Forwarded from YeneTube
አስደሳች ዜና 12ኛ ክፍል ለጨረሳቹ እና በመማር ላይ ላላቹ!!!
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
ከትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች ለተፈናቀሉ ተማሪዎች ዲግሪ እንደማይሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ!
ከትግራይ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ተፈናቅለው በአደራ በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተምረው ለተመረቁ ተማሪዎች፣ መደበኛ ዲግሪ ሚኒስቴሩ ለመስጠት እንደሚቸገር ተገለጸ፡፡ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በትምህርት ሚኒስቴር ዋስትና ገብተው የተመረቁ ከትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች የተፈናቀሉ ከ4,000 በላይ ተማሪዎች መደበኛ ዲግሪ ስለተከለከልን ሥራ ለመቀጠርና ለመወዳዳር አልቻልንም ሲሉ ለሪፖርተር ተደጋጋሚ ቅሬታዎችን ሲያሰሙ ቆይተዋል፡፡
የእነዚሁ የተማሪዎች ቅሬታ የቀረበላቸው ትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ (ፕሮፌሰር) እንደተናገሩት፣ ‹‹የተማሪዎቹ ሙሉ መረጃ ሳይገኝ መደበኛ ዲግሪ ለመስጠት እንቸገራለን፡፡ ጦርነቱ ሲቆምና ሰላምና መረጋጋት በሰሜን ኢትዮጵያ በአስተማማኝ ሁኔታ ሲሰፍን ከመጡባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርት ያቆሙበት መረጃ ተሟልቶ ሲቀርብ ዲግሪው ይሰጣቸዋል፡፡ እስከዚያው ግን በተሰጣቸው ውጤታቸውን በሚገልጽ ሰርተፊኬት ሥራ መፈለግ ይችላሉ፤›› ብለዋል፡፡
ሚኒስትሩ ይህን ቢሉም ከትግራይ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች በጦርነት ሳቢያ ተፈናቅለው ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ለመመረቅ የተገደዱ ተማሪዎች ግን፣ ትምህርት ሚኒስቴር በአንድ ሴሚስተር የውጤት መግለጫ ወረቀት (በግሬድ ሪፖርት) አሰናብቶናል ሲሉ ቅሬታ ያሰማሉ፡፡ ይህ ወረቀት ደግሞ በሥራ ዓለም ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቀጠር እንደማያስችላቸው በመጥቀስ፣ ትምህርት ሚኒስቴር ዘላቂ መፍትሔ እንዲፈልግላቸው እየጠየቁ ነው፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ግን አሁን ካደረኩት የተለየ አማራጭ የለኝም የሚል ምላሽ ነው የሰጠው፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ: http://bit.ly/36ZDgNi
@YeneTube @FikerAssefa
ከትግራይ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ተፈናቅለው በአደራ በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተምረው ለተመረቁ ተማሪዎች፣ መደበኛ ዲግሪ ሚኒስቴሩ ለመስጠት እንደሚቸገር ተገለጸ፡፡ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በትምህርት ሚኒስቴር ዋስትና ገብተው የተመረቁ ከትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች የተፈናቀሉ ከ4,000 በላይ ተማሪዎች መደበኛ ዲግሪ ስለተከለከልን ሥራ ለመቀጠርና ለመወዳዳር አልቻልንም ሲሉ ለሪፖርተር ተደጋጋሚ ቅሬታዎችን ሲያሰሙ ቆይተዋል፡፡
የእነዚሁ የተማሪዎች ቅሬታ የቀረበላቸው ትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ (ፕሮፌሰር) እንደተናገሩት፣ ‹‹የተማሪዎቹ ሙሉ መረጃ ሳይገኝ መደበኛ ዲግሪ ለመስጠት እንቸገራለን፡፡ ጦርነቱ ሲቆምና ሰላምና መረጋጋት በሰሜን ኢትዮጵያ በአስተማማኝ ሁኔታ ሲሰፍን ከመጡባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርት ያቆሙበት መረጃ ተሟልቶ ሲቀርብ ዲግሪው ይሰጣቸዋል፡፡ እስከዚያው ግን በተሰጣቸው ውጤታቸውን በሚገልጽ ሰርተፊኬት ሥራ መፈለግ ይችላሉ፤›› ብለዋል፡፡
ሚኒስትሩ ይህን ቢሉም ከትግራይ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች በጦርነት ሳቢያ ተፈናቅለው ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ለመመረቅ የተገደዱ ተማሪዎች ግን፣ ትምህርት ሚኒስቴር በአንድ ሴሚስተር የውጤት መግለጫ ወረቀት (በግሬድ ሪፖርት) አሰናብቶናል ሲሉ ቅሬታ ያሰማሉ፡፡ ይህ ወረቀት ደግሞ በሥራ ዓለም ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቀጠር እንደማያስችላቸው በመጥቀስ፣ ትምህርት ሚኒስቴር ዘላቂ መፍትሔ እንዲፈልግላቸው እየጠየቁ ነው፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ግን አሁን ካደረኩት የተለየ አማራጭ የለኝም የሚል ምላሽ ነው የሰጠው፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ: http://bit.ly/36ZDgNi
@YeneTube @FikerAssefa
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳሰቡ!
ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጩ አካላት ከድርጊታቸው መቆጠብ እንዳለባቸው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ አሳሰቡ።
1 ሺህ 443ኛውን የኢድ በአልና ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ፤ ያልተረጋገጠ ወሬ ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጭ ጉዳይ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
ከሰሞኑ በተከሰተው ግጭት አሳዛኝ ድርጊት መፈጸሙ የሚወገዝ እና የትኛውንም ሃይማኖት የማይወክል እንደሆነ ገልጸዋል።
ለህዝቡ ቅርብ የሆኑና ተሰሚነት ያላቸው አካላት ግጭት አባባሽ መልእክቶችን በማሰራጨት እልቂት እንዲፈጠር እየሠሩ እንደሚገኙ አመልክተው፤ ህዝቡ የተነገረው ሁሉ አምኖ መቀበል ብቻ ሳይሆን መርምሮ ማረጋገጥ እንዳለበት አስረድተዋል።
ግጭቱ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ያሉ የፀጥታ አካላት እና የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ሀላፊነታቸውን መወጣት ላይ ክፍተት እንዳሉባቸው ገልፀው፤ ችግሩ ከዚህ የከፋ ጉዳት ሳያስከትል በቁርጠኝነት እንዲሰሩ አፅንኦት ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ኮሚቴ በማቋቋም እና ቦታው ድረስ በማቅናት ችግሩን ለመፍታት ጥረት ይደረጋል ማለታቸዉን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጩ አካላት ከድርጊታቸው መቆጠብ እንዳለባቸው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ አሳሰቡ።
1 ሺህ 443ኛውን የኢድ በአልና ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ፤ ያልተረጋገጠ ወሬ ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጭ ጉዳይ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
ከሰሞኑ በተከሰተው ግጭት አሳዛኝ ድርጊት መፈጸሙ የሚወገዝ እና የትኛውንም ሃይማኖት የማይወክል እንደሆነ ገልጸዋል።
ለህዝቡ ቅርብ የሆኑና ተሰሚነት ያላቸው አካላት ግጭት አባባሽ መልእክቶችን በማሰራጨት እልቂት እንዲፈጠር እየሠሩ እንደሚገኙ አመልክተው፤ ህዝቡ የተነገረው ሁሉ አምኖ መቀበል ብቻ ሳይሆን መርምሮ ማረጋገጥ እንዳለበት አስረድተዋል።
ግጭቱ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ያሉ የፀጥታ አካላት እና የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ሀላፊነታቸውን መወጣት ላይ ክፍተት እንዳሉባቸው ገልፀው፤ ችግሩ ከዚህ የከፋ ጉዳት ሳያስከትል በቁርጠኝነት እንዲሰሩ አፅንኦት ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ኮሚቴ በማቋቋም እና ቦታው ድረስ በማቅናት ችግሩን ለመፍታት ጥረት ይደረጋል ማለታቸዉን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ በኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ የተነሳ በአራት ክፍለ ከተሞች የውሃ አቅርቦት ተቋርጧል!
በአዲስ አበባ ከተማ በኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ የተነሳ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ 12 ወረዳዎች ፣በቂርቆስ ክፍለ ከተማ 10 ወረዳዎች ፣በቦሌ ክፍለ ከተማ 3 ወረዳዎች እና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 5 ወረዳዎች የሚገኙ ደንበኞች ከእሁድ እለት ጀምሮ ውሃ በበቂ ሁኔታ እያገኙ አለመሆኑን የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታቸው በተለይ ለብስራ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
በኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ የተነሳ ከዚህ ቀደም ውሃ በፈረቃ ያገኙ ለነበሩ አካባቢዎች አገልግሎቱን መስጠት መቸገራቸውን ያነሱት ዳይሬክተሯ በተለይ ውሃ በሳምንት አንዴ ያገኙ የነበሩ አካባቢዎች ላይ ችግሩ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ገልፀዋል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ችግሩን ለመፍታት ከአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመናበብ በመስራት ላይ መሆናቸውን የሚናገሩት ዳይሬክተሯ በተለይ ከእሁድ ጀምሮ እስከ ድርብ ድረስ ባሉት ቀናት በርካታ ምሶሶዎች መውደቃቸውን ተከትሎ እና መሬት ውስጥ የነበረ ኬብል በመፈንዳቱ ዳግም የመጠገን ስራዎች ላይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
አሁን ላይ የፈረቃ ሂደቱ በመዛባቱ ባለስልጣኑ ባሉት ቦቲ ተሸከርካሪዎች ውሃ ለማዳረስ እየሰራ ሲሆን ችግሩን በአፋጣኝ ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል። የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ የተፈጠረው በቴክኒክ ችግር ምክንያት መሆኑን ለብስራት ሬዲዮ ያስረዱት በአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ በቀለ ክፍሌ ሲሆኑ ችግሩን ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
[ዳጉ ጆርናል]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ በኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ የተነሳ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ 12 ወረዳዎች ፣በቂርቆስ ክፍለ ከተማ 10 ወረዳዎች ፣በቦሌ ክፍለ ከተማ 3 ወረዳዎች እና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 5 ወረዳዎች የሚገኙ ደንበኞች ከእሁድ እለት ጀምሮ ውሃ በበቂ ሁኔታ እያገኙ አለመሆኑን የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርካለም ጌታቸው በተለይ ለብስራ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
በኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ የተነሳ ከዚህ ቀደም ውሃ በፈረቃ ያገኙ ለነበሩ አካባቢዎች አገልግሎቱን መስጠት መቸገራቸውን ያነሱት ዳይሬክተሯ በተለይ ውሃ በሳምንት አንዴ ያገኙ የነበሩ አካባቢዎች ላይ ችግሩ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ገልፀዋል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ችግሩን ለመፍታት ከአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመናበብ በመስራት ላይ መሆናቸውን የሚናገሩት ዳይሬክተሯ በተለይ ከእሁድ ጀምሮ እስከ ድርብ ድረስ ባሉት ቀናት በርካታ ምሶሶዎች መውደቃቸውን ተከትሎ እና መሬት ውስጥ የነበረ ኬብል በመፈንዳቱ ዳግም የመጠገን ስራዎች ላይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
አሁን ላይ የፈረቃ ሂደቱ በመዛባቱ ባለስልጣኑ ባሉት ቦቲ ተሸከርካሪዎች ውሃ ለማዳረስ እየሰራ ሲሆን ችግሩን በአፋጣኝ ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል። የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ የተፈጠረው በቴክኒክ ችግር ምክንያት መሆኑን ለብስራት ሬዲዮ ያስረዱት በአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ በቀለ ክፍሌ ሲሆኑ ችግሩን ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
[ዳጉ ጆርናል]
@YeneTube @FikerAssefa
የወልዲያ ከተማ አስተዳዳር ‹‹ሰርጎ ገቦች››ን ለመለየት የነዋሪዎችን መታወቂያ ሊቀይር ነው!
የወልዲያ ከተማ አስተዳደር በከተማው ውስጥ የሚገኙ ‹‹ሰርጎ ገቦችን›› ለመለየት እንዲቻል፣ የከተማዋ ነዋሪዎችን በሙሉ መታወቂያ ሊቀር እንደሆነ አስታወቀ፡፡በከተማው ውስጥ ካለው ሁኔታ አንፃር እየተለዩ የሚታሰሩ ግለሰቦች እንዳሉ የገለጸው የከተማ አስተዳደሩ፣ አዲስ መታወቂያ የሚወስዱ ሰዎች ያላቸውን መታወቂያ ከከተማዋ ወሳኝ ኩነት መረጃ ጋር እንደሚያመሳክር ገልጿል፡፡
ለወራት በሕወሓት ቁጥጥር ሥር ከቆየች በኋላ በታኅሳስ ወር ላይ በመንግሥት ቁጥጥር ሥር በሆነችው ወልዲያ፣ ‹‹ሰርጎ ገቦች›› የቀድሞውን መታወቂያ መያዛቸውን ለሪፖርተር የተናገሩት የወልድያ ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ ዳዊት መሰለ (ዶ/ር)፣ በዚህም ምክንያት የከተማው አስተደዳር የከተማዋን ነዋሪዎች መታወቂያ ለመቀየር ውሳኔ ማስተላለፉን ገልጸዋል፡፡
እንደ ዳዊት (ዶ/ር) ገለጻ፣ ከዚህ ቀደም መታወቂያ ሲሰጥ የነበረው መረጃዎችን በመዝገብ ላይ በመጻፍ ብቻ የነበረ ሲሆን፣ ይህም በቀበሌዎች መካከል የሚጣራበት ሁኔታ እንዳይኖር በማድረጉ የተለያዩ ቀበሌዎች ላይ ከአንድ በላይ መታወቂያ ያላቸው ሰዎች አሉ፡፡
‹‹ሰርጎ ገብ›› የተባሉትን ሰዎች ማንነት አብራርተው ባይገልጹም፣ የከተማዋ ነዋሪዎች መታወቂያ እንዲይዙ የሚያደርጉ የቀበሌ አመራሮች አሉ የሚል ጥርጣሬ እንዳለ አስረድተዋል፡፡ አሁን መታወቂያ የማደስ አገልግሎት እንዲቆም መደረጉን አክለዋል፡፡
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
የወልዲያ ከተማ አስተዳደር በከተማው ውስጥ የሚገኙ ‹‹ሰርጎ ገቦችን›› ለመለየት እንዲቻል፣ የከተማዋ ነዋሪዎችን በሙሉ መታወቂያ ሊቀር እንደሆነ አስታወቀ፡፡በከተማው ውስጥ ካለው ሁኔታ አንፃር እየተለዩ የሚታሰሩ ግለሰቦች እንዳሉ የገለጸው የከተማ አስተዳደሩ፣ አዲስ መታወቂያ የሚወስዱ ሰዎች ያላቸውን መታወቂያ ከከተማዋ ወሳኝ ኩነት መረጃ ጋር እንደሚያመሳክር ገልጿል፡፡
ለወራት በሕወሓት ቁጥጥር ሥር ከቆየች በኋላ በታኅሳስ ወር ላይ በመንግሥት ቁጥጥር ሥር በሆነችው ወልዲያ፣ ‹‹ሰርጎ ገቦች›› የቀድሞውን መታወቂያ መያዛቸውን ለሪፖርተር የተናገሩት የወልድያ ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ ዳዊት መሰለ (ዶ/ር)፣ በዚህም ምክንያት የከተማው አስተደዳር የከተማዋን ነዋሪዎች መታወቂያ ለመቀየር ውሳኔ ማስተላለፉን ገልጸዋል፡፡
እንደ ዳዊት (ዶ/ር) ገለጻ፣ ከዚህ ቀደም መታወቂያ ሲሰጥ የነበረው መረጃዎችን በመዝገብ ላይ በመጻፍ ብቻ የነበረ ሲሆን፣ ይህም በቀበሌዎች መካከል የሚጣራበት ሁኔታ እንዳይኖር በማድረጉ የተለያዩ ቀበሌዎች ላይ ከአንድ በላይ መታወቂያ ያላቸው ሰዎች አሉ፡፡
‹‹ሰርጎ ገብ›› የተባሉትን ሰዎች ማንነት አብራርተው ባይገልጹም፣ የከተማዋ ነዋሪዎች መታወቂያ እንዲይዙ የሚያደርጉ የቀበሌ አመራሮች አሉ የሚል ጥርጣሬ እንዳለ አስረድተዋል፡፡ አሁን መታወቂያ የማደስ አገልግሎት እንዲቆም መደረጉን አክለዋል፡፡
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
የኩፍኝ፣ ፖሊዮና ቢጫ ወባ ወረርሽኝን ለመከላከል ያለመ የክትባት ሣምንት ሊካሄድ ነው!
የኩፍኝ፣ ፖሊዮና ቢጫ ወባ ወረርሽኝን ለመከላከል ያለመ የክትባት ሣምንት ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ሊካሄድ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ በሰጡት መግለጫ ÷ የአፍሪካ የክትባት ሣምንትን ምክንያት በማድረግ የሚከናወነው የክትባት ዘመቻው በተለይም በጸጥታ ችግር ምክንያት ክትባት ባልተሰጠባቸው ቦታዎች ይሰጣል ብለዋል፡፡
የክትባት ሣምንቱ ማህበረሰቡ በክትባት ጠቀሜታ ላይ ትክክለኛውን ግንዛቤ እንዲጨብጥ ለማድረግና የክትባት ተደራሽነትን ለማስፋት መሆኑንም አመላክተዋል፡፡
የክትባት ዘመቻው ዓላማ በወረርሽኝ ደረጃ ሊነሱ ይችላሉ ተብሎ የተሰጉትን ኩፍኝ፣ ፖሊዮ እና ቢጫ ወባን ለመከላከል መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ደረጄ፤ ይህም ተፈናቃይ ዜጎች ባሉባቸው አካባቢዎች በስፋት የሚሰጥ ይሆናል ብለዋል፡፡
ከወረርሽኝ መከላከል ባለፈ ለሕጻናት የአንጀት ተወሃሲያን መከላከያ፣ ቫይታሚን ኤ እና በምግብ እጥረት የተጎዱ ሕጻናትን በመለየት ሕክምና እንደሚሰጥ መናገራቸዉን የኢዜአ ዘገባ ያስረዳል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኩፍኝ፣ ፖሊዮና ቢጫ ወባ ወረርሽኝን ለመከላከል ያለመ የክትባት ሣምንት ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ሊካሄድ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ በሰጡት መግለጫ ÷ የአፍሪካ የክትባት ሣምንትን ምክንያት በማድረግ የሚከናወነው የክትባት ዘመቻው በተለይም በጸጥታ ችግር ምክንያት ክትባት ባልተሰጠባቸው ቦታዎች ይሰጣል ብለዋል፡፡
የክትባት ሣምንቱ ማህበረሰቡ በክትባት ጠቀሜታ ላይ ትክክለኛውን ግንዛቤ እንዲጨብጥ ለማድረግና የክትባት ተደራሽነትን ለማስፋት መሆኑንም አመላክተዋል፡፡
የክትባት ዘመቻው ዓላማ በወረርሽኝ ደረጃ ሊነሱ ይችላሉ ተብሎ የተሰጉትን ኩፍኝ፣ ፖሊዮ እና ቢጫ ወባን ለመከላከል መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ደረጄ፤ ይህም ተፈናቃይ ዜጎች ባሉባቸው አካባቢዎች በስፋት የሚሰጥ ይሆናል ብለዋል፡፡
ከወረርሽኝ መከላከል ባለፈ ለሕጻናት የአንጀት ተወሃሲያን መከላከያ፣ ቫይታሚን ኤ እና በምግብ እጥረት የተጎዱ ሕጻናትን በመለየት ሕክምና እንደሚሰጥ መናገራቸዉን የኢዜአ ዘገባ ያስረዳል።
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ክልል መንግሥት ሽብር በሚፈጠሩ አካላት የማያዳግም እርምጃ እወስዳለው አለ!
የአማራ ክልል መንግሥት በጎንደር ከተማ በተፈጠረው ግጭት ተገቢውን ክትትል አድርጎ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ።የአማራ ክልል ርዕሠ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ፤ እንደ ሀገር ከገጠሙን ችግሮች ሙሉ በሙሉ ሳንላቀቅ ሃይማኖትን ምክንያት በማድረግ የእርስ በርስ ግጭት ለመፍጠር የሚታትሩ እኩይ አካላትን እንደማይታገሱ ተናግረዋል።
ርዕሠ መሥተዳድሩ "ክልሉን የትርምስ ቀጣና ለማድረግ የሽብር ድርጊት በሚፈጠሩ አካላት ላይ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን" ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡ይህ ሙከራ ኢትዮጵያን ካለችበት ነባራዊ ሁኔታ ለባሰ ቀውስ የሚዳርግ በመሆኑ ድርጊቱ ሊወገዝ ይገባዋል ያሉት ርዕሠ መሥተዳድሩ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ለሰላም ዘብ እንዲቆሙም አሳስበዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ክልል መንግሥት በጎንደር ከተማ በተፈጠረው ግጭት ተገቢውን ክትትል አድርጎ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ።የአማራ ክልል ርዕሠ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ፤ እንደ ሀገር ከገጠሙን ችግሮች ሙሉ በሙሉ ሳንላቀቅ ሃይማኖትን ምክንያት በማድረግ የእርስ በርስ ግጭት ለመፍጠር የሚታትሩ እኩይ አካላትን እንደማይታገሱ ተናግረዋል።
ርዕሠ መሥተዳድሩ "ክልሉን የትርምስ ቀጣና ለማድረግ የሽብር ድርጊት በሚፈጠሩ አካላት ላይ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን" ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡ይህ ሙከራ ኢትዮጵያን ካለችበት ነባራዊ ሁኔታ ለባሰ ቀውስ የሚዳርግ በመሆኑ ድርጊቱ ሊወገዝ ይገባዋል ያሉት ርዕሠ መሥተዳድሩ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ለሰላም ዘብ እንዲቆሙም አሳስበዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
**ጤና ይስጥልን የተወደዳችሁ ቤተሰቦች
መሪጌታ ጥበቡ የባህል ህክምና መስጫ ከአባቶቻችን በተሰጠንና ባገኘነው ጥበብ መሰረት የተለያዩ የጤና መፍትሄወችን እንሰጣለን።**
የምንሰጣቸው አገልግሎቶችም:-
- የኪንታሮት መድሀኒት በሚቀባ ታማሚው ወደቤቱ ወስዶ ሌላ ገላ ሳይነካ በመቀባት ሳያቆስል ስራወትን ሳያስተጓጉል በሽታውን ለይቶ በማውጣት ሁለተኛም እንዳይተካ አድርጎ ይፈውሳል።
-የሪህ መድሀኒት ወስዶ በመቀባት ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል።
- የአስም
_ የስንፈተ ወሲብ
_የአይነጥላ
_የገርጋሪ
_ለመፍትሄ ስራይ
እነዚህንና ሌሎችን አገልግሎቶችን እንሰጣለን
በሁሉም አገልግሎቶቻችን ውጤቱን እንዳዩ ክፍያ ይፈፅማሉ።
የሚፈልጉትን መድሀኒት ያሉበት ቦታ መላላክ ይቻላል።
አድርሻ:-
ባህር ዳር:- ቀበሌ 11
ለበለጠ መረጃ:-በ0917040506
0912718883
ይደውሉ።
መሪጌታ ጥበቡ ባህላዊ መድሀኒት መስጫ
ለጤናወ መፍትሄ👇
https://tttttt.me/meritibe
መሪጌታ ጥበቡ የባህል ህክምና መስጫ ከአባቶቻችን በተሰጠንና ባገኘነው ጥበብ መሰረት የተለያዩ የጤና መፍትሄወችን እንሰጣለን።**
የምንሰጣቸው አገልግሎቶችም:-
- የኪንታሮት መድሀኒት በሚቀባ ታማሚው ወደቤቱ ወስዶ ሌላ ገላ ሳይነካ በመቀባት ሳያቆስል ስራወትን ሳያስተጓጉል በሽታውን ለይቶ በማውጣት ሁለተኛም እንዳይተካ አድርጎ ይፈውሳል።
-የሪህ መድሀኒት ወስዶ በመቀባት ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል።
- የአስም
_ የስንፈተ ወሲብ
_የአይነጥላ
_የገርጋሪ
_ለመፍትሄ ስራይ
እነዚህንና ሌሎችን አገልግሎቶችን እንሰጣለን
በሁሉም አገልግሎቶቻችን ውጤቱን እንዳዩ ክፍያ ይፈፅማሉ።
የሚፈልጉትን መድሀኒት ያሉበት ቦታ መላላክ ይቻላል።
አድርሻ:-
ባህር ዳር:- ቀበሌ 11
ለበለጠ መረጃ:-በ0917040506
0912718883
ይደውሉ።
መሪጌታ ጥበቡ ባህላዊ መድሀኒት መስጫ
ለጤናወ መፍትሄ👇
https://tttttt.me/meritibe
ሀይማኖትን ሽፋን አድርገው የሚነሱ ግጭቶች በቂ ትኩረት ይሻሉ ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ አሰሰበ።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ከሰሞኑ ጎንደር ላይ የተፈጠረውን ያወገዘ ሲሆን በዚው ዙሪያ መግለጫ አውጥቷል:: ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ከሰሞኑ ጎንደር ላይ የተፈጠረውን ያወገዘ ሲሆን በዚው ዙሪያ መግለጫ አውጥቷል:: ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማኅበር መንግሥት የሸቀጥ አቅርቦት እና ዋጋ ንርትን የሚያረጋጋ ጊዜያዊ ቦርድ እንዲያቋቁም ጠይቋል።
ማኅበሩን ጥያቄውን ያቀረበው፣ በዋጋ ግሽበት መዋቅራዊ ተግዳሮቶች እና የፖሊሲ አማራጮች ላይ ለ6 ወራት ያስጠናውን ጥናት ይፋ ባደረገበት ወቅት ነው። ቦርዱ ቢቋቋም፣ የአገራዊ ምርትና የገቢ ንግድ አቅርቦት ሚዛንን ማስጠበቅ፣ የዋጋ ግሽበትን የሚቀንስ ግብ ማስቀመጥ፣ በግሽበቱ የሚጎዱ የኅብረተሰብ ክፍሎችን መለየት እና በተለያዩ ኢኮኖሚ ዘርፎች መካከል ቅንጅት ለመፍጠር ይችላል ተብሏል።
Via Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
ማኅበሩን ጥያቄውን ያቀረበው፣ በዋጋ ግሽበት መዋቅራዊ ተግዳሮቶች እና የፖሊሲ አማራጮች ላይ ለ6 ወራት ያስጠናውን ጥናት ይፋ ባደረገበት ወቅት ነው። ቦርዱ ቢቋቋም፣ የአገራዊ ምርትና የገቢ ንግድ አቅርቦት ሚዛንን ማስጠበቅ፣ የዋጋ ግሽበትን የሚቀንስ ግብ ማስቀመጥ፣ በግሽበቱ የሚጎዱ የኅብረተሰብ ክፍሎችን መለየት እና በተለያዩ ኢኮኖሚ ዘርፎች መካከል ቅንጅት ለመፍጠር ይችላል ተብሏል።
Via Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ስድስት ቅርንጫፎች ሠራተኞች በወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ!
በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ስድስት የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ቅርንጫፍ ሠራተኞች በወንጀል ተጠርጥረው በክልሉ የጸጥታ ኃይሎች ዛሬ ሚያዚያ 20 ቀን 2014 ዓም በቁጥጥር ስር ውለው መታሰራቸው ታወቀ።
ቅርንጫፍ መስሪያቤቶቹ በአዳማ፣ነቀምት፣ ጅማ፣ጊምቢ፣በደሌ፣መቱ ሲሆኑ ሁሉም መታሸጋቸው ታውቋል።የቅርንጫፍ ሠራተኞቹ በቁጥጥር ስር መዋላቸውንና መታሰራቸውን የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ለሪፖርተር ያረጋገጠ ቢሆንም የታሰሩትን ሠራተኞች ብዛትና የታሰሩበትን ቦታ ከመግለጽ ተቆጥቧል።
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ስድስት የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ቅርንጫፍ ሠራተኞች በወንጀል ተጠርጥረው በክልሉ የጸጥታ ኃይሎች ዛሬ ሚያዚያ 20 ቀን 2014 ዓም በቁጥጥር ስር ውለው መታሰራቸው ታወቀ።
ቅርንጫፍ መስሪያቤቶቹ በአዳማ፣ነቀምት፣ ጅማ፣ጊምቢ፣በደሌ፣መቱ ሲሆኑ ሁሉም መታሸጋቸው ታውቋል።የቅርንጫፍ ሠራተኞቹ በቁጥጥር ስር መዋላቸውንና መታሰራቸውን የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ለሪፖርተር ያረጋገጠ ቢሆንም የታሰሩትን ሠራተኞች ብዛትና የታሰሩበትን ቦታ ከመግለጽ ተቆጥቧል።
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
በሃይማኖት ሽፋን ግጭት በመቀስቀስ ጸረ-ኢትዮጵያ የሆኑ ሃይሎችን ፍላጎት ለማሳካት በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን የፌደራል የደህንነትና የጸጥታ የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ!
ሚያዝያ 18 ቀን 2014 ዓ.ም በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጎንደር ከተማ ከቀብር ስፍራ ጋር በተያያዘ በክርስትናና በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የተቀሰቀሰውን ግጭት መነሻ በማድረግ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎችም በሃይማኖት ሽፋን ሁከትና ብጥብጥ በመፍጠር ጸረ-ኢትዮጵያ የሆኑ ሃይሎችን ፍላጎት ለማሳካት በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን የፌደራል የደህንነትና የጸጥታ የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቋል፡፡
የጋራ ግብረ ኃይሉ ዛሬ ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ ጸረ ኢትዮጵያ አቋም የሚያራምዱ የተለያዩ የውስጥና የውጭ ኃይሎች ብሔርን መሰረት ያደረገ የጥላቻ አጀንዳ በማሰራጨት ሃገሪቱን ወደ ቀውስ ለማስገባት ጥረት ሲያደርጉ ነበር፡፡
ህብረተሰቡ ለአመታት በገነባው ጠንካራ የሆነ የጋራ እሴት ይህ ሙከራ የከሸፈባቸው ኃይሎች፣ቀሪውን የሃይማኖት ካርድ በመምዘዝ በተለያዩ እምነት ተከታዮች ዘንድ መጠራጠርና ጥላቻ እንዲፈጠር ብሎም ወደ ግጭት እንዲያመራ በተለያዩ መንገዶች ሲቀሰቅሱ ቆይተዋል፡፡
በጎንደር የተከሰተው ግጭት በተለያዩ ዕምነቶች መካከል ግጭት በመቀስቀስ ወደ ሃገራዊ ቀውስ እንዲያመራ የሚደረገው ሴራ አካል መሆኑን ያመለከተው መግለጫው፤ በዚህ ድርጊት በተሳተፉ አካላት ላይ ተገቢ እርምጃ መወሰደ መጀመሩን ጠቁሟል፡፡
በዚህ መሰረት በጎንደር በተከሰተው ግጭት የተሳተፉና ሁከቱን ለማባባስ የተንቀሳቀሱ 280 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን አመልክቷል፡፡
እንደ መግለጫው፤ በጎንደር የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ በሌሎች አካባቢዎችም በተለያዩ እምነት ተከታዮች መካከል ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር የሚጋብዙ ቅስቀሳዎች እንዲሁም ሃሰተኛ መረጃዎችም በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በስፋት እየተሰራጩ ይገኛሉ፡፡
በአንዳንድ አካባቢዎችም የእምነት ተቋማትና ግለሰቦች ላይ ጥቃት በመፈጸም ግጭቱ ሃገራዊ ቅርጽ እንዲኖረው ሙከራ እየተደረገ ነው፡፡
የፌደራል የደህንትና የጸጥታ መዋቅር በድርጊቱ በሚሳተፉት ላይ ብቻ ሳይሆን ከኋላ በመሆን በሚዘውሩት ላይ በቂ መረጃና ማስረጃ ያለው በመሆኑ ተከታታይ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቀው መግለጫው፤ ችግሩ ወደ ሌሎች አካባቢዎችም እንዲስፋፋ በየትኛውም የመገናኛ ዘዴ የሚቀሰቅሱ፤ በተለይም ደግሞ የማህበራዊ ትስስር ገፆችን በመጠቀም ሃሰተኛና የጥላቻ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት በህግ የሚጠየቁበት አግባብ መኖሩን የጠቆመው መግለጫው፤ በዚህ ህግወጥ ድርጊት የሚሳተፉ ባስቸኳይ ከድርጊታቸው እንዲታቀቡም በጥብቅ አሳስቧል፡፡
ኢትዮጵያውያን ለዓመታት የገነቡት በአብሮነትና በመከባበር ላይ የተመሰረተ ግንኙነት እኩይ ዓላማ ባነገቡ የውስጥና የውጭ ፀረ ሰላም ሃይሎች እኩይ ሴራ ለማስፈጸም የሚንቀሳቀሱ አካላት በሚፈጥሩት የግጭት አጀንዳ አይሸረሸርም ያለው መግለጫው፤ ህብረተሰቡ ለዘመናት ባዳበራቸው መልካም እሴቶች እንደዚህ አይነት የፈተና ወቅቶችን በውይይትና በሰከነ መንፈስ በመፍታት እንደሚያስመሰክር የጋራ ግብረ ኃይሉ እምነት መሆኑንም ጠቁሟል፡፡
ዛሬም ኢትዮጵያን ሌላ የግጭት አጀንዳ በመስጠት ለማተራመስ ሙከራ ቢደረግም በደኀንነትና በጸጥታ መዋቅሩ ከፍተኛ ጥረት በቁጥጥር ስር ውሏል ያለው የፌደራል የደህንነትና የጸጥታ የጋራ ግብረ ኃይል፤ ህብረተሰቡ ከመንግስት ጎን በመሆን ችግሩ እንዳይስፋፋ ያደረገው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመልክቷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ሚያዝያ 18 ቀን 2014 ዓ.ም በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጎንደር ከተማ ከቀብር ስፍራ ጋር በተያያዘ በክርስትናና በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የተቀሰቀሰውን ግጭት መነሻ በማድረግ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎችም በሃይማኖት ሽፋን ሁከትና ብጥብጥ በመፍጠር ጸረ-ኢትዮጵያ የሆኑ ሃይሎችን ፍላጎት ለማሳካት በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን የፌደራል የደህንነትና የጸጥታ የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቋል፡፡
የጋራ ግብረ ኃይሉ ዛሬ ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ ጸረ ኢትዮጵያ አቋም የሚያራምዱ የተለያዩ የውስጥና የውጭ ኃይሎች ብሔርን መሰረት ያደረገ የጥላቻ አጀንዳ በማሰራጨት ሃገሪቱን ወደ ቀውስ ለማስገባት ጥረት ሲያደርጉ ነበር፡፡
ህብረተሰቡ ለአመታት በገነባው ጠንካራ የሆነ የጋራ እሴት ይህ ሙከራ የከሸፈባቸው ኃይሎች፣ቀሪውን የሃይማኖት ካርድ በመምዘዝ በተለያዩ እምነት ተከታዮች ዘንድ መጠራጠርና ጥላቻ እንዲፈጠር ብሎም ወደ ግጭት እንዲያመራ በተለያዩ መንገዶች ሲቀሰቅሱ ቆይተዋል፡፡
በጎንደር የተከሰተው ግጭት በተለያዩ ዕምነቶች መካከል ግጭት በመቀስቀስ ወደ ሃገራዊ ቀውስ እንዲያመራ የሚደረገው ሴራ አካል መሆኑን ያመለከተው መግለጫው፤ በዚህ ድርጊት በተሳተፉ አካላት ላይ ተገቢ እርምጃ መወሰደ መጀመሩን ጠቁሟል፡፡
በዚህ መሰረት በጎንደር በተከሰተው ግጭት የተሳተፉና ሁከቱን ለማባባስ የተንቀሳቀሱ 280 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን አመልክቷል፡፡
እንደ መግለጫው፤ በጎንደር የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ በሌሎች አካባቢዎችም በተለያዩ እምነት ተከታዮች መካከል ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር የሚጋብዙ ቅስቀሳዎች እንዲሁም ሃሰተኛ መረጃዎችም በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በስፋት እየተሰራጩ ይገኛሉ፡፡
በአንዳንድ አካባቢዎችም የእምነት ተቋማትና ግለሰቦች ላይ ጥቃት በመፈጸም ግጭቱ ሃገራዊ ቅርጽ እንዲኖረው ሙከራ እየተደረገ ነው፡፡
የፌደራል የደህንትና የጸጥታ መዋቅር በድርጊቱ በሚሳተፉት ላይ ብቻ ሳይሆን ከኋላ በመሆን በሚዘውሩት ላይ በቂ መረጃና ማስረጃ ያለው በመሆኑ ተከታታይ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቀው መግለጫው፤ ችግሩ ወደ ሌሎች አካባቢዎችም እንዲስፋፋ በየትኛውም የመገናኛ ዘዴ የሚቀሰቅሱ፤ በተለይም ደግሞ የማህበራዊ ትስስር ገፆችን በመጠቀም ሃሰተኛና የጥላቻ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት በህግ የሚጠየቁበት አግባብ መኖሩን የጠቆመው መግለጫው፤ በዚህ ህግወጥ ድርጊት የሚሳተፉ ባስቸኳይ ከድርጊታቸው እንዲታቀቡም በጥብቅ አሳስቧል፡፡
ኢትዮጵያውያን ለዓመታት የገነቡት በአብሮነትና በመከባበር ላይ የተመሰረተ ግንኙነት እኩይ ዓላማ ባነገቡ የውስጥና የውጭ ፀረ ሰላም ሃይሎች እኩይ ሴራ ለማስፈጸም የሚንቀሳቀሱ አካላት በሚፈጥሩት የግጭት አጀንዳ አይሸረሸርም ያለው መግለጫው፤ ህብረተሰቡ ለዘመናት ባዳበራቸው መልካም እሴቶች እንደዚህ አይነት የፈተና ወቅቶችን በውይይትና በሰከነ መንፈስ በመፍታት እንደሚያስመሰክር የጋራ ግብረ ኃይሉ እምነት መሆኑንም ጠቁሟል፡፡
ዛሬም ኢትዮጵያን ሌላ የግጭት አጀንዳ በመስጠት ለማተራመስ ሙከራ ቢደረግም በደኀንነትና በጸጥታ መዋቅሩ ከፍተኛ ጥረት በቁጥጥር ስር ውሏል ያለው የፌደራል የደህንነትና የጸጥታ የጋራ ግብረ ኃይል፤ ህብረተሰቡ ከመንግስት ጎን በመሆን ችግሩ እንዳይስፋፋ ያደረገው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመልክቷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የጎንደሩን ግድያ የፈፀመዉ ማን እንደሆነ እየተጣራ ነዉ!
የአማራ ክልል መንግስት የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ዛሬ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት የፀጥታ ኃይሉ አጥፊ ግለሰቦችንና ቡድኖችን እያደነ እንደሆነም ኃላፊ አመልክተዋል፡፡
ማክሰኞ ዕለት በጎንደር ከተማ በአንድ ታዋቂ አባት መቃብር ላይ የተፈጠረውን የህይወት ማጥፋት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት መውደምን ተከትሎ የነበረው አለመረጋጋት እየተሻሻለ መምጣቱን የአማራ ክልል መንግስት አስታውቋል።
በጥቃቱ ህይወታቸው ያለፉ ወገኖች የቀብር ሥነ-ስርዓትም እየተከናወነ እንደሆነ ተመልክቷል።አንድ የዓይን እማኝ ዛሬ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ቢከፈቱም አንዳንድ የንግድ ተቋማት እንደተዘጉ ናቸው ብለዋል፡፡የአማራ ክልል የሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰሞኑን በጎንደር የተካሄደውን ግድያ አውግዟል፡፡
ማክሰኞ ዕለት በጎንደር ከተማ የአንድ ታላቅ አባት የቀብር ሥነ-ስርዓትን ተከትሎ በንፁሐን ላይ የሞት የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት ተፈፅሟል፣ ያን ተከትሎ በከተማዋ አለመረጋጋት ሰፍኖ መቆየቱን የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡
የአማራ ክልል መንግስት የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ዛሬ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ከሁለቱም የሐይማኖት አባቶች ጋር ውይይቶች ተካሂደው የቀብር ሥነ-ስርዓት እየተካሄደ ነው፡፡የፀጥታ ኃይሉ አጥፊ ግለሰቦችንና ቡድኖችን እያደነ እንደሆነም ኃላፊ አመልክተዋል፡፡
የጉዳቱ መጠን ገና እየተጠና መሆኑን የተናገሩት አቶ ደሳለኝ ጉዳቱ ከሁለቱም ወገን ነው ብለዋል፡፡መንግስቱ የተባሉ የዓይን እማኝ በስልክ እንዳብራሩት ዛሬ በከተማዋ የተረጋጋ ሁኔታ ቢኖርም ሥራ ያልጀመሩ ሱቆችን ተመልክተዋል፡፡መሐመድ የተባሉ ሌላ የዓይን እማኝ “ቀብር አናስቀብርም” የሚል ጥያቄ ያነሱ ወገኖች እንደነበሩ ጠቁመው መጨረሻ ግን በተደረሰ ውይይት ቀብር ተፈፅሟል ነው ያሉት፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በጎንደር ከተማ የተፈፀመው ድርጊት እንደሚያወግዘው የአማራ ክልል የሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ አስታወቋል፡፡ጉባዔው ትናንት ለአገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛ ብቻ በሰጠው መግለጫ «በከተማዋ የተፈፀመው ድርጊት የማንንም ሐይማኖት አይወክልም ፣ የሐይማኖቶችን አስተምሮምሆነ እሴት ያልተከተለ ነው» ብሏል፡፡መንግስት አጥፊዎችን ተከታትሎ በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲያቀርብ፣ ህዝቡም እንዲተባበር ነው የጉባዔው አባላት ያመለከቱት፡፡
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ክልል መንግስት የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ዛሬ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት የፀጥታ ኃይሉ አጥፊ ግለሰቦችንና ቡድኖችን እያደነ እንደሆነም ኃላፊ አመልክተዋል፡፡
ማክሰኞ ዕለት በጎንደር ከተማ በአንድ ታዋቂ አባት መቃብር ላይ የተፈጠረውን የህይወት ማጥፋት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት መውደምን ተከትሎ የነበረው አለመረጋጋት እየተሻሻለ መምጣቱን የአማራ ክልል መንግስት አስታውቋል።
በጥቃቱ ህይወታቸው ያለፉ ወገኖች የቀብር ሥነ-ስርዓትም እየተከናወነ እንደሆነ ተመልክቷል።አንድ የዓይን እማኝ ዛሬ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ቢከፈቱም አንዳንድ የንግድ ተቋማት እንደተዘጉ ናቸው ብለዋል፡፡የአማራ ክልል የሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰሞኑን በጎንደር የተካሄደውን ግድያ አውግዟል፡፡
ማክሰኞ ዕለት በጎንደር ከተማ የአንድ ታላቅ አባት የቀብር ሥነ-ስርዓትን ተከትሎ በንፁሐን ላይ የሞት የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት ተፈፅሟል፣ ያን ተከትሎ በከተማዋ አለመረጋጋት ሰፍኖ መቆየቱን የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡
የአማራ ክልል መንግስት የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ዛሬ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ከሁለቱም የሐይማኖት አባቶች ጋር ውይይቶች ተካሂደው የቀብር ሥነ-ስርዓት እየተካሄደ ነው፡፡የፀጥታ ኃይሉ አጥፊ ግለሰቦችንና ቡድኖችን እያደነ እንደሆነም ኃላፊ አመልክተዋል፡፡
የጉዳቱ መጠን ገና እየተጠና መሆኑን የተናገሩት አቶ ደሳለኝ ጉዳቱ ከሁለቱም ወገን ነው ብለዋል፡፡መንግስቱ የተባሉ የዓይን እማኝ በስልክ እንዳብራሩት ዛሬ በከተማዋ የተረጋጋ ሁኔታ ቢኖርም ሥራ ያልጀመሩ ሱቆችን ተመልክተዋል፡፡መሐመድ የተባሉ ሌላ የዓይን እማኝ “ቀብር አናስቀብርም” የሚል ጥያቄ ያነሱ ወገኖች እንደነበሩ ጠቁመው መጨረሻ ግን በተደረሰ ውይይት ቀብር ተፈፅሟል ነው ያሉት፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በጎንደር ከተማ የተፈፀመው ድርጊት እንደሚያወግዘው የአማራ ክልል የሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ አስታወቋል፡፡ጉባዔው ትናንት ለአገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛ ብቻ በሰጠው መግለጫ «በከተማዋ የተፈፀመው ድርጊት የማንንም ሐይማኖት አይወክልም ፣ የሐይማኖቶችን አስተምሮምሆነ እሴት ያልተከተለ ነው» ብሏል፡፡መንግስት አጥፊዎችን ተከታትሎ በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲያቀርብ፣ ህዝቡም እንዲተባበር ነው የጉባዔው አባላት ያመለከቱት፡፡
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
በነገው እለት በአዲስ አበባ ለሚካሄደው ታላቁ የኢፍጣር ፕሮግራም ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች
ሚያዚያ 21 ቀን 2014 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከሚካሄደው ታላቁ የኢፍጣር ፕሮግራም ጋር ተያይዞ ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ከቅዱስ ኡራኤል አካባቢ ጀምሮ እስከ መስቀል አደባባይ እና በዙሪያዋ የሚገኙ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ እንደሚሆኑ የፀጥታና የደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል።
በዚህም መሰረት፦
- ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሀያ ሁለት ወይም ዘሪሁን ህንፃ አካባቢ ዝግ ይደረጋል፣
- ከወሎ ሰፈር ወደ መስቀል አደባባይ ወሎ ሰፈር ኦሎምፒያ፤
- ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ አሽከርካሪዎች አጎና ሲኒማ፤
- ከጦር ኃይሎች በሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ እና ከሜኪሲኮ ወደ ብሔራዊ ቴአትር ለሚጓዙ ሜክሲኮ አደባባይ፤
- ከጌጃ ሰፈርና ከጎማ ቁጠባ በሰንጋ ተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚጓዙ የቀድሞው ደሳለኝ ሆቴል መስቀለኛ ላይ፤
- ከጎማ ቁጠባ ወደ ብሔራዊ ለሚጓዙ ጎማ ቁጠባ ላይ እና ከሜክሲኮ ወደ ፖስታ ቤት ለሚሄዱ ሚትሮሎጂ አካባቢ እንዲሁም ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ኢሚግሬሽን ለሚሄዱ አሽከርካሪዎች ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በር አካባቢ፤
- ከተክለኃይማኖት በጎላ ሚካኤል ለሚመጡ ጎላ ሚካኤል መስቀለኛ ላይ እና ከተክለኃይማኖት ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ ለሚመጡ ተክለኃይማኖት ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም ከተክለ ኃይማኖት በሶማሌ ተራ ወደ ባንኮ ዲሮማ ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ሸዋ ሱፐር ማርኬት ጋር ዝግ የሚደረግ ይሆናል።
- ከቀድሞ አትክልት ተራ አካባቢ በአሮጌው ፖስታ ቤት ወደ ቸርችል ጎዳና የሚወስደው መንገድ አሮጌው ፖስታ ቤት፤
- ከደጎል አደባባይ ወደ እሪ በከንቱ ደጎል አደባባይ ላይ እና ከአራት ኪሎ በፓርላማ ወደ ውጭ ጉዳይ የሚወስደው መንገድ ሸራተን ሆቴል መውረጃ ላይ፤
- ከአራት ኪሎ በብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ ለሚጓዙ አሽከርካሪዎች ብሔራዊ ቤተ መንግስት መስቀለኛ ላይ የሚዘጋ ሲሆን ከካዛንቺስ ሼል ወደ ፍል ውሀና ወደ ባምቢስ የሚወስዱት መንገዶች ካዛንስ ሼል ላይ ከቀኑ7፡00 ሰዓት ጀምሮ የኢፍጠር ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅበት ሰዓት ድረስ ዝግ የሚደረጉ ይሆናል።
በተጨማሪም በተገለፁት መንገዶች ላይ ለአጭርም ሆነ ለረጅመ ሰዓታት ተሽከርካሪዎችን አቁሞ መሄድ የተከለከለ ሲሆን ህብረተሰቡ ፕሮግራሙ በሠላም ተጀምሮ በሠላም እንዲጠናቀቅና ማንኛውም ዓይነት አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ በፖሊስ የመረጃ ስልኮች 0111 11 01 11 እና ነፃ የስልክ መስመር 991 ላይ በመደወልና መረጃ በመስጠት የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ የፀጥታና የደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ሚያዚያ 21 ቀን 2014 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከሚካሄደው ታላቁ የኢፍጣር ፕሮግራም ጋር ተያይዞ ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ከቅዱስ ኡራኤል አካባቢ ጀምሮ እስከ መስቀል አደባባይ እና በዙሪያዋ የሚገኙ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ እንደሚሆኑ የፀጥታና የደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል።
በዚህም መሰረት፦
- ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሀያ ሁለት ወይም ዘሪሁን ህንፃ አካባቢ ዝግ ይደረጋል፣
- ከወሎ ሰፈር ወደ መስቀል አደባባይ ወሎ ሰፈር ኦሎምፒያ፤
- ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ አሽከርካሪዎች አጎና ሲኒማ፤
- ከጦር ኃይሎች በሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ እና ከሜኪሲኮ ወደ ብሔራዊ ቴአትር ለሚጓዙ ሜክሲኮ አደባባይ፤
- ከጌጃ ሰፈርና ከጎማ ቁጠባ በሰንጋ ተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚጓዙ የቀድሞው ደሳለኝ ሆቴል መስቀለኛ ላይ፤
- ከጎማ ቁጠባ ወደ ብሔራዊ ለሚጓዙ ጎማ ቁጠባ ላይ እና ከሜክሲኮ ወደ ፖስታ ቤት ለሚሄዱ ሚትሮሎጂ አካባቢ እንዲሁም ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ኢሚግሬሽን ለሚሄዱ አሽከርካሪዎች ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በር አካባቢ፤
- ከተክለኃይማኖት በጎላ ሚካኤል ለሚመጡ ጎላ ሚካኤል መስቀለኛ ላይ እና ከተክለኃይማኖት ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ ለሚመጡ ተክለኃይማኖት ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም ከተክለ ኃይማኖት በሶማሌ ተራ ወደ ባንኮ ዲሮማ ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ሸዋ ሱፐር ማርኬት ጋር ዝግ የሚደረግ ይሆናል።
- ከቀድሞ አትክልት ተራ አካባቢ በአሮጌው ፖስታ ቤት ወደ ቸርችል ጎዳና የሚወስደው መንገድ አሮጌው ፖስታ ቤት፤
- ከደጎል አደባባይ ወደ እሪ በከንቱ ደጎል አደባባይ ላይ እና ከአራት ኪሎ በፓርላማ ወደ ውጭ ጉዳይ የሚወስደው መንገድ ሸራተን ሆቴል መውረጃ ላይ፤
- ከአራት ኪሎ በብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ ለሚጓዙ አሽከርካሪዎች ብሔራዊ ቤተ መንግስት መስቀለኛ ላይ የሚዘጋ ሲሆን ከካዛንቺስ ሼል ወደ ፍል ውሀና ወደ ባምቢስ የሚወስዱት መንገዶች ካዛንስ ሼል ላይ ከቀኑ7፡00 ሰዓት ጀምሮ የኢፍጠር ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅበት ሰዓት ድረስ ዝግ የሚደረጉ ይሆናል።
በተጨማሪም በተገለፁት መንገዶች ላይ ለአጭርም ሆነ ለረጅመ ሰዓታት ተሽከርካሪዎችን አቁሞ መሄድ የተከለከለ ሲሆን ህብረተሰቡ ፕሮግራሙ በሠላም ተጀምሮ በሠላም እንዲጠናቀቅና ማንኛውም ዓይነት አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ በፖሊስ የመረጃ ስልኮች 0111 11 01 11 እና ነፃ የስልክ መስመር 991 ላይ በመደወልና መረጃ በመስጠት የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ የፀጥታና የደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
🥳መልካም የትንሳኤ በአል እያልን የበአል ልዩ ቅናሽ ይዘን መጥተናል🥳
https://tttttt.me/getitonlinee
የወንድም የሴትም
🎯ኦርጂናል ጥሩ ሽታ ያላቸው ሽቶዎች
🎯የስጦታ ጥቅሎች(package)🎁
🎯ኦርጂናል ሰአቶች
🎯 ቦርሳዎች እና የውበት መጠበቂያዎች
🎯 አልባሳት እና ጫማዎች
🎯ለተጨማሪ መረጃ ይደውሉ በ0929011031
🎯አድራሻ፣ ቦሌ መድሀኒያለም
ያሉበት ቦታ ድረስ በነጻ እናደርሳለን
የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቅለው ቤተሰብ ይሁኑ https://tttttt.me/getitonlinee
https://tttttt.me/getitonlinee
የወንድም የሴትም
🎯ኦርጂናል ጥሩ ሽታ ያላቸው ሽቶዎች
🎯የስጦታ ጥቅሎች(package)🎁
🎯ኦርጂናል ሰአቶች
🎯 ቦርሳዎች እና የውበት መጠበቂያዎች
🎯 አልባሳት እና ጫማዎች
🎯ለተጨማሪ መረጃ ይደውሉ በ0929011031
🎯አድራሻ፣ ቦሌ መድሀኒያለም
ያሉበት ቦታ ድረስ በነጻ እናደርሳለን
የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቅለው ቤተሰብ ይሁኑ https://tttttt.me/getitonlinee
Forwarded from YeneTube
አስደሳች ዜና 12ኛ ክፍል ለጨረሳቹ እና በመማር ላይ ላላቹ!!!
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
ትናንት የጀመረው የሲዳማ ብሔር አዲስ ዓመት መቀበያ (ፊቼ ጨምበላላ) በዓል በዛሬው ዕለትም በሀዋሳ ከተማ በድምቀት መከበሩን ቀጥሏል።
በዓሉ በትናትናው ዕለት በሀዋሳ ከተማ በሚገኘው የሲዳማ ባህል አዳራሽ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ፣ ከፌዴራልና ከተለያዩ አከባቢዎች የተጋበዙ እንግዶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ወጣቶች በተገኙበት በድምቀት የተከበረ ሲሆን፤ የበዓሉ አካል የሆኑ የተለያዩ ሁነቶች በድምቀት ተከናውበታል።
በዓሉ በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ከፍተኛ የክልል እና የፌዴራል ባለሥልጣናት የአገር ሽማግሌዎች ፣ አባገዳዎች፣ አደ ሲቂዎች እንዲሁም ከደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ከተለያዩ ዞኖች የመጡ ተወካዮች በተገኙበት በጉዱማሌ በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች ታጅቦ በመከበር ላይ ነው።
ከንጋት ጀምሮ እየተከበረ በሚገኘው በዚህ በዓል ላይ ከተለያዩ አካባቢዎች የተገኙ የባህሉ ባለቤቶች በባህላዊ አልባሳት ደምቀው በቄጣላ ክዋኔና በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች አጅበው በዓሉን እያከበሩ ይገኛሉ።
የሲዳማ ብሔር አዲስ ዓመት መቀበያ (ፊቼ ጨምበላላ) ልጅ አዋቂው የሚደሰትበት ባህላዊ ክዋኔዎች በስፋት የሚታዩበት ልዩ በዓል ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
በዓሉ በትናትናው ዕለት በሀዋሳ ከተማ በሚገኘው የሲዳማ ባህል አዳራሽ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ፣ ከፌዴራልና ከተለያዩ አከባቢዎች የተጋበዙ እንግዶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ወጣቶች በተገኙበት በድምቀት የተከበረ ሲሆን፤ የበዓሉ አካል የሆኑ የተለያዩ ሁነቶች በድምቀት ተከናውበታል።
በዓሉ በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ከፍተኛ የክልል እና የፌዴራል ባለሥልጣናት የአገር ሽማግሌዎች ፣ አባገዳዎች፣ አደ ሲቂዎች እንዲሁም ከደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ከተለያዩ ዞኖች የመጡ ተወካዮች በተገኙበት በጉዱማሌ በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች ታጅቦ በመከበር ላይ ነው።
ከንጋት ጀምሮ እየተከበረ በሚገኘው በዚህ በዓል ላይ ከተለያዩ አካባቢዎች የተገኙ የባህሉ ባለቤቶች በባህላዊ አልባሳት ደምቀው በቄጣላ ክዋኔና በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች አጅበው በዓሉን እያከበሩ ይገኛሉ።
የሲዳማ ብሔር አዲስ ዓመት መቀበያ (ፊቼ ጨምበላላ) ልጅ አዋቂው የሚደሰትበት ባህላዊ ክዋኔዎች በስፋት የሚታዩበት ልዩ በዓል ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
የዩክሬን ፕሬዝዳንት በአፍሪካ ህብረት ንግግር ለማድረግ በድጋሚ ጠየቁ!
የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪ በአፍሪካ ህብረት ንግግር ለማድረግ በድጋሚ ጠየቁ፡፡ዜሌንስኪ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው ዲሜትሮ ኩሌባ በኩል ነው ጥያቄውን በድጋሚ ያቀረቡት፡፡
የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ከዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲሜትሪ ኩሌባ ጋር በስልክ ማውራታቸውን አስታውቀዋል፡፡
ለሙሳ ፋኪ የደወሉት ኩሌባ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪ ለአፍሪካ ህብረት አባል ሃገራት መሪዎች ንግግር ለማድረግ ከአሁን ቀደም ያነሱትን ጥያቄ ደግመው አንስተዋል፡፡ከህብረቱ ጋር ጠንካራ ግንኙነት ለመመስረት እንፈልጋለን ስለማለታቸውም ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የገለጹት፡፡
ሙሳ ፋኪ በበኩላቸው ዩክሬን ከሩሲያ ጋር ለገባችበት ጦርነት ሰላማዊ መፍትሔዎች ሊፈለጉለት እንደሚገባ አስረግጠው መናገራቸውን ገልጸዋል፡፡
[Alain]
@YeneTube @FikerAssefa
የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪ በአፍሪካ ህብረት ንግግር ለማድረግ በድጋሚ ጠየቁ፡፡ዜሌንስኪ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው ዲሜትሮ ኩሌባ በኩል ነው ጥያቄውን በድጋሚ ያቀረቡት፡፡
የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ከዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲሜትሪ ኩሌባ ጋር በስልክ ማውራታቸውን አስታውቀዋል፡፡
ለሙሳ ፋኪ የደወሉት ኩሌባ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪ ለአፍሪካ ህብረት አባል ሃገራት መሪዎች ንግግር ለማድረግ ከአሁን ቀደም ያነሱትን ጥያቄ ደግመው አንስተዋል፡፡ከህብረቱ ጋር ጠንካራ ግንኙነት ለመመስረት እንፈልጋለን ስለማለታቸውም ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የገለጹት፡፡
ሙሳ ፋኪ በበኩላቸው ዩክሬን ከሩሲያ ጋር ለገባችበት ጦርነት ሰላማዊ መፍትሔዎች ሊፈለጉለት እንደሚገባ አስረግጠው መናገራቸውን ገልጸዋል፡፡
[Alain]
@YeneTube @FikerAssefa
ከጎንደር ከተማ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ቁጥራቸው ያልተገለፁ ሰዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን መንግስት ገለፀ!
በጎንደር ከተማ ከግጭቱ መከሰት በኋላ የአማራ ክልል እና የፌደራል መንግስት የፀጥታ አካላት በሰሩት ስራ በርካታ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል ሲል የመንግስት ኮምኒኬሽን አገልግሎት ገለፀ።ሚኒስትሩ ለገሰ ቱሉ በቁጥጥር ስር ስለዋሉት ተጠርጣሪዎች ብዛት “በርካታ” ከማለት ባለፈ ቁጥራዊ መረጃ አልገለፁም።
በጎንደር ከተማ ያለው አለመረጋጋት “በተወሰኑ ግለሰቦች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት” የተከሰተ ግጭት ነው ሲልም የመንግስት ኮምኒኬሽን አገልግሎት ገለጿል።የፌደራል መንግስቱ አሁንም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር እያዋለ ይገኛል ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
በጎንደር ከተማ የተከሰተውን ችግር “የተናበበ በሚመስል ሁኔታ” ወደተለያዩ አካባቢዎች በተለይም ወደ ወራቤ አካባቢ ለማስፋፋት የሚደረገውን እንቅስቃሴ የሚወገዝ ነው ሲል የመንግስት ኮምኒኬሽን መግለጫ አስታውቋል።
“የአማራ ክልል ነዋሪዎች ከሌሎች ህዝቦች ጋር ግጭት ውስጥ እንዲገባ አልመው የሚሰሩ ፅንፈናኛ እና አክራሪ የፖለቲካ ልሂቃን እና የማህበረሰብ አንቂዎች ሚና አላቸው። ክልሉን የህገ ወጥ የጦር መሳሪያ እና ህገ ወጥ የገንዘብ ዝውውር መናኸሪያ ለማድረግ ሆን ብለው የሚሰሩም አሉ” ያለው መግለጫው እነዚህ ኃይሎች የተሰጣቸውን የመጨረሻ የእርምት እድል ተሰጥቷቸዋል ብሏል።
[@AddisZeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
በጎንደር ከተማ ከግጭቱ መከሰት በኋላ የአማራ ክልል እና የፌደራል መንግስት የፀጥታ አካላት በሰሩት ስራ በርካታ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል ሲል የመንግስት ኮምኒኬሽን አገልግሎት ገለፀ።ሚኒስትሩ ለገሰ ቱሉ በቁጥጥር ስር ስለዋሉት ተጠርጣሪዎች ብዛት “በርካታ” ከማለት ባለፈ ቁጥራዊ መረጃ አልገለፁም።
በጎንደር ከተማ ያለው አለመረጋጋት “በተወሰኑ ግለሰቦች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት” የተከሰተ ግጭት ነው ሲልም የመንግስት ኮምኒኬሽን አገልግሎት ገለጿል።የፌደራል መንግስቱ አሁንም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር እያዋለ ይገኛል ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
በጎንደር ከተማ የተከሰተውን ችግር “የተናበበ በሚመስል ሁኔታ” ወደተለያዩ አካባቢዎች በተለይም ወደ ወራቤ አካባቢ ለማስፋፋት የሚደረገውን እንቅስቃሴ የሚወገዝ ነው ሲል የመንግስት ኮምኒኬሽን መግለጫ አስታውቋል።
“የአማራ ክልል ነዋሪዎች ከሌሎች ህዝቦች ጋር ግጭት ውስጥ እንዲገባ አልመው የሚሰሩ ፅንፈናኛ እና አክራሪ የፖለቲካ ልሂቃን እና የማህበረሰብ አንቂዎች ሚና አላቸው። ክልሉን የህገ ወጥ የጦር መሳሪያ እና ህገ ወጥ የገንዘብ ዝውውር መናኸሪያ ለማድረግ ሆን ብለው የሚሰሩም አሉ” ያለው መግለጫው እነዚህ ኃይሎች የተሰጣቸውን የመጨረሻ የእርምት እድል ተሰጥቷቸዋል ብሏል።
[@AddisZeybe]
@YeneTube @FikerAssefa