የመድኀኒት አቅርቦት ባለማቅረብ ተገቢውን አገልግሎት እየሰጠ አይደለም የሚል አቤቱታ ከሠራተኞቹ ቀረበበት።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የሆስፒታሉ ሠራተኞች ለአዲስ ማለዳ እንዳስታወቁት፣ በሆስፒታሉ ያሉ ላቦራቶሪዎች ግማሾቹ ከጥቅም ውጪ ሆነዋል፣ ግማሾቹ ደግሞ የት እንደገቡ እንደማይታወቅና ታካሚዎች በዚህ ሳቢያ ለምርመራ ወደ ግል ህክምና ተቋማት እየተላኩ ለለከፍተኛ ወጪ መዳረጋቸውን አስታውቀዋል።

ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
ባልደራሱ" የተሰኘ የጥቅል እቃ መቀበልና ማድረስ አገልግሎት ስራ ጀመረ።

በሆራይዘን ኤክስፕረስ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ይፋ የተደረገው ይህ አዲስ አገልግሎት የስራ ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።ባልደራሱ የተሰኘው ይህ አዲስ ፕሮግራም በዋናነት በቴክኖሎጂ የታገዘ የጥቅል እቃ መቀበልና ማድረስ አገልግሎት ላይ ያተኩራል ተብሏል።ይህ አገልግሎት ከዚህ በፊት በተለያዩ ተቊማት ተሞክሮ ውጤታማ መሆኑ መረጋገጡ ተገልጿል።

ይህ አገልግሎት በዋና ማሰራጫ ማዕከል በመደራጀት በሞባይል መተግበሪያዎችና በድረገጽ ተቀናጅቶ እንደሚሰጥ በፕሮግራሙ ማስተዋወቂያ ላይ ተጠቅሷል።በዚህ ድርጅት ከሚሰጡ አገልግሎቶች መካከልም ቀላልና ከባድ እቃወችን በሞተርና በሌሎች ተሽከርካሪዎች ይሰጣል ተብሏል።አገልግሎቱ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ከመፍጠሩ ባለፈ በተለይም እያደገ ለመጣው የሎጅስቲክ አገልግሎት ዘርፍ ጊዜንና ወጭን በመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በእስራኤል አገር የሚገኝ አንድ መዋዕለ ሕፃናት ኢትዮጵያዊያን ዝርያ ያላቸውን ሕፃናት ተማሪዎች ላይ ማግለል በመፈፀሙ መዘጋቱን ሰምተናል።

@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
7 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ወርቅና በርካታ የዉጪ አገር ገንዘቦች ተያዙ! በጉምሩክ ኮሚሽን የጅግጅጋ ቅ/ፅ/ቤት የቶጎ ጫሌ መቅርጫ ጣቢያ 7 ሚሊየን ብር የሚያወጣ 5ከ.ግ ወርቅና የዉጪ አገር ገኝዘቦችን ያዘ።በቀን 13/01/12 ከለሊቱ 9 ሰአት አካባቢ ከሰ/ቁጥር ኮድ3-05861 ድሬ አይሱዚ ኤክስፖርት የሚደረግ ጫት የጫነ ተሽከርካሪ የቶጎጫሌ ፈታሾች ባደረጉት ጥረትና ጠንካራ ፍተሻ 5 ኪ.ግ ጥፍጥፍ ወርቅ…
ተጨማሪ መረጃ!

በጉምሩክ ኮሚሽን ጅግጂጋ ቅርንጫፍ የቶጎ ጫሌ መቅረጫ ጣቢያ ዛሬ ጠዋት ከተያዘዉ 7 ሚሊየን ብር የሚያወጣ 5ኪ.ግ ወርቅና የዉጪ አገራት ገንዘብ በተጨማሪ የተሽከርካሪውን አካል ጠዋት በጥንቃቄ በዝርዝር ሲፈተሽ 63,035 የአሜሪካን ዶላር እና 146,500 የሳውዲ ሪያል ተገኝቷል፡፡የገቢዎች ሚኒስቴር ቀንና ሌሊት ከኮንትሮባንዲስት ጋር ተጋፍጠዉ ህገ ወጥነትን ለመከለከል የሚሰሩ የመቅረጫ ጣቢያዉን ፈታሾችና ሰራተኞች ያለዉን አድናቆት ገልጿል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
⬆️⬆️

ምርጫ ቦርድ የኢዜማ ፓርቲ መሪ እውነታ አዛብቶ የሚያቀርብ ንግግር በኢሳት ቴሌቪዥን አድርገዋል ሲል ማስተካከያ የሰጠ ሲሆን ወደፊትም በተመሳሳይ ክትትል በማድረግ የተዛቡ መረጃዎችን ሳገኝ እርምት እሰጣለው ብሏል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
በ2011 ዓ/ም ከ8 ሺ በላይ ትዳሮች በፍቺ ተጠናቀዋል ተባለ፡፡

በተሸሻለው የቤተሰብ ህግ መሰረት በየትኛውም የጋብቻ ማስፈጸሚያ ስርአቶች የተፈጸመ ጋብቻ መመዝገብ እንዳለበት ያስገድዳል፡፡በዚህም መሰረት በመላ ሃገሪቱ በ2011 ዓ/ም 79 ሺህ 54 ሰዎች ትዳር መስርተው ህጋዊ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ማካሄዳቸውን ነው ኢትዮ ኤፍ ኤም ከኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ የሰማው፡፡

የኤጀንሲው ኮምዩኒኬሽንና ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደሳለኝ ታሬሳ እንደነገሩን በዚሁ ባሳለፍነው አመት 8ሺህ 652 ትዳሮች ፍጻሜአቸው በፍቺ ተደምድሟል፡፡በተለያዩ ምክንያቶች ያልተመዘገቡ ጋብቻዎችና ፍቺዎች መኖራቸው ይታወቃል፡፡በሌላ በኩል 393 የጉዲፈቻ ምዝገባ ተካሂዷል፡፡

እንደ አቶ ደሳለኝ ገለጻ ኤጀንሲው የአምስት ዋና ዋና ኩነቶች ማለትም ልደት፣ሞት፣ጋብቻ፣ፍቺና ጉዲፈቻ ምዝገባ ያካሂዳል፡፡ይሁንና ባለፈው አመት በሃገሪቷ አንዳንድ አካባቢዎች በተከሰቱ ግጭቶች፣ ምክንያትና በህብረተሰቡ የግንዛቤ እጥረት እንዲሁም በተጨማሪ ምክንያቶች ለመመዝገብ የታሰበውን ያክል የኩነቶች ምዝገባ ማካሄድ አለመቻሉን ነግረውናል፡፡

Via:- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
ጅማ ⬆️ መስከረም 15 ኦሬንቴሽን ይሰጣል በመንደራ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት። @YeneTube @Fikerassefa
🔝 ሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) ዋና ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ። (መስከረም 12)

ሲአን በመግለጫው የሲዳማ ህዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር ጉዳይ ላይ ሲአን እንደማይደራደር ገልጿል ።

@YeneTube @Fikerassefa
20 ክላሺንኮቭ ጠብመንጃ፣ አንድ ሽጉጥ፣ 45,392 የክላሽ ጥይት፣ 8,484 የM14 ጥይትና 45 የመትረየስ ጥይት በቁጥጥር ስር ዋለ።

የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት እና የአፋር ክልል የአሊዳር ወረዳ ዴሼቶ ቀበሌ ሕዝብ እና ፖሊስ አባላት ባደረጉት ክትትል ሕገ-ወጥ መሣሪያዎች ቁጥጥር ሥር ውለዋል። በቁጥጥር ሥር የዋሉት ሕገ-ወጥ መሣሪያዎችም 20 ክላሺንኮቭ፣ አንድ ሽጉጥ፣ 45,392 የክላሽ ጥይቶች፣ 8,484 የM14 ጥይቶች እና 45 የመትረየስ ጥይቶች መሆናቸውን የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር አህመድ ሁመድ ገልጸዋል።ሕገ-ወጥ መሣሪያው ከጅቡቲ ተስነስቶ ወደ መሃል ሀገር ሊገባ እንደነበር ተገልጿል።

ምንጭ:ETV
@YeneTube @FikerAssefa
የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ከሲዳማ ዞን ሕዝበ ውሳኔ በፊት ምቹ የፖለቲካ ሁኔታ እንዲፈጠር አሳሰበ።

በኅዳር ወር 2012 ዓ.ም. ይካሄዳል ተብሎ ከታቀደው የደቡብ ክልል የሲዳማ ዞን ሕዝበ ውሳኔ አስቀድሞ አስተዳደራዊና ሕጋዊ ማዕቀፎች በማዘጋጀት፣ እንዲሁም ተዓማኒ በሆነ የጊዜ ሰሌዳ ላይ አስቀድሞ መግባባት ላይ በመድረስ ሕዝበ ውሳኔውን ለማካሄድ የሚያስችል ምቹ የፖለቲካ ሁኔታ ለመፍጠር አፋጣኝ ዕርምጃ መውሰድ እንደሚያስፈልግ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) አሳሰቡ፡፡ዋና ኮሚሽነሩ ይህን ማሳሰቢያ የሰጡት ከመስከረም 7 እስከ 9 ቀን 2012 ዓ.ም. በሐዋሳ ከተማ ያደረጉትን የሥራ ጉብኝት አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ወቅት ነው፡፡

በሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም. ከሲዳማ ዞን የክልልነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ በተነሳው ግጭት ምክንያት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የሚገኙ ዜጎችን የጎበኙት ዋና ኮሚሽነሩ ከጉብኝቱ በኋላ፣ ‹‹ለችግሩ መነሻ የሆነው ዋነኛ ምክንያት በሲዳማ ዞን ምክር ቤት ለቀረበው የክልልነት ጥያቄ በሚመለከታቸው አካላት ሲሰጥ የነበረው ምላሽ ወቅታዊና ሥልታዊ አለመሆን፣ በሌላ በኩል ጥያቄውን በተናጠል ውሳኔና በኃይል ጭምር ለማስፈጸም የፈለጉ ቡድኖች ባራመዱት አስተሳሰብ የተነሳ የተፈጠረ የፖለቲካ ውጥረትና ቀውስ በመሆኑ ነው፤›› በማለት፣ አሁንም ከመጪው ኅዳር ሕዝበ ውሳኔ አስቀድሞ ምቹ የፖለቲካ ሁኔታ መፍጠሩ አስፈላጊ መሆኑን አበክረው አሳስበዋል፡፡

ምንጭ: ሪፖርተር
@YeneTube @FikerAssefa
አብያተ ክርስቲያናቱ የይዞታ ማረጋገጫ ሊሰጣቸው ነው፡፡

በአዲስ አበባ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ አብያተ ክርስቲያናት የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ሊሰጣቸው ነው፡፡‹‹በቤተ ክርስቲያኗና ምዕመኖቿ ላይ ጥቃት እየደረሰ ነው፤ መንግሥት ሕግን ሊያስከብር ይገባል›› በሚል በ10 የቤተ ክርስቲያኗ ማኅበራት የተዋቀረው ኮሚቴ በጥያቄዎቹ ላይ ከመንግሥት ጋር እየመከረ መሆኑ ይታወቃል፡፡ኮሚቴው ካነሳቸው 10 ዋና ዋና ጥያቄዎች ማካከል የይዞታ ማረጋገጫ ላልተሰጣቸው አብያተ ክርስቲያናት የይዞታ ማረጋገጫ እንዲሰጥ ፣ ያለ አግባብ የተወሰዱ ቦታዎችም እንዲመለሱ የሚለው ይገኝበታል፡፡

በዚህም በአዲስ አበባ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናትን የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ የከተማዋ አስተዳደር መስከረም 14/2012 አመሻሽ 10፡00 ላይ ለቤተ ክርስቲያኗ ፓትሪያርክ ለማስረከብ መርሃ ግብር መያዙን ኮሚቴው ለአሐዱ ቴሌቪዥን ገልጿል፡፡አስተዳደሩ በሚያነሳቸው የተለያዩ ምክንያቶች በአዲስ አበባ ከሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት 70 በመቶ ገደማዎቹ እስካሁን የይዞታ ማረጋገጫ እንዳልተሰጣቸው ኮሚቴው አክሏል፡፡

ምንጭ:አሐዱ ቴሌቪዥን
@YeneTube @FikerAssefa
"ለስልጣን ተብሎ የሚፈጠር ውህደትን ህወሓት ፈጽሞ አይቀበለውም" አቶ ጌታቸው ረዳ

የገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ተዋህዶ አንድ ወጥ ሃገራዊ ፓርቲ ይሆናል እየተባለ የሚነገረውን ጉዳይ ህወሓት ፈጽሞ እንደማይቀበለው የህወሓትና የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ ለቢቢሲ ተናገሩ።ኢህአዴግ አጋር ድርጅቶችን ጨምሮ በመዋሃድ "የኢትዮጵያ የብልጽግና ፓርቲ" ይሆናል እየተባለ የሚነገረውን ጉዳይ በተመለከተ የግንባሩ መስራችና እስከቅርብ ጊዜ ድረስ የድርጅቱ ቁንጮ ሆኖ የቆየው ህወሓት ያሉ ችግሮች መፍትሄ ሳያገኙ እንደማይቀበለው አቶ ጌታቸው ገልጸዋል።

shorturl.at/afGX5

@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ክልል ፍትሕ ቢሮ እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የትግራይ ክልል ተወካዮች አማካኝነት፣ የወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽንን ለማቋቋም በወጣው ረቂቅ አዋጅ ላይ የቀረበው የሕገ መንግሥት ትርጓሜ ጥያቄ፣ በሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ውድቅ ተደረገ።የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ፀድቆ የቀረበለትን የአስተዳደር ወሰንና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅን በታኅሳስ 2011 በ33 ተቃውሞና በ4 ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፅ ማፅደቁ ይታወሳል።

Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
በኒውዮርክ ከተማ እየተካሄደ ባለው የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ላስመዘገበችው ውጤት የእውቅና ሽልማት ለፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተበርክቶላቸዋል::

በሀገራችን የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ስኬት የጀርባ አጥንት ሆነው በሚሰሩት የጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች ትጋት የመጣ ነው::ይህንን የእውቅና ሽልማት ያበረከተው አክሰስ ቻሌንጅ በመባል የሚታወቅ መቀመጫውን አሜሪካን ሀገር ያደረገ በጤና እና ትምህርት ተደራሽነት ላይ የሚሰራ ድርጅት ነው::ሽልማቱን ዶ/ር ጽዮን ፍሬው ኢትዮጵያን በመወከል ተቀብላለች::

Via Amir Aman[Dr]
@YeneTube @FikerAssefa
በሲዳማ ብሔር የክልልነት ጥያቄ ማስፈፀሚያ ዕቅድ እና አተገባበር ዙሪያ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ገለፃ አደረገ።

በሀገር ደረጃ ለአስተዳደራዊ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ለመጀመሪያ ጊዜ የሲዳማ ብሔር የክልልነት ጥያቄ ህዝበ ውሳኔ ህዳር 3 ቀን 2012 ዓ.ም እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡በዚህ መነሻ በተደረገው ገለፃ በከተማ አስተዳደሩ በሁሉም እርከን የሚገኘው አመራር የተሳተፈ ሲሆን የሲዳማ ብሔር ክልል የመሆን ጥያቄ ህዝበ ውሳኔ መላውን ህዝብ ያሳተፈ፣ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የከተማ አመራሩ እንደሚሰራ ተገልጿል፡፡

የሲዳማን የክልልነት ጥያቄ ህዝበ ውሳኔ ለማካሄድ ከተቋቋሙ 19 የድምፅ መስጫ ክልልሎች አንዷ በሆነችው ሀዋሳ ከተማ በ166 የምርጫ ጣቢያዎች እድሜው ከ18 ዓመት በላይ የሆነ ከ190 ሺህ በላይ ሰው ድምፅ ይሰጣል ተብሎ ዕቅድ ተይዟል፡፡ይህን ዕቅድ ለማሳካትና ቅድመ ህዝበ ውሳኔውን፣ ህዝበውሳኔውንና ድህረ ህዝበ ውሳኔውን ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለመምራት የሚያስችል ቅንጅታዊ አሰራር በመዘርጋት ህዝብን አሳትፎ መንቀሳቀስ እንደሚገባ አቶ ጥራቱ በየነ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ገልፀዋል፡፡

ህዝበ ውሳኔውን ለማካሄድ የሚያስችሉ የምርጫ ጣቢያዎች ማዘጋጀት፣ ሎጂስቲክ ማሟላት፣ ህዝበ ውሳኔውን የሚያስተባበሩ የተለያዩ ኮሚቴዎች የማቋቋም ስራ እንዲሁም ለመራጭ የሚቀርብ ምልክት የማስተዋወቅ እና የህዝበ ውሳኔ ቅስቀሳ ስራዎች የጊዜ ሰሌዳቸውን ጠብቀው በመከናወን ላይ መሆናቸውም በመድረኩ ተመላክቷል፡፡ታሪካዊ የሆነውን ህዝበ ውሳኔ ለማካሄድ ከቀረው ጊዜ አንፃር በተቻለ ፍጥነት ልንቀሳቀስ ይገባል ያሉት ተሳታፊዎች የሲዳማ ብሔር የክልልነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት እንደሀገር ተያይዘን ቀጣዩን ጊዜ ብሩህ የምናደርግበትን ዕድል የሚያሰፋ ነውም ብለዋል፡፡

ምንጭ፡ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የህዝብ ግንኙነት ጽ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
በህዳሴ ግድብ ላይ የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጣልቃ ገብነት ያስፈልጋል - ግብጽ

በኒውዮርክ እየተካሄደ ባለው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታ አል ሲሲ የሀገራቱን እሰጣ ገባ ለመቅረፈ የአለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጣልቃ ገብነት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡አል ሲሲ የናይል ወንዝ ለግብፅ የህይወትና የሞት ሽረት ጉዳይ ነው ፤ እናም ኢትዮጵያ እየገነባች ያለው ታላቁ የህዳሴ ግድብ ፍርሃት ውስጥ ከቶናል ብለዋል፡፡

ስለዚህም የሀገራቱን አለመግባባት ለመፍታት አለም አቀፋዊ ጣልቃ ገብነት ወይም ተፅዕኖ ያስፈልጋል ሲሉም ተደምጠዋል፡፡ፕሬዝዳንቱ ከሳምንታት በፊት በሀገሪቱ በተከበረው የወጣቶች ቀን ላይ ኢትዮጵያ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የጀመረችው እኛ አለመረጋጋት ውስጥ ስለነበርን እንጂ ግንባታውን አትሞክረውም ነበር ማለታቸው ይታወሳል፡፡ኢትዮጵያም ግብፅ ያቀረበችውን የድርድር ኃሣብ ውድቅ ማድረጓ ይታወቃል ሲል አሽራቅ አል አውሳትን ዋቢ አድርጎ አሃዱ ቴሌቪዥን ነው የዘገበው።

@YeneTube @FikerAssefa