የአንበጣ መንጋ በተከሰተባቸው አካባቢዎች በቀጣዩ ሣምንት የአውሮፕላን ርጭት ይጀመራል!
የአንበጣ መንጋ በተከሰተባቸው አካባቢዎች በቀጣዩ ሣምንት በአውሮፕላን የታገዘ የኬሚካል ርጭት እንደሚጀመር ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡እስካሁን አንበጣው እንደሀገር ከፍተኛ ጉዳት አለማድረሱን የገለፀው ሚኒስቴሩ፥ በቀጣይም ጉዳት እንዳይደርስ እየተሠራ ነው ብሏል።በሚኒስቴሩ የእጽዋት ጥበቃ መሪ ሥራ አስፈጻሚ በላይነህ ንጉሴ የአንበጣ መንጋው ቀጣይነት ባለው ሁኔታ ወደ ሀገር ውስጥ አለመግባቱን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።
ግብርና ሚኒስቴር ከክልሎቹ ጋር በመቀናጀት የአንበጣ መንጋ ወደ ሀገር ውስጥ ገብቶ ጉዳት እንዳያደርስ የመከላከልና የመቆጣጠር ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።ሚኒስቴሩ ለክልሎች የአንበጣ መንጋ መከላከያ ኬሚካል፣ የኬሚካል መርጫ ተሽከርካሪዎች እንዲሁም የባለሙያዎች ድጋፍ ማድረጉን ጠቁመው፥ ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ያረጋገጡት።
ወቅቱ ለአንበጣ መራባት ምቹ መሆኑን እና ለሰውም ሆነ ለተሽከርካሪ በማይመች ተራራማ ቦታ ላይ እያረፈ መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት በቀጣይ ሣምንት የአውሮፕላን ርጭት ይጀመራል ነው ያሉት፡፡በ62 ሺህ 107 ሔክታር ላይ የበረሃ አንበጣ አሰሳ ተካሂዶ፥ በማደግ ላይ ያለ የበረሃ አንበጣ በትግራይ፣ አፋርና አማራ ክልሎች 12 ሺህ 653 ሔክታር መውረሩን አብራርተዋል።
ከዚህ ውስጥ 470 ሔክታር በባሕላዊ መንገድ መከላከል መቻሉን ነው ያስረዱት።ዘንድሮ የተከሰተው የአንበጣ መንጋ ካለፈው ዓመት አንጻር ሲታይ የከፋ እንዳልሆነ የጠቀሱት አቶ በላይ÷ ባለፈው ዓመት በስድስት ክልሎችና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ተከስቶ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የአንበጣ መንጋ በተከሰተባቸው አካባቢዎች በቀጣዩ ሣምንት በአውሮፕላን የታገዘ የኬሚካል ርጭት እንደሚጀመር ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡እስካሁን አንበጣው እንደሀገር ከፍተኛ ጉዳት አለማድረሱን የገለፀው ሚኒስቴሩ፥ በቀጣይም ጉዳት እንዳይደርስ እየተሠራ ነው ብሏል።በሚኒስቴሩ የእጽዋት ጥበቃ መሪ ሥራ አስፈጻሚ በላይነህ ንጉሴ የአንበጣ መንጋው ቀጣይነት ባለው ሁኔታ ወደ ሀገር ውስጥ አለመግባቱን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።
ግብርና ሚኒስቴር ከክልሎቹ ጋር በመቀናጀት የአንበጣ መንጋ ወደ ሀገር ውስጥ ገብቶ ጉዳት እንዳያደርስ የመከላከልና የመቆጣጠር ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።ሚኒስቴሩ ለክልሎች የአንበጣ መንጋ መከላከያ ኬሚካል፣ የኬሚካል መርጫ ተሽከርካሪዎች እንዲሁም የባለሙያዎች ድጋፍ ማድረጉን ጠቁመው፥ ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ያረጋገጡት።
ወቅቱ ለአንበጣ መራባት ምቹ መሆኑን እና ለሰውም ሆነ ለተሽከርካሪ በማይመች ተራራማ ቦታ ላይ እያረፈ መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት በቀጣይ ሣምንት የአውሮፕላን ርጭት ይጀመራል ነው ያሉት፡፡በ62 ሺህ 107 ሔክታር ላይ የበረሃ አንበጣ አሰሳ ተካሂዶ፥ በማደግ ላይ ያለ የበረሃ አንበጣ በትግራይ፣ አፋርና አማራ ክልሎች 12 ሺህ 653 ሔክታር መውረሩን አብራርተዋል።
ከዚህ ውስጥ 470 ሔክታር በባሕላዊ መንገድ መከላከል መቻሉን ነው ያስረዱት።ዘንድሮ የተከሰተው የአንበጣ መንጋ ካለፈው ዓመት አንጻር ሲታይ የከፋ እንዳልሆነ የጠቀሱት አቶ በላይ÷ ባለፈው ዓመት በስድስት ክልሎችና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ተከስቶ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተፈጻሚነት በአማራ ክልል ብቻ እንዲገደብ፤ ጊዜውም ወደ አንድ ወር እንዲያጥር ኢሰመኮ ምክረ ሃሳብ አቀረበ!
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የተፈጻሚነት ጊዜ “ከአንድ ወር ወይም የተወሰኑ ሳምንታት ላልበለጠ ጊዜ ብቻ” እንዲሆን እንዲያደርግ እና የተፈጻሚነት ወሰኑንም በአማራ ክልል ብቻ እንዲገድብ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጠየቀ። በአዋጁ ለአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ “የተለያዩ የአስተዳደር እርከኖችን እና መዋቅሮችን መልሶ ለማቋቋም” የተሰጠውን ስልጣን ፓርላማው እንዲሰርዝም ጥያቄ አቅርቧል፡፡
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን እነዚህን ጥያቄዎች ያቀረበው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በተመለከተ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ባለ 22 ገጽ የምክረ ሃሳብ ሰነድ ላይ ነው።ኢሰመኮ ይህንን ምክረ ሃሳብ ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 6፤ 2015 ይፋ ያደረገው፤ የተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን መርምሮ ውሳኔ ለማሳለፍ ከነገ በስቲያ አስቸኳይ ስብሰባ እንደሚያካሄድ መገለጹን ተከትሎ ነው።
ብሔራዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም፤ የሰብአዊ መብቶች ስጋቶች እና የማሻሻያ ምክረ ሃሳቦች ባካተተበት ሰነድ ላይ በቅድሚያ ያነሳው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለተወካዮች ምክር ቤት ያለመቅረቡን ጉዳይ ነው። አዋጁ በፓርላማ ሳይጸድቅ ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ ተፈጻሚ መሆኑ፤ “የመንግስት የአስቸኳይ ጊዜ ስልጣን ለበርካታ ቀናት ያለ ምክር ቤቱ እይታ እና ቁጥጥር” እንዲቆይ ምክንያት እንደሆነ ኢሰመኮ አመልክቷል።ፓርላማው በሰኞ ስብሰባው አዋጁን የሚያጸድቀው ከሆነ፤ ድንጋጌው ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የነበረውን አፈጻጸም የተመለከተ ሪፖርት መንግስት እንዲያቀርብ እንዲደረግ ኮሚሽኑ ጠይቋል።
[Ethiopia Insider]
@YeneTube @FikerAssefa
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የተፈጻሚነት ጊዜ “ከአንድ ወር ወይም የተወሰኑ ሳምንታት ላልበለጠ ጊዜ ብቻ” እንዲሆን እንዲያደርግ እና የተፈጻሚነት ወሰኑንም በአማራ ክልል ብቻ እንዲገድብ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጠየቀ። በአዋጁ ለአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ “የተለያዩ የአስተዳደር እርከኖችን እና መዋቅሮችን መልሶ ለማቋቋም” የተሰጠውን ስልጣን ፓርላማው እንዲሰርዝም ጥያቄ አቅርቧል፡፡
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን እነዚህን ጥያቄዎች ያቀረበው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በተመለከተ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ባለ 22 ገጽ የምክረ ሃሳብ ሰነድ ላይ ነው።ኢሰመኮ ይህንን ምክረ ሃሳብ ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 6፤ 2015 ይፋ ያደረገው፤ የተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን መርምሮ ውሳኔ ለማሳለፍ ከነገ በስቲያ አስቸኳይ ስብሰባ እንደሚያካሄድ መገለጹን ተከትሎ ነው።
ብሔራዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም፤ የሰብአዊ መብቶች ስጋቶች እና የማሻሻያ ምክረ ሃሳቦች ባካተተበት ሰነድ ላይ በቅድሚያ ያነሳው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለተወካዮች ምክር ቤት ያለመቅረቡን ጉዳይ ነው። አዋጁ በፓርላማ ሳይጸድቅ ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ ተፈጻሚ መሆኑ፤ “የመንግስት የአስቸኳይ ጊዜ ስልጣን ለበርካታ ቀናት ያለ ምክር ቤቱ እይታ እና ቁጥጥር” እንዲቆይ ምክንያት እንደሆነ ኢሰመኮ አመልክቷል።ፓርላማው በሰኞ ስብሰባው አዋጁን የሚያጸድቀው ከሆነ፤ ድንጋጌው ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የነበረውን አፈጻጸም የተመለከተ ሪፖርት መንግስት እንዲያቀርብ እንዲደረግ ኮሚሽኑ ጠይቋል።
[Ethiopia Insider]
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
ብሔራዊ ባንክ ለመንግሥት የሚሰጠው የቀጥታ ብድር መጠን በ25 በመቶ እንዲገደብ ወሰነ!
የፋይናንስ ዘርፉን ለማረጋጋት የሚረዱ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ይፋ እንደሚያደርግ ሲያስታውቅ የቆየው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ በተያዘው የበጀት ዓመት ለመንግሥት የሚሰጠውን የቀጥታ ብድር መጠን በ25 በመቶ እንዲገደብ ወሰነ፡፡
የብሔራዊ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ነሐሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ወዲያውኑ ሥራ ላይ እንዲውሉ ካሳለፋቸው በርካታ የፖሊሲ ዕርምጃዎች መካከል፣ በተያዘው የበጀት ዓመት ብሔራዊ ባንክ ለመንግሥት የሚሰጠው የቀጥታ ብድር መጠን በእጅጉ ለመቀነስ የተወሰነው ይገኝበታል፡፡ የቦርዱ ውሳኔ ይፋ የተደረገው ዓርብ ነሐሴ 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ነው፡፡
ብሔራዊ ባንክ ለመንግሥት የሚሰጠውን የቀጥታ ብድር መጠን በእጅጉ በመቀነስ ከዓምናው ከሲሶ ወይም ከ1/3ኛ አንዳይበልጥ የወሰነ ሲሆን፣ በሌላ አነጋገር ይህ የብድር መጠን በ25 በመቶ ይገደባል፡፡
የገንዘብ ሚኒስቴር ቀጥታ ብድርን እንደ የመጨረሻ አማራጭ የሚጠቀመው የመንግሥት የግምጃ ቤት ሰነድ፣ በበቂ መጠን ለገበያ መቅረብ ሳይችል ሲቀር ብቻ እንደሚሆን መግባባት ላይ መደረሱን ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
የፋይናንስ ዘርፉን ለማረጋጋት የሚረዱ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ይፋ እንደሚያደርግ ሲያስታውቅ የቆየው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ በተያዘው የበጀት ዓመት ለመንግሥት የሚሰጠውን የቀጥታ ብድር መጠን በ25 በመቶ እንዲገደብ ወሰነ፡፡
የብሔራዊ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ነሐሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ወዲያውኑ ሥራ ላይ እንዲውሉ ካሳለፋቸው በርካታ የፖሊሲ ዕርምጃዎች መካከል፣ በተያዘው የበጀት ዓመት ብሔራዊ ባንክ ለመንግሥት የሚሰጠው የቀጥታ ብድር መጠን በእጅጉ ለመቀነስ የተወሰነው ይገኝበታል፡፡ የቦርዱ ውሳኔ ይፋ የተደረገው ዓርብ ነሐሴ 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ነው፡፡
ብሔራዊ ባንክ ለመንግሥት የሚሰጠውን የቀጥታ ብድር መጠን በእጅጉ በመቀነስ ከዓምናው ከሲሶ ወይም ከ1/3ኛ አንዳይበልጥ የወሰነ ሲሆን፣ በሌላ አነጋገር ይህ የብድር መጠን በ25 በመቶ ይገደባል፡፡
የገንዘብ ሚኒስቴር ቀጥታ ብድርን እንደ የመጨረሻ አማራጭ የሚጠቀመው የመንግሥት የግምጃ ቤት ሰነድ፣ በበቂ መጠን ለገበያ መቅረብ ሳይችል ሲቀር ብቻ እንደሚሆን መግባባት ላይ መደረሱን ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
በሃዋሳ ሀይቅ ዳርቻ በታቦር ተራራ ስር የሚገኙት ጨረቃ ቤቶችን ለማንሳት ጥናት እየተካሄደ መሆኑ ተገለፀ!
ቤቶቹ የያዙት ቦታ ለቱሪስት አገልግሎት መስጫ መሆን እንደሚገባ ለፊደል ፖስት የሀዋሳ ከንቲባ ፀጋዬ ቱኬ የገለፁ ሲሆን ጥናቱ በአንድ አመት ውስጥ ተጠናቆ ተግባራዊ ይሆናል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
ከ 2,100 በላይ የጨረቃ ቤቶች በሀይቁ ዳርቻ የተገነቡ ሲሆን ቤቶቹን የያዙት ስፍራ ለሪዞርት ፣ ሆቴል እና ለመሳሰሉት አገልግሎት ይውላል ተብሏል።
ቤቶቹ በሚነሱበት አግባብ ላይ ጥናት እየተካሄደ መሆኑን ከንቲባው ገልፀዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
ቤቶቹ የያዙት ቦታ ለቱሪስት አገልግሎት መስጫ መሆን እንደሚገባ ለፊደል ፖስት የሀዋሳ ከንቲባ ፀጋዬ ቱኬ የገለፁ ሲሆን ጥናቱ በአንድ አመት ውስጥ ተጠናቆ ተግባራዊ ይሆናል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
ከ 2,100 በላይ የጨረቃ ቤቶች በሀይቁ ዳርቻ የተገነቡ ሲሆን ቤቶቹን የያዙት ስፍራ ለሪዞርት ፣ ሆቴል እና ለመሳሰሉት አገልግሎት ይውላል ተብሏል።
ቤቶቹ በሚነሱበት አግባብ ላይ ጥናት እየተካሄደ መሆኑን ከንቲባው ገልፀዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
👍2❤1
በትራፊክ አደጋ 3 የአንድ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ የ6 ሰዎች ሕይወት አለፈ!
በአፋር ክልል ሚሌ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ ሶስት የአንድ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ የ6 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡አደጋው ከሚሌ ከተማ 14 ሰዎችን አሳፍሮ ወደ ሰመራ ከተማ በመጓዝ ላይ የነበረ መለስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከከባድ መኪና ጋር በመጋጨቱ ነው የተከሰተው፡፡
በአደጋው የአንድ ቤተሰሰብ አባል የሆኑ አባት፣ እናትና የ4 ዓመት ህጻን ልጅን ጨምሮ የ6 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ÷ 7 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት መድረሱ ተጠቁሟል፡፡በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች አቅራቢያ በሚገኙ የጤና ተቋማት የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን የአውሲ-ረሱ ዞን ትራፊክ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
የከባድ መኪና አሸከርካሪው በሕግ ቁጥጥር ስር ውሎ ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገበት ነው ተብሏል፡፡የመለስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ አሽከርካሪውን በቁጥጥር ስር ለማዋልም ክትትል እየተደረገ መሆኑን የአፋር ክልል መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል፡፡
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
በአፋር ክልል ሚሌ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ ሶስት የአንድ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ የ6 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡አደጋው ከሚሌ ከተማ 14 ሰዎችን አሳፍሮ ወደ ሰመራ ከተማ በመጓዝ ላይ የነበረ መለስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከከባድ መኪና ጋር በመጋጨቱ ነው የተከሰተው፡፡
በአደጋው የአንድ ቤተሰሰብ አባል የሆኑ አባት፣ እናትና የ4 ዓመት ህጻን ልጅን ጨምሮ የ6 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ÷ 7 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት መድረሱ ተጠቁሟል፡፡በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች አቅራቢያ በሚገኙ የጤና ተቋማት የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን የአውሲ-ረሱ ዞን ትራፊክ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
የከባድ መኪና አሸከርካሪው በሕግ ቁጥጥር ስር ውሎ ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገበት ነው ተብሏል፡፡የመለስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ አሽከርካሪውን በቁጥጥር ስር ለማዋልም ክትትል እየተደረገ መሆኑን የአፋር ክልል መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል፡፡
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
ምክር ቤቱ በዛሬው ዕለት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መርምሮ ውሳኔ ያሳልፋል!
የፌዴራል መንግሥት የሚኒስትሮች ምክር ቤት አርብ ሐምሌ 28/2015 ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባ፤ "በአማራ ክልል ለስድስት ወራት እንዲሁም "እንዳስፈላጊነቱ" በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ይተገበራል" ሲል ባስተላለፈው "የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015" ላይ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ተወያይቶ ውሳኔ ያሳልፋል።
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ያጋጠመውን የጸጥታ መደፍረስ ተከትሎ፤ ችግሩ ከክልሉ መንግሥት አቅም በላይ በመሆኑ የፌደራል መንግሥቱ ጣልቃ እንዲገባ በቀረበው ጥያቄ መሠረት፤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 እንዲታወጅ መወሰኑ ይታወሳል።
ይህንንም ተከትሎ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አማካሪ ኮሚቴ ለምክር ቤቱ የቀረበውን የአስቸኳይ ጊዜ አጀንዳ በተመለከተ የጉዳዩን አሳሳቢነት አይቶና ተወያይቶ፤ በዛሬው ዕለት የምክር ቤቱ አስቸኳይ ጉባኤ እንዲጠራ የወሰነ ሲሆን፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁም በአጀንዳነት እንዲቀርብ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
በዚህም መሰረት ከእረፍት የተጠራው ምክር ቤት በዛሬው አስቸኳይ ስብሰባው፤ በግጭት ውስጥ በሰነበተው የአማራ ክልል ለስድስት ወራት በታወጀውና "እንዳስፈላጊነቱ" በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ይተገበራል በተባለው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ላይ፤ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ ተወያይቶ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
እንዲሁም ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ በምክር ቤት አባልነታቸው በቁጥጥር ሥር ያለመዋል ሕጋዊ መብታቸው ሳይነሳ፤ በቁጥጥር ሥር በሚገኙት የምክር ቤቱ አባል ያለመከሰስ መብት ጉዳይ ላይ የውይይት ሀሳብ ቀርቦ ውሳኔ ሊሰጥበት ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ምክር ቤቱ በአስቸኳይ አዋጁ ላይ ለመምከር እና ለመወሰን የጠራውን አስቸኳይ ስብሰባ አስመልክቶ ቅዳሜ ነሐሴ 6/2015 ባወጣው መግለጫ፤ የአዋጁ አስፈላጊነት፣ ተመጣጣኝነት እና ሕጋዊነት እንዲሁም አዋጁ ተፈጻሚ የሚሆንበት አካባቢ እና የጊዜ ወሰን እንዲመረመር ለምክር ቤቱ ሃሳብ ማቅረቡን አስታውቋል።በተጨማሪም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እና የዳኞችን ያለምክር ቤቱ ውሳኔ አለመያዝ እና ያለመከሰስ ልዩ መብት እና ሌሎችም ሊገደቡ ስለማይችሉ መብቶች ጥበቃም በምክር ቤቱ እንዲመረመር ጠይቋል።
እንዲሁም፤ "በአሁኑ ጊዜ በአማራ ክልል ውስጥ ተከስቶ የነበረው ችግር ተወግዶ መደበኛ እንቅስቃሴዎች ወደ ቀድሞ ኹኔታቸው መመለስ መጀመራቸው" በመንግሥት በመገለጹን ያስታወሰው ኮሚሽኑ፤ ምክር ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የሚያጸድቀው ከሆነ ተፈጻሚነቱ ከአንድ ወር ወይም ከተወሰኑ ሳምንታት እንዳይበልጥ እንዲሁም ከአማራ ክልል ውጭ አዋጁ ተግባራዊ እንዳይሆን መጠየቁን ገልጿል።በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ከሰሞኑ የተከሰተው የጸጥታ መደፍረስ በክልሉ ከፍተኛ የሰብዓዊ፣ የማህበራዊ እና የኢኮኖሚያዊ ጉዳቶችን ማስከተሉ ይታወቃል።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
የፌዴራል መንግሥት የሚኒስትሮች ምክር ቤት አርብ ሐምሌ 28/2015 ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባ፤ "በአማራ ክልል ለስድስት ወራት እንዲሁም "እንዳስፈላጊነቱ" በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ይተገበራል" ሲል ባስተላለፈው "የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015" ላይ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ተወያይቶ ውሳኔ ያሳልፋል።
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ያጋጠመውን የጸጥታ መደፍረስ ተከትሎ፤ ችግሩ ከክልሉ መንግሥት አቅም በላይ በመሆኑ የፌደራል መንግሥቱ ጣልቃ እንዲገባ በቀረበው ጥያቄ መሠረት፤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 እንዲታወጅ መወሰኑ ይታወሳል።
ይህንንም ተከትሎ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አማካሪ ኮሚቴ ለምክር ቤቱ የቀረበውን የአስቸኳይ ጊዜ አጀንዳ በተመለከተ የጉዳዩን አሳሳቢነት አይቶና ተወያይቶ፤ በዛሬው ዕለት የምክር ቤቱ አስቸኳይ ጉባኤ እንዲጠራ የወሰነ ሲሆን፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁም በአጀንዳነት እንዲቀርብ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
በዚህም መሰረት ከእረፍት የተጠራው ምክር ቤት በዛሬው አስቸኳይ ስብሰባው፤ በግጭት ውስጥ በሰነበተው የአማራ ክልል ለስድስት ወራት በታወጀውና "እንዳስፈላጊነቱ" በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ይተገበራል በተባለው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ላይ፤ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ ተወያይቶ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
እንዲሁም ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ በምክር ቤት አባልነታቸው በቁጥጥር ሥር ያለመዋል ሕጋዊ መብታቸው ሳይነሳ፤ በቁጥጥር ሥር በሚገኙት የምክር ቤቱ አባል ያለመከሰስ መብት ጉዳይ ላይ የውይይት ሀሳብ ቀርቦ ውሳኔ ሊሰጥበት ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ምክር ቤቱ በአስቸኳይ አዋጁ ላይ ለመምከር እና ለመወሰን የጠራውን አስቸኳይ ስብሰባ አስመልክቶ ቅዳሜ ነሐሴ 6/2015 ባወጣው መግለጫ፤ የአዋጁ አስፈላጊነት፣ ተመጣጣኝነት እና ሕጋዊነት እንዲሁም አዋጁ ተፈጻሚ የሚሆንበት አካባቢ እና የጊዜ ወሰን እንዲመረመር ለምክር ቤቱ ሃሳብ ማቅረቡን አስታውቋል።በተጨማሪም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እና የዳኞችን ያለምክር ቤቱ ውሳኔ አለመያዝ እና ያለመከሰስ ልዩ መብት እና ሌሎችም ሊገደቡ ስለማይችሉ መብቶች ጥበቃም በምክር ቤቱ እንዲመረመር ጠይቋል።
እንዲሁም፤ "በአሁኑ ጊዜ በአማራ ክልል ውስጥ ተከስቶ የነበረው ችግር ተወግዶ መደበኛ እንቅስቃሴዎች ወደ ቀድሞ ኹኔታቸው መመለስ መጀመራቸው" በመንግሥት በመገለጹን ያስታወሰው ኮሚሽኑ፤ ምክር ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የሚያጸድቀው ከሆነ ተፈጻሚነቱ ከአንድ ወር ወይም ከተወሰኑ ሳምንታት እንዳይበልጥ እንዲሁም ከአማራ ክልል ውጭ አዋጁ ተግባራዊ እንዳይሆን መጠየቁን ገልጿል።በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ከሰሞኑ የተከሰተው የጸጥታ መደፍረስ በክልሉ ከፍተኛ የሰብዓዊ፣ የማህበራዊ እና የኢኮኖሚያዊ ጉዳቶችን ማስከተሉ ይታወቃል።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
‹‹ በአማራ ክልል በጎንደርና ሸዋ ሮቢት ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጪ ሰላማዊ ሰዎች በፀጥታ ሐይሎች ሰለመገደላቸው ተዓማኒነት ያላቸው መረጃዎች ደርሰውኛል ›› - ኢሰመኮ
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን(ኢሰመኮ) ‹‹ በአማራ ክልል፣ ጎንደርና ሸዋሮቢት በርካታ አካባቢዎች ከፍርድ ቤት ትዕዛዘው ውጪ ሰላማዊ ሰዎች በፀጥታ ሀይሎች መገደላቸውን የሚያመላክቱ ተዓማሚነት ያላቸው መረጃዎች ደርሰውኛል ›› ብሏል፡፡ኮሚሽኑ ይህን ያለው ነሐሴ 8 ቀን 2015 ዓ.ም በአማራ ክልል ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ በላከው ባለአራት ገፅ መግለጫ ላይ ነው፡፡
ኢሰመኮ ተፋላሚ ሀይላት ያለምንም ቅደመ ሁኔታ ግጭቶችን እንዲያቆሙ፣ ለሰላማዊ ንግግር ስፍራ እንዲያመቻቹና ግጭቱ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡በአማራ ክልል ያለው ግጭት በሰብዓዊ መብቶች ላይ እያሳደረ ያለውን ተፅዕኖ እየተከታተለ መሆኑን የገለፀው ኮሚሽኑ ‹‹ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከመደንገጉ በፊትና በኋላ ከአዲስ አበባና ከሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መረጃዎች እየተቀበልሁ ነው ›› ብሏል፡፡
በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ‹‹ ከባድ የመድፍ ተኩስ ጭምር ጥቅም ላይ የዋለባቸው ከፍተኛ ውግያዎች እየተካሄደ መሆናቸውን አረጋግጬያለሁ ›› ያለው ኮሚሽኑ በዚህም ሞት ሰላማዊ ሰዎች እና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን በመግለጫው አመልክቷል፡፡
መግለጫው ሲቀጥል ‹‹ መንገድ ለመዝጋት የሞከሩ ሰላማዊ ተቃዋሚዎች ጭምር መገደላቸውን ›› ይፋ አድርጓል፡፡ ‹‹እስር ቤቶችና ፖሊስ ጣቢያዎች ተሰብረዋል፤ የጦር መሣሪያዎችና ጥይቶች ተዘርፈዋል፤ ቅድመ ፍርድ ያሉ እና ታራሚዎች አመልጠዋል ›› ሲል አመልክቷል፡፡የአማራ ክልል መንግስት አመራሮች የጥቃት ዒላማ መሆናቸውንም በዚሁ መግለጫው ጠቁሟል፡፡
በተለያዩ አካባቢዎች እንደ ኤሌክትሪክ ሐይል፣ ውሃ፣ ባንክ፣ ሆስፒታል፣ ትምህርት ቤቶች፣ ሰልክ፣ ኢነንተርኔት ያሉ መሠረታዊ አገልገሎቶች መሰተጓገላቸውንም አክሏል፡፡‹‹በደብረ ብርሃን ከተማ ለሁለት ቀናት፣ በአራት ብዙ ህዝብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በተካሄደ ከፍተኛ ውግያ በሆስፒታል፣ ቤተ ከርስቲያን፣ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በስራ ቦታዎች ያሉ ሰለማዊ ሰዎች በመድፍና ተኩስ ልውውጥ ተገድለዋል ›› ባይ ነው፡፡
ኢሰመኮ ‹‹ እንደ ደብረብርሃን፣ ፍኖተ ሰላምና ቡሬ ባሉ ከተሞች ‹ የአየር ድበደባዎች › በመፈፀሙ ሰላማዊ ሰዎች፣ በመኖሪያ ቤቶችና ሕዝብ በሚበዛበቸው ስፍራዎች ጉዳት መድረሱን ›› አመልክቷል፡፡ይህ የኮሚሽኑ መግለጫ ሲቀጥል ‹‹ በባህርዳር ከተማ በርካታ አካባቢዎች ሰላማዊ ሰዎች በየጎዳናውና ከቤታቸው ውጪ ተግደለዋል፤ አንዳንድ ወጣቶችን ደግሞ ለመደብደብና ለመግደል ፍለጋ ሲደረግ እንደነበረ የሚያመላክቱ ተዓማኒ መረጃዎች ደርሰውኛል ›› ሲል ይፋ አድርጓል፡፡
የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቱ በአማራ ክልል ብቻ የተገደበ አለመሆኑን የሚጠቅሰው ኮሚሽኑ ‹‹ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአማራ ተወላጆችን እያሰረ መሆኑን ›› ገልፆል፡፡በርካታ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን ያተተው የኮሚሽኑ መግለጫ አምስት ያህል ምክረ ሀሳቦችን ቢደረጉ ሲል በመግለጫው አስቀምጧል፡፡
ከእነዚህም መካከል ‹‹ የፌደራሉ መንግስት የጅምላ እስሩን እንዲያቆም፣ ክህግ አግባብ ውጪ የታሰሩት ሁሉም እንዲፈቱ፣ ኮሚሽኑን ጨምሮ ሌሎች ተቋማት በየእስር ቤቶቹ ጉብኝት ለማድረግ ያልተገደበ መንገድ እንዲመቻችላቸው ›› የጠየቀበት ይገኝበታል፡፡የመንግስት ባለስጣናትን ጨምሮ ተሰመኒነት ያላቸው ግለሰቦች ሰላማዊ መንገዶችን ከመጠቆም ይልቅ ግጭቱን ከሚያጋግሙ መግለጫዎች እንዲቀቆጠቡ ጥሪ አቅርቧል፡፡ በመጨረሻም በኢትዮጵያ ያሉ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ)፣ የአፍሪካ ህብረት፣ የተባባሩት መንግስታትና ዓለምአቀፉ ማህበረሰብ ግጭቶቹ እንዲቆሙ ድጋፍ እንዲያደርጉ፣ የመነጋገሪያ ስፋራዎችን እንዲያመቻቹ ጠይቋል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን(ኢሰመኮ) ‹‹ በአማራ ክልል፣ ጎንደርና ሸዋሮቢት በርካታ አካባቢዎች ከፍርድ ቤት ትዕዛዘው ውጪ ሰላማዊ ሰዎች በፀጥታ ሀይሎች መገደላቸውን የሚያመላክቱ ተዓማሚነት ያላቸው መረጃዎች ደርሰውኛል ›› ብሏል፡፡ኮሚሽኑ ይህን ያለው ነሐሴ 8 ቀን 2015 ዓ.ም በአማራ ክልል ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ በላከው ባለአራት ገፅ መግለጫ ላይ ነው፡፡
ኢሰመኮ ተፋላሚ ሀይላት ያለምንም ቅደመ ሁኔታ ግጭቶችን እንዲያቆሙ፣ ለሰላማዊ ንግግር ስፍራ እንዲያመቻቹና ግጭቱ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡በአማራ ክልል ያለው ግጭት በሰብዓዊ መብቶች ላይ እያሳደረ ያለውን ተፅዕኖ እየተከታተለ መሆኑን የገለፀው ኮሚሽኑ ‹‹ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከመደንገጉ በፊትና በኋላ ከአዲስ አበባና ከሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መረጃዎች እየተቀበልሁ ነው ›› ብሏል፡፡
በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ‹‹ ከባድ የመድፍ ተኩስ ጭምር ጥቅም ላይ የዋለባቸው ከፍተኛ ውግያዎች እየተካሄደ መሆናቸውን አረጋግጬያለሁ ›› ያለው ኮሚሽኑ በዚህም ሞት ሰላማዊ ሰዎች እና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን በመግለጫው አመልክቷል፡፡
መግለጫው ሲቀጥል ‹‹ መንገድ ለመዝጋት የሞከሩ ሰላማዊ ተቃዋሚዎች ጭምር መገደላቸውን ›› ይፋ አድርጓል፡፡ ‹‹እስር ቤቶችና ፖሊስ ጣቢያዎች ተሰብረዋል፤ የጦር መሣሪያዎችና ጥይቶች ተዘርፈዋል፤ ቅድመ ፍርድ ያሉ እና ታራሚዎች አመልጠዋል ›› ሲል አመልክቷል፡፡የአማራ ክልል መንግስት አመራሮች የጥቃት ዒላማ መሆናቸውንም በዚሁ መግለጫው ጠቁሟል፡፡
በተለያዩ አካባቢዎች እንደ ኤሌክትሪክ ሐይል፣ ውሃ፣ ባንክ፣ ሆስፒታል፣ ትምህርት ቤቶች፣ ሰልክ፣ ኢነንተርኔት ያሉ መሠረታዊ አገልገሎቶች መሰተጓገላቸውንም አክሏል፡፡‹‹በደብረ ብርሃን ከተማ ለሁለት ቀናት፣ በአራት ብዙ ህዝብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በተካሄደ ከፍተኛ ውግያ በሆስፒታል፣ ቤተ ከርስቲያን፣ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በስራ ቦታዎች ያሉ ሰለማዊ ሰዎች በመድፍና ተኩስ ልውውጥ ተገድለዋል ›› ባይ ነው፡፡
ኢሰመኮ ‹‹ እንደ ደብረብርሃን፣ ፍኖተ ሰላምና ቡሬ ባሉ ከተሞች ‹ የአየር ድበደባዎች › በመፈፀሙ ሰላማዊ ሰዎች፣ በመኖሪያ ቤቶችና ሕዝብ በሚበዛበቸው ስፍራዎች ጉዳት መድረሱን ›› አመልክቷል፡፡ይህ የኮሚሽኑ መግለጫ ሲቀጥል ‹‹ በባህርዳር ከተማ በርካታ አካባቢዎች ሰላማዊ ሰዎች በየጎዳናውና ከቤታቸው ውጪ ተግደለዋል፤ አንዳንድ ወጣቶችን ደግሞ ለመደብደብና ለመግደል ፍለጋ ሲደረግ እንደነበረ የሚያመላክቱ ተዓማኒ መረጃዎች ደርሰውኛል ›› ሲል ይፋ አድርጓል፡፡
የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቱ በአማራ ክልል ብቻ የተገደበ አለመሆኑን የሚጠቅሰው ኮሚሽኑ ‹‹ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአማራ ተወላጆችን እያሰረ መሆኑን ›› ገልፆል፡፡በርካታ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን ያተተው የኮሚሽኑ መግለጫ አምስት ያህል ምክረ ሀሳቦችን ቢደረጉ ሲል በመግለጫው አስቀምጧል፡፡
ከእነዚህም መካከል ‹‹ የፌደራሉ መንግስት የጅምላ እስሩን እንዲያቆም፣ ክህግ አግባብ ውጪ የታሰሩት ሁሉም እንዲፈቱ፣ ኮሚሽኑን ጨምሮ ሌሎች ተቋማት በየእስር ቤቶቹ ጉብኝት ለማድረግ ያልተገደበ መንገድ እንዲመቻችላቸው ›› የጠየቀበት ይገኝበታል፡፡የመንግስት ባለስጣናትን ጨምሮ ተሰመኒነት ያላቸው ግለሰቦች ሰላማዊ መንገዶችን ከመጠቆም ይልቅ ግጭቱን ከሚያጋግሙ መግለጫዎች እንዲቀቆጠቡ ጥሪ አቅርቧል፡፡ በመጨረሻም በኢትዮጵያ ያሉ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ)፣ የአፍሪካ ህብረት፣ የተባባሩት መንግስታትና ዓለምአቀፉ ማህበረሰብ ግጭቶቹ እንዲቆሙ ድጋፍ እንዲያደርጉ፣ የመነጋገሪያ ስፋራዎችን እንዲያመቻቹ ጠይቋል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ወደ ሰሜን ሸዋ ደራ ወረዳ እየገቡ መሆናቸውን ነዋሪዎች አስታወቁ፡፡
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ የቡድኑ ታጣቂዎች በወረዳው የገጠር ቀበሌዎች በስፋት እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውን ሰምተናል።የወረዳው ነዋሪዎች ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቁት ታጣቂዎቹ ከሰሞኑ በስፋት መንቀሳቀስ በመጀመራቸው ስጋት እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል።ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች ወደ ወረዳው የገጠር ቀበሌዎች እየገቡ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ታጣቂዎቹ ከዚህ ቀደም በወረዳው በተደጋጋሚ ባደረሱት ጥቃት በርካታ ዜጎች መገደላቸውንም ነዋሪዎቹ አስታውሰዋል።በተጨማሪም በወረዳው የገጠር ቀበሌ ይኖሩ የነበሩ ዜጎች ታጣቂዎችን ሸሽት ወደ ወረዳዋ ከተማ ጉንዶ መስቀልና ወደሌሎች አካባቢዎች መሰደዳቸውንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
አሁን ላይ የሽብር ቡድኑ ታጣቂውች በወረዳው የገጠር ቀበሌ በሆኑ ባቡ ድሬ፣ ራቾና ድሬ መንቃታ አካባቢዎች በስፋት እየተንቀሳቀሱ መሆናቸው ነው የተነገረው።ኦነግ ሸኔ ከ ሁለት አመት በፊት ጀምሮ ወደ ወረዳው በመግባት ዜጎችን በማገት ገንዘብ መቀበል እንዲሁም ግድያና ማፈናቀል እያደረሰ ነው ተብሏል።
በተለይም የደራ ወረዳን ከሰላሌ ጋር የሚያገናኘውን የጀማን ድልድይ በመቆጣጠሩ የወረዳዋ ነዋሪዎች በአማራ ክልል መርሐቤቴ ወረዳ በኩል ወደ አዲስ አበባ እንዲሚመጡ ተገደዋል።የደራ ወረዳ ከአዲስ አበባ 2 መቶ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ወረዳ መሆኑ ይታወቃል።እኛም ወቅታዊውን የታጣቂዎች እንቅስቃሴ በተመለከተ የወረዳውን አስተዳዳሪ ለማናገር ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም አልተሳካም።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ የቡድኑ ታጣቂዎች በወረዳው የገጠር ቀበሌዎች በስፋት እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውን ሰምተናል።የወረዳው ነዋሪዎች ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቁት ታጣቂዎቹ ከሰሞኑ በስፋት መንቀሳቀስ በመጀመራቸው ስጋት እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል።ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች ወደ ወረዳው የገጠር ቀበሌዎች እየገቡ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ታጣቂዎቹ ከዚህ ቀደም በወረዳው በተደጋጋሚ ባደረሱት ጥቃት በርካታ ዜጎች መገደላቸውንም ነዋሪዎቹ አስታውሰዋል።በተጨማሪም በወረዳው የገጠር ቀበሌ ይኖሩ የነበሩ ዜጎች ታጣቂዎችን ሸሽት ወደ ወረዳዋ ከተማ ጉንዶ መስቀልና ወደሌሎች አካባቢዎች መሰደዳቸውንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
አሁን ላይ የሽብር ቡድኑ ታጣቂውች በወረዳው የገጠር ቀበሌ በሆኑ ባቡ ድሬ፣ ራቾና ድሬ መንቃታ አካባቢዎች በስፋት እየተንቀሳቀሱ መሆናቸው ነው የተነገረው።ኦነግ ሸኔ ከ ሁለት አመት በፊት ጀምሮ ወደ ወረዳው በመግባት ዜጎችን በማገት ገንዘብ መቀበል እንዲሁም ግድያና ማፈናቀል እያደረሰ ነው ተብሏል።
በተለይም የደራ ወረዳን ከሰላሌ ጋር የሚያገናኘውን የጀማን ድልድይ በመቆጣጠሩ የወረዳዋ ነዋሪዎች በአማራ ክልል መርሐቤቴ ወረዳ በኩል ወደ አዲስ አበባ እንዲሚመጡ ተገደዋል።የደራ ወረዳ ከአዲስ አበባ 2 መቶ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ወረዳ መሆኑ ይታወቃል።እኛም ወቅታዊውን የታጣቂዎች እንቅስቃሴ በተመለከተ የወረዳውን አስተዳዳሪ ለማናገር ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም አልተሳካም።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
👍1😁1
በጅማ ዞን በሞቱ ሰዎች ስም የአፈር ማዳበሪያ እንደሚሸጥ ተነገረ!
በጅማ ዞን ቀርሳ እና አሰንዳቦ ወረዳዎች በተደረገ ቁጥጥር በህገወጥ መንገድ በተሽከርካሪ ተጭኖ ሲጓዝ እንዲሁም በመኖሪያ ቤት ዉስጥ ተከማችቶ በዉድ ዋጋ ሊሸጥ የተዘጋጀ 1 ሺህ 47 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በጅማ ዞን ፖሊስ መምሪያ መያዙ ተነግሯል።የአፈር ማዳበሪያዉ ግምታዊ ዋጋዉ 5 ሚሊዮን 500 ሺህ ብር የሚገመት መሆኑን የጅማ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሚዲያ እና የኮሚኒኬሽን ክፍል ሀላፊ ኮማንደር ወንድሙ ሞቲ ተናግረዋል።የቀርሳ ወረዳ የህብረት ስራ ማህበር ማስፋፊያ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ነዚብ አባተማም ፤ በዞኑ ህገወጥ የፈር ማዳበሪያ ዝዉዉር እና ሽያጭ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ተናግረዉ ፤ በመዋቅር የተደራጀ ሌብነት ፈተና መሆኑን አክለዋል።
በዚህም አመራሮችን አሳታፊ ባደረገዉ ህገወጥ ድርጊት ፤ በህይወት በሌሉ ሰዎች ስም ጭምር ማዳበሪያ እንደሚወጣ እና እንደሚሸጥ ገልጸዋል። በቀርሳ ወረዳ 314 ኩንታል ማዳበሪያ በቁጥጥር ስር መዋሉንም አክለዋል። በወረዳዉ በህገወጥ መንገድ የሚሸጥ አንድ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ከ 10 ሺህ ብር በላይ እንደሚጠይቅ ሀላፊዉ ጠቁመዋል።በጅማ ዞን በርበሬ የሚዘሩ አርሶ አደሮች ወቅቱ እንዳያልፍባቸዉ በሚልም በህገወጥ የማዳበሪያ ግዢ ላይ ተሳታፊ ለመሆን እንደተገገዱም ገልጸዋል።
በሌላ በኩል ሰንዳቦ እና ጊቤ ኬላ ላይ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 428 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በህገወጥ መንገድ ተጭኖ ሲጓጓዝ መያዙን ኮማንደር ወንድሙ ሞቲ ተናግረዋል። በተጨማሪም ከቦነያ የህብረት ስራ ማህበር በ ሁለት ተሽከርካሪዎች ተጭኖ ሲጓጓዝ የነበረ 95 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ መያዙንም አክለዋል።
በተመሳሳይ በኦሞ ናዳ ወረዳ ዋቅቶላ ቀበሌ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ዉስጥ 210 ኩንታል ማዳበሪያ በተደረገ ፍተሻ ተይዟል። የአፈር ማዳበሪያዉ ሲያጓጉዙ የነበሩ እና አራት የህብረት ስራ ማህበራት ሰራተኞችን ጨምሮ ስድስት ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸዉን የጅማ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሚዲያ እና የኮሚኒኬሽን ክፍል ሀላፊ ኮማንደር ወንድሙ ሞቲ ጨምረዉ ተናግረዋል።
[ዳጉ ጆርናል/Bisrat FM]
@YeneTube @FikerAssefa
በጅማ ዞን ቀርሳ እና አሰንዳቦ ወረዳዎች በተደረገ ቁጥጥር በህገወጥ መንገድ በተሽከርካሪ ተጭኖ ሲጓዝ እንዲሁም በመኖሪያ ቤት ዉስጥ ተከማችቶ በዉድ ዋጋ ሊሸጥ የተዘጋጀ 1 ሺህ 47 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በጅማ ዞን ፖሊስ መምሪያ መያዙ ተነግሯል።የአፈር ማዳበሪያዉ ግምታዊ ዋጋዉ 5 ሚሊዮን 500 ሺህ ብር የሚገመት መሆኑን የጅማ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሚዲያ እና የኮሚኒኬሽን ክፍል ሀላፊ ኮማንደር ወንድሙ ሞቲ ተናግረዋል።የቀርሳ ወረዳ የህብረት ስራ ማህበር ማስፋፊያ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ነዚብ አባተማም ፤ በዞኑ ህገወጥ የፈር ማዳበሪያ ዝዉዉር እና ሽያጭ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ተናግረዉ ፤ በመዋቅር የተደራጀ ሌብነት ፈተና መሆኑን አክለዋል።
በዚህም አመራሮችን አሳታፊ ባደረገዉ ህገወጥ ድርጊት ፤ በህይወት በሌሉ ሰዎች ስም ጭምር ማዳበሪያ እንደሚወጣ እና እንደሚሸጥ ገልጸዋል። በቀርሳ ወረዳ 314 ኩንታል ማዳበሪያ በቁጥጥር ስር መዋሉንም አክለዋል። በወረዳዉ በህገወጥ መንገድ የሚሸጥ አንድ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ከ 10 ሺህ ብር በላይ እንደሚጠይቅ ሀላፊዉ ጠቁመዋል።በጅማ ዞን በርበሬ የሚዘሩ አርሶ አደሮች ወቅቱ እንዳያልፍባቸዉ በሚልም በህገወጥ የማዳበሪያ ግዢ ላይ ተሳታፊ ለመሆን እንደተገገዱም ገልጸዋል።
በሌላ በኩል ሰንዳቦ እና ጊቤ ኬላ ላይ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 428 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በህገወጥ መንገድ ተጭኖ ሲጓጓዝ መያዙን ኮማንደር ወንድሙ ሞቲ ተናግረዋል። በተጨማሪም ከቦነያ የህብረት ስራ ማህበር በ ሁለት ተሽከርካሪዎች ተጭኖ ሲጓጓዝ የነበረ 95 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ መያዙንም አክለዋል።
በተመሳሳይ በኦሞ ናዳ ወረዳ ዋቅቶላ ቀበሌ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ዉስጥ 210 ኩንታል ማዳበሪያ በተደረገ ፍተሻ ተይዟል። የአፈር ማዳበሪያዉ ሲያጓጉዙ የነበሩ እና አራት የህብረት ስራ ማህበራት ሰራተኞችን ጨምሮ ስድስት ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸዉን የጅማ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሚዲያ እና የኮሚኒኬሽን ክፍል ሀላፊ ኮማንደር ወንድሙ ሞቲ ጨምረዉ ተናግረዋል።
[ዳጉ ጆርናል/Bisrat FM]
@YeneTube @FikerAssefa
🔥1
Betስኬት ለስፖርታዊ ውርርዶች የሚጠቅሙ መረጃዎችን ይዞ ወደናንተ መጥቷል።
ስፖርታዊ ውርርድ(ቤቲንግ) መጫወት ሚያዘወትሩ ከሆነ ይህ ዌብሳይት ጨዋታዎችን ከቁጥራዊ መረጃዎች በመነሳት በጥልቀት በመተንተን የትኛውን ቡድን ወይም Possibility መምረጥ እንዳለብዎ ስራዎን እናቀልሎታለን፤ ትንተናዎቻችንን ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ።
ወደፊትን መገመት ከባድ ቢሆንም እኛ ግን ለእርሶ ለማቅለል ተግተን እንሰራልን!
ለዛሬ ምሽት የመረጥንላችሁ ጨዋታዎች:
https://www.betsket.com/man-utd-atletico-hoffenheim-cremonese-betting-tips/
ስፖርታዊ ውርርድ(ቤቲንግ) መጫወት ሚያዘወትሩ ከሆነ ይህ ዌብሳይት ጨዋታዎችን ከቁጥራዊ መረጃዎች በመነሳት በጥልቀት በመተንተን የትኛውን ቡድን ወይም Possibility መምረጥ እንዳለብዎ ስራዎን እናቀልሎታለን፤ ትንተናዎቻችንን ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ።
ወደፊትን መገመት ከባድ ቢሆንም እኛ ግን ለእርሶ ለማቅለል ተግተን እንሰራልን!
ለዛሬ ምሽት የመረጥንላችሁ ጨዋታዎች:
https://www.betsket.com/man-utd-atletico-hoffenheim-cremonese-betting-tips/
ተቋርጦ የነበረው የደሴ-ኮምቦልቻ-ከሚሴ-ደብረብርሐን አዲስ አበባ የየብስ ትራንስፖርት አገልግሎት በዛሬው እለት ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተገለፀ።
በአንድአንድ የአማራ ክልል አካባቢዎች ሰሞኑን ተፈጥሮ በነበረው አለመረጋጋት በተጠቀሱት አካባቢዎች በተወሰነ መልኩ አገልግሎቱ ተቋርጦ እንደነበር ይታወሳል፡፡
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
በአንድአንድ የአማራ ክልል አካባቢዎች ሰሞኑን ተፈጥሮ በነበረው አለመረጋጋት በተጠቀሱት አካባቢዎች በተወሰነ መልኩ አገልግሎቱ ተቋርጦ እንደነበር ይታወሳል፡፡
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
😁1
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ አባላት ሹመት ፀደቀ!
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ6ኛ ዙር 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ስብሰባው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ አባላትን ሹመት አጸደቀ፡፡
ሹመቱ የጸደቀው በውሳኔ ቁጥር 17/2015 በ1 ድምፅ ተዓቅቦ እና በአብላጫ ድምፅ መሆኑን የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል፡፡
በዚህ መሰረትም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርዱ አባላት ፡-
1. አዝመራው አንዴሞ --- ሰብሳቢ
2. ነጃት ግርማ (ዶ/ር) ምክትል --- ሰብሳቢ
3. አቶ ሣዲቅ አደም --- አባል
4. አቶ መስፍን እርካቤ --- አባል
5. አብርሃም በርታ ዶ/ር) --- አባል
6. ወ/ሮ ፍሬሕይወት ተሾመ --- አባል
7. አቶ ወንድሙ ግዛው --- አባል
በመሆን የተሰየሙ ሲሆን÷ የቦርዱ አባላትም በጉባዔው ፊት ቃለ መሐላ ፈጽመዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ6ኛ ዙር 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ስብሰባው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ አባላትን ሹመት አጸደቀ፡፡
ሹመቱ የጸደቀው በውሳኔ ቁጥር 17/2015 በ1 ድምፅ ተዓቅቦ እና በአብላጫ ድምፅ መሆኑን የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል፡፡
በዚህ መሰረትም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርዱ አባላት ፡-
1. አዝመራው አንዴሞ --- ሰብሳቢ
2. ነጃት ግርማ (ዶ/ር) ምክትል --- ሰብሳቢ
3. አቶ ሣዲቅ አደም --- አባል
4. አቶ መስፍን እርካቤ --- አባል
5. አብርሃም በርታ ዶ/ር) --- አባል
6. ወ/ሮ ፍሬሕይወት ተሾመ --- አባል
7. አቶ ወንድሙ ግዛው --- አባል
በመሆን የተሰየሙ ሲሆን÷ የቦርዱ አባላትም በጉባዔው ፊት ቃለ መሐላ ፈጽመዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጁ ከስሕተት ያለመማር ውጤት እንደኾነ ገዱ አንዳርጋቸው ተናገሩ!
በዐማራ ክልል፣ እስከ ስድስት ወር ተፈጻሚ እንዲኾን በሚኒስትሮች ም/ቤት የታወጀውና ዛሬ ሰኞ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የጸደቀው የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ፣ “ካለፉት አምስት ዓመታት ስሕተቶቻችን ያለመማራችን ውጤት ነው፤” ሲሉ፣ የቀድሞው የዐማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ ተቃውሟቸውን ገለጹ፡፡
በአሁኑ ወቅት፣ በዐማራ ክልል የተስፋፋው ችግር መሠረታዊ ምክንያት፣ የብልጽግና መንግሥት የፖለቲካ አመራር ክፍተት ነው፤ ያሉት አንዱ የፓርቲው መሥራች አቶ ገዱ፣ ራሱ የሚፈጥራቸውን ፖለቲካዊ ችግሮች፣ በወታደራዊ ኀይል መፍታት የመንግሥት ባሕርይ ኾኗል፤ ሲሉ ተችተዋል፡፡
አቶ ገዱ ይህን ተቃውሟቸውን ያሰሙት፣ ባለፈው ሳምንት ዐርብ፣ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የተደነገገው የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ረቂቅ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲጸድቅ በቀረበበት ወቅት ነው፡፡
የምክር ቤቱ አባላት፣ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጁን በመደገፍ እና በመቃወም ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ፣ በአብላጫ ድምፅ ጸድቋል፤ ስድስት የምክር ቤቱ አባላት ያሉበት፣ “የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መርማሪ ቦርድ”ም ሠይሟል፡፡
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
በዐማራ ክልል፣ እስከ ስድስት ወር ተፈጻሚ እንዲኾን በሚኒስትሮች ም/ቤት የታወጀውና ዛሬ ሰኞ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የጸደቀው የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ፣ “ካለፉት አምስት ዓመታት ስሕተቶቻችን ያለመማራችን ውጤት ነው፤” ሲሉ፣ የቀድሞው የዐማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ ተቃውሟቸውን ገለጹ፡፡
በአሁኑ ወቅት፣ በዐማራ ክልል የተስፋፋው ችግር መሠረታዊ ምክንያት፣ የብልጽግና መንግሥት የፖለቲካ አመራር ክፍተት ነው፤ ያሉት አንዱ የፓርቲው መሥራች አቶ ገዱ፣ ራሱ የሚፈጥራቸውን ፖለቲካዊ ችግሮች፣ በወታደራዊ ኀይል መፍታት የመንግሥት ባሕርይ ኾኗል፤ ሲሉ ተችተዋል፡፡
አቶ ገዱ ይህን ተቃውሟቸውን ያሰሙት፣ ባለፈው ሳምንት ዐርብ፣ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የተደነገገው የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ረቂቅ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲጸድቅ በቀረበበት ወቅት ነው፡፡
የምክር ቤቱ አባላት፣ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጁን በመደገፍ እና በመቃወም ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ፣ በአብላጫ ድምፅ ጸድቋል፤ ስድስት የምክር ቤቱ አባላት ያሉበት፣ “የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መርማሪ ቦርድ”ም ሠይሟል፡፡
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
Facebook, Twitter, Instagram እና በመሳሳሉት የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ድርጅትዎን ፤ አገልግሎትዎን እና ምርትዎን ማስተዋወቅ ፈልገዋል? እንግዲያውስ መፍትሄው እኛ ጋር ነው።
በማንኛውም Social Media Boost ለማድረግ ካሰቡ ይደውሉልን፤ በተመጣጣኝ ዋጋ ታማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት እንሰጣለን::
ከዚህም በተጨማሪ የቴሌግራም ፕሪሚየም ጨምሮ ለተለያዩ ኢንተርናሽናል አገልግሎቶች ክፍያዎችን መፈጸም ካስፈለግዎ ከስር በተቀመጡ አድራሻዎች ያናግሩን።
Telegram: @adsommar
📞0929334267
በማንኛውም Social Media Boost ለማድረግ ካሰቡ ይደውሉልን፤ በተመጣጣኝ ዋጋ ታማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት እንሰጣለን::
ከዚህም በተጨማሪ የቴሌግራም ፕሪሚየም ጨምሮ ለተለያዩ ኢንተርናሽናል አገልግሎቶች ክፍያዎችን መፈጸም ካስፈለግዎ ከስር በተቀመጡ አድራሻዎች ያናግሩን።
Telegram: @adsommar
📞0929334267
መንግሥት በአማራ ክልል የሚወስዳቸው እርምጃዎች በግጭቱ ተሳትፎ የሌላቸውን ሰዎች እንዲለይ ተጠየቀ!
መንግሥት በአማራ ክልል ያለውን ግጭት ለመቆጣጠር የሚወስዳቸው እርምጃዎች በግጭቱ ተሳትፎ የሌላቸውን ሰዎች በመለየት እንዲፈጸሙ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ጠየቀ።
በመከላከያ እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል እየተደረገ ያለው ውጊያ የሰላማዊ ዜጎችን ህይወት መቅጠፉን ተከትሎም ነው ኢሰመጉ መንግሥት “የሚወስዳቸው ሰላም የማስከበር እርምጃዎች ተመጣጣኝ እና በግጭቱ ተሳታፊዎች ላይ” ተፈጻሚ እንዲሆኑ ነሐሴ 8/2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ የጠየቀው።
በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተ ሰላም ከተማ ነሐሴ 7/2015 ዓ.ም የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ተመጣጣኝ ያልሆነ እና በግጭቱ ተሳታፊ ያልሆኑ ሰዎችን ሳይለዩ ጥቃት መፈጸማቸውን ኢሰመጉ በመግለጫው አትቷል።ከፍኖተ ሰላም በተጨማሪ በቡሬ ከተማም ነሐሴ 6/2015 ዓ.ም ተመሳሳይ ጥቃት መድረሱን ገልጾ በዚህም በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች እንደሞቱና የአካል ጉዳት እና ንብረት መውደሙንም ኢሰመጉ በመግለጫው አስፍሯል።
በነዚህ ጥቃቶች የሞቱ ሰዎችን ቁጥር መግለጫው ባያትትም በፍኖተ ሰላም ከተማ ላይ በተፈጸመ ጥቃት ቢያንስ 25 ሰዎች መገደላቸውንና ከ50 በላይ ሰዎችም እንደቆሰሉ የሆስፒታል ምንጮች ለቢቢሱ ተናግረዋል።ጥቃቶቹን በተመለከተ አንዳንዶች የደረሰው በከባድ መሳሪያ ነው ሲሉ ሌሎች ደግሞ በሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) የተፈጸመ መሆኑንም ነው ለቢበሲ የገለጹት።
በአማራ ክልል እንደ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ሸዋ ሮቢት፣ ደብረ ብርሃን፣ ላሊበላ እና ሌሎችም ከተሞች በፋኖ ታጣቂዎች እና በመንግሥት ኃይሎች መካከል ከሰሞኑ የተኩስ ልውውጦች የነበሩ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎችም ላይ ከባድ መሳሪያዎች ጭምር ጥቅም ላይ መዋላቸውንም ኢሰመጉ አስታውቋል።ኢሰመጉ በዚህም በግጭቱ ተሳታፊ ያልሆኑ በርካታ ሰዎች መሞታቸውን፣ የአካል ጉዳት መድረሱንም በትናንትናው መግለጫው አስፍሯል። በተጨማሪም የማረሚያ ቤቶችና የፖሊስ ጣቢያዎች ሰበራ ተፈጽሞባቸው የመሳሪያዎች ዝርፊያ እና ከፍተኛ የንብረት መውደም ደርሷል ብሏል።በአማራ ክልል በተከሰተው ግጭት የንጹሃን ሕይወት መጥፋቱን፣ ንብረት መውደሙን እና ዘረፋ መፈጸሙን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ከሰሞኑ አስታውቋል።
በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ለቀናት በዘለቀው ግጭት በአማራ ክልል ከተሞች እና የተለያዩ አካባቢዎች እስካሁን በውል ያልታወቁ ሰዎች መሞታቸው መዘገቡ ይታወሳል።በአማራ ክልል ያሉ ከተሞችን ከፋኖ ታጣቂዎች ነጻ ማድረጉን መንግሥት ከሰሞኑ ማስታወቁንም ተከተሎ በአንዳንድ አካባቢዎች አንጻራዊ መረጋጋት መታየቱን የጠቆመው የኢሰመጉ መግለጫ አሁንም ውጥረት እና ስጋት ያለባቸው አካባቢዎችም አሉ ብሏል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
መንግሥት በአማራ ክልል ያለውን ግጭት ለመቆጣጠር የሚወስዳቸው እርምጃዎች በግጭቱ ተሳትፎ የሌላቸውን ሰዎች በመለየት እንዲፈጸሙ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ጠየቀ።
በመከላከያ እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል እየተደረገ ያለው ውጊያ የሰላማዊ ዜጎችን ህይወት መቅጠፉን ተከትሎም ነው ኢሰመጉ መንግሥት “የሚወስዳቸው ሰላም የማስከበር እርምጃዎች ተመጣጣኝ እና በግጭቱ ተሳታፊዎች ላይ” ተፈጻሚ እንዲሆኑ ነሐሴ 8/2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ የጠየቀው።
በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተ ሰላም ከተማ ነሐሴ 7/2015 ዓ.ም የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ተመጣጣኝ ያልሆነ እና በግጭቱ ተሳታፊ ያልሆኑ ሰዎችን ሳይለዩ ጥቃት መፈጸማቸውን ኢሰመጉ በመግለጫው አትቷል።ከፍኖተ ሰላም በተጨማሪ በቡሬ ከተማም ነሐሴ 6/2015 ዓ.ም ተመሳሳይ ጥቃት መድረሱን ገልጾ በዚህም በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች እንደሞቱና የአካል ጉዳት እና ንብረት መውደሙንም ኢሰመጉ በመግለጫው አስፍሯል።
በነዚህ ጥቃቶች የሞቱ ሰዎችን ቁጥር መግለጫው ባያትትም በፍኖተ ሰላም ከተማ ላይ በተፈጸመ ጥቃት ቢያንስ 25 ሰዎች መገደላቸውንና ከ50 በላይ ሰዎችም እንደቆሰሉ የሆስፒታል ምንጮች ለቢቢሱ ተናግረዋል።ጥቃቶቹን በተመለከተ አንዳንዶች የደረሰው በከባድ መሳሪያ ነው ሲሉ ሌሎች ደግሞ በሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) የተፈጸመ መሆኑንም ነው ለቢበሲ የገለጹት።
በአማራ ክልል እንደ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ሸዋ ሮቢት፣ ደብረ ብርሃን፣ ላሊበላ እና ሌሎችም ከተሞች በፋኖ ታጣቂዎች እና በመንግሥት ኃይሎች መካከል ከሰሞኑ የተኩስ ልውውጦች የነበሩ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎችም ላይ ከባድ መሳሪያዎች ጭምር ጥቅም ላይ መዋላቸውንም ኢሰመጉ አስታውቋል።ኢሰመጉ በዚህም በግጭቱ ተሳታፊ ያልሆኑ በርካታ ሰዎች መሞታቸውን፣ የአካል ጉዳት መድረሱንም በትናንትናው መግለጫው አስፍሯል። በተጨማሪም የማረሚያ ቤቶችና የፖሊስ ጣቢያዎች ሰበራ ተፈጽሞባቸው የመሳሪያዎች ዝርፊያ እና ከፍተኛ የንብረት መውደም ደርሷል ብሏል።በአማራ ክልል በተከሰተው ግጭት የንጹሃን ሕይወት መጥፋቱን፣ ንብረት መውደሙን እና ዘረፋ መፈጸሙን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ከሰሞኑ አስታውቋል።
በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ለቀናት በዘለቀው ግጭት በአማራ ክልል ከተሞች እና የተለያዩ አካባቢዎች እስካሁን በውል ያልታወቁ ሰዎች መሞታቸው መዘገቡ ይታወሳል።በአማራ ክልል ያሉ ከተሞችን ከፋኖ ታጣቂዎች ነጻ ማድረጉን መንግሥት ከሰሞኑ ማስታወቁንም ተከተሎ በአንዳንድ አካባቢዎች አንጻራዊ መረጋጋት መታየቱን የጠቆመው የኢሰመጉ መግለጫ አሁንም ውጥረት እና ስጋት ያለባቸው አካባቢዎችም አሉ ብሏል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
ከምርት ጥራት በታች የሚያመርቱ 32 ፋብሪካዎች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ!
በ2015 በጀት ዓመት አስገዳጅ የኢትዮጵያ ደረጃ ያላቸውን ምርቶች የሚያመርቱ 382 ፋብሪካዎች ላይ ባተደረገ የኢንስፔክሽን ሥራ የ32 ፋብሪካ ምርቶች ጥራት ከደረጃ በታች ሆኖ በመገኘቱ እርምጃ መውሰዱንየንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
እርምጃ የተወሰደባቸው 25 የልብስ ሳሙና፣ ውኃ፣ ሽንሽን ቆርቆሮ፣ ሚስማር፣ አርማታ ብርት፣ non-carbonated fruit juice፣ ሶኬት እና ዋይን ፋብሪካዎች የማምረት ሂደቱን አቁመው የማስተካከያ ሥራዎችን እንዲሰሩ የተደረገ ሲሆን፤ 7 አኩሪ አተር ማከፋፋያ፣ የውኃ እና የሳሙና የፋብሪካዎች ላይ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱ ተነግሯል።
ሸማቹን ህብረተሰብ ጥራታቸውና ደህንነታቸው ካልተረጋገጡ ምርቶች በመከላከል ጤናና ደህንነቱ እንዲጠበቅ ለማድረግ በቀጣይም በየፋብሪካዎቹ ላይ የሚደረገው የምርት ጥራት ቁጥጥር ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።ሚኒስቴሩ በፋብሪካዎቹ ላይ እርምጃ መውሰዱን ይግለጽ እንጂ፤ በየትኞቹ ፋብሪካዎች ላይ እርምጃው እንደተወሰደ በዝርዝር ይፋ አላደረገም፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በ2015 በጀት ዓመት አስገዳጅ የኢትዮጵያ ደረጃ ያላቸውን ምርቶች የሚያመርቱ 382 ፋብሪካዎች ላይ ባተደረገ የኢንስፔክሽን ሥራ የ32 ፋብሪካ ምርቶች ጥራት ከደረጃ በታች ሆኖ በመገኘቱ እርምጃ መውሰዱንየንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
እርምጃ የተወሰደባቸው 25 የልብስ ሳሙና፣ ውኃ፣ ሽንሽን ቆርቆሮ፣ ሚስማር፣ አርማታ ብርት፣ non-carbonated fruit juice፣ ሶኬት እና ዋይን ፋብሪካዎች የማምረት ሂደቱን አቁመው የማስተካከያ ሥራዎችን እንዲሰሩ የተደረገ ሲሆን፤ 7 አኩሪ አተር ማከፋፋያ፣ የውኃ እና የሳሙና የፋብሪካዎች ላይ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱ ተነግሯል።
ሸማቹን ህብረተሰብ ጥራታቸውና ደህንነታቸው ካልተረጋገጡ ምርቶች በመከላከል ጤናና ደህንነቱ እንዲጠበቅ ለማድረግ በቀጣይም በየፋብሪካዎቹ ላይ የሚደረገው የምርት ጥራት ቁጥጥር ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።ሚኒስቴሩ በፋብሪካዎቹ ላይ እርምጃ መውሰዱን ይግለጽ እንጂ፤ በየትኞቹ ፋብሪካዎች ላይ እርምጃው እንደተወሰደ በዝርዝር ይፋ አላደረገም፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል የባጃጅ ትራንስፖርት ክልከላ በተጣለባቸው ከተሞች አገልግሎቱ ነገ እንዲጀመር ዕዙ ፈቀደ!
በአማራ ክልል ክልከላ በተጣለባቸው ስድስት ከተሞች ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጅ) መደበኛ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲጀምሩ የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ፈቀደ።ዕዙ በሰጠው ቁጥር ሁለት ወቅታዊ መረጃ ዛሬ ማለዳ ላይ ባደረገዉ ግምገማ የሁለተኛዉ ዙር ወታደራዊ ኦፕሬሽን ሥራዎች ከሞላ ጎደል እየተጠናቀቁና እየተወሰደ ባለዉ ርምጃ አብዛኞቹ አካባቢዎች ወደ መደበኛ ሁኔታ እየተመለሱ መሆናቸዉን አረጋግጧል፡፡
በሁሉም አካባቢዎች ከልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ዉይይት መጀመሩን፣ የመንግሥት፣ የግልና የማኅበረሰብ አገልግሎቶች ወደ መደበኛ ሥራቸዉ እንዲመለሱ እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።ሕዝቡ ለመከላከያ ሠራዊታችን እያሳየ ያለው አቀባበል፣ የስንቅና የማበረታቻ ድጋፍ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱን፣ ማኅበረ ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ሥራ እንዲጀምሩ ያለው ፍላጎትና እንቅስቃሴ አበረታች መሆኑን ዕዙ አረጋግጧል፡፡
አርሶ አደሩ ወደ መኸር አዝመራ ሥራዉ እየተመለሰ እንዲሁም የግብርና ግብአቶችን ወደየአካባቢዎቹ ለማጓጓዝ የሚያስችል ሁኔታ መፈጠሩን ዕዙ ገምግሟል።የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥብቅ መመሪያ የሰጠው ዕዙ፤ ክልከላ በተደረገባቸው ከተሞች የባጃጅ ተሸከርካሪዎች አገልግሎት እንዲጀምሩ ከኅብረተሰቡ የቀረበዉን ጥያቄ መርምሮ ከነገ ጀምሮ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ፈቅዷል፡፡
ከዚህም ጋር በማያያዝ ክልከላዉ ከተነሣበት ጊዜ ጀምሮ የባጃጅ ባለቤቶችና አሽካርካሪዎች የጽንፈኛ ቡድኑን አባላት፣ የዘረፉትን ንብረቶችና የትኛዉንም ዓይነት የጦር መሣሪያ ከማጓጓዝ እንዲቆጠቡና ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥብቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ይህንን ተላልፈዉ በተገኙት ላይ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማሕቀፍ ሕጋዊ ርምጃ እንዲወሰድ ትዕዛዝ መስጠቱን በመግለጫው አመልክቷል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል ክልከላ በተጣለባቸው ስድስት ከተሞች ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጅ) መደበኛ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲጀምሩ የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ፈቀደ።ዕዙ በሰጠው ቁጥር ሁለት ወቅታዊ መረጃ ዛሬ ማለዳ ላይ ባደረገዉ ግምገማ የሁለተኛዉ ዙር ወታደራዊ ኦፕሬሽን ሥራዎች ከሞላ ጎደል እየተጠናቀቁና እየተወሰደ ባለዉ ርምጃ አብዛኞቹ አካባቢዎች ወደ መደበኛ ሁኔታ እየተመለሱ መሆናቸዉን አረጋግጧል፡፡
በሁሉም አካባቢዎች ከልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ዉይይት መጀመሩን፣ የመንግሥት፣ የግልና የማኅበረሰብ አገልግሎቶች ወደ መደበኛ ሥራቸዉ እንዲመለሱ እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።ሕዝቡ ለመከላከያ ሠራዊታችን እያሳየ ያለው አቀባበል፣ የስንቅና የማበረታቻ ድጋፍ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱን፣ ማኅበረ ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ሥራ እንዲጀምሩ ያለው ፍላጎትና እንቅስቃሴ አበረታች መሆኑን ዕዙ አረጋግጧል፡፡
አርሶ አደሩ ወደ መኸር አዝመራ ሥራዉ እየተመለሰ እንዲሁም የግብርና ግብአቶችን ወደየአካባቢዎቹ ለማጓጓዝ የሚያስችል ሁኔታ መፈጠሩን ዕዙ ገምግሟል።የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥብቅ መመሪያ የሰጠው ዕዙ፤ ክልከላ በተደረገባቸው ከተሞች የባጃጅ ተሸከርካሪዎች አገልግሎት እንዲጀምሩ ከኅብረተሰቡ የቀረበዉን ጥያቄ መርምሮ ከነገ ጀምሮ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ፈቅዷል፡፡
ከዚህም ጋር በማያያዝ ክልከላዉ ከተነሣበት ጊዜ ጀምሮ የባጃጅ ባለቤቶችና አሽካርካሪዎች የጽንፈኛ ቡድኑን አባላት፣ የዘረፉትን ንብረቶችና የትኛዉንም ዓይነት የጦር መሣሪያ ከማጓጓዝ እንዲቆጠቡና ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥብቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ይህንን ተላልፈዉ በተገኙት ላይ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማሕቀፍ ሕጋዊ ርምጃ እንዲወሰድ ትዕዛዝ መስጠቱን በመግለጫው አመልክቷል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
👍2
ከተበተኑ የአማራ ክልል የልዩ ኃይል አባላት መካከል፤ “አብዛኛዎቹ” ታጣቂ ቡድኖችን መቀላቀላቸውን የሰላም ሚኒስትሩ ገለጹ!
በአማራ ክልል የልዩ ኃይል አባላትን ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማስገባት ስራ ከተጀመረ በኋላ 50 በመቶ የሚሆኑ የልዩ ኃይል አባላት “እንደተበተኑ” እና ከእነዚህ ውስጥ “አብዛኛዎቹ” ታጣቂ ቡድኖችን እንደተቀላቀሉ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዷለም ተናገሩ። በአማራ ክልል ከሰሞኑ የተቀሰቀሰው ግጭት የተጀመረው፤ ታጣቂዎች በመከላከያ ሰራዊት ካምፕ ላይ “ዘግናኝ የሚባል ጥቃት መክፈታቸውን” ተከትሎ እንደሆነም ገልጸዋል።
የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ ይህንን የተናገሩት፤ በአማራ ክልል ከሰሞኑ የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር አስመልክቶ ትላንት ሰኞ ነሐሴ 8፤ 2015 ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በአዲስ አበባው ካፒታል ሆቴል በተደረገ ውይይት ላይ ነው። አቶ ብናልፍ እና የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በመሩት በዚህ ስብሰባ 16 የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ተሳትፈውበታል።
አቶ ብናልፍ በስብሰባው መጀመሪያ ላይ ባቀረቡት ማብራሪያ፤ መንግስት በአማራ ክልል ያጋጠመው ግጭት “ዝም ብሎ በድንገት የተፈጠረ” ነው የሚል እምነት እንደሌለው እና “በተለያዩ ጊዜ የሚነሱ እና እየተደመሩ የመጡ ችግሮች የፈጠሩት” እንደሆነ አስረድተዋል። የሰላም ሚኒስትሩ በዚሁ ማብራሪያቸው ላይ በአማራ ክልል ለተፈጠረው ችግር ምክንያት የሆኑ ካሏቸው “የህዝብ ጥያቄዎች” ውስጥ፤ የወሰን እና ማንነት ጉዳይ፣ የፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና የእኩልነት ጥያቄ እንዲሁም “የፈለጉትን የፖለቲካ ሀሳብ ለማራመድ የሚያስችል ሁኔታ አለመኖር” የሚሉት ይገኙበታል።
ዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11795/
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል የልዩ ኃይል አባላትን ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማስገባት ስራ ከተጀመረ በኋላ 50 በመቶ የሚሆኑ የልዩ ኃይል አባላት “እንደተበተኑ” እና ከእነዚህ ውስጥ “አብዛኛዎቹ” ታጣቂ ቡድኖችን እንደተቀላቀሉ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዷለም ተናገሩ። በአማራ ክልል ከሰሞኑ የተቀሰቀሰው ግጭት የተጀመረው፤ ታጣቂዎች በመከላከያ ሰራዊት ካምፕ ላይ “ዘግናኝ የሚባል ጥቃት መክፈታቸውን” ተከትሎ እንደሆነም ገልጸዋል።
የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ ይህንን የተናገሩት፤ በአማራ ክልል ከሰሞኑ የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር አስመልክቶ ትላንት ሰኞ ነሐሴ 8፤ 2015 ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በአዲስ አበባው ካፒታል ሆቴል በተደረገ ውይይት ላይ ነው። አቶ ብናልፍ እና የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በመሩት በዚህ ስብሰባ 16 የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ተሳትፈውበታል።
አቶ ብናልፍ በስብሰባው መጀመሪያ ላይ ባቀረቡት ማብራሪያ፤ መንግስት በአማራ ክልል ያጋጠመው ግጭት “ዝም ብሎ በድንገት የተፈጠረ” ነው የሚል እምነት እንደሌለው እና “በተለያዩ ጊዜ የሚነሱ እና እየተደመሩ የመጡ ችግሮች የፈጠሩት” እንደሆነ አስረድተዋል። የሰላም ሚኒስትሩ በዚሁ ማብራሪያቸው ላይ በአማራ ክልል ለተፈጠረው ችግር ምክንያት የሆኑ ካሏቸው “የህዝብ ጥያቄዎች” ውስጥ፤ የወሰን እና ማንነት ጉዳይ፣ የፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና የእኩልነት ጥያቄ እንዲሁም “የፈለጉትን የፖለቲካ ሀሳብ ለማራመድ የሚያስችል ሁኔታ አለመኖር” የሚሉት ይገኙበታል።
ዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11795/
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
👍2
በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የፕሮግራሞች አከፋፈት የዩኒቨርስቲዎችን የትኩረትና ተልእኮ ልየታ የተከተለ እንዲሆን አቅጣጫ ተሰጠ::
በ2016 የትምህርት ዘመን በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የፕሮግራሞች አከፋፈት የዩኒቨርስቲዎችን የትኩረትና ተልእኮ ልየታ የተከተለ እንዲሆን በትምህርት ሚኒስቴር ነሃሴ 09/2015ዓ. ም በተጻፈ ደብዳቤ አቅጣጫ ተሰጥቷል።
እስካሁን በመሰጠት ላይ ያሉ የቅድመና ድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች በ2016 ዓ.ም በዝርዝር ተፈትሸውና ተገምግመው ከዩኒቨርስቲዎች ልየታ ጋር መጣጣማቸውን የማረጋገጥ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ለሁሉም ዩኒቨርስቲዎች በጻፉት ደብዳቤ የታቀዱ አዳዲስ ፕሮግራሞች ለመክፈት የሚደረጉ ጥናቶች ባሉበት እንዲቆዩ፣ መጪው የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በአዳዲስ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን እንዳይቀበሉ እንዲሁም በቦርድ በጸደቁና በትምህርት ሚኒስቴር በተመዘገቡ አዳዲስ ፕሮግራሞችም ዩኒቨርስቲዎች ተማሪ መቀበል እንዳይጀምሩ አሳስበዋል።
አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች ባሉበት እንዲቆዩ የተወሰነው የትምህርት ፕሮግራሞች ተገምግመው ከዩኒቨርስቲዎች ተልዕኮና ትኩረት ጋር መጣጣማቸው እስኪረጋገጥ ድረስ አዳዲስ ፕሮግራሞችን የመክፈት ስራ መግታት አስፈላጊ በመሆኑ ነው ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በ2016 የትምህርት ዘመን በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የፕሮግራሞች አከፋፈት የዩኒቨርስቲዎችን የትኩረትና ተልእኮ ልየታ የተከተለ እንዲሆን በትምህርት ሚኒስቴር ነሃሴ 09/2015ዓ. ም በተጻፈ ደብዳቤ አቅጣጫ ተሰጥቷል።
እስካሁን በመሰጠት ላይ ያሉ የቅድመና ድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች በ2016 ዓ.ም በዝርዝር ተፈትሸውና ተገምግመው ከዩኒቨርስቲዎች ልየታ ጋር መጣጣማቸውን የማረጋገጥ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ለሁሉም ዩኒቨርስቲዎች በጻፉት ደብዳቤ የታቀዱ አዳዲስ ፕሮግራሞች ለመክፈት የሚደረጉ ጥናቶች ባሉበት እንዲቆዩ፣ መጪው የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በአዳዲስ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን እንዳይቀበሉ እንዲሁም በቦርድ በጸደቁና በትምህርት ሚኒስቴር በተመዘገቡ አዳዲስ ፕሮግራሞችም ዩኒቨርስቲዎች ተማሪ መቀበል እንዳይጀምሩ አሳስበዋል።
አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች ባሉበት እንዲቆዩ የተወሰነው የትምህርት ፕሮግራሞች ተገምግመው ከዩኒቨርስቲዎች ተልዕኮና ትኩረት ጋር መጣጣማቸው እስኪረጋገጥ ድረስ አዳዲስ ፕሮግራሞችን የመክፈት ስራ መግታት አስፈላጊ በመሆኑ ነው ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
Betስኬት ለስፖርታዊ ውርርዶች የሚጠቅሙ መረጃዎችን ይዞ ወደናንተ መጥቷል።
ስፖርታዊ ውርርድ(ቤቲንግ) መጫወት ሚያዘወትሩ ከሆነ ይህ ዌብሳይት ጨዋታዎችን ከቁጥራዊ መረጃዎች በመነሳት በጥልቀት በመተንተን የትኛውን ቡድን ወይም Possibility መምረጥ እንዳለብዎ ስራዎን እናቀልሎታለን፤ ትንተናዎቻችንን ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ።
ወደፊትን መገመት ከባድ ቢሆንም እኛ ግን ለእርሶ ለማቅለል ተግተን እንሰራልን!
ለዛሬ ምሽት የመረጥንላችሁ ጨዋታዎች:
👇👇
https://rb.gy/d76bx
ስፖርታዊ ውርርድ(ቤቲንግ) መጫወት ሚያዘወትሩ ከሆነ ይህ ዌብሳይት ጨዋታዎችን ከቁጥራዊ መረጃዎች በመነሳት በጥልቀት በመተንተን የትኛውን ቡድን ወይም Possibility መምረጥ እንዳለብዎ ስራዎን እናቀልሎታለን፤ ትንተናዎቻችንን ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ።
ወደፊትን መገመት ከባድ ቢሆንም እኛ ግን ለእርሶ ለማቅለል ተግተን እንሰራልን!
ለዛሬ ምሽት የመረጥንላችሁ ጨዋታዎች:
👇👇
https://rb.gy/d76bx
👍1