እርማት ~የኔቲቱብ
በርካታ ጋዜጠኞች፣ አክቲቪስቶች እና ብዙ የሶሻል ሚድያ ተከታታይ ያላቸው ግለሰቦች የአፍሪካ ህብረት አማርኛን ስድስተኛ የስራ ቋንቋው አድርጎ እንደመረጠ ትናንት ሲፅፉ ነበር። እውን ሆኖ "እልል" ባስባሉን እያልኩ ነበር፣ ነገር ግን መረጃው #የሀሰት ነው።
ዛሬ በጠዋቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ቃል አቀባይ የሆነችው ኤባ ካሎንዶ ጋር ደወልኩ። በመልሷም፦
"የቋንቋ ምርጫ የመሪዎቹ አጀንዳ ላይ ጭራሽ አልነበረም። እርግጥ ጠ/ሚር አብይ ስለ አፍሪካ ሀገር በቀል ቋንቋዎች ጥቅም አውርተዋል። የኢኳቶርያል ጊኒው መሪም ቋንቋቸው የአፍሪካ ህብረት ቋንቋ እንዲሆን ይፈልጋሉ። ይህ ማለት ግን ሆኑ ማለት አይደለም። ስለዚህ ኤልያስ፣ አማርኛ የአፍሪካ ህብረት ኦፊሴላዊ ቋንቋ ሆነ የተባለው የሀሰት ዜና (fake news) ነው።"
ምንጭ:- ኤልያስ መሰረት
@YeneTube @FikerAssefa
በርካታ ጋዜጠኞች፣ አክቲቪስቶች እና ብዙ የሶሻል ሚድያ ተከታታይ ያላቸው ግለሰቦች የአፍሪካ ህብረት አማርኛን ስድስተኛ የስራ ቋንቋው አድርጎ እንደመረጠ ትናንት ሲፅፉ ነበር። እውን ሆኖ "እልል" ባስባሉን እያልኩ ነበር፣ ነገር ግን መረጃው #የሀሰት ነው።
ዛሬ በጠዋቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ቃል አቀባይ የሆነችው ኤባ ካሎንዶ ጋር ደወልኩ። በመልሷም፦
"የቋንቋ ምርጫ የመሪዎቹ አጀንዳ ላይ ጭራሽ አልነበረም። እርግጥ ጠ/ሚር አብይ ስለ አፍሪካ ሀገር በቀል ቋንቋዎች ጥቅም አውርተዋል። የኢኳቶርያል ጊኒው መሪም ቋንቋቸው የአፍሪካ ህብረት ቋንቋ እንዲሆን ይፈልጋሉ። ይህ ማለት ግን ሆኑ ማለት አይደለም። ስለዚህ ኤልያስ፣ አማርኛ የአፍሪካ ህብረት ኦፊሴላዊ ቋንቋ ሆነ የተባለው የሀሰት ዜና (fake news) ነው።"
ምንጭ:- ኤልያስ መሰረት
@YeneTube @FikerAssefa