YeneTube
118K subscribers
31.4K photos
485 videos
79 files
3.87K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2013 ዓ፣ም ኢትዮጵያ ከቱርክ ጋር የፈረመቻቸውን የወታደራዊ ማዕቀፍ ስምምነት፣ የወታደራዊ ፋይናንስ ስምምነት እና የፋይናንስ ድጋፍ ማስፈጸሚያ ፕሮቶኮል ዛሬ ማጽደቁን የዋዜማ ሪፖርተር ዘግባለች። የወታደራዊ ማዕቀፍ ስምምነቱ በወታደራዊ ልምምዶች፣ በመከላከያ ኢንዱስትሪ፣ በወታደራዊ መረጃ፣ ልውውጥ፣ በወታደራዊ ኮምንኬሽን ወዘተ የሁለትዮሽ ትብብር ለማድረግ የሚያስችል ነው። የወታደራዊ ፋይናንስ ስምምነቱ ደሞ ኢትዮጵያ ለአምስት ዓመታት ቱርክ ሰራሽ የመከላከያ መሳሪያዎችን ከቱርክ ኩባንያዎች እንድትገዛና ያለ ቱርክ ፍቃድ መሳሪያዎቹን ለሦስተኛ ወገን አሳልፋ እንዳትሰጥ የሚከለክል ነው።

[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
👉 ለጤናው ቅድሚያ እንሰጣለን


መሪጌታ ጥበቡ
የባህል ህክምና መስጫ ከአባቶቻችን
በተሰጠንና ባገኘነው ልምድና ጥበብ መሰረት የተለያዩ የጤና መፍትሔወችን እንሰጣለን።፦

የምንሰጣቸው አገልግሎቶችም

👉 የኪንታሮት መድኀኒት በሚቀባ ታማሚው
ወደቤቱ ወስዶ በመቀባት ሌላ ገላሳይነካ
ሳያቆስል ስራ ሳያስተጓጉል በሽታውን ለይቶ በማውጣት ሁለተኛ እንዳይተካ አድርጎ የፈውሳል።
👉 የእሪህ መድአኒት ወስዶ በመቀባት ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል
👉 ገብያ ለገረገረው ለገብያ
👉 ለመፍትሔ ስራይ
👉 ለአይነ ጥላ (ለገርጋሪ)
👉 ለስንፈተ ወሲቢ ለሚቸኩልበት
👉 የአስም (የሳይነስ)
👉 ለማይስማሙ (ለመስተፋቅር)
👉 ገንዘብ ለሚበተንበት
👉 ስራ አልሳካለት ላለ
👉 ለቡዳ
👉 ለሚጥል በሽታ
👉 ለማህጸን እንፌክሽን
👉 ህይወቱ ለሚመሰቃቀልበት
👉 ለአዕምሮ ጭንቀት
👉 ሌሊት ለሚሸና
👉 ለነገረ በትን
👉 ለሆድ ሀህመም
👉 ለስኳር መቀነሻ
👉 ለነርብ
👉 እራሱን ለሚያመው

እነዚህንና ሌሎች አገልግሎቶችን እንሰጣለን

መዳኒቱን ባሉበት ቦታ መላላክ ይቻላል

በሁሉም አገልግሎቶቻችን ውጤቱን እንዳዪ ክፍያ ይፈጽማሉ

አድራሻ
ባህርዳር ቀበሌ 11
ዲያስፖራ በኮብሉ

ለበለጠ መረጃ
☎️ 0917040506
📞 0912718883

ይደውሉ👍

መፍትሔ ሥራይ ወአይነ ጥላ ለጤናወ
መፍትሔ ከመሪጌታ ጥበቡ
የሚፈልጉትን ለማግኔት ይሄን ቻናል ይቀላቀሉ
🩺
https://tttttt.me/meritibe
https://tttttt.me/meritibe👇
👇
አስደሳች ዜና 12ኛ ክፍል ለጨረሳቹ እና በመማር ላይ ላላቹ!!!

ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።

እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!

በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል

የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy

አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102

ስልክ: 0960612222
0118345171

ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
125 አዳዲስ የገጠር ከተሞችና መንደሮች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆናቸው ተገለፀ!

ባለፉት ዘጠኝ ወራት 125 አዳዲስ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡ተቋሙ አገልግሎቱን ለኹሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ ከ1997 ጀምሮ የአገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራም በመቅረፅ በርካታ ሥራዎች ሲያከናውን የቆየ ሲሆን፤ ፕሮግራሙ ከመጀመሩ በፊት 667 የገጠር ከተሞች ብቻ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ እንደነበሩ ገልጿል፡፡

ከ1998 ጀምሮ በተደረገው ከፍተኛ ፍትሃዊ የኤሌክትሪክ የማዳረስ ሥራ እስከ መጋቢት 30 ቀን 2014 ድረስ 7 ሺህ 892 የገጠር ከተሞችንና መንደሮች ኤሌከትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም አስታውቋል።ተቋሙ በተመሳሳይ በ2012 በጀት ዓመት 308፣ በ2013 በጀት ዓመት ደግሞ 341 አዳዲስ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የአገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራም ዳይሬክተር ሁሴን መሀመድ ገልፀዋል፡፡

አዳዲስ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ሲታቃድ፤ ዕድሉን የሚያገኙ አካባቢዎች ለይተው እንዲያሳወቁ የሚደረጉት ክልሎች መሆናቸውና እነሱ ቅድሚያ ይሰጣቸው ብለው ለይተው ሲያሳውቁ ሥራውን እንደሚከናወንም ዳይሬክተሩ አክለው ተናግረዋል፡፡የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን በብሄራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም እ.ኤ.አ በ2025 ከዋናው ግሪድ 65 በመቶ እንዲሁም በአማራጭ የኃይል ምንጮች 35 በመቶ የሚሆነውን ህብረተሰብ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ መሆኑንም አስታውቋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
ፊንላንድ እና ስዊድን የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን ድርጅት (ኔቶ) አባል ለመሆን ይፋዊ ደብደቤ ማስገባታቸውን አልጃዚራ ዘግቧል።

@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጲያ በተከሰቱ ግጭቶች ሳቢያ ፆታዊ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተዘጋጀ!

ተፈጥሯዊ አደጋን ጨምሮ በአንዳንድ የኢትዮጲያ ክፍሎች ባጋጠሙ የፀጥታ መደፍረሶች ሳቢያ በርካታ ሴቶች እና ህፃናት የከፋ ችግር ውስጥ እንደሚገኙ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቋል ፡፡ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በተፈጥሯዊ አደጋዎች ሳቢያ ተፈናቅለው በመጠለያ ጣቢያ ውስጥ የሚገኙ ሴቶች እና ህፃናት ድጋፍ እና ክትትል እየተደረገ እንደሚገኝ አሳውቋል፡፡

በተጨማሪም በግጭቶቹ ሳቢያ ለፆታዊ ጥቃት የተዳረጉ በርካታ ዜጎች ይገኛሉ ያሉት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትሯ ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ እነዚህን ሴቶች እና ህፃናትን የአንድ ማዕከል የጤና እና የስነ ልቦና ድጋፍ ማድረግ የሚችሉበትን መንገድ ለመፍጠር የሚያስችል የአንድ ማዕከል አገልግሎት መዘጋጀቱን ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል፡፡

ከእዚህ በተጨማሪ በግጭቱ ምክንያት ከወላጆቻቸው ጋር የተለያዩ ህፃናትን በተለያዩ አማራጮች ለማገዝ የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል። ለአብነት አንድ ዲያስፖራ ለአንድ ህፃናት በሚል መረሃ ግብር የተደረገው የድጋፍ መንገድ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡በቀጣይም ከአለም ባንክ ጋር በመተባበር ተጠቂ ዜጎች ከለላ የሚያገኙበትን እና መጠለያ ስፍራዎች በዘላቂነት ለማዘጋጀት እየተሰራ ይገኛል ሲሉ ዶ/ር ኤርጎጌ ጨምረው ተናግረዋል፡፡

Via Bisrat FM
@YeneTube @FikerAssefa
የኢድ አልፈጥር በዓል ላይ አስለቃሽ ጭስ ቦንብ በማፈንዳት ወንጀል የተጠረጠረው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ በዕለቱ በደረሰብኝ ድብደባ ግራ አይኔ እና ኩላሊቴ ላይ ጉዳት ደርሷብኛል ሲል ለፍርድ ቤት አስታወቀ!

የኢዳልፈጥር በዓል ላይ በመስቀል አደባባይ አካባቢ አስለቃጭ ጭስ ቦንብ በማፈንዳት ወንጀል የተጠረጠረው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ በዕለቱ በደረሰብኝ ድብደባ ግራ አይኔ እና ኩላሊቴ ላይ ጉዳት ደርሷብኛል ሲል ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት አስታወቀ።

የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል አድማ ብተና ዘርፍ ባልደረባ የሆነው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ ባሳለፍነው ሚያዚያ 24 ቀን በተከበረው የኢዳል ፈጥር ባአል በአ/አ ከተማ በመስቀል ሰማታት መታሰቢያ ሙዚዬም አካባቢ በተመደበበት የወንጀል መከላከል ስራ ላይ ኦያለ ከፈነዳው አስለቃሽ ጭስ ቦንብ ጋር ተያይዞ ተጠርጥሮ ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ካለጠበቃ ፍርድ ቤት ቀርቧል።

ተጠርጣሪው ኢድ አልፈጥር በዓል በተመደበበት ሥራ ላይ በአጋጣሚ ሳላውቅ የፈነዳብኝ አስለቃጭ ጭስ ቦንብ ሲፈነዳብኝ ጭሱ ወደ ህዝቡ እንዳሄድ ወዲያው ሸገር ባስ ውስጥ ወርውሬ ከትቻለሁ፤ በአካባቢው የነበሩት ሰዎች ግን የፌደራል ፖሊስ ልብስ ለብሼ ሳለሁ አንገቴን አንቀው ባደረሱብኝ ድብደባ የግራ አይኔና ኩላሊቴ ላይ ጉዳት አድርሰውብኛል ሲል ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።

ተጠርጣሪውን ያቀረቡት ሁለት መርማሪ ፖሊሶች ባሳለፍነው ሚያዚያ 26 ቀን ጀምሮ ለተጨማሪ ምርመራ በተሰጣቸው የ10 ቀን ጊዜ ውስጥ የሰሩትን የምርመራ ውጤት ለችሎቱ አቅርበዋል።በዚህም የሦስት ሰዎች ምስክርነት ቃል መቀበላቸውንና የሥራ ሀላፊዎችን ቃል መውሰዳቸውን፣ የተጠርጣሪው የግል ስልክ ምርመራ እንዲደረግ ለብሔራዊ መረጃ ደህንነትና ለኢትዮ ቴሌኮም ደብዳቤ መጻፋቸውን አብራርተዋል።

የፋይናንስ ድጋፍ እንዳለውና እና እንደሌለው ለማጣራት ለባንኮች ደብዳቤ መጻፋቸውን ተናግረዋል።ግብረአበሮችን ተከታትሎ የመያዝ ሥራ ለመስራትና ምርመራ አጠናቀው ለሚመለከተው ዓቃቢህግ ለመስጠት ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።በፍርድ ቤቱ በኩል ግብረአበር ለመያዝ ማለት ምን ለማለት እንደሆነ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል።

ከፍንዳታው በፊት ከአንዲት ሴት በአካል ማዋራቱን እና በወቅቱ ስልክ ተደውሎለት ሲያወራ እንደነበር ጠቁመው ይህን ተከትሎ ግብረአበር ካለ የመያዝ ሥራ እንደሚሰራ አብራርተዋል።ተጠርጣሪው በበኩሉ “የፈነዳው ቦንብ አውቄ አደለም ባጋጣሚ እንጂ ምንም አይነት ወንጀል እኔ አልሰራሁም በኔ የደረሰ ችግር የለም”ሲል ምላሽ ሰጥቷል።ከደቡብ ክልል ዳውሮ ዞን ለሥራ መምጣቱን ገልጾ፤ ጠያቂ ዘመድ እንደሌለው ወላጆቹን በሞት በማጣቱ ትንሽ ወንደሰሙን በሱ እርዳታ እንደሚያስተምር በመግለጽ ዋስትና እንዲፈቀድለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

መርማሪዎቹ በበኩላቸው በዕለቱ አንድ የጭስ ቦንብ ሳይሆን 3 የጭስ ቦንብ ነው የፈነዳው ያሉ ሲሆን፤ ተጠርጣሪው ከተመደበበት የሥራ ምድብ ውጪ በህዝብ መሀል ሆኖ ነበር ያሉ ብለዋል። ሲጀመር አስለቃሽ ጭስ ቦንብ ይዞ ህዝብ መሀል መቆም አይፈቀድም ይሁንና እንዲወጣ ታዞ ሳይወጣ ቀርቷል ኹከትና ብጥብጡም በዚህ መነሻ ነው የተነሳው ሲሉ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በዚህ መነሻ በመንግስትና በግል ድርጅቶች ላይ የደረሰው የንብረት ጉዳት ፍርድ ቤቱ እንዲረዳላቸውና ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀን እንዲፈቅድላቸው ጠይቀዋል።ጉዳዩን የተከታተለው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀሪ ምርመራ ማድረግ እንደማያስፈልግ በመግለጽ ለተጨማሪ ምርመራ 13 ቀናትን በመፍቀድ የምርመራ ውጤት ለመጠባበቅ ለግንቦት23 ቀን 2014 ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠጹን ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ ዘግባለች።

@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ መንግስት በህወሓት ጉዳይ የኡጋንዳን አምባሳደር ጠርቶ ማወያየቱን ገለጸ!

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ኡጋንዳ በህወሃት ላይ ያላትን አቋም ለማወቅ የኡጋንዳን አምባሳደር ጠርተው ማነጋገራቸውን ገልጸል፡፡ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በትናንትናው እለት ኡጋንዳ ለህወሓት ወታደራዊ ድጋፍ ለማድረግ እየተንቀሳቀሰች መሆኑን እና ይህን የኢትዮጵያ መንግስት እንዴት እያየው ነው በሚል ከህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ለተነሳላቸው ጥያቄ ነው፡፡

ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኡጋንዳ ካምፓላ ያሉት የኢትዮጵያ አምባሳደርም ይፋዊ መልእክት ለኡጋንዳ መንግስት ማቅረባቸውን እና ማብራሪያ መጠየቃቸውን ተናግረዋል፡፡በቅርቡ በኢትዮጵያ በተካሄደው የወታደራዊ ኦፊሰሮች ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ ከኡጋንዳ መከላከያ ሚኒስቴር ጋር መወያየቷን የገለጹት ሚኒስትሩ ጉዳዮ “በቀላሉ የሚያይ እና የሚተው አይደለም” ብለዋል፡፡

ጉዳዩ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዝርዝር መገምገሙን ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡
“እንዳንዴ የሚሉት ምንድነው፣ ይሄ በራሳቸው የሚኖሩና እና ራሳቸው የሚጠየቁበት ነው፤ እኛ ይሄን አንደግፍም ይላሉ፡፡”ነገር ግን የኢትዮጵያ መንግስት አንድ የኡጋንዳ ከፍተኛ ባለስልጣን በአንድ ሀገር ጉዳይ ላይ አቋም ከወሰደ፣ የመንግስት አቋም አድርገን ነው የምንወስደው ብለዋል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፡፡ሚኒስትሩ ኡጋንዳ ግልጽ አቋሟን እንድታሳውቀን እንፈልጋለን ብለዋል፡፡የኢትዮጵያ መንግስት ሱዳንንም ህወሓትን ትደግፋለች በሚል ከሷል፡፡

Via Alain
@YeneTube @FikerAssefa
የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክትል ዋና ጸሐፊ ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው!

የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክትል ዋና ጸሐፊ ኢሊዝ ብራንድስ ኬሪስ ኢትዮጵያን እና ደቡብ ሱዳንን ሊጎበኙ ነው፡፡

ምክትል ዋና ጸሐፊዋ ጉብኝታቸውን ዛሬ በደቡብ ሱዳን የጀምሩ ሲሆን ከቀጣዩ አርብ ግንቦት 12 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደርጋሉ ተብሏል፡፡

ኬሪስ በደቡብ ሱዳን ቆይታቸው ከአገሪቱ የፌደራል እና የየአካባቢው ባለስልጣናት፣ ከኅብረተሰብ ተወካዮች፣ ከሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና በአገሪቱ ከሚገኙ ዓለም ዐቀፍ እና ቀጣናዊ አጋር አካላት ጋር ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በተጨማሪም በጁባ እና ዬኢ ከተሞች የሚገኙ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ካምፕ እንደሚጎበኙ ተገልጿል፡፡

የደቡብ ሱዳን ቆይታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ በማቅናት የአፍሪካ ኅብረት፣ የአውሮፓ ኅብረት እና የተባበሩት መንግሥታት በትብብር የሚያከናውኑት የአፍሪካ ኅብረትን አሰራር ማሻሻያ ፕሮጀክት ይፋ በሚደረግበት መርኃ ግብር ላይ ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡

ይህ ትብብር የአፍሪካ ኅብረት በሰላም ዙሪያ የሚያከናውናቸውን ተግባራት ለመደገፍ እና አሰራሩም የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ደንብን የተከተለ እንዲሆን የሚያስችል መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ይፋ ያደረገው መረጃ ያመለክታል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
የፑሽኪን አደባባይ -ጎተራ ማሳለጫ የመንገድ ፕሮጀክት በግንቦት ወር መጨረሻ ላይ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ይሆናል ተባለ!

የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በስራ ተቋራጭ እያስገነባው የሚገኘው የፑሽኪን አደባባይ - ጎተራ ማሳለጫ የመንገድ ግንባታ ስራ በግንቦት ወር መጨረሻ ላይ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ያደርጋል፡፡

ከፑሽኪን አደባባይ እስከ ጎተራ ማሳለጫ ያለው ዋና መንገድ ግንባታ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ተደርጓል።

አሁን ላይ በተለምዶ ጎፋ ማዞሪያ ተብሎ በሚጠራው የቄራ አካባቢ ከቂርቆስ አቅጣጫ ወደ ጎፋና ላፍቶ የሚወስደው ተሻጋሪ ድልድይ የመጀመሪያ ደረጃ የአስፋልት ማንጠፍ ስራ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡

መንገዱን በግንቦት ወር መጨረሻ ላይ ሙሉ ለሙሉ አጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቋል።

@YeneTube @FikerAssefa
1ሺህ 22 ኢትዮጵያውያን ከሳኡዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ!

ዛሬ ግንቦት 10 ቀን 2014 ዓ.ም በሶስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳኡዲ አረቢያ የመመለስ ስራ በአጠቃላይ ቁጥራቸው 1ሺህ 22 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው መመለስ የተቻለ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 108 ሴቶች 9 ህጻናትና 905 ወንዶች መሆናቸው ታውቋል፡፡

ለተመላሽ ዜጎችም ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ወደ ተዘጋጀላቸው የማቆያ ማእከላት እንዲሄዱ ተደርጓል፡፡ እስካሁን ድርስ በተከናወነው ዜጎችን የመመለስ ስራ ቁጥራቸው ከ 24,660 በላይ ኢትዮጵያውያንን መመለስ መቻሉን ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

@YeneTube @FikerAssefa
ለቤትዎ ለቢሮዎ እንዲሁም ለድርጅትዎ ይተለያየ ውበት ያላቸውን የፍይበር ግላስ የአበባ መትከያ ከፈለጉ እኛ አለን የድርጅትዎን እርማም መትከያው ላይ እናትምሎታለን
👋👋እንዲሁም ይሄን አዋጭ ቢዝነስ
ለመጀመር ካሰቡ ሙሉ ስልጠና እንሰጣለን ይደውሉልን
https://tttttt.me/+xvCuMwxhK19kODg0
☝️☝️☝️Join our group
Phone number:0987414243
0913676664
ለመሆኑ ቅጥረኛ ወታደሮች በወር ምን ያህል ይከፈላቸዋል???
============
ከሰሞኑ በርከት ያሉ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በዩክሬይኑ ጦርነት ከሩሲያ ጎን ለመዋጋት ተሰልፈው ታይቷል። ወዶ መዝመት ከጥንት ጀምሮ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ የወጣቱን ልብ ያሸፈተው የርዕዮተ ዓለም ፍቅር አይደለም። አማላይ ክፍያው እንጂ። ለመሆኑ ቅጥረኛ ወታደሮች ምን ያህል ይከፈላቸዋል??? የሚሰጣቸው ስልጠና እና ዋነኛ ስራቸው ምንድነው? ይህን አጭር ቪዲዮ ይመልከቱ። ቻናሉን ሰብስክራይብ ያድርጉ!!!

https://youtu.be/Q0Uj40oaOho
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ የክልሉ ጸጥታ ኃይሎች በሰሜኑ ክፍል የሕወሃት ተላላኪ አካላትን እየተፋለሙ መሆኑን ዛሬ ለክልሉ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ተናግረዋል።

ይልቃል ክልሉን ለማዳከም የሚንቀሳቀሱ የውስጥ "ጠላቶች" እንዳሉ በጥናት ደርሰንበታል ብለዋል። "የሕወሃት ተላላኪ" ያሏቸውን አካላት ማንነት ግን ይልቃል አላብራሩም። መንግሥታቸው በሕግ ማስከበር እንቅስቃሴው እንደሚገፋበት የገለጹት ይልቃል፣ ጦር መሳሪያ ከመመዝገብ ውጭ ትጥቅ የማስፈታት እና የፋኖ አደረጃጀትን የመበተን ዓላማ እንደሌለው ገልጸዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
ሰኞ ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ በድንገት የተሰወሩት የቀድሞው የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አዛዥ ብ/ጀኔራል ተፈራ ማሞ እስካሁን የት እንደደረሱ የተገኘ መረጃ የለም።

ባለቤታቸው ዛሬ ለሪፖርተር በሰጡት ቃል፣ ብ/ጀኔራል ተፈራ ከቀድሞው የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ስትራቴጂ ጥናት ኢንስቲትዩት ሃላፊ ዮሃንስ ቧያሌው ጋር በአካል ለመገናኘት ከወጡ በኋላ እንዳልተመለሱ ተናግረዋል። ባለቤታቸው ጨምረውም፣ ብ/ጀኔራል ተፈራ አዲሶቹ የአማራ ክልል አመራሮች ብቃት የላቸውም በማለት በቅርቡ ለኢሳት እና ናሁ ቴሌቪዥኖች የሰጡት ቃለ ምልልስ በክልሉ አመራሮች ዘንድ እንዳልተወደደ ጠቁመዋል። ፌደራል ፖሊስ ስለ ግለሰቡ አድራሻ መረጃ እንደሌለው ገልጦ ሁኔታውን አጣራለሁ ብሏል።

[Reporter/Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
#update

ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ ባሕር ዳር እንደሚገኙ እንደተነገራቸው ባለቤታቸው ገለጹ!

ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ የደረሱበት ሳይታወቅ ከቆዩ ከሁለት ቀናት በኋላ ባሕር ዳር እንዳሉና ደህና መሆናቸውን የሚገልጽ መልዕክት እንደደረሳቸው ባለቤታቸው ለቢቢሲ ተናገሩ።ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ ሰኞ ግንቦት 08/2014 ዓ.ም. ከቤታቸው ረፋድ ላይ ከወጡ በኋላ የደረሱበት ሳይታወቅ እስከ ረቡዕ አመሻሽ ድረስ ቆይተዋል።

ባለቤታቸው ወ/ሮ መነን ኃይሌ ረቡዕ ምሽት ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት የጄነራል ተፈራ ጠበቃና የሚያውቋቸው ሰዎች ባለቤታቸው ባሕር ዳር ውስጥ በሚገኘው ዘጠነኛ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ እንዳሉ ገልጸዋል።

ወ/ሮ መነን ባለቤታቸው በላኩት መልዕክት ደህና መሆናቸውን እና አሁን ያሉበት ቦታ በመግለጽ ቤተሰባቸው እንዲረጋጋ መልዕክት ልከዋል ብለዋል።ቢቢሲ ይህንኑ በተመለከተ ከአማራ ክልል የፀጥታና ደኅንነት እንዲሁም ፖሊስ ማብራሪያ ለመጠየቅ ያደረገው ሙከራ አልተሳካም።

[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በነኮሎኔል ገመቹ አያና እስር ላይ ማብራሪያ እንዲሰጥ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጠ!

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር ኮሎኔል ገመቹ አያና እስር እና ሰብኣዊ መብት አያያዝ ሁኔታ ላይ የፌዴራል ወንጀል ምርመራ ቢሮ ኃላፊዎች ቀርበው ማብራሪያ እንዲሰጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት ከሌሎች በመዝገቡ ከተጠቀሱት ተከሳሾች ጋር በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነጻ ተብለው የነበሩት ኮሎኔል ገመቹ አያና ለአንድ ዓመት ያህል “በህገወጥ እስር” ላይ እንደነበሩ ጠበቆቻቸው ይገልጻሉ፡፡

ዛሬ በአዲስ አበባ ያስቻለው የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ተከሳሹ ኮሎኔሉ እና ከሳሽ አቃቤ ህግ በቀረቡበት ቀሪ ተከሳሾች እና የፌዴራል ወንጀል ምርመራ ቢሮ ኃላፊዎች እንዲቀርቡ በማለት መዝገቡን በይደር ይዟል፡፡

ሙሉ ዘገባው: https://p.dw.com/p/4BTgX?maca=amh-RED-Telegram-dwcom

@YeneTube @FikerAssefa
👉 ለጤናው ቅድሚያ እንሰጣለን


መሪጌታ ጥበቡ
የባህል ህክምና መስጫ ከአባቶቻችን
በተሰጠንና ባገኘነው ልምድና ጥበብ መሰረት የተለያዩ የጤና መፍትሔወችን እንሰጣለን።፦

የምንሰጣቸው አገልግሎቶችም

👉 የኪንታሮት መድኀኒት በሚቀባ ታማሚው
ወደቤቱ ወስዶ በመቀባት ሌላ ገላሳይነካ
ሳያቆስል ስራ ሳያስተጓጉል በሽታውን ለይቶ በማውጣት ሁለተኛ እንዳይተካ አድርጎ የፈውሳል።
👉 የእሪህ መድአኒት ወስዶ በመቀባት ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል
👉 ገብያ ለገረገረው ለገብያ
👉 ለመፍትሔ ስራይ
👉 ለአይነ ጥላ (ለገርጋሪ)
👉 ለስንፈተ ወሲቢ ለሚቸኩልበት
👉 የአስም (የሳይነስ)
👉 ለማይስማሙ (ለመስተፋቅር)
👉 ገንዘብ ለሚበተንበት
👉 ስራ አልሳካለት ላለ
👉 ለቡዳ
👉 ለሚጥል በሽታ
👉 ለማህጸን እንፌክሽን
👉 ህይወቱ ለሚመሰቃቀልበት
👉 ለአዕምሮ ጭንቀት
👉 ሌሊት ለሚሸና
👉 ለነገረ በትን
👉 ለሆድ ሀህመም
👉 ለስኳር መቀነሻ
👉 ለነርብ
👉 እራሱን ለሚያመው

እነዚህንና ሌሎች አገልግሎቶችን እንሰጣለን

መዳኒቱን ባሉበት ቦታ መላላክ ይቻላል

በሁሉም አገልግሎቶቻችን ውጤቱን እንዳዪ ክፍያ ይፈጽማሉ

አድራሻ
ባህርዳር ቀበሌ 11
ዲያስፖራ በኮብሉ

ለበለጠ መረጃ
☎️ 0917040506
📞 0912718883

ይደውሉ👍

መፍትሔ ሥራይ ወአይነ ጥላ ለጤናወ
መፍትሔ ከመሪጌታ ጥበቡ
የሚፈልጉትን ለማግኔት ይሄን ቻናል ይቀላቀሉ
🩺
https://tttttt.me/meritibe
https://tttttt.me/meritibe👇
👇
አስደሳች ዜና 12ኛ ክፍል ለጨረሳቹ እና በመማር ላይ ላላቹ!!!

ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።

እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!

በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል

የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy

አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102

ስልክ: 0960612222
0118345171

ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
ግንባታቸው የተጠናቀቁ 528 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለሰራዊት አባላት የማስተላለፍ መርሃግብር እየተካሄደ ነው!

ግንባታቸው የተጠናቀቁ 528 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ተመዝግበው ለቆጠቡ ለኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን አባላትና ለተቋሙ የሲቪል ሰራተኞች በእጣ የማስተላለፍ መርሃግብር እየተካሄደ ነው።

ዕጣው በግዳጅ ላይ ያሉ የሰራዊት አባላት፣ በክብር የተሰናበቱ የሰራዊት አባላትን ያካተተ ነው። ሴት የሰራዊት አባላትን በልዩ ሁኔታ ተጠቃሚ ያደረገ መሆኑም ተጠቁሟል።

በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተፕራይዝ እየተገነቡ ካሉት የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል በአዲስ አበባ በሰሚት ቁጥር ሁለት ግንባታቸው የተጠናቀቁ 528 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ተመዝግበው ለቆጠቡ የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን አባላትና የተቋሙ ቋሚ የሲቪል ሰራተኞች በእጣ የማስተላለፍ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው።

የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የክልል ከተሞች የመከላከያ ሰራዊት የጋራ መኖሪያ ቤቶችን እየገነባ ሲሆን በቅርቡም ግንባታቸው የተጠናቀቁ ቤቶችን ለሰራዊቱና ለቋሚ ሰራተኞች ያስተልፋል ተብሏል።

የተገነቡ ቤቶች በእጣ ለባለእድለኞች በሚተላለፍበት መርሃግብር ላይ የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስትር ዶክተር አብራሃም በላይን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕይዝ በኢትዮጵያ ካሉ ታላላቅ የግንባታ ኩባንያዎች አንዱ ሲሆን የኢንፎርሜሽን ደህንነት ዋና መስሪያ ቤት፣ የመከላከያ ዋና መስሪያ ቤት ህንጻን ጨምሮ በርካታ አገራዊ ፕሮጀክቶችን ገንብቷል።

Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa