Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
❤2
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለፀጥታ ሥጋት የሆኑ የውጭ አገር ስደተኞች መኖራቸውን አስታወቀ!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምን በተመለከተ የተለየ አቋም ይዘው ለፀጥታ ሥጋት በመሆን የሚንቀሳቀሱ የውጭ አገር ስደተኞች በከተማዋ እንዳሉ አስታወቀ፡፡የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለፀጥታ ሥጋት የሆኑ ዜጎች መኖራቸውን ያስታወቀው 4ኛ መደበኛ ጉባዔውን ከሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ በዓድዋ ሙዚየም ሲያካሂድ ነው፡፡
በጉባዔው የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው በሰጡት አስተያየት፣ ከአንዳንድ ጎረቤት አገሮች አዲስ አበባ መጥተው በሐሰተኛ የገንዘብ ኅትመትና የገንዘብ ዝውውር የማታለልና የማጭበርበር ወንጀል የሚሳተፉ የውጭ ዜጎች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡
ወንጀለኞቹ ሐሰተኛ ዶላር በማተም ድርጊት እንደሚሳተፉ፣ መኖሪያቸውን በከተማዋ ካደረጉ በርካታ ስድተኞች ውስጥ በግድያና በዝርፊያ የሚሳተፉ እንዳሉም አስረድተዋል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ: https://ethiopianreporter.com/143314/
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምን በተመለከተ የተለየ አቋም ይዘው ለፀጥታ ሥጋት በመሆን የሚንቀሳቀሱ የውጭ አገር ስደተኞች በከተማዋ እንዳሉ አስታወቀ፡፡የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለፀጥታ ሥጋት የሆኑ ዜጎች መኖራቸውን ያስታወቀው 4ኛ መደበኛ ጉባዔውን ከሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ በዓድዋ ሙዚየም ሲያካሂድ ነው፡፡
በጉባዔው የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው በሰጡት አስተያየት፣ ከአንዳንድ ጎረቤት አገሮች አዲስ አበባ መጥተው በሐሰተኛ የገንዘብ ኅትመትና የገንዘብ ዝውውር የማታለልና የማጭበርበር ወንጀል የሚሳተፉ የውጭ ዜጎች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡
ወንጀለኞቹ ሐሰተኛ ዶላር በማተም ድርጊት እንደሚሳተፉ፣ መኖሪያቸውን በከተማዋ ካደረጉ በርካታ ስድተኞች ውስጥ በግድያና በዝርፊያ የሚሳተፉ እንዳሉም አስረድተዋል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ: https://ethiopianreporter.com/143314/
@YeneTube @FikerAssefa
❤18😁9🔥1
ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 4ሺህ 700 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ማስገባቱን ቢሮው አስታወቀ!
ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2017 በጀት ዓመት 1ሺህ 500 ኪሎ ግራም ወርቅ ወደ ብሔራዊ ባንክ ለማስገባት አቅዶ 4ሺህ 700 ኪሎ ግራም ወርቅ ማስገባቱን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ አድማሱ ሞርካ፤ ከዕቅዱ በላይ የተከናወነበት ምክንያት መንግስት ለወርቅ አቅራቢዎች ያደረገው “ማበረታቻ እና ህገ-ወጥ ግብይት መቀነስ ትልቅ አስተዋፅኦ ነበራቸው" ሲሉ ለኢዜአ ተናግረዋል።
በተለይም በሀገር አቀፍ ደረጃ በተተገበረው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ዘርፉ እንዲነቃቃና አምራቹ ተጠቃሚ እንዲሆን ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ጠቅሰዋል።በክልሉ የተመረተው ወርቅ በአነስተኛና ባህላዊ ወርቅ አምራቾች መሆኑን ገልጸው፤ ይህም የህብረተሰቡን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት አሳድጓል ነው ያሉት።
ከወርቅ በተጨማሪ የድንጋይ ከሰልና እምነበረድ በስፋት እየተመረተ መሆኑን ጠቅሰው በክልሉ የሚገኙ የማዕድን ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።
አቶ አድማሱ ከማዕድን ምርቱ 49 ሚሊዮን ብር መሰበሰቡንም ጠቅሰው፤ በቀጣይ ትላልቅ ካምፓኒዎችን በመጋበዝ በክልሉ በማዕድን ዘርፍ ለማሰማራት ዝግጅት መጠናቀቁንም አስታውቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2017 በጀት ዓመት 1ሺህ 500 ኪሎ ግራም ወርቅ ወደ ብሔራዊ ባንክ ለማስገባት አቅዶ 4ሺህ 700 ኪሎ ግራም ወርቅ ማስገባቱን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ አድማሱ ሞርካ፤ ከዕቅዱ በላይ የተከናወነበት ምክንያት መንግስት ለወርቅ አቅራቢዎች ያደረገው “ማበረታቻ እና ህገ-ወጥ ግብይት መቀነስ ትልቅ አስተዋፅኦ ነበራቸው" ሲሉ ለኢዜአ ተናግረዋል።
በተለይም በሀገር አቀፍ ደረጃ በተተገበረው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ዘርፉ እንዲነቃቃና አምራቹ ተጠቃሚ እንዲሆን ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ጠቅሰዋል።በክልሉ የተመረተው ወርቅ በአነስተኛና ባህላዊ ወርቅ አምራቾች መሆኑን ገልጸው፤ ይህም የህብረተሰቡን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት አሳድጓል ነው ያሉት።
ከወርቅ በተጨማሪ የድንጋይ ከሰልና እምነበረድ በስፋት እየተመረተ መሆኑን ጠቅሰው በክልሉ የሚገኙ የማዕድን ሀብቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።
አቶ አድማሱ ከማዕድን ምርቱ 49 ሚሊዮን ብር መሰበሰቡንም ጠቅሰው፤ በቀጣይ ትላልቅ ካምፓኒዎችን በመጋበዝ በክልሉ በማዕድን ዘርፍ ለማሰማራት ዝግጅት መጠናቀቁንም አስታውቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
❤19👎6🔥1👀1
በጅቡቲ የሚገኘው የሆራይዘን ነዳጅ ማጠራቀሚያ ተርሚናል ጥገና አለመከናወኑ የነዳጅ ጭነቱ እንዲቀንስ ምክንያት ሆኗል ተባለ!
ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባው ነዳጅ ጅቡቲ በሚገኘው የሆራይዘን ነዳጅ ማጠራቀሚያ ተርሚናል በኩል መሆኑን ተከትሎ፤ የማጠራቀሚያ ተርሚናሉ ጥገና ባለመከናወኑ የነዳጅ ጭነቱ እንዲቀንስ ማድረጉን የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት አስታውቋል፡፡የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ እስመላለም ምህረቱ ለአሐዱ እንደገለጹት ከሆነ፤ ችግሩን ለመፍታት ተጨማሪ 2 የነዳጅ ተርሚናሎችን እንዲኖሩ ከጅቡቲ መንግሥት ጋር ውይይት እንደተደረገ ይገኛል።
በጅቡቲ ከውጭ የሚገባው ነዳጅ በሆራይዘን ተርሚናል በኩል ከመርከብ ወርዶ ወደ ተሽከርካሪዎች እንደሚጫን ያስረዱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ዴፖው በምስረታው ጊዜ 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን እንደነበርና አሁን ያለው ፍላጎት 4 ነጥብ 2 እንደደረሰ ተናግረዋል።ነዳጅ ማጠራቀሚያው ከ20 ዓመት በፊት የተቋቋመ እንደሆነ የተናገሩ ሲሆን፤ ረዘም ላለ ጊዜ የነዳጅ ማውረድ እና ጭነት አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ተርሚናል በመሆኑ በፖምፕ እና የሲስተም ክፍተቶች በመኖራቸው በነዳጅ የጭነት አገልግሎቱ ላይ አልፎ አልፎ ጭነቱ እንዲቀንስ ምክንያት ስለመሆኑ ተናግረዋል።
ዋና ሥራ አስፈፃሚው ነዳጅ ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ የሚጓጓዝበት መንገድ ለተሽከርካሪዎች ምቹ አለመሆኑን በማንሳት፤ በአሽከርካሪዎች ዘንድ ቅሬታ እንደሚነሳም ለአሐዱ ተናግረዋል።አክለውም ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገባ ከተደረገ በኃላ በሕገ-ወጥ መንገድ የሚደረግ የነዳጅ ዝውውር እና የነዳጅ ሽያጭ ለነዳጅ አቅርቦቱ ላይ እጥረት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል ብለዋል።
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባው ነዳጅ ጅቡቲ በሚገኘው የሆራይዘን ነዳጅ ማጠራቀሚያ ተርሚናል በኩል መሆኑን ተከትሎ፤ የማጠራቀሚያ ተርሚናሉ ጥገና ባለመከናወኑ የነዳጅ ጭነቱ እንዲቀንስ ማድረጉን የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት አስታውቋል፡፡የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ እስመላለም ምህረቱ ለአሐዱ እንደገለጹት ከሆነ፤ ችግሩን ለመፍታት ተጨማሪ 2 የነዳጅ ተርሚናሎችን እንዲኖሩ ከጅቡቲ መንግሥት ጋር ውይይት እንደተደረገ ይገኛል።
በጅቡቲ ከውጭ የሚገባው ነዳጅ በሆራይዘን ተርሚናል በኩል ከመርከብ ወርዶ ወደ ተሽከርካሪዎች እንደሚጫን ያስረዱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ዴፖው በምስረታው ጊዜ 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን እንደነበርና አሁን ያለው ፍላጎት 4 ነጥብ 2 እንደደረሰ ተናግረዋል።ነዳጅ ማጠራቀሚያው ከ20 ዓመት በፊት የተቋቋመ እንደሆነ የተናገሩ ሲሆን፤ ረዘም ላለ ጊዜ የነዳጅ ማውረድ እና ጭነት አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ተርሚናል በመሆኑ በፖምፕ እና የሲስተም ክፍተቶች በመኖራቸው በነዳጅ የጭነት አገልግሎቱ ላይ አልፎ አልፎ ጭነቱ እንዲቀንስ ምክንያት ስለመሆኑ ተናግረዋል።
ዋና ሥራ አስፈፃሚው ነዳጅ ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ የሚጓጓዝበት መንገድ ለተሽከርካሪዎች ምቹ አለመሆኑን በማንሳት፤ በአሽከርካሪዎች ዘንድ ቅሬታ እንደሚነሳም ለአሐዱ ተናግረዋል።አክለውም ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገባ ከተደረገ በኃላ በሕገ-ወጥ መንገድ የሚደረግ የነዳጅ ዝውውር እና የነዳጅ ሽያጭ ለነዳጅ አቅርቦቱ ላይ እጥረት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል ብለዋል።
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
❤23
ኤክሳይዝ ታክስ የሚከፈልባቸው ምርቶች ምልክት እንዲለጠፍባቸው የሚያስገድድ መመርያ ወጣ።
ቢው ከአገራዊ ጠቅላላ ምርት 1.4 በመቶ እንዲሸፍን መታቀዱ ተሰምቷል።የኤክሳይዝ ታክስ እንዲከፈልባቸው በገንዘብ ሚኒስቴር የተመረጡ ምርቶች፣ ምልክት እንዲለጠፍባቸው የሚያስገድድ መመርያ ወጣ፡፡
በኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ቁጥር 1186/2012 (በተሻሻለው) አንቀጽ 29 እና 42 (2) በተሰጠው ሥልጣን መሠረት፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ያዘጋጀው ‹‹የኤክሳይዝ ምልክቶች አስተዳደር ሥርዓትን ለመወሰን የወጣው መመርያ ቁጥር 1072/2017››፣ የኤክሳይዝ ታክስ በሚከፈልባቸው በተለይ በአልኮልና በትምባሆ ምርቶች ላይ የሚደረገውን ክትትልና ቁጥጥር የሚያጠናክር የኤክሳይዝ ምልክት እንዲለጠፍባቸው አስገዳጅ ሆኗል።
የአልኮል መጠጦች፣ አልኮል አልባ ቢራ፣ የወይን ጠጅ ወይም የተጣራ አልኮል የታከለበት ወይን ጠጅ፣ የአልኮል መጠናቸው ከ0.5 በመቶ በላይ የሆነ ተመሳሳይ ምርቶች የኤክሳይዝ ምልክት ሊደረግባቸው እንደሚገባ በመመርያው ተደንግጓል።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ቢው ከአገራዊ ጠቅላላ ምርት 1.4 በመቶ እንዲሸፍን መታቀዱ ተሰምቷል።የኤክሳይዝ ታክስ እንዲከፈልባቸው በገንዘብ ሚኒስቴር የተመረጡ ምርቶች፣ ምልክት እንዲለጠፍባቸው የሚያስገድድ መመርያ ወጣ፡፡
በኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ቁጥር 1186/2012 (በተሻሻለው) አንቀጽ 29 እና 42 (2) በተሰጠው ሥልጣን መሠረት፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ያዘጋጀው ‹‹የኤክሳይዝ ምልክቶች አስተዳደር ሥርዓትን ለመወሰን የወጣው መመርያ ቁጥር 1072/2017››፣ የኤክሳይዝ ታክስ በሚከፈልባቸው በተለይ በአልኮልና በትምባሆ ምርቶች ላይ የሚደረገውን ክትትልና ቁጥጥር የሚያጠናክር የኤክሳይዝ ምልክት እንዲለጠፍባቸው አስገዳጅ ሆኗል።
የአልኮል መጠጦች፣ አልኮል አልባ ቢራ፣ የወይን ጠጅ ወይም የተጣራ አልኮል የታከለበት ወይን ጠጅ፣ የአልኮል መጠናቸው ከ0.5 በመቶ በላይ የሆነ ተመሳሳይ ምርቶች የኤክሳይዝ ምልክት ሊደረግባቸው እንደሚገባ በመመርያው ተደንግጓል።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
❤10👍7👎1
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ዶላር ውጪ በሌሎች ምንዛሬዎች ለመገበያየት እየሰራች መሆኑን ገለጸች!
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ዶላር ውጪ በሌሎች ምንዛሬዎች ለመገበያየት በሚያስችሏት እርምጃዎች ላይ እየሰራች መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ገለጸ።በዚህም በተለያዩ ጊዜያት ከሀገራት ጋር የተደረሱ ስምምነቶች መኖራቸውም ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ እንዳስታወቀው፤ ውሳኔው ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ለማጠናከር፣ የንግድ ሚዛንን ለመጠበቅ እና በአንድ ምንዛሪ ላይ የመመካትን አሉታዊ ተፅእኖ ለመከላከል ያለመ ነው።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ባሳለፍነው አርብ ዕለት ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ኢትዮጵያ እንደ የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ካሉ ሀገሮች ጋር በምንዛሬያቸው እንዲገበያዩ የሚያስችል ስምምነት ላይ መድረሷን ተናግረዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው፤ መንግስት የኢትዮጵያን ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብርን ለማመቻቸት ከአሜሪካን ዶላር ውጪ በሌሎች ምንዛሬዎች ለመገበያየት በሚያስችሉ መንገዶች ላይ እየሰራ ነው ብለዋል።
ይህ እርምጃ የሀገሪቱን የውጭ ገበያዎች መዳረሻ ለማስፋት ያለመ ነው ብለዋል። አክለውም ከአሜሪካ ዶላር ውጪ ተጨማሪ ምንዛሬዎች መኖራቸው አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ሲሉ ተናግረዋል።
Via AS/EBC
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ዶላር ውጪ በሌሎች ምንዛሬዎች ለመገበያየት በሚያስችሏት እርምጃዎች ላይ እየሰራች መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ገለጸ።በዚህም በተለያዩ ጊዜያት ከሀገራት ጋር የተደረሱ ስምምነቶች መኖራቸውም ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ እንዳስታወቀው፤ ውሳኔው ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ለማጠናከር፣ የንግድ ሚዛንን ለመጠበቅ እና በአንድ ምንዛሪ ላይ የመመካትን አሉታዊ ተፅእኖ ለመከላከል ያለመ ነው።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ባሳለፍነው አርብ ዕለት ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ኢትዮጵያ እንደ የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ካሉ ሀገሮች ጋር በምንዛሬያቸው እንዲገበያዩ የሚያስችል ስምምነት ላይ መድረሷን ተናግረዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው፤ መንግስት የኢትዮጵያን ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብርን ለማመቻቸት ከአሜሪካን ዶላር ውጪ በሌሎች ምንዛሬዎች ለመገበያየት በሚያስችሉ መንገዶች ላይ እየሰራ ነው ብለዋል።
ይህ እርምጃ የሀገሪቱን የውጭ ገበያዎች መዳረሻ ለማስፋት ያለመ ነው ብለዋል። አክለውም ከአሜሪካ ዶላር ውጪ ተጨማሪ ምንዛሬዎች መኖራቸው አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ሲሉ ተናግረዋል።
Via AS/EBC
@YeneTube @FikerAssefa
❤28👍16😁9🔥1
ኬንያ ለአፍሪካ አገሮች የቪዛ ገደቦችን ሙሉ በሙሉ አነሳች!
ኬንያ ለአፍሪካ እና ለአብዛኛዎቹ የካሪቢያን አገሮች ዜጎች የቪዛ መስፈርቶችን ሙሉ በሙሉ መሰረዟን አስታውቃለች። ይህ ውሳኔ የኤሌክትሮኒክ የጉዞ ፈቃድ ረጅም ቅጾች መሙላት ወይም የቪዛ ክፍያ መክፈል ሳያስፈልግ ወደ ኬንያ መግባት ያስችላል።
ይህን ተከትሎ ብቁ ተጓዦችም ያለምንም ችግር ወደ ድንበር በመሄድ ወደ አገር ውስጥ መግባት ተብሏል።
የዚህ አዲስ ፖሊሲ ትልቁ ተጠቃሚዎች የአፍሪካ አገሮች ዜጎች ሲሆኑ፣ በኬንያ እስከ ሁለት ወራት ድረስ የመቆየት መብት አግኝተዋል። በተጨማሪም፣ የምስራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ አባል አገራት ዜጎች አሁን ባሉት የነጻ እንቅስቃሴ ፕሮቶኮሎች መሠረት እስከ ስድስት ወራት ድረስ መቆየት ይችላሉ።
@YeneTube @FikerAssefa
ኬንያ ለአፍሪካ እና ለአብዛኛዎቹ የካሪቢያን አገሮች ዜጎች የቪዛ መስፈርቶችን ሙሉ በሙሉ መሰረዟን አስታውቃለች። ይህ ውሳኔ የኤሌክትሮኒክ የጉዞ ፈቃድ ረጅም ቅጾች መሙላት ወይም የቪዛ ክፍያ መክፈል ሳያስፈልግ ወደ ኬንያ መግባት ያስችላል።
ይህን ተከትሎ ብቁ ተጓዦችም ያለምንም ችግር ወደ ድንበር በመሄድ ወደ አገር ውስጥ መግባት ተብሏል።
የዚህ አዲስ ፖሊሲ ትልቁ ተጠቃሚዎች የአፍሪካ አገሮች ዜጎች ሲሆኑ፣ በኬንያ እስከ ሁለት ወራት ድረስ የመቆየት መብት አግኝተዋል። በተጨማሪም፣ የምስራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ አባል አገራት ዜጎች አሁን ባሉት የነጻ እንቅስቃሴ ፕሮቶኮሎች መሠረት እስከ ስድስት ወራት ድረስ መቆየት ይችላሉ።
@YeneTube @FikerAssefa
❤39👎1
የሰራተኞች ማህበራት 'ፌስታል ይዘው ምግብ የሚለምኑ ሰራተኞችን ማሳየት እንችላለን' አሉ!
የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን፣ አዲስ በታቀደው የፌዴራል ገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ገለጸ።
ኮንፌዴሬሽኑ፣ ፓርላማው ከፈቀደ ከስራ ሰዓት በኋላ ሆቴሎች አካባቢ ፌስታል ይዘው ምግብ የሚለምኑ ሰራተኞችን ማሳየት እንደሚችል አስደንጋጭ በሆነ መልኩ አስታወቀ።
የኮንፌዴሬሽኑ ዋና ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ፣ አሁን ያለው የኑሮ ውድነት ሰራተኞችን በቀን አንድ ጊዜ እንኳ በአግባቡ እንዳይመገቡ ማድረጉን ገልጸዋል።
በረቂቅ አዋጁ የገቢ ግብር መነሻ ከ2,000 ብር ጀምሮ በ15 በመቶ ግብር እንዲከፈል የቀረበው ሀሳብ፣ የኑሮ ውድነትን ያላገናዘበ እና ሰራተኞችን ለከፋ ችግር የሚዳርግ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
አቶ ካሳሁን፣ አንድ ድርጅት ከትርፉ 35 በመቶ ግብር ሲከፍል፣ ሰራተኛው ደግሞ ከሚበላው ደሞዙ ላይ 35 በመቶ መክፈሉ ፍትሃዊ አይደለም በማለት የግብር ፍትሃዊነት እንዲረጋገጥ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ረቂቅ አዋጁ ለሁለት ዓመታት በጥናት ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጿል። የ2,000 ብር መነሻ የተደረገበት ምክንያትም የአገሪቱ የመክፈል አቅም ዝቅተኛ በመሆኑ እንደሆነ ተብራርቷል።
ሚኒስትሩ አሁን ያለው የኑሮ ውድነት በግብር ብቻ የመጣ ሳይሆን፣ ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ምክንያትም እንደሆነ ጠቁመው፣ መንግስት የደሞዝ ጭማሪ በማድረግ ድጋፍ እያደረገ ነው ብለዋል። ሸገር እንደዘገበው የግብር መነሻውን ከዚህ በላይ ከፍ ማድረግ ከመንግስት ገቢ ላይ ከፍተኛ ጫና እንደሚፈጥርም አስጠንቅቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን፣ አዲስ በታቀደው የፌዴራል ገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ገለጸ።
ኮንፌዴሬሽኑ፣ ፓርላማው ከፈቀደ ከስራ ሰዓት በኋላ ሆቴሎች አካባቢ ፌስታል ይዘው ምግብ የሚለምኑ ሰራተኞችን ማሳየት እንደሚችል አስደንጋጭ በሆነ መልኩ አስታወቀ።
የኮንፌዴሬሽኑ ዋና ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ፣ አሁን ያለው የኑሮ ውድነት ሰራተኞችን በቀን አንድ ጊዜ እንኳ በአግባቡ እንዳይመገቡ ማድረጉን ገልጸዋል።
በረቂቅ አዋጁ የገቢ ግብር መነሻ ከ2,000 ብር ጀምሮ በ15 በመቶ ግብር እንዲከፈል የቀረበው ሀሳብ፣ የኑሮ ውድነትን ያላገናዘበ እና ሰራተኞችን ለከፋ ችግር የሚዳርግ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
አቶ ካሳሁን፣ አንድ ድርጅት ከትርፉ 35 በመቶ ግብር ሲከፍል፣ ሰራተኛው ደግሞ ከሚበላው ደሞዙ ላይ 35 በመቶ መክፈሉ ፍትሃዊ አይደለም በማለት የግብር ፍትሃዊነት እንዲረጋገጥ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ረቂቅ አዋጁ ለሁለት ዓመታት በጥናት ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጿል። የ2,000 ብር መነሻ የተደረገበት ምክንያትም የአገሪቱ የመክፈል አቅም ዝቅተኛ በመሆኑ እንደሆነ ተብራርቷል።
ሚኒስትሩ አሁን ያለው የኑሮ ውድነት በግብር ብቻ የመጣ ሳይሆን፣ ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ምክንያትም እንደሆነ ጠቁመው፣ መንግስት የደሞዝ ጭማሪ በማድረግ ድጋፍ እያደረገ ነው ብለዋል። ሸገር እንደዘገበው የግብር መነሻውን ከዚህ በላይ ከፍ ማድረግ ከመንግስት ገቢ ላይ ከፍተኛ ጫና እንደሚፈጥርም አስጠንቅቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
❤39😭15
የገቢ ግብር መነሻ ገቢ ወደ 5,000 ብር ከፍ እንዲል ጥያቄ ቀረበ!
የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ፣ የኑሮ ውድነትን ታሳቢ በማድረግ የገቢ ግብር መነሻ ገቢ ከ2,000 ብር ወደ 5,000 ብር ከፍ እንዲል ጠንካራ ጥያቄ ቀርቧል። በአሁኑ ረቂቅ አዋጅ መሰረት፣ ከ2,000 ብር በላይ በሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር እንዲከፈል ሀሳብ ቀርቧል።
ይህ የተገለጸው በፓርላማው የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በተካሄደው ውይይት ላይ ሲሆን፣ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ፣ የአዋጁ ማሻሻያ የመንግስትን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ እንደሚያግዝ ገልጸዋል።ከግብር ነፃ የሚሆነው ገቢ አሁን ባለው ማሻሻያ በ300% በማደግ ወደ 2,000 ብር ከፍ እንዲል የተደረገ ሲሆን፣ ከፍተኛው 35% ግብር የሚያርፍበት ገቢ ደግሞ ወደ 14,000 ብር ከፍ እንዲል ሆኗል።
በውይይቱ ወቅት፣ የገቢ ግብር መነሻው ከአምስት ሺህ ብር ጀምሮ እንዲሆን፣ ለአካል ጉዳተኞች በተለየ መልኩ ግብር እንዲቀነስ፣ እንዲሁም በተለያዩ የሙያና የንግድ ዘርፎች አንፃር በደንብ እንዲታይ የሚሉ አስተያየቶች ቀርበዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ፣ የኑሮ ውድነትን ታሳቢ በማድረግ የገቢ ግብር መነሻ ገቢ ከ2,000 ብር ወደ 5,000 ብር ከፍ እንዲል ጠንካራ ጥያቄ ቀርቧል። በአሁኑ ረቂቅ አዋጅ መሰረት፣ ከ2,000 ብር በላይ በሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር እንዲከፈል ሀሳብ ቀርቧል።
ይህ የተገለጸው በፓርላማው የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በተካሄደው ውይይት ላይ ሲሆን፣ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ፣ የአዋጁ ማሻሻያ የመንግስትን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ እንደሚያግዝ ገልጸዋል።ከግብር ነፃ የሚሆነው ገቢ አሁን ባለው ማሻሻያ በ300% በማደግ ወደ 2,000 ብር ከፍ እንዲል የተደረገ ሲሆን፣ ከፍተኛው 35% ግብር የሚያርፍበት ገቢ ደግሞ ወደ 14,000 ብር ከፍ እንዲል ሆኗል።
በውይይቱ ወቅት፣ የገቢ ግብር መነሻው ከአምስት ሺህ ብር ጀምሮ እንዲሆን፣ ለአካል ጉዳተኞች በተለየ መልኩ ግብር እንዲቀነስ፣ እንዲሁም በተለያዩ የሙያና የንግድ ዘርፎች አንፃር በደንብ እንዲታይ የሚሉ አስተያየቶች ቀርበዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
❤46👍9😭3
Forwarded from YeneTube
ፒያሳ የመጨረሻው ሱቅ እና ቤት ሽያጭ ❗️
ፒያሳ ሀገር ፍቅር ቲያትር እና ሚኒሊክ አደባባይ መሀል የንግድ ሱቆች
* የግል የሚያደርጉት የንግድ ሱቆች ፒያሳ ላይ ብቸኛው እየሸጠ ያለው ቴምር ሪልስቴት ነው
* ሚኒሊክ አደባባይ ጋር በመንግስት የሚሰራው የ አውቶብስ እና የታክሲ ተርሚናል አጠገብ
* በከተማው ከፍተኛ እንቅስቃሴ የሚደረግበት ቦታ ከተማው ላይ ሱቅ የፈረሰባቸው ነጋዴዎች የከተሙበት
* 4700 ካሬ ላይ ያረፈ ዘመናዊ እስኬሌተር የሚገጠምለት G+5 የሆነ የገበያ ማዕከል
* በ 1 ዓመት ከ 6 ወር የሚያልቅ ከፍለው እስኪጨርሱ በዶላርም ሆነ በግንባታ እቃዎች ግሽበት ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አይደረግም
* በወር ከ80,000 ብር በላይ የኪራይ ገቢ የሚኖራቸው
* ከ 900,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
ቴምር ሪልስቴት.......
ከሀገር ውጪ ለምትኖሩ ወገኖቻችን በሙሉ ካላችሁበት ሀገር ሆናችሁ ፕሮሰስ ማድረግ የምትችሉበትን እና መግዛት መዋዋል የምትችሉበትን መንገዶች አመቻችተናል!
ለበለጠ መረጃ በቀጥታ ወይም በዋትሳፕ ዋናው ቢሮ ይደውሉ
☎️ +251976195835
በዋትሳፕ ያገኙናል -
https://wa.me/251976195835
Telegram username
@Ruthtemersales
🙏🙏🙏
🌴🌴🌴
https://www.facebook.com/share/1ABkH3oH9x/
ፒያሳ ሀገር ፍቅር ቲያትር እና ሚኒሊክ አደባባይ መሀል የንግድ ሱቆች
* የግል የሚያደርጉት የንግድ ሱቆች ፒያሳ ላይ ብቸኛው እየሸጠ ያለው ቴምር ሪልስቴት ነው
* ሚኒሊክ አደባባይ ጋር በመንግስት የሚሰራው የ አውቶብስ እና የታክሲ ተርሚናል አጠገብ
* በከተማው ከፍተኛ እንቅስቃሴ የሚደረግበት ቦታ ከተማው ላይ ሱቅ የፈረሰባቸው ነጋዴዎች የከተሙበት
* 4700 ካሬ ላይ ያረፈ ዘመናዊ እስኬሌተር የሚገጠምለት G+5 የሆነ የገበያ ማዕከል
* በ 1 ዓመት ከ 6 ወር የሚያልቅ ከፍለው እስኪጨርሱ በዶላርም ሆነ በግንባታ እቃዎች ግሽበት ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አይደረግም
* በወር ከ80,000 ብር በላይ የኪራይ ገቢ የሚኖራቸው
* ከ 900,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
ቴምር ሪልስቴት.......
ከሀገር ውጪ ለምትኖሩ ወገኖቻችን በሙሉ ካላችሁበት ሀገር ሆናችሁ ፕሮሰስ ማድረግ የምትችሉበትን እና መግዛት መዋዋል የምትችሉበትን መንገዶች አመቻችተናል!
ለበለጠ መረጃ በቀጥታ ወይም በዋትሳፕ ዋናው ቢሮ ይደውሉ
☎️ +251976195835
በዋትሳፕ ያገኙናል -
https://wa.me/251976195835
Telegram username
@Ruthtemersales
🙏🙏🙏
🌴🌴🌴
https://www.facebook.com/share/1ABkH3oH9x/
❤7
Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
❤2
የኤርትራ መንግስት ተቃዋሚ የሆነው የቀይ ባህር አፋር በሰመራ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የታደሙበት ህዝባዊ ጉባኤ ማካሄዱ ተገለጸ!
- “በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ውጥረት መንገሱን ጠቁሞ የአፋር ህዝብ የጦርነት ሜዳ እንዳይሆን አስግቶናል” ብሏል
በኤርትራ በተቀዋሚነት የሚንቀሳቀሰው የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (RSADO) በአፋር ክልል ሰመራ-ሎጊያ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ በታደሙበት ሕዝባዊ ጉባኤ ሐምሌ 6 ቀን 2017 ዓ.ም በአፋር ክልል ሰመራ-ሎጊያ ከተማ ማካሄዱ ተገለጸ።
ድርጅቱ በኤርትራ የሚያደርገውን የትጥቅ ትግል እንቅስቃሴ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፤ጉባኤው የተዘጋጀው በቀይ ባሕር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እና በሌሎች የሲቪክ ማህበራት መሆኑም ተጠቁሟል።
“በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ባለስልጣናት መካከል የቃላት ጦርነትን ተከትሎ ባሁኑ ወቅት በድንበር አከባቢዎች ላይ ውጥረት መንገሱን ያመለከተው ድርጅቱ (RSADO) የቀይ ባሕር አፋር ህዝብ የጦርነት ሜዳ እንዳይሆን አስግቶናል” ሲል ገልጿል፡፡
አሁን ላይ በኤርትራ ያለው መንግስት ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ወደብ እንድትጠቀም ፍላጎት የለውም በማለት ስርዓቱን በመታገል የህዝባቸውንም ሆነ የኢትዮጵያን ፍላጎት ማስከበር ለነሱ በጎ አጋጣሚ መሆኑን የድርጅቱ ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ሀሩን አመላክተዋል፡፡
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
- “በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ውጥረት መንገሱን ጠቁሞ የአፋር ህዝብ የጦርነት ሜዳ እንዳይሆን አስግቶናል” ብሏል
በኤርትራ በተቀዋሚነት የሚንቀሳቀሰው የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (RSADO) በአፋር ክልል ሰመራ-ሎጊያ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ በታደሙበት ሕዝባዊ ጉባኤ ሐምሌ 6 ቀን 2017 ዓ.ም በአፋር ክልል ሰመራ-ሎጊያ ከተማ ማካሄዱ ተገለጸ።
ድርጅቱ በኤርትራ የሚያደርገውን የትጥቅ ትግል እንቅስቃሴ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፤ጉባኤው የተዘጋጀው በቀይ ባሕር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እና በሌሎች የሲቪክ ማህበራት መሆኑም ተጠቁሟል።
“በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ባለስልጣናት መካከል የቃላት ጦርነትን ተከትሎ ባሁኑ ወቅት በድንበር አከባቢዎች ላይ ውጥረት መንገሱን ያመለከተው ድርጅቱ (RSADO) የቀይ ባሕር አፋር ህዝብ የጦርነት ሜዳ እንዳይሆን አስግቶናል” ሲል ገልጿል፡፡
አሁን ላይ በኤርትራ ያለው መንግስት ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ወደብ እንድትጠቀም ፍላጎት የለውም በማለት ስርዓቱን በመታገል የህዝባቸውንም ሆነ የኢትዮጵያን ፍላጎት ማስከበር ለነሱ በጎ አጋጣሚ መሆኑን የድርጅቱ ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ሀሩን አመላክተዋል፡፡
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
❤23👎4🔥3😁1
ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን ሠራተኞቹ በኢትዮጵያ መከላከያ መገደላቸውን አስታወቀ!
ከአራት ዓመታት በፊት በትግራይ ጦርነት ወቅት በክልሉ የሰብዓዊ ተልእኮ ላይ የነበሩ ድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን (ኤምኤስኤፍ) ሶስት ሰራተኞች "ሆን ተብሎ እና በግልጽ ተለይተው" በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት "ያነጣጠረ ግድያ" እንደተፈጸመባቸው ድርጅቱ አስታወቀ።
የረድዔት ድርጅቱ ሰራተኞቹ በተገደሉበት መንገድ ላይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት 'ኮንቮይ' [ተሽከርካሪዎች] እንደነበር ማረጋገጡን እንዲሁም አንድ የጦሩ አዛዥ "ተኩስ" እና "አስወግዳቸው" የሚል ትዕዛዝ መስጠታቸውን ጠቁሟል።
አንድ የኤም.ኤስ.ኤፍ ከፍተኛ ኃላፊ ራኬል አዮራ "ሆን ተብሎ ነው የተገደሉት፤ ከአጥቂዎቻቸው ጋር ፊት ለፊት እየተያዩ ነበር እና በጣም በቅርብ ርቀት ብዙ ጊዜ በጥይት ተመተው ነበር" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ድርጅቱ ይህን ያስታወቀው ከአራት ዓመታት በፊት፣ ሰኔ 2013 ዓ.ም በትግራይ ክልል በሶስት ሰራተኞቹ ላይ "ሆን ተብሎ ያነጣጠረ" ግድያ መፈጸሙን አስመልክቶ በውስጣዊ ምርመራ የደረሰባቸውን ግኝቶች ይፋ ባደረገበት ወቅት ነው።
ሙሉ ዘገባው:
https://www.bbc.com/amharic/articles/cvg9zqgng55o
@YeneTube @FikerAssefa
ከአራት ዓመታት በፊት በትግራይ ጦርነት ወቅት በክልሉ የሰብዓዊ ተልእኮ ላይ የነበሩ ድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን (ኤምኤስኤፍ) ሶስት ሰራተኞች "ሆን ተብሎ እና በግልጽ ተለይተው" በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት "ያነጣጠረ ግድያ" እንደተፈጸመባቸው ድርጅቱ አስታወቀ።
የረድዔት ድርጅቱ ሰራተኞቹ በተገደሉበት መንገድ ላይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት 'ኮንቮይ' [ተሽከርካሪዎች] እንደነበር ማረጋገጡን እንዲሁም አንድ የጦሩ አዛዥ "ተኩስ" እና "አስወግዳቸው" የሚል ትዕዛዝ መስጠታቸውን ጠቁሟል።
አንድ የኤም.ኤስ.ኤፍ ከፍተኛ ኃላፊ ራኬል አዮራ "ሆን ተብሎ ነው የተገደሉት፤ ከአጥቂዎቻቸው ጋር ፊት ለፊት እየተያዩ ነበር እና በጣም በቅርብ ርቀት ብዙ ጊዜ በጥይት ተመተው ነበር" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ድርጅቱ ይህን ያስታወቀው ከአራት ዓመታት በፊት፣ ሰኔ 2013 ዓ.ም በትግራይ ክልል በሶስት ሰራተኞቹ ላይ "ሆን ተብሎ ያነጣጠረ" ግድያ መፈጸሙን አስመልክቶ በውስጣዊ ምርመራ የደረሰባቸውን ግኝቶች ይፋ ባደረገበት ወቅት ነው።
ሙሉ ዘገባው:
https://www.bbc.com/amharic/articles/cvg9zqgng55o
@YeneTube @FikerAssefa
😭28❤22👎3😁1
በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት ሸገር ዳቦ ከ260 ሚሊየን በላይ ዳቦ እንዳመረተ ተነገረ!
ሸገር ዳቦን ጨምሮ በመዲናችን አዲስ አበባ የሚገኙ በመንግስት እና በግል ባለሀብቶች ከተገነቡ 30 የሚሆኑ የዳቦ ፋብሪካዎች 26ቱ በስራ ላይ እንደሚገኙ በአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ ብርሀኑ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል።
በአዲስ አበባ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የሸገር ዳቦ የሽያጭ ቦታዎች እንዳሉ የሚገልፁት አቶ አሸናፊ ከዚህ በተጨማሪ በትምህርት ቤቶች ላይ ለሚከናወነው የተማሪዎች ምገባ ስነስርዓት ዳቦ እንደሚቀርብ ገልፀዋል። ለትምህርት ቤቶች ብቻ በቀን ከ800 ሺህ በላይ ዳቦ ለተማሪዎች እንደሚቀርብ በማንሳት ከዚህ ባሻገር ዳቦው ለሜቅዶንያ እና በየወረዳው ላሉ የምገባ ማዕከሎች እና ሱቆች ተደራሽነት እንደሆነ ገልጸዋል።
በአጠቃላይ በአመት በመዲናዋ ከ360 ሚሊየን በላይ ዳቦ እየተመረተ ሲሆን ከ260 ሚሊየን በላይ የሚሆነው ሸገር ዳቦ እንደሆነ የገለፁት አቶ አሸናፊ የከተማ አስተዳደሩ ከ 36 ቢሊየን ብር በላይ በየወሩ ድጎማ በማድረግ ለህብረተስቡ ዳቦ በዝቅተኛ ዋጋ እየተከፋፈለ እንዳለ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ በቅርቡ ሶስት የዳቦ ፋብሪካዎች ስራ እንደሚጀምሩም አክለዋል።
በተያያዛ ጉዳይ ብስራት "በዳቦ መጠን ማነስ ይታያል" በሚል ከከተማይቱ ነዋሪዎች የደረሰውን ቅሬታ ለአቶ አሸናፊ ብርሃኑ ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን ግራም በሚሰርቁ የዳቦ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ ገልፀው ነዋሪው እንደዚህ አይነት አጠራጣሪ ነገሮችን ሲያጋጥመውና የግራም ስርቆቶችን ሲመለከት በቢሮው ነፃ የስልክ መስመር 8588 ላይ በመደወል ጥቆማ መስጠት እንደሚችል ዳይሬክተሩ ጨምረው ገልጸዋል።
Via Bisrat FM
@YeneTube @FikerAssefa
ሸገር ዳቦን ጨምሮ በመዲናችን አዲስ አበባ የሚገኙ በመንግስት እና በግል ባለሀብቶች ከተገነቡ 30 የሚሆኑ የዳቦ ፋብሪካዎች 26ቱ በስራ ላይ እንደሚገኙ በአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ ብርሀኑ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል።
በአዲስ አበባ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የሸገር ዳቦ የሽያጭ ቦታዎች እንዳሉ የሚገልፁት አቶ አሸናፊ ከዚህ በተጨማሪ በትምህርት ቤቶች ላይ ለሚከናወነው የተማሪዎች ምገባ ስነስርዓት ዳቦ እንደሚቀርብ ገልፀዋል። ለትምህርት ቤቶች ብቻ በቀን ከ800 ሺህ በላይ ዳቦ ለተማሪዎች እንደሚቀርብ በማንሳት ከዚህ ባሻገር ዳቦው ለሜቅዶንያ እና በየወረዳው ላሉ የምገባ ማዕከሎች እና ሱቆች ተደራሽነት እንደሆነ ገልጸዋል።
በአጠቃላይ በአመት በመዲናዋ ከ360 ሚሊየን በላይ ዳቦ እየተመረተ ሲሆን ከ260 ሚሊየን በላይ የሚሆነው ሸገር ዳቦ እንደሆነ የገለፁት አቶ አሸናፊ የከተማ አስተዳደሩ ከ 36 ቢሊየን ብር በላይ በየወሩ ድጎማ በማድረግ ለህብረተስቡ ዳቦ በዝቅተኛ ዋጋ እየተከፋፈለ እንዳለ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ በቅርቡ ሶስት የዳቦ ፋብሪካዎች ስራ እንደሚጀምሩም አክለዋል።
በተያያዛ ጉዳይ ብስራት "በዳቦ መጠን ማነስ ይታያል" በሚል ከከተማይቱ ነዋሪዎች የደረሰውን ቅሬታ ለአቶ አሸናፊ ብርሃኑ ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን ግራም በሚሰርቁ የዳቦ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ ገልፀው ነዋሪው እንደዚህ አይነት አጠራጣሪ ነገሮችን ሲያጋጥመውና የግራም ስርቆቶችን ሲመለከት በቢሮው ነፃ የስልክ መስመር 8588 ላይ በመደወል ጥቆማ መስጠት እንደሚችል ዳይሬክተሩ ጨምረው ገልጸዋል።
Via Bisrat FM
@YeneTube @FikerAssefa
😁38❤24
ቪዛ እና ጊዜያዊ የመኖሪያ ፈቃድ ያላደሱ የውጭ ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደረገⵑ
-የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከ34 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡንም አስታውቋል
አገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት እንደገለጹት በ2017 በጀት ዓመት አንድ ሚሊዮን 465 ሺህ 989 ፓስፖርት ሊሰጥ ችሏል፡፡በሰጠው አገልግሎቶች 34 ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር ገቢ እንደሰበሰበም አስታውቀዋል፡፡
አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ችግር የሚፈጥሩ የማጭበርበርና የማታለል ተግባር፣ በሕገ-ወጥ መንገድ በኦንላይን አስቸኳይ ፓስፖርት የሚሞሉ 231 ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል።በተመሳሳይ ሦስት ሺህ 868 ግለሰቦች የተጭበርበረ ሰነድ በመጠቀም ፓስፓርት ሊያወጡ ሲሞክሩ በሕግ እንዲጠየቁ መደረጉን ያስረዱት ወይዘሩ ሰላማዊት፤ 12 ሺህ 127 የውጭ ዜጎች ሃሰተኛ ሰነዶችን በመያዝ በሕገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ተይዘው ርምጃ ሊወሰድባቸው ችሏል።
ሦስት ሺህ 263 የቪዛ እና ጊዜያዊ የመኖሪያ ፈቃድ ሳያድሱ የቀሩ ሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የውጭ ዜጎችን በመያዝ የክፍያ መመሪያው በሚያዘው መሠረት አስፈላጊውን ውዝፍ ከፍለው ከሀገር እንዲወጡ መደረጉንም የኢፕድ ዘገባ ያሳያል።
@YeneTube @FikerAssefa
-የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከ34 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡንም አስታውቋል
አገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት እንደገለጹት በ2017 በጀት ዓመት አንድ ሚሊዮን 465 ሺህ 989 ፓስፖርት ሊሰጥ ችሏል፡፡በሰጠው አገልግሎቶች 34 ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር ገቢ እንደሰበሰበም አስታውቀዋል፡፡
አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ችግር የሚፈጥሩ የማጭበርበርና የማታለል ተግባር፣ በሕገ-ወጥ መንገድ በኦንላይን አስቸኳይ ፓስፖርት የሚሞሉ 231 ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል።በተመሳሳይ ሦስት ሺህ 868 ግለሰቦች የተጭበርበረ ሰነድ በመጠቀም ፓስፓርት ሊያወጡ ሲሞክሩ በሕግ እንዲጠየቁ መደረጉን ያስረዱት ወይዘሩ ሰላማዊት፤ 12 ሺህ 127 የውጭ ዜጎች ሃሰተኛ ሰነዶችን በመያዝ በሕገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ተይዘው ርምጃ ሊወሰድባቸው ችሏል።
ሦስት ሺህ 263 የቪዛ እና ጊዜያዊ የመኖሪያ ፈቃድ ሳያድሱ የቀሩ ሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የውጭ ዜጎችን በመያዝ የክፍያ መመሪያው በሚያዘው መሠረት አስፈላጊውን ውዝፍ ከፍለው ከሀገር እንዲወጡ መደረጉንም የኢፕድ ዘገባ ያሳያል።
@YeneTube @FikerAssefa
😁22❤16🔥1
“በአፋር ክልል የሚገኙ ታጣቂዎች የሚፈጽሙት ማንኛውም ትንኮሳ የፌደራል ወይንም የአፋር ክልል መንግስት ትንኮሳ አድርገን ነው የምንወስደው” - ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ
በአፋር ክልል የሚገኙ የትግራይ ታጣቂዎች የሚፈጽሙት ማንኛውም ትንኮሳ የፌደራል መንግስት ወይንም የአፋር ክልል መንግስት ትነኮሳ አደርገን ነው የምንወስደው ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረዳ ገለጹ።
የክልሉ የሰማዕታት ኮሚሽን ባዘጋጀው መድረክ ላይ ትላንት ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ተገኝተው ንግግር ያደረጉት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ “በዚያ በኩል የሚኖር ምንም አይነት ተነሳሽነት/እንቅስቃሴ እንደ ትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ እዚያ ያሉ ሀይሎች ብቻ አድርጎ አይወስደውም፣ ወይ የፌደራል መንግስት ነው ካልሆነም የአፋር መንግስት ነው ብሎ ነው የሚወስደው” ብለዋል።
“እዛ ካሉት (ነጻ መሬት) ሀይሎች ጋር ያለው ልዩነት መቶ በመቶ መፈታት ያለበት በሰላማዊ መንገድ ነው፤ ነገር ግን ማንኛውም ትንኮሳ ከአፋር ክልል በኩል ከመጣ ወይ የአፋር መንገስት ነው አልያም የፌደራል መንግስቱ ነው ተብሎ የሚወሰድ እንጂ የትግራይ ተወላጆች/ተጋሩ ተደርጎ የሚወሰድ አይደለም” ሲሉም አስታውቀዋል፤ ታጣቂዎች “የውክልና (Proxy) ሀይሎች ሁነው እንዳያገለግሉ የሚቻለንን ሁሉ እናደርጋለን ሲሉ ተደምጠዋል።
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
በአፋር ክልል የሚገኙ የትግራይ ታጣቂዎች የሚፈጽሙት ማንኛውም ትንኮሳ የፌደራል መንግስት ወይንም የአፋር ክልል መንግስት ትነኮሳ አደርገን ነው የምንወስደው ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረዳ ገለጹ።
የክልሉ የሰማዕታት ኮሚሽን ባዘጋጀው መድረክ ላይ ትላንት ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ተገኝተው ንግግር ያደረጉት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ “በዚያ በኩል የሚኖር ምንም አይነት ተነሳሽነት/እንቅስቃሴ እንደ ትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ እዚያ ያሉ ሀይሎች ብቻ አድርጎ አይወስደውም፣ ወይ የፌደራል መንግስት ነው ካልሆነም የአፋር መንግስት ነው ብሎ ነው የሚወስደው” ብለዋል።
“እዛ ካሉት (ነጻ መሬት) ሀይሎች ጋር ያለው ልዩነት መቶ በመቶ መፈታት ያለበት በሰላማዊ መንገድ ነው፤ ነገር ግን ማንኛውም ትንኮሳ ከአፋር ክልል በኩል ከመጣ ወይ የአፋር መንገስት ነው አልያም የፌደራል መንግስቱ ነው ተብሎ የሚወሰድ እንጂ የትግራይ ተወላጆች/ተጋሩ ተደርጎ የሚወሰድ አይደለም” ሲሉም አስታውቀዋል፤ ታጣቂዎች “የውክልና (Proxy) ሀይሎች ሁነው እንዳያገለግሉ የሚቻለንን ሁሉ እናደርጋለን ሲሉ ተደምጠዋል።
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
❤40👍6👎5😁2
በደቡብ ጎንደር ዞን በድርቅ ምክንያት ከ175ሺህ በላይ ሠዎች እርዳታ ይፈልጋሉ!
በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን ከመቀጠዋ፣ ከጋይንትና ከእብናት ወረዳዎች አስተያየታቸውን የሰጡን አረሶ አደሮች እንዳሉት በአካባቢዎቹ በተደጋጋሚ የተከሰተው ድርቅ ነዋሪዎቹ አካባቢያቸውን እንዲልቁ እያደረጋቸው ነው፡፡
ከላይ ጋይንት ወረዳ አስተያየታቸውን የሰጡን ነዋሪ የአካባቢው ነዋሪዎች የሚቀምሱት ነገር የለም፣ እርዳታ መጣ ቢባልም በቂ ባለመሆኑ ነዋሪው ስደቱን መርጧል ሲሉ ነው ለዶይቼ ቬሌ የተናገሩት፣ በተለይ ምጥራባ፣ ዳባ ወቶክሶስ፣ ላይ ነጋላና ታች ነጋላ በተባሉ ቀበሌዎች ጉዳቱ የከፋ መሆኑን ማየታቸውን አስረድተውናል፡፡
ሌላው አረሶ አደር በበኩላቸው ቁመና (እንስሳት ማለታቸው ነው) ያላቸው ሠዎች እየሸጡ ለጊዜው ከሩቅ ቦታ እህል በውድ ዋጋ እየሸመቱ ለመመገብ ቢሞክሩም ዘላቂ ሊሆን እንዳልቻለ አመልክተዋል፣ የሚሽጥ እንስሳት የሌላቸው ወገኖች ግን በርህብ እየተሰቃዩ እንደሆነ ነው የገለጡት፡፡ወጣቶች የቀን ሥራ ሰርተው ለማደር ቢሞክሩም የሚሰራ ሥራ ባለመኖሩ ምርጫቸው ወደ ሌላ አካባቢ መሄድና ስደት ሆኗል ሲሉ ነው ያስረዱት፡፡
በስልክ ያገኝናቸው አንዲት እናት እንዳስረዱን “እንኳን ሠው እንስሳቱ በድርቁ ምክንያት እየተጎዱ ነው” ብለዋል፡፡ የሚሰጠው እርዳታም ከጥራትም ከመጠንም እጅግ ያነስ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የበላሳ ወረዳ ነዋሪ በሰጡን አስተያየት ሳሚ፣ ላቫ፣ ሳውጋሪ፣ አጃንዳብ፣ ላየና ሴራ በተባሉ ቀበለኤዎች የሚኖሩ በሺህ የሚጠሩ ነዋሪዎች በድርቅ ተጠቅተዋል ብለዋል፡፡
የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አደጋ መከላክልና ምግብ ዋስትና ጽ/ቤት ኃላፊ ተጨማሪ አስተያየት እንዲሰጡን በስልክ ብንጠይቅም ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ነዋሪዎቹ መንግሥት፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ አካላት፣ በተለያዩ ዓለማት የሚኖሩ የአካባቢው ተወላጆች ለችግራቸው እንዲደርሱላቸው ጠይቀዋል፡፡
በአማራ ክልል የደቡብ ጎንደር ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽ/ቤት የኮሙዩኒኬሽን ባለሙያ አቶ አበባው አየነው በጉዳዩ ዙሪያ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ በዞኑ በሚገኙ 7 ወረዳዎች በሚገኙ 57 ቀበሌዎች በተከሰተው ድርቅ 175ሺ 915 ሠዎች መጠቃታቸውን ጠቅሰው በምንግሥት ለእብናት፣ ለስማዳ፣ለሰዴ ሙጃና መቀጠዋ ተረጂዎች 12ሺ 419 ኩንታል የምግብ እህል ተከፋፍሏል ነው ያሉት፣ የኢተዮጵያ ቀይ መስቀልም 1ሺህ 500 ለሚሆኑ የእብናትና መቀተዋ ተርጂዎች ይፊኖ ዱቄት እርዳታ ማድረሱን ተናግረዋል፡፡
በድርቁ ምክንያት ቤቱን ዘግቶ የተፈናቀለ ሠው የለም ሲሉ የተናገሩት አቶ አበባው፣ ሆኖም ሥራ ለመፈለግ ወደሌሎች ቦታዎች የተንቀሳቀሱ ሠዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ አመልክተዋል፡ለድርቁ መባባስና ለምርት መቀነስ ከዝናብ እጥረቱ በተጨማሪ በክልሉ ያለው ወቅታዊ የሠላም እጦት ሌላው ምክንያት እንደሆነ አስተያየት ሰጪዎቹ ገልጠዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን ከመቀጠዋ፣ ከጋይንትና ከእብናት ወረዳዎች አስተያየታቸውን የሰጡን አረሶ አደሮች እንዳሉት በአካባቢዎቹ በተደጋጋሚ የተከሰተው ድርቅ ነዋሪዎቹ አካባቢያቸውን እንዲልቁ እያደረጋቸው ነው፡፡
ከላይ ጋይንት ወረዳ አስተያየታቸውን የሰጡን ነዋሪ የአካባቢው ነዋሪዎች የሚቀምሱት ነገር የለም፣ እርዳታ መጣ ቢባልም በቂ ባለመሆኑ ነዋሪው ስደቱን መርጧል ሲሉ ነው ለዶይቼ ቬሌ የተናገሩት፣ በተለይ ምጥራባ፣ ዳባ ወቶክሶስ፣ ላይ ነጋላና ታች ነጋላ በተባሉ ቀበሌዎች ጉዳቱ የከፋ መሆኑን ማየታቸውን አስረድተውናል፡፡
ሌላው አረሶ አደር በበኩላቸው ቁመና (እንስሳት ማለታቸው ነው) ያላቸው ሠዎች እየሸጡ ለጊዜው ከሩቅ ቦታ እህል በውድ ዋጋ እየሸመቱ ለመመገብ ቢሞክሩም ዘላቂ ሊሆን እንዳልቻለ አመልክተዋል፣ የሚሽጥ እንስሳት የሌላቸው ወገኖች ግን በርህብ እየተሰቃዩ እንደሆነ ነው የገለጡት፡፡ወጣቶች የቀን ሥራ ሰርተው ለማደር ቢሞክሩም የሚሰራ ሥራ ባለመኖሩ ምርጫቸው ወደ ሌላ አካባቢ መሄድና ስደት ሆኗል ሲሉ ነው ያስረዱት፡፡
በስልክ ያገኝናቸው አንዲት እናት እንዳስረዱን “እንኳን ሠው እንስሳቱ በድርቁ ምክንያት እየተጎዱ ነው” ብለዋል፡፡ የሚሰጠው እርዳታም ከጥራትም ከመጠንም እጅግ ያነስ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የበላሳ ወረዳ ነዋሪ በሰጡን አስተያየት ሳሚ፣ ላቫ፣ ሳውጋሪ፣ አጃንዳብ፣ ላየና ሴራ በተባሉ ቀበለኤዎች የሚኖሩ በሺህ የሚጠሩ ነዋሪዎች በድርቅ ተጠቅተዋል ብለዋል፡፡
የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አደጋ መከላክልና ምግብ ዋስትና ጽ/ቤት ኃላፊ ተጨማሪ አስተያየት እንዲሰጡን በስልክ ብንጠይቅም ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ነዋሪዎቹ መንግሥት፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ አካላት፣ በተለያዩ ዓለማት የሚኖሩ የአካባቢው ተወላጆች ለችግራቸው እንዲደርሱላቸው ጠይቀዋል፡፡
በአማራ ክልል የደቡብ ጎንደር ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽ/ቤት የኮሙዩኒኬሽን ባለሙያ አቶ አበባው አየነው በጉዳዩ ዙሪያ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ በዞኑ በሚገኙ 7 ወረዳዎች በሚገኙ 57 ቀበሌዎች በተከሰተው ድርቅ 175ሺ 915 ሠዎች መጠቃታቸውን ጠቅሰው በምንግሥት ለእብናት፣ ለስማዳ፣ለሰዴ ሙጃና መቀጠዋ ተረጂዎች 12ሺ 419 ኩንታል የምግብ እህል ተከፋፍሏል ነው ያሉት፣ የኢተዮጵያ ቀይ መስቀልም 1ሺህ 500 ለሚሆኑ የእብናትና መቀተዋ ተርጂዎች ይፊኖ ዱቄት እርዳታ ማድረሱን ተናግረዋል፡፡
በድርቁ ምክንያት ቤቱን ዘግቶ የተፈናቀለ ሠው የለም ሲሉ የተናገሩት አቶ አበባው፣ ሆኖም ሥራ ለመፈለግ ወደሌሎች ቦታዎች የተንቀሳቀሱ ሠዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ አመልክተዋል፡ለድርቁ መባባስና ለምርት መቀነስ ከዝናብ እጥረቱ በተጨማሪ በክልሉ ያለው ወቅታዊ የሠላም እጦት ሌላው ምክንያት እንደሆነ አስተያየት ሰጪዎቹ ገልጠዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
❤13😭7