የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ወደነበረበት የሚመልስ ረቂቅ ዕቅድ ተዘጋጀ⤵️
ለመጀመርያ ጊዜ በአዲስ አበባ የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ይቋቋማል
በግንቦት 1997 ዓ.ም. ከተካሄደው ምርጫ በኋላ በተፈጠረው ቀውስ ወደ ፌዴራል መንግሥት የተዘዋወረውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ወደ ከተማው አስተዳደር መመለስ የሚያስችል ረቂቅ ዕቅድ ተዘጋጀ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አደረጃጀትና መዋቅር ጥናት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ባካሄደው ጥናት፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የራሱ የሆነ አዲስ የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ እንዲመሠርት ምክረ ሐሳብ አቅርቧል፡፡
የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ ባከናወነው ጥናት ላይ የመጀመርያ ዙር ውይይት ረቡዕ መስከረም 16 ቀን 2011 ዓ.ም. ተካሂዷል፡፡
በውይይቱ ወቅት በቀረበው ጥናታዊ ጽሑፍ፣ ‹‹የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ›› የተሰኘ አዲስ የካቢኔ አባል የሚሆን ተቋም እንዲመሠረት ሐሳብ ቀርቧል፡፡
ይህ አዲስ ተቋም ላለፉት 14 ዓመታትአስተዳደር በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ሥር ሆኖ የቆየውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በድጋሚ ወደ ከተማው በመመለስ፣ የከተማውን ደንብ ማስከበር አገልግሎትና በክፍለ ከተማና በወረዳ የሚቋቋሙትን የፀጥታ አስተዳደር ጽሕፈት ቤቶችን አቅፎ ይይዛል፡፡
#የአዲስ አበባ ከተማ የፀጥታና ቢሮ ተጠሪነቱ በቀጥታ ለከተማ #አስተዳደሩ ከንቲባ ይሆናል ተብሏል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አደረጃጀትና መዋቅር ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይፈ ፍቃዱ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የተዘጋጀው ጥናት ለካቢኔ ቀርቦ ይሁንታ ካገኘ ለአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ቀርቦ ሲፀድቅ ተግባራዊ ይሆናል፡፡
📌#በቀረበው ረቂቅ ጥናት ላይ #በሕገ_መንግሥቱ_አንቀጽ_49_ንዑስ_አንቀጽ_2_እና_በቻርተሩ_95_አንቀጽ_10_መሠረት፣ አዲስ አበባ ከተማ ራሱን የማስተዳደር #መብት አለው፡፡
📌‹‹የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ሥልጣን ይኖረዋል፣ ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል፤›› ሲል ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ ደንግጓል፡፡
ረቂቅ ጥናቱን ያቀረቡት የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ ከፍተኛ አማካሪ አቶ ቤተ ማርያም መኮንን እንዳሉት፣ አዲስ አበባ ከተማ እስካሁን የራሱ የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የለውም፡፡
‹‹ራሱን የቻለ የፀጥታ መዋቅር ባለመኖሩ የከተማውን ነባራዊ ሁኔታ መሠረት ባደረገ መንገድ ባለመደራጀቱ፣ የፀጥታ ተቋማቱ በተለያየ መዋቅር እንዲመሩ ሆኗል፤›› በማለት የገለጹት አቶ ቤተ ማርያም፣ ‹‹አዲስ የፀጥታ አስተዳደር መዋቅር ተግባራዊ ሲሆን ይህ ችግር ይፈታል፤›› ብለዋል፡፡
በአዲሱ መዋቅር መሠረት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ የፀጥታ አስተዳደር ጽሕፈት ቤቶች፣ በማዕከል፣ በክፍለ ከተማና በወረዳ ያሉ የደንብ ማስከበር ጽሕፈት ቤቶች በቢሮው ሥር ይተዳደራሉ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ዓመታት የፍትሕ፣ የፀጥታ፣ የሰላም፣ የመልካም አስተዳደርና የሰብዓዊ መብት ጥያቄዎች መነሳታቸውን ያስታወሱት ደግሞ፣ የከተማው ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አማካሪ አቶ ኤፍሬም ግዛው ናቸው፡፡
ከነዋሪዎች የሚነሱትን እነዚህን ችግሮች ለመፍታት፣ የከተማውን ሰላምና ፀጥታ አስተማማኝ ለማድረግ አዲሱ መዋቅር ወሳኝ ድርሻ እንዳለው አቶ ኤፍሬም ተናግረዋል፡፡
ይህ ጥናት እንዲካሄድ መመርያ የሰጠው የከተማ አስተዳደር ካቢኔ በመሆኑ፣ በሒደት ላይ ያሉ ሥራዎች ሲጠናቀቁ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል፡፡
@YeneTube @Fikerassefa
ለመጀመርያ ጊዜ በአዲስ አበባ የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ይቋቋማል
በግንቦት 1997 ዓ.ም. ከተካሄደው ምርጫ በኋላ በተፈጠረው ቀውስ ወደ ፌዴራል መንግሥት የተዘዋወረውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ወደ ከተማው አስተዳደር መመለስ የሚያስችል ረቂቅ ዕቅድ ተዘጋጀ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አደረጃጀትና መዋቅር ጥናት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ባካሄደው ጥናት፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የራሱ የሆነ አዲስ የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ እንዲመሠርት ምክረ ሐሳብ አቅርቧል፡፡
የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ ባከናወነው ጥናት ላይ የመጀመርያ ዙር ውይይት ረቡዕ መስከረም 16 ቀን 2011 ዓ.ም. ተካሂዷል፡፡
በውይይቱ ወቅት በቀረበው ጥናታዊ ጽሑፍ፣ ‹‹የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ›› የተሰኘ አዲስ የካቢኔ አባል የሚሆን ተቋም እንዲመሠረት ሐሳብ ቀርቧል፡፡
ይህ አዲስ ተቋም ላለፉት 14 ዓመታትአስተዳደር በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ሥር ሆኖ የቆየውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በድጋሚ ወደ ከተማው በመመለስ፣ የከተማውን ደንብ ማስከበር አገልግሎትና በክፍለ ከተማና በወረዳ የሚቋቋሙትን የፀጥታ አስተዳደር ጽሕፈት ቤቶችን አቅፎ ይይዛል፡፡
#የአዲስ አበባ ከተማ የፀጥታና ቢሮ ተጠሪነቱ በቀጥታ ለከተማ #አስተዳደሩ ከንቲባ ይሆናል ተብሏል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አደረጃጀትና መዋቅር ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይፈ ፍቃዱ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የተዘጋጀው ጥናት ለካቢኔ ቀርቦ ይሁንታ ካገኘ ለአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ቀርቦ ሲፀድቅ ተግባራዊ ይሆናል፡፡
📌#በቀረበው ረቂቅ ጥናት ላይ #በሕገ_መንግሥቱ_አንቀጽ_49_ንዑስ_አንቀጽ_2_እና_በቻርተሩ_95_አንቀጽ_10_መሠረት፣ አዲስ አበባ ከተማ ራሱን የማስተዳደር #መብት አለው፡፡
📌‹‹የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ሥልጣን ይኖረዋል፣ ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል፤›› ሲል ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ ደንግጓል፡፡
ረቂቅ ጥናቱን ያቀረቡት የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ ከፍተኛ አማካሪ አቶ ቤተ ማርያም መኮንን እንዳሉት፣ አዲስ አበባ ከተማ እስካሁን የራሱ የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የለውም፡፡
‹‹ራሱን የቻለ የፀጥታ መዋቅር ባለመኖሩ የከተማውን ነባራዊ ሁኔታ መሠረት ባደረገ መንገድ ባለመደራጀቱ፣ የፀጥታ ተቋማቱ በተለያየ መዋቅር እንዲመሩ ሆኗል፤›› በማለት የገለጹት አቶ ቤተ ማርያም፣ ‹‹አዲስ የፀጥታ አስተዳደር መዋቅር ተግባራዊ ሲሆን ይህ ችግር ይፈታል፤›› ብለዋል፡፡
በአዲሱ መዋቅር መሠረት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ የፀጥታ አስተዳደር ጽሕፈት ቤቶች፣ በማዕከል፣ በክፍለ ከተማና በወረዳ ያሉ የደንብ ማስከበር ጽሕፈት ቤቶች በቢሮው ሥር ይተዳደራሉ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ዓመታት የፍትሕ፣ የፀጥታ፣ የሰላም፣ የመልካም አስተዳደርና የሰብዓዊ መብት ጥያቄዎች መነሳታቸውን ያስታወሱት ደግሞ፣ የከተማው ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አማካሪ አቶ ኤፍሬም ግዛው ናቸው፡፡
ከነዋሪዎች የሚነሱትን እነዚህን ችግሮች ለመፍታት፣ የከተማውን ሰላምና ፀጥታ አስተማማኝ ለማድረግ አዲሱ መዋቅር ወሳኝ ድርሻ እንዳለው አቶ ኤፍሬም ተናግረዋል፡፡
ይህ ጥናት እንዲካሄድ መመርያ የሰጠው የከተማ አስተዳደር ካቢኔ በመሆኑ፣ በሒደት ላይ ያሉ ሥራዎች ሲጠናቀቁ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል፡፡
@YeneTube @Fikerassefa
አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ቀጥጥር ስር ውለዋል‼️
ፖሊስ አቶ ተስፋዬ ኡርጌን በተጨማሪነት በሰብዓዊ #መብት_ጥሰትና በሙስና ወንጀል ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ
መርማሪ ፖሊስ የቀድሞው የብሄራዊ መረጃና ደህንነት የስራ ባልደረባ አቶ ተስፋዬ ኡርጌን በተጨማሪነት በሰብዓዊ መብት ጥሰትና በሙስና ወንጀል ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
አቶ ተስፋዬ ኡርጌ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ የወንጀል #ችሎት ቀርበዋል።
መርማሪ ፖሊስም የቀድሞውን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት የስራ ባልደረባ በተጨማሪነት በሰብዓዊ መብት ጥሰትና በሙስና ወንጀል ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸው ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።
አቶ ተስፋዬ የደህንነት መምሪያ ሀላፊ ሆነው ሲሰሩ ሰዎችን በሽብር ተጠርጥራችኋል በሚል በስውር እስር ቤት በማሰርና በማሰቃየት፥ እርቃናቸውን በካቴና አስረው ቆሻሻ ገንዳ ውስጥ በማቆየት፣ ግለሰቦችን ባልተገባ መልኩ ለሽብር መልምለው ወደ ኤርትራ በመላክ እንደጠረጠራቸው ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ገልጿል።
ከዚህ ባለፈም በሽብር ከተጠረጠሩ ሰዎች ላይ ገንዘብ በመቀበል እና በሀዋላ ከተጠርጣሪዎች ላይ ህገ ወጥ ገንዘብ በመቀበል በሰብዓዊ መብት ጥሰትና በሙስና ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁም ብሏል መርማሪ ፖሊስ።
ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅም 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀን ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
አቶ ተስፋዬ በሰጡት ምላሽ እርሳቸው የተጠረጠሩበት ጉዳይ በግልጽና በተናጠል እንዳልቀረበ በመግለጽ፥ እርሳቸውን ለመያዝ በቂና ዝርዝር ጉዳይ አለመኖሩን አስረድተዋል።
በተጨማሪም ሀብት የመፍጠር ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው ሃብት ማፍራታቸውንና ለአራት ወራት ፍርድ ቤት እየተመላለሱ መሆኑን በመጥቀስ፥ ሃብት ከማፍራት ጋር ተያይዞ ሀምሌ 5 ቀን 2010 ዓ.ም ቤታቸው መበርበሩንና ምርመራው በወቅቱ ማለቅ ነበረበት ብለዋል።
አሁን ላይ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀው ተጨማሪ ጊዜም ሊሰጥ አይገባም በማለት ተቃውመዋል።
ችሎቱም አቶ ተስፋዬ በተጨማሪነት የተጠረጠሩበት ወንጀል በተብራራ መልኩ እንዲቀርብና ፖሊስ የጠየቀውን 14 ቀን በመፍቀድ ለህዳር 24 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ምንጭ:- ፋና ብሮድካስቲንግ
@YeneTube @Fikerassefa
ፖሊስ አቶ ተስፋዬ ኡርጌን በተጨማሪነት በሰብዓዊ #መብት_ጥሰትና በሙስና ወንጀል ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ
መርማሪ ፖሊስ የቀድሞው የብሄራዊ መረጃና ደህንነት የስራ ባልደረባ አቶ ተስፋዬ ኡርጌን በተጨማሪነት በሰብዓዊ መብት ጥሰትና በሙስና ወንጀል ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
አቶ ተስፋዬ ኡርጌ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ የወንጀል #ችሎት ቀርበዋል።
መርማሪ ፖሊስም የቀድሞውን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት የስራ ባልደረባ በተጨማሪነት በሰብዓዊ መብት ጥሰትና በሙስና ወንጀል ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸው ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።
አቶ ተስፋዬ የደህንነት መምሪያ ሀላፊ ሆነው ሲሰሩ ሰዎችን በሽብር ተጠርጥራችኋል በሚል በስውር እስር ቤት በማሰርና በማሰቃየት፥ እርቃናቸውን በካቴና አስረው ቆሻሻ ገንዳ ውስጥ በማቆየት፣ ግለሰቦችን ባልተገባ መልኩ ለሽብር መልምለው ወደ ኤርትራ በመላክ እንደጠረጠራቸው ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ገልጿል።
ከዚህ ባለፈም በሽብር ከተጠረጠሩ ሰዎች ላይ ገንዘብ በመቀበል እና በሀዋላ ከተጠርጣሪዎች ላይ ህገ ወጥ ገንዘብ በመቀበል በሰብዓዊ መብት ጥሰትና በሙስና ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁም ብሏል መርማሪ ፖሊስ።
ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅም 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀን ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
አቶ ተስፋዬ በሰጡት ምላሽ እርሳቸው የተጠረጠሩበት ጉዳይ በግልጽና በተናጠል እንዳልቀረበ በመግለጽ፥ እርሳቸውን ለመያዝ በቂና ዝርዝር ጉዳይ አለመኖሩን አስረድተዋል።
በተጨማሪም ሀብት የመፍጠር ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው ሃብት ማፍራታቸውንና ለአራት ወራት ፍርድ ቤት እየተመላለሱ መሆኑን በመጥቀስ፥ ሃብት ከማፍራት ጋር ተያይዞ ሀምሌ 5 ቀን 2010 ዓ.ም ቤታቸው መበርበሩንና ምርመራው በወቅቱ ማለቅ ነበረበት ብለዋል።
አሁን ላይ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀው ተጨማሪ ጊዜም ሊሰጥ አይገባም በማለት ተቃውመዋል።
ችሎቱም አቶ ተስፋዬ በተጨማሪነት የተጠረጠሩበት ወንጀል በተብራራ መልኩ እንዲቀርብና ፖሊስ የጠየቀውን 14 ቀን በመፍቀድ ለህዳር 24 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ምንጭ:- ፋና ብሮድካስቲንግ
@YeneTube @Fikerassefa
አስር የቀድሞ መርማሪዎች አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈፅመዋል የሚል ክስ ቀረበባቸው። ‼️
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ከ2002 እስከ 2010 ዓ.ም. ባሉት አመታት የፌድራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል መርማሪ የነበሩ አስር ሰዎችን በሰብዓዊ #መብት #ጥሰት መክሰሱን አስታወቀ።
የቀድሞዎቹ ፌድራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት በምርመራ ወቅት ተጠርጣሪዎችን በኤሌክትሪክ ገርፈዋል፤ በብረት ጉጠት የጣት #ጥፍር_ነቅለዋል፤ አፋቸው ውስጥ #ሽጉጥ ከተዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል።
ተከሳሾች በኦሮሞ ነፃነት ግንባር እና በአርበኞች ግንቦት ሰባት አባልነት የጠረጠሯቸውን ግለሰቦች «በግንብ ላይ በተሰካ ብረት ላይ ለረጅም ጊዜ እጃቸውን በካቴና በማሰርና በማንጠልጠል፤ ከግድግዳ ጋር በማጋጨት፣ ፊታቸውን በጥፊ በመምታት፣ የፊትንና የጺም ጸጉር ፒንሳ በሚመስል ነገር በመንጨት እንዲሁም ራሳቸውን በሚስትቱበት ወቅት ውኃ በመድፋት በግድ የአሸባሪ ድርጅቶች አባል መሆናቸውን እንዲያምኑ በማድረግ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ፈፅመዋል» ሲል የፌድራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።
አስሩ ተከሳሾች ኮማንደር ዓለማየሁ ኃይሉ፣ ዋና ሳጅን እቴነሽ አረፋይኔ ወልደ ሚካኤል፣ ዋና ሳጅን ኪዳኔ አሰፋ ሸማ፤ ዋና ሳጅን ርዕሶም ክህሽን፣ ኢንስፔክተር ፈይሳ ደሜ በዳዳ፣ ምክትል ኢንስፔክተር የሱፍ ሐሰን መኮንን፣ ምክትል ኢንስፔክተር ምንላርግልህ ጥላሁን፣ ረዳት ኢንስፔክተር መንግሥቱ ታደሰ አየለ፣ ረዳት ኢንስፔክተር ኃይሉ ሁንዴ እና ኢንስፔክተር ስንታየሁ ፈጠነ ለገሰ ናቸው።
ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስሩ የቀድሞ መርማሪዎች በአጠቃላይ 78 ክሶች እንደተመሰረተባቸው አስታውቋል። ከክሶቹ መካከል «እጃቸውን በካቴና በማሰር፣ በጣት እንዲቆሙ በማድረግ፣ በኤሌትሪክ ገመድ በመግረፍና በግንባር ግድግዳ በማስገፋት፣ በብልታቸው ላይ 2 እስከ 4 ሊትር ሃይላንድ ውኃ በማንጠልጠል ከ2 ሰዓት እስከ 3 ሰዓት እንዲቆዩ በማስደረግ፣ በኤሌክትሪክ በማስነዘር ፣ ብልታቸውን በፒንሳ በመሳብ የጭንቀት ህመም እና ተያያዥ ድብርት እንዲደርስባቸው አድርገዋል» የሚሉት ይገኙበታል።
ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስሩ ተከሳሾች «በቀዝቃዛና ጨለማ እስር ቤት ውስጥ በማሰር፣ በእግራቸው መሀል እንጨት አስገብቶ በመገልበጥ የውስጥ እግራቸውን በኤሌትሪክ ገመድ በመግረፍ፣ በምርመራ ክፍሉ በተዘጋጀ ሚስማር ላይ በማንጠልጠል ለረዥም ሰዓት እንዲቆዩ በማድረግ፤ አድካሚ እና ከባድ ስፖርት በማሰራት፤ አፍንጫ ውስጥ እስክሪብቶ በመክተት፣ መቀመጫቸውን እና ጀርባቸውን ውኃ እየደፉ በኤሌክትሪክ ሽቦ በመግረፍ፣ ጺማቸውን በመንጨት ፣ብልታቸውን በቀጭን ሲባጎ በማሰር በግል ተበዳዮች ላይ ሞራላዊና ስነ-ልቦናዊ ጉዳት አስከትለዋል» ብሏል።
ተከሳሾች በፌድራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 12ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ክስ መቀበላቸውን ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል። በመጪው የካቲት 22 ቀን 2011 ዓ.ም. ክሱ በችሎት የሚነበብ ሲሆን በተከሳሾች የዋስትና መብት ላይ ክርክር ይደረጋል።
ምንጭ፦ DW
@Yenetube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ከ2002 እስከ 2010 ዓ.ም. ባሉት አመታት የፌድራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል መርማሪ የነበሩ አስር ሰዎችን በሰብዓዊ #መብት #ጥሰት መክሰሱን አስታወቀ።
የቀድሞዎቹ ፌድራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት በምርመራ ወቅት ተጠርጣሪዎችን በኤሌክትሪክ ገርፈዋል፤ በብረት ጉጠት የጣት #ጥፍር_ነቅለዋል፤ አፋቸው ውስጥ #ሽጉጥ ከተዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል።
ተከሳሾች በኦሮሞ ነፃነት ግንባር እና በአርበኞች ግንቦት ሰባት አባልነት የጠረጠሯቸውን ግለሰቦች «በግንብ ላይ በተሰካ ብረት ላይ ለረጅም ጊዜ እጃቸውን በካቴና በማሰርና በማንጠልጠል፤ ከግድግዳ ጋር በማጋጨት፣ ፊታቸውን በጥፊ በመምታት፣ የፊትንና የጺም ጸጉር ፒንሳ በሚመስል ነገር በመንጨት እንዲሁም ራሳቸውን በሚስትቱበት ወቅት ውኃ በመድፋት በግድ የአሸባሪ ድርጅቶች አባል መሆናቸውን እንዲያምኑ በማድረግ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ፈፅመዋል» ሲል የፌድራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።
አስሩ ተከሳሾች ኮማንደር ዓለማየሁ ኃይሉ፣ ዋና ሳጅን እቴነሽ አረፋይኔ ወልደ ሚካኤል፣ ዋና ሳጅን ኪዳኔ አሰፋ ሸማ፤ ዋና ሳጅን ርዕሶም ክህሽን፣ ኢንስፔክተር ፈይሳ ደሜ በዳዳ፣ ምክትል ኢንስፔክተር የሱፍ ሐሰን መኮንን፣ ምክትል ኢንስፔክተር ምንላርግልህ ጥላሁን፣ ረዳት ኢንስፔክተር መንግሥቱ ታደሰ አየለ፣ ረዳት ኢንስፔክተር ኃይሉ ሁንዴ እና ኢንስፔክተር ስንታየሁ ፈጠነ ለገሰ ናቸው።
ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስሩ የቀድሞ መርማሪዎች በአጠቃላይ 78 ክሶች እንደተመሰረተባቸው አስታውቋል። ከክሶቹ መካከል «እጃቸውን በካቴና በማሰር፣ በጣት እንዲቆሙ በማድረግ፣ በኤሌትሪክ ገመድ በመግረፍና በግንባር ግድግዳ በማስገፋት፣ በብልታቸው ላይ 2 እስከ 4 ሊትር ሃይላንድ ውኃ በማንጠልጠል ከ2 ሰዓት እስከ 3 ሰዓት እንዲቆዩ በማስደረግ፣ በኤሌክትሪክ በማስነዘር ፣ ብልታቸውን በፒንሳ በመሳብ የጭንቀት ህመም እና ተያያዥ ድብርት እንዲደርስባቸው አድርገዋል» የሚሉት ይገኙበታል።
ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስሩ ተከሳሾች «በቀዝቃዛና ጨለማ እስር ቤት ውስጥ በማሰር፣ በእግራቸው መሀል እንጨት አስገብቶ በመገልበጥ የውስጥ እግራቸውን በኤሌትሪክ ገመድ በመግረፍ፣ በምርመራ ክፍሉ በተዘጋጀ ሚስማር ላይ በማንጠልጠል ለረዥም ሰዓት እንዲቆዩ በማድረግ፤ አድካሚ እና ከባድ ስፖርት በማሰራት፤ አፍንጫ ውስጥ እስክሪብቶ በመክተት፣ መቀመጫቸውን እና ጀርባቸውን ውኃ እየደፉ በኤሌክትሪክ ሽቦ በመግረፍ፣ ጺማቸውን በመንጨት ፣ብልታቸውን በቀጭን ሲባጎ በማሰር በግል ተበዳዮች ላይ ሞራላዊና ስነ-ልቦናዊ ጉዳት አስከትለዋል» ብሏል።
ተከሳሾች በፌድራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 12ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ክስ መቀበላቸውን ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል። በመጪው የካቲት 22 ቀን 2011 ዓ.ም. ክሱ በችሎት የሚነበብ ሲሆን በተከሳሾች የዋስትና መብት ላይ ክርክር ይደረጋል።
ምንጭ፦ DW
@Yenetube @FikerAssefa