ፕሬዘዳንት ባይደን የ“ጓንታናሞ” እስርቤትን ለመዝጋት ማቀዳቸውን ኋይት ኃውስ አስታወቀ!
የቀድሞው ፕሬዘዳንት ትራምፕ በ2016 የምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የጓንታናሞ ባይ እስርቤትን በስራ ላይ እንደሚቆይና በ “መጥፎ ሰዎች” እንደሚሞላ ገልጸው ነበር።
ኋይት ኃውስ ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን የስልጣን ዘመናቸው ከማብቃቱ በፊት በሽብር የተጠረጠሩ ግለሰቦች የሚታሰሩበትን የጓንታናሞ ባይ እስርቤትን የመዝጋት አላማ እንዳላቸው አስታውቋል፡፡
መቼ ይዘጋል ተብሎው በጋዜጠኞች የተጠየቁት የኋይት ኃውስ ፕሬስ ሴክሬታሪ“ያ እርግጠኛ ግብ ነው፤ ፍላጎታችን ነው” የሚል መልስ ሰጥተዋል፡፡ፕሬስ ሴክሬታሪዋ እንዳሉት አስተዳደሩ የባይደን አስተዳደር ያለበት መጫውቻ ምን እንደሚመስልና ከበፊቱ አስተዳደር ምን ወርሷል የሚለውን ለማወቅ ዳሰሳ እየተካሄደ ነው ብለዋል፡፡
[አል ዐይን]
@YeneTube @FikerAssefa
የቀድሞው ፕሬዘዳንት ትራምፕ በ2016 የምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የጓንታናሞ ባይ እስርቤትን በስራ ላይ እንደሚቆይና በ “መጥፎ ሰዎች” እንደሚሞላ ገልጸው ነበር።
ኋይት ኃውስ ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን የስልጣን ዘመናቸው ከማብቃቱ በፊት በሽብር የተጠረጠሩ ግለሰቦች የሚታሰሩበትን የጓንታናሞ ባይ እስርቤትን የመዝጋት አላማ እንዳላቸው አስታውቋል፡፡
መቼ ይዘጋል ተብሎው በጋዜጠኞች የተጠየቁት የኋይት ኃውስ ፕሬስ ሴክሬታሪ“ያ እርግጠኛ ግብ ነው፤ ፍላጎታችን ነው” የሚል መልስ ሰጥተዋል፡፡ፕሬስ ሴክሬታሪዋ እንዳሉት አስተዳደሩ የባይደን አስተዳደር ያለበት መጫውቻ ምን እንደሚመስልና ከበፊቱ አስተዳደር ምን ወርሷል የሚለውን ለማወቅ ዳሰሳ እየተካሄደ ነው ብለዋል፡፡
[አል ዐይን]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዕጩዎች ምዝገባ ማከናወን የተራዘመባቸው ክልሎችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ለ6ተኛው ሀገር ዐቀፍ ምርጫ የተለያዩ ተግባራትን እየፈጸመ እንደሆነ ይታወቃል።
ቦርዱ በማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 1133/2011 አንቀጽ 8 ንዑስ አንቀጽ (1) እና የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 37 ንዑስ አንቀጽ (7) እና አንቀፅ 163 ንዑስ አንቀፅ (2) ላይ በተሰጠው ሥልጣን ባወጣው የዕጩዎች ምዝገባ መመሪያ መሠረት፤ የዕጩዎችን ምዝገባ ለማከናወን የሚያስችሉትን ከክልል መስተዳድሮች እና ከከተማ መስተዳድሮች የሚጠበቁ የትብብር ግዴታዎችን ለሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ገልፆ ዝግጅቶችን እያደረገ እንደነበር ይታወቃል።
በዚህም መሰረት የክልሎች ዝግጁነት ምን እንደሚመስል ሰኞ የካቲት 01 ቀን 2013 ዓ.ም ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።
በመግለጫውም
• አዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር
• ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• ድሬዳዋ ከተማ መስተዳድር
• ጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• ኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና
• ሐረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አስፈላጊ የሆኑትን ለምርጫ ክልል እና ለዞን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሊያገለግሉ የሚችሉ ቢሮዎችን አዘጋጅተው ለቦርዱ እንዳስታወቁ በመግለጽ፤ በጊዜ ሠሌዳው በተቀመጠው ቀን መሠረት ከየካቲት 08 እስከ የካቲት 21 ቀን 2013 ዓ.ም. የዕጩ ምዝገባ የሚከናወነው ከላይ በተጠቀሱት ክልልሎች በሚገኙ የምርጫ ክልል ቢሮዎች መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን በቀሪዎቹ ክልሎች የክልል መስተዳድሮቹ ደግሞ አስፈላጊውን ትብብር ሲያደርጉ ምዝገባው የሚጀመርበትን ቀን ቦርዱ የሚያሳውቅ ገልፆ ነበር።
መሆኑን በዚሁ መሠረት እጩ ምዝገባ በማይጀመርባቸው ቀሪ ክልሎቹ የሚካሄዱት የዕጩዎች ምዝገባ ሂደት እንደሚከተለው ይሆናል፤
• አፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• አማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• ሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• ደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት እና
• ሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከየካቲት 05 እስከ የካቲት 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ለዕጩዎች ምዝገባ የሚውሉ ቁሳቁሶች የሚጓጓዙበትና የዕጩዎች ምዝገባ አስፈጻሚዎች ሥልጠና የሚሰጥበት ጊዜ ሲሆን፤ ከየካቲት 15 እስከ የካቲት 26 ቀን 2013 ዓ.ም. ደግሞ የዕጩዎች ምዝገባ የሚከናወንበት ጊዜ እንዲሆን ቦርዱ ወስኗል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
የካቲት 06 ቀን 2013 ዓ.ም
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ለ6ተኛው ሀገር ዐቀፍ ምርጫ የተለያዩ ተግባራትን እየፈጸመ እንደሆነ ይታወቃል።
ቦርዱ በማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 1133/2011 አንቀጽ 8 ንዑስ አንቀጽ (1) እና የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 37 ንዑስ አንቀጽ (7) እና አንቀፅ 163 ንዑስ አንቀፅ (2) ላይ በተሰጠው ሥልጣን ባወጣው የዕጩዎች ምዝገባ መመሪያ መሠረት፤ የዕጩዎችን ምዝገባ ለማከናወን የሚያስችሉትን ከክልል መስተዳድሮች እና ከከተማ መስተዳድሮች የሚጠበቁ የትብብር ግዴታዎችን ለሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ገልፆ ዝግጅቶችን እያደረገ እንደነበር ይታወቃል።
በዚህም መሰረት የክልሎች ዝግጁነት ምን እንደሚመስል ሰኞ የካቲት 01 ቀን 2013 ዓ.ም ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።
በመግለጫውም
• አዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር
• ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• ድሬዳዋ ከተማ መስተዳድር
• ጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• ኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና
• ሐረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አስፈላጊ የሆኑትን ለምርጫ ክልል እና ለዞን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሊያገለግሉ የሚችሉ ቢሮዎችን አዘጋጅተው ለቦርዱ እንዳስታወቁ በመግለጽ፤ በጊዜ ሠሌዳው በተቀመጠው ቀን መሠረት ከየካቲት 08 እስከ የካቲት 21 ቀን 2013 ዓ.ም. የዕጩ ምዝገባ የሚከናወነው ከላይ በተጠቀሱት ክልልሎች በሚገኙ የምርጫ ክልል ቢሮዎች መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን በቀሪዎቹ ክልሎች የክልል መስተዳድሮቹ ደግሞ አስፈላጊውን ትብብር ሲያደርጉ ምዝገባው የሚጀመርበትን ቀን ቦርዱ የሚያሳውቅ ገልፆ ነበር።
መሆኑን በዚሁ መሠረት እጩ ምዝገባ በማይጀመርባቸው ቀሪ ክልሎቹ የሚካሄዱት የዕጩዎች ምዝገባ ሂደት እንደሚከተለው ይሆናል፤
• አፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• አማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• ሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• ደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት እና
• ሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከየካቲት 05 እስከ የካቲት 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ለዕጩዎች ምዝገባ የሚውሉ ቁሳቁሶች የሚጓጓዙበትና የዕጩዎች ምዝገባ አስፈጻሚዎች ሥልጠና የሚሰጥበት ጊዜ ሲሆን፤ ከየካቲት 15 እስከ የካቲት 26 ቀን 2013 ዓ.ም. ደግሞ የዕጩዎች ምዝገባ የሚከናወንበት ጊዜ እንዲሆን ቦርዱ ወስኗል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
የካቲት 06 ቀን 2013 ዓ.ም
@YeneTube @FikerAssefa
በሶማሊያ በፕሬዘዳንታዊ ቤተመንግስት አካባቢ አጥፍቶ ጠፊ ጉዳት አደረሰ!
በሶማሊያ ሞቃዲሹ በፕሬዘዳንታዊ ቤተመንግስት አካባቢ አንድ አጥፍቶ ጠፊ ባፈነዳው ቦንብ ራሱ ሲሞት ሌሎች ሰባት ንጹሃን መቁሰላቸውን ፖሊስ ገልጿል፡፡ የፖሊስ ቃል አቀባይ ሳዲቅ አሊ አሽከርካሪው እንዲቆም ሲጠየቅ ተባባሪ ባለመሆኑ ፖሊስ ተኩስ መክፈቱን ተናግረዋል፡፡በፍንዳታው ከ10 በላይ የሚሆኑ ተሽከርካሪዎች በፍንዳታው መውደማቸውን ፖሊስ አስታውቋል፡፡በሶማሊያ ለመጨረሻ ጊዜ ቦንብ የፈነዳው የሶማሊያ ፖለቲከኞች እንዴት ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ እንናካሂድ የሚል ክርክር ባሰሙበት ወቅት ነው፡፡ምርጫው በፈረንጆቹ የካቲት 8 ቀነ ቀጠሮ ተይዞለታል፡፡
[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
በሶማሊያ ሞቃዲሹ በፕሬዘዳንታዊ ቤተመንግስት አካባቢ አንድ አጥፍቶ ጠፊ ባፈነዳው ቦንብ ራሱ ሲሞት ሌሎች ሰባት ንጹሃን መቁሰላቸውን ፖሊስ ገልጿል፡፡ የፖሊስ ቃል አቀባይ ሳዲቅ አሊ አሽከርካሪው እንዲቆም ሲጠየቅ ተባባሪ ባለመሆኑ ፖሊስ ተኩስ መክፈቱን ተናግረዋል፡፡በፍንዳታው ከ10 በላይ የሚሆኑ ተሽከርካሪዎች በፍንዳታው መውደማቸውን ፖሊስ አስታውቋል፡፡በሶማሊያ ለመጨረሻ ጊዜ ቦንብ የፈነዳው የሶማሊያ ፖለቲከኞች እንዴት ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ እንናካሂድ የሚል ክርክር ባሰሙበት ወቅት ነው፡፡ምርጫው በፈረንጆቹ የካቲት 8 ቀነ ቀጠሮ ተይዞለታል፡፡
[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ በሕገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የተገኘ ከ2 ሚሊየን ጄሪካን በላይ ፓልም የምግብ ዘይት ተያዘ!
በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ጀሞ ሚካኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በልዩ ስሙ አንበሳ ጋራዥ በሚባለው ቦታ በሕገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የተገኘ ከ2 ሚሊየን ጄሪካን በላይ ፓልም የምግብ ዘይት ዛሬ ተይዟል፡፡
በሕገ ወጥ መንገድ የተከማቸው ዘይት ሊያዝ የቻለው ፌዴራል ፖሊስ እና የላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከህብረተሰቡ የደረሳቸውን ጥቆማ መነሻ በማድረግ ለ2 ሳምንታት ባደረጉት ጥብቅ ክትትል መሆኑን ኢብኮ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ጀሞ ሚካኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በልዩ ስሙ አንበሳ ጋራዥ በሚባለው ቦታ በሕገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የተገኘ ከ2 ሚሊየን ጄሪካን በላይ ፓልም የምግብ ዘይት ዛሬ ተይዟል፡፡
በሕገ ወጥ መንገድ የተከማቸው ዘይት ሊያዝ የቻለው ፌዴራል ፖሊስ እና የላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከህብረተሰቡ የደረሳቸውን ጥቆማ መነሻ በማድረግ ለ2 ሳምንታት ባደረጉት ጥብቅ ክትትል መሆኑን ኢብኮ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
መቀሌ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በመቀበል የመማር ማስተማሩን ሥራ መጀመሩን አስታወቀ።
የዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር ዶ/ር ከሰተ ለገሰ፣ የመማር ማስተማሩን ሥራ የጀመሩት ከሚጠበቁት 13ሺህ ተማሪዎች ውስጥ አብዛኛዎቹን በመቀበል ላይ መሆኑንና የቀሩትንም እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል።
ተማሪዎቹ በመቀሌ ማኅበረሰብ እና ተማሪዎች ኅብረት አቀባበል እየተደረገላቸው ከየካቲት 1 ቀን 2013 ዓ.ም አንሥቶ ትምህርታቸውን መከታተል መጀመራቸውን አስታውቀዋል።
የተማሪዎች መማሪያ ክፍሎች፣ መኝታ ቤቶች፣ ምግብ ማብሰያ እና መመገቢያ አዳራሾችን የኮሮና ወረረሽኝን ለመከላከል ታሳቢ ባደረገ መልኩ ቀድመው መሰናዳታቸውን ዶ/ር ከሰተ አስረድተዋል።
ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ዓመት ድረስ የሚማሩት እነዚህ ተማሪዎቹ የተቋሙን ሕግ እና ሥርዓት አክብረው ትምህርታቸውን መከታታል እንደሚጠበቅባቸውም ገልጸዋል።
ትምህርታቸው መከታተል ከጀመሩት መካከል ከደቡብ ክልል የመጣው የአዲሀቂ ካምፓሰ የሶሾሎጂ ሁለተኛ ዓመት ተማሪ ቸርነት ሺፈራው ትምህርት በመጀመሩ መደሰቱን ገልጾ፣ በንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት በኩል ግን እጥረት ስላለ እንዲስተካከል አስተያየቱን ሰጥቷል።
የእኛ ተማሪዎች ሕልም በሰላም እና ፍቅር ትምህርታችንን መከታተል እና ተመርቀን ራሳችንና ሀገራችን መጥቀም ነው ያለው ደግሞ የሁለተኛ ዓመት ሶሾሎጂ ተማሪ እንድሪስ አብዱ ነው።
ከኦሮሚያ ክልል የመጣው ተማሪ ጫላ ሳፋይ በበኩሉ ዩኒቨርሲቲው ለመማር ማስተማር የሚያስችል የግቢው መሠረተ ልማት ማሟላቱን ገልጿል።
በምግብ ሰዓት ግን በወረፋ ብዛት ምክንያት ለብዙ ሰዓታት እየጠበቅን መሆኑን ታውቆ መፍትሔ ሊበጅለት ይገባል ማለቱን ኢዜአ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
የዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር ዶ/ር ከሰተ ለገሰ፣ የመማር ማስተማሩን ሥራ የጀመሩት ከሚጠበቁት 13ሺህ ተማሪዎች ውስጥ አብዛኛዎቹን በመቀበል ላይ መሆኑንና የቀሩትንም እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል።
ተማሪዎቹ በመቀሌ ማኅበረሰብ እና ተማሪዎች ኅብረት አቀባበል እየተደረገላቸው ከየካቲት 1 ቀን 2013 ዓ.ም አንሥቶ ትምህርታቸውን መከታተል መጀመራቸውን አስታውቀዋል።
የተማሪዎች መማሪያ ክፍሎች፣ መኝታ ቤቶች፣ ምግብ ማብሰያ እና መመገቢያ አዳራሾችን የኮሮና ወረረሽኝን ለመከላከል ታሳቢ ባደረገ መልኩ ቀድመው መሰናዳታቸውን ዶ/ር ከሰተ አስረድተዋል።
ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ዓመት ድረስ የሚማሩት እነዚህ ተማሪዎቹ የተቋሙን ሕግ እና ሥርዓት አክብረው ትምህርታቸውን መከታታል እንደሚጠበቅባቸውም ገልጸዋል።
ትምህርታቸው መከታተል ከጀመሩት መካከል ከደቡብ ክልል የመጣው የአዲሀቂ ካምፓሰ የሶሾሎጂ ሁለተኛ ዓመት ተማሪ ቸርነት ሺፈራው ትምህርት በመጀመሩ መደሰቱን ገልጾ፣ በንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት በኩል ግን እጥረት ስላለ እንዲስተካከል አስተያየቱን ሰጥቷል።
የእኛ ተማሪዎች ሕልም በሰላም እና ፍቅር ትምህርታችንን መከታተል እና ተመርቀን ራሳችንና ሀገራችን መጥቀም ነው ያለው ደግሞ የሁለተኛ ዓመት ሶሾሎጂ ተማሪ እንድሪስ አብዱ ነው።
ከኦሮሚያ ክልል የመጣው ተማሪ ጫላ ሳፋይ በበኩሉ ዩኒቨርሲቲው ለመማር ማስተማር የሚያስችል የግቢው መሠረተ ልማት ማሟላቱን ገልጿል።
በምግብ ሰዓት ግን በወረፋ ብዛት ምክንያት ለብዙ ሰዓታት እየጠበቅን መሆኑን ታውቆ መፍትሔ ሊበጅለት ይገባል ማለቱን ኢዜአ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) በቀጣዩ ሃገር አቀፍ ምርጫ እንደሚወዳደር አስታወቀ፡፡
ምርጫውን በተመለከተ ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ቆታ ያደረጉት የፓርቲው ሊቀመንበር መረራ ጉዲና (ፕ/ር) በመጪው ሃገራዊ ምርጫ እንደሚወዳደሩ አስታውቀዋል፡፡
ሆኖም በምርጫው የመወዳደራቸው ሁኔታ በመንግስት የሚወሰን ነው እንደ ሊቀመንበሩ ገለጻ፡፡ ሊወዳደሩ የሚችሉባቸውን ቅድመ ሁኔታዎችንም አስቀምጠዋል፡፡
ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ እንዲሆን “የምናነሳቸው መሰረታዊ ጥያቄዎች አሉን” የሚሉት መረራ “መንግስት ካላስወጣን በስተቀር ከምርጫው አንወጣም” ሲሉ ይናገራሉ፡፡
መሰረታዊ የሚሏቸውን ጥያቄዎች ምንነት በተመለከተ ሲያብራሩም በሺዎች የሚቆጠሩ አባልና ደጋፊዎቻችን እንዲሁም ከፍተኛ አመራሮቻችን ታስረዋል ይላሉ፡፡
ዘገባው የአልዐይን ነው፣ ዝርዝሩን ለማንበብ👇👇👇
https://am.al-ain.com/article/we-won-t-miss-the-election-unless-gov-t-compel-us-prof-merera-gudina
@YeneTube @FikerAssefa
ምርጫውን በተመለከተ ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ቆታ ያደረጉት የፓርቲው ሊቀመንበር መረራ ጉዲና (ፕ/ር) በመጪው ሃገራዊ ምርጫ እንደሚወዳደሩ አስታውቀዋል፡፡
ሆኖም በምርጫው የመወዳደራቸው ሁኔታ በመንግስት የሚወሰን ነው እንደ ሊቀመንበሩ ገለጻ፡፡ ሊወዳደሩ የሚችሉባቸውን ቅድመ ሁኔታዎችንም አስቀምጠዋል፡፡
ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ እንዲሆን “የምናነሳቸው መሰረታዊ ጥያቄዎች አሉን” የሚሉት መረራ “መንግስት ካላስወጣን በስተቀር ከምርጫው አንወጣም” ሲሉ ይናገራሉ፡፡
መሰረታዊ የሚሏቸውን ጥያቄዎች ምንነት በተመለከተ ሲያብራሩም በሺዎች የሚቆጠሩ አባልና ደጋፊዎቻችን እንዲሁም ከፍተኛ አመራሮቻችን ታስረዋል ይላሉ፡፡
ዘገባው የአልዐይን ነው፣ ዝርዝሩን ለማንበብ👇👇👇
https://am.al-ain.com/article/we-won-t-miss-the-election-unless-gov-t-compel-us-prof-merera-gudina
@YeneTube @FikerAssefa
ድራጊ አዲሱ የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ቃለ መሃላ ፈጸሙ!
ማሪዮ ድራጊ አዲሱ የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ቃለ መሃላ ፈጸሙ፡፡የቀድሞው የአውሮፓ ማዕከላዊ ባንክ ፕሬዝዳንት ጁሴፔ ኮንቴን ተክተው ጣሊያንን በጠቅላይ ሚኒስትርነት ለመምራት ቃለ መሃላ የፈጸሙት በፕሬዝዳንት ሰርጂዮ ማታሬላ ጥሪ ነው፡ማታሬላ የህግ ፕሮፌሰሩ ኮንቴ በገዛ ፈቃዳቸው ስልጣን ለመልቀቅ መጠየቃቸውን ተከትሎ ነው ድራጊን መንግስት እንዲያዋቅሩ የጠሩት፡፡ድራጊም መንግስት ለማዋቀር የሚያስችል የካቢኔ አባላት ምርጫ ማድረጋቸውንም ገልጸዋል፡፡በፋይቭ ስታር ሙቭመንት እና በሊግ ኋላ ላይ ደግሞ በፋይቭ ስታር ሙቭመንት እና በዴሞክራቲክ ፓርቲ ጥምረት በሁለት የተለያዩ ጊዜያት የተመሰረቱ መንግስታትን በገለልተኛነት ተመርጠው የመሩት ኮንቴ ጣሊያንን ላለፉት 4 ዓመታት መርተዋል፡፡ሆኖም በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት የገቡበት ፖለቲካዊ ቅርቃር በስልጣን ሳያስቀጥላቸው ቀርቷል፡፡
[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ማሪዮ ድራጊ አዲሱ የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ቃለ መሃላ ፈጸሙ፡፡የቀድሞው የአውሮፓ ማዕከላዊ ባንክ ፕሬዝዳንት ጁሴፔ ኮንቴን ተክተው ጣሊያንን በጠቅላይ ሚኒስትርነት ለመምራት ቃለ መሃላ የፈጸሙት በፕሬዝዳንት ሰርጂዮ ማታሬላ ጥሪ ነው፡ማታሬላ የህግ ፕሮፌሰሩ ኮንቴ በገዛ ፈቃዳቸው ስልጣን ለመልቀቅ መጠየቃቸውን ተከትሎ ነው ድራጊን መንግስት እንዲያዋቅሩ የጠሩት፡፡ድራጊም መንግስት ለማዋቀር የሚያስችል የካቢኔ አባላት ምርጫ ማድረጋቸውንም ገልጸዋል፡፡በፋይቭ ስታር ሙቭመንት እና በሊግ ኋላ ላይ ደግሞ በፋይቭ ስታር ሙቭመንት እና በዴሞክራቲክ ፓርቲ ጥምረት በሁለት የተለያዩ ጊዜያት የተመሰረቱ መንግስታትን በገለልተኛነት ተመርጠው የመሩት ኮንቴ ጣሊያንን ላለፉት 4 ዓመታት መርተዋል፡፡ሆኖም በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት የገቡበት ፖለቲካዊ ቅርቃር በስልጣን ሳያስቀጥላቸው ቀርቷል፡፡
[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
በርሀብ አድማ ላይ የሚገኙት የእነ አቶ ጃዋር መሃመድ እና አቶ በቀለ ገርባን የሚከታተል የግል ሃኪሞቻቸው ቡድን ሲያደርግላቸው የቆየውን የህክምና ክትትል ማቆሙን አስታውቋል።
የህክምና ቡድኑ አስተባባሪ ዶ/ር ኢሊሊ ጀማል ለዶይቼ ቬለ እንዳሉት የህክምና ክትትሉን ከትናንት ምሽት ጀምሮ ለማቆም የተገደዱት በማረሚያ ቤት እና በታካሚዎች በኩል ያለው ፍላጎት ባለመጣጣሙ ነው ብለዋል፡፡ ማረሚያ ቤቱ ወደ መንግስት ህክምና ማዕከል እንዲወሰዱ ፍላጎት ሲያሳይ ታካሚዎች ደግሞ በግል ሆስፒታል ለመታየት በመፈለጋቸው ቡድኑ ህክምናውን መስጠት አለመቻሉም ተገልጿል።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የህክምና ቡድኑ አስተባባሪ ዶ/ር ኢሊሊ ጀማል ለዶይቼ ቬለ እንዳሉት የህክምና ክትትሉን ከትናንት ምሽት ጀምሮ ለማቆም የተገደዱት በማረሚያ ቤት እና በታካሚዎች በኩል ያለው ፍላጎት ባለመጣጣሙ ነው ብለዋል፡፡ ማረሚያ ቤቱ ወደ መንግስት ህክምና ማዕከል እንዲወሰዱ ፍላጎት ሲያሳይ ታካሚዎች ደግሞ በግል ሆስፒታል ለመታየት በመፈለጋቸው ቡድኑ ህክምናውን መስጠት አለመቻሉም ተገልጿል።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በትግራይ ክልል ጾታዊ ጥቃትን ጨምሮ ተፈጽመዋል ላላቸው የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መንግሥት ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ እና ወንጀለኞችንም ለፍርድ እንደሚያቀርብ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል፡፡ መንግሥት የሰብዓዊ መብት ጥበቃን ለማሻሻል ቁርጠኛ እንደሆነም ሚንስቴሩ ገልጧል፡፡ ኮሚሽኑ እየሰራ ያለው ሥራ የሀገሪቱ ፖለቲካዊ ለውጥ ፍሬ እያፈራ መሆኑን ያሳያል በማለትም አክሏል ሚንስቴሩ፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
ዶናልድ ትራምፕ የቀረበባቸው ክስ በሴኔቱ ውድቅ ተደረገ!
በፈረንጆቹ ጃንዋሪ 6 አመፅን አነሳስተዋል በሚል በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ክስ የቀረበባቸው የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይከሰሱ አይከሰሱ የሚለውን ለመወሰን ዛሬ የተሰበሰበው ሴኔት 57 ለ 43 በሆነ አብላጫ ድምፅ እንዳይከሰሱ ወስኗል። ክሱ ተፈፃሚ እንዲሆን የሴኔቱ ሁለት ሶስተኛ ወይም 67 ድምፅ ያስፈልግ ነበር። ሁሉም የዴሞክራት ፓርቲ ተወካዮች ትራምፕ እንዲከሰሱ ድምፅ የሰጡ ሲሆን 7 ሪፐብሊካኖችም ተባብረዋቸዋል። ዶናልድ ትራምፕ በተመሳሳይ ሂደት ውስጥ ሲያልፉ ይሄኛው ለሁለተኛ ጊዜያቸው ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
በፈረንጆቹ ጃንዋሪ 6 አመፅን አነሳስተዋል በሚል በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ክስ የቀረበባቸው የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይከሰሱ አይከሰሱ የሚለውን ለመወሰን ዛሬ የተሰበሰበው ሴኔት 57 ለ 43 በሆነ አብላጫ ድምፅ እንዳይከሰሱ ወስኗል። ክሱ ተፈፃሚ እንዲሆን የሴኔቱ ሁለት ሶስተኛ ወይም 67 ድምፅ ያስፈልግ ነበር። ሁሉም የዴሞክራት ፓርቲ ተወካዮች ትራምፕ እንዲከሰሱ ድምፅ የሰጡ ሲሆን 7 ሪፐብሊካኖችም ተባብረዋቸዋል። ዶናልድ ትራምፕ በተመሳሳይ ሂደት ውስጥ ሲያልፉ ይሄኛው ለሁለተኛ ጊዜያቸው ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
ሦስት መቶ አርባ ሦስት ዜጎች ከሳዑዲ አረብያ ወደ አገራቸው ተመለሱ!
ሦስት መቶ አርባ ሦስት ኢትዮጵያዊያን ከሳዑዲ አረብያ ጂዳ ከተማ ወደ አገራቸው መመለሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቆንስላ ጉዳዮች ዳይረክቶሬት ጄኔራል ተወካይ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተገኝተው ለተመላሾቹ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ሦስት መቶ አርባ ሦስት ኢትዮጵያዊያን ከሳዑዲ አረብያ ጂዳ ከተማ ወደ አገራቸው መመለሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቆንስላ ጉዳዮች ዳይረክቶሬት ጄኔራል ተወካይ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተገኝተው ለተመላሾቹ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሻምቡ ባኮን የአስፓልት ኮንክሪት መንገድ በይፋ መርቀው ስራ አስጀመሩ።
መንገዱ ከ60 ኪሎሜትር በላይ ርዝመት ያለው ነው።በተጨማሪም የሻምቡ ሀገምሳ የ95 ኪሎሜትር መንገድ ፕሮጀክት የማስጀመር ስነስርአትም ተካሂዷል።ከኦቢኤን የተገኘው መረጃ እንዳመለከተው ግንባታውን የማስጀመር እና የምረቃ ስነስርአቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፥ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፥ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰመስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ እና ሌሎች የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት በሆሮ ጉዱሩ ዞን ሻምቡ ከተማ ተካሂዷል።
[OBN/Walta]
@YeneTube @FikerAssefa
መንገዱ ከ60 ኪሎሜትር በላይ ርዝመት ያለው ነው።በተጨማሪም የሻምቡ ሀገምሳ የ95 ኪሎሜትር መንገድ ፕሮጀክት የማስጀመር ስነስርአትም ተካሂዷል።ከኦቢኤን የተገኘው መረጃ እንዳመለከተው ግንባታውን የማስጀመር እና የምረቃ ስነስርአቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፥ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፥ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰመስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ እና ሌሎች የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት በሆሮ ጉዱሩ ዞን ሻምቡ ከተማ ተካሂዷል።
[OBN/Walta]
@YeneTube @FikerAssefa
ሱዳን የቀድሞው ገዢ ፓርቲ አባላት ተይዘው እንዲከሰሱ ወሰነች!
የአልበሽር ደጋፊዎች ከያሉበት እንዲታደኑ እና ክስ እንዲመሰረትባቸው ውሳኔ ተላልፏል፡፡የቀድሞውን ም/ፕሬዝዳንት ጨምሮ ከፍተኛ ባለስልጣናት ባለፈው ሳምንት መያዛቸው ይታወሳል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የአልበሽር ደጋፊዎች ከያሉበት እንዲታደኑ እና ክስ እንዲመሰረትባቸው ውሳኔ ተላልፏል፡፡የቀድሞውን ም/ፕሬዝዳንት ጨምሮ ከፍተኛ ባለስልጣናት ባለፈው ሳምንት መያዛቸው ይታወሳል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በጊኒ በኢቦላ የሶስት ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ የበሽታው መቀስቀስ ይፋ ተደረገ!
በጊኒ ደቡብ ምስራቃዊ ግዛት በኢቦላ የሶስት ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን አራት ሰዎች ደግሞ ክፉኛ ታመዋል፡በላይቤሪያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኝ ስፍራ የቀብር ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት ሶስት ሰዎች የደም መፍሰስ ፣ ማስመለስና ፣ ተቅማት ምልክቶች ታይቶባቸዋል፡፡
በኢቦላ መያዛቸው ከተረጋገጠ በኋላ በለይቶ ማቆያ እንዲገቡ መደረጋቸውን የጊኒ የጤና ሚኒስትር አስታውቋል፡፡የጤና ሚኒስትሩ ሪማይ ላማህ በኢቦላ የሰዎች ህለፈት መመዝገቡ ስጋት እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል፡፡ጊ ከዓለም የጤና ድርጅት ጋር በመሆን በኢቦላ የሚሞቱ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስ የኢቦላ ክትባት እንደምትሰጥ አስታውቃለች፡፡እ.ኤ.አ ከ 2013 እስከ 2016 ባሉት ዓመታት በጊኒ ፣ ላይቤሪያ ፣ ሴራሊዮን ፤ በኢቦላ የተነሳ የ11,300 ሰዎች ህልፈት መመዝገቡ ይታወቃል፡፡
✍Bisrat FM
@YeneTube @FikerAssefa
በጊኒ ደቡብ ምስራቃዊ ግዛት በኢቦላ የሶስት ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን አራት ሰዎች ደግሞ ክፉኛ ታመዋል፡በላይቤሪያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኝ ስፍራ የቀብር ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት ሶስት ሰዎች የደም መፍሰስ ፣ ማስመለስና ፣ ተቅማት ምልክቶች ታይቶባቸዋል፡፡
በኢቦላ መያዛቸው ከተረጋገጠ በኋላ በለይቶ ማቆያ እንዲገቡ መደረጋቸውን የጊኒ የጤና ሚኒስትር አስታውቋል፡፡የጤና ሚኒስትሩ ሪማይ ላማህ በኢቦላ የሰዎች ህለፈት መመዝገቡ ስጋት እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል፡፡ጊ ከዓለም የጤና ድርጅት ጋር በመሆን በኢቦላ የሚሞቱ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስ የኢቦላ ክትባት እንደምትሰጥ አስታውቃለች፡፡እ.ኤ.አ ከ 2013 እስከ 2016 ባሉት ዓመታት በጊኒ ፣ ላይቤሪያ ፣ ሴራሊዮን ፤ በኢቦላ የተነሳ የ11,300 ሰዎች ህልፈት መመዝገቡ ይታወቃል፡፡
✍Bisrat FM
@YeneTube @FikerAssefa
ሕብረ ብሔራዊ ወንድማማችነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል የምርጫ 2013 የብልጽግና ፓርቲ ማኒፌስቶ እና የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት ይፋዊ የእውቅና መድረክ በሸራተን አዲስ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የዕውቅና መድረኩን በእንኳን ደህና መጣችሁ የከፈቱት የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ብናልፍ አንዷለም ፓርቲያችን ብልጽግና የአገራችንንና አለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን በጥልቀት የገመገመ፣አገራችንን አደጋ ላይ ሊጥሉ የሚችሉ ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን በውል ለይቶ ትክክለኛ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ያስቀመጠ፣ሁሉንም የኢትዮጵያ ህዝቦች በእኩል አካቶና አቅፎ የማታገያ ሜዳ ያመቻቸ፣በሚሊዬን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን በአባልነትና በደጋፊነት ከጎኑ ያሰለፈ፣በለውጥ ውስጥ የተወለደ፣ለለውጥ የሚተጋ፣የተስፋ ብርሐን የሰነቀ የዛሬና የነገ ፓርቲ ነው ብለዋል፡፡
በመድረኩ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ ፓርቲው በምርጫ ወቅት የሚጠቀምበትን ማኒፌስቶና የምርጫ መወዳደሪያ ምልክትን ይፋ አድርገዋል፡፡
በመድረኩ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ በርካታ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
Via:- FBC
@Yenetube @Fikerassefa
የዕውቅና መድረኩን በእንኳን ደህና መጣችሁ የከፈቱት የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ብናልፍ አንዷለም ፓርቲያችን ብልጽግና የአገራችንንና አለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን በጥልቀት የገመገመ፣አገራችንን አደጋ ላይ ሊጥሉ የሚችሉ ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን በውል ለይቶ ትክክለኛ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ያስቀመጠ፣ሁሉንም የኢትዮጵያ ህዝቦች በእኩል አካቶና አቅፎ የማታገያ ሜዳ ያመቻቸ፣በሚሊዬን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን በአባልነትና በደጋፊነት ከጎኑ ያሰለፈ፣በለውጥ ውስጥ የተወለደ፣ለለውጥ የሚተጋ፣የተስፋ ብርሐን የሰነቀ የዛሬና የነገ ፓርቲ ነው ብለዋል፡፡
በመድረኩ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ ፓርቲው በምርጫ ወቅት የሚጠቀምበትን ማኒፌስቶና የምርጫ መወዳደሪያ ምልክትን ይፋ አድርገዋል፡፡
በመድረኩ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ በርካታ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
Via:- FBC
@Yenetube @Fikerassefa
ቻይና የለገሰችው የመጀመሪያው ዙር የኮሮና ቫይረስ ክትባት ዛሬ ጠዋት ዚምባብዌ ዋና ከተማ ሐራሬ መግባቱ ተሰምቷል፡፡
የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ኮንስታቲኖ ቺዌንጋ፤ ሮበርት ጋብሬል ሙጋቤ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን በመገኘት ድጋፉን ተቀብለዋል፡፡
ከምክትል ፕሬዚዳንቱ በጨማሪ በዚምባብዌ የቻይና አምባሳደርም ተገኝተዋል፡፡
ቻይና የለገሰችው የኮሮና ቫይረስ ክትባት 200 ሺህ መጠን ያለው ነው ተብሏል፡፡
የኮሮና ቫይረስ ክትባቱ የበለጸገው ሲኖፋርማ በተባለው የሀገሪቱ ብሔራዊ የመድኃኒት አምራች ኩባንያ መሆኑም ተነግሯል፡፡
ምንጭ፡-ሲጂቲኤን
@Yenetube @Fikerassefa
የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ኮንስታቲኖ ቺዌንጋ፤ ሮበርት ጋብሬል ሙጋቤ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን በመገኘት ድጋፉን ተቀብለዋል፡፡
ከምክትል ፕሬዚዳንቱ በጨማሪ በዚምባብዌ የቻይና አምባሳደርም ተገኝተዋል፡፡
ቻይና የለገሰችው የኮሮና ቫይረስ ክትባት 200 ሺህ መጠን ያለው ነው ተብሏል፡፡
የኮሮና ቫይረስ ክትባቱ የበለጸገው ሲኖፋርማ በተባለው የሀገሪቱ ብሔራዊ የመድኃኒት አምራች ኩባንያ መሆኑም ተነግሯል፡፡
ምንጭ፡-ሲጂቲኤን
@Yenetube @Fikerassefa
አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ እና ጌትነት ዋለ በፈረንሳይ የተካሄደውን የቤት ውስጥ ሻምፒዮን በበላይነት አጠናቀቁ
በፈረንሳይ ቫል ዴ ሪዩል በተካሄደው የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አትሌት ጉዳግፍ በዚያው በፈረንሳይ ክብረ ወሰን ከሰበረች በሳምንት ውስጥ ሁለተኛ ድሏን 800 ሜትር አሸንፋለች።
አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ እ.አ.አ ከ2006 ወዲህ ርቀቱን 1:57.52 በሆነ ጊዜ የአለም ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ነው ለማሸነፍ የቻለችው።
አትሌት ጌትነት ዋለ ደግሞ በ1500 ሜትር የመሰናክል ሩጫ ለሜቻ ግርማን አስከትሎ በመግባት ሌላ አንጸባራቂ ድል አስመዝግቧል።
አትሌት ጌትነት ዋለ 1500 ሜትሩን በ3:35.54 ጊዜ ሲጨርስ ፣ አትሌት ለሜቻ ግርማ ደግሞ 3:35.60 በሆነ ጊዜ ሁለተኛ ሆኖ በማጠናቀቅ የሳምንቱን ድል ለኢትዮጵያ ያማረ እንዲሆን አድርጎታል።
Via: EBC
@Yenetube @Fikerassefa
በፈረንሳይ ቫል ዴ ሪዩል በተካሄደው የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አትሌት ጉዳግፍ በዚያው በፈረንሳይ ክብረ ወሰን ከሰበረች በሳምንት ውስጥ ሁለተኛ ድሏን 800 ሜትር አሸንፋለች።
አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ እ.አ.አ ከ2006 ወዲህ ርቀቱን 1:57.52 በሆነ ጊዜ የአለም ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ነው ለማሸነፍ የቻለችው።
አትሌት ጌትነት ዋለ ደግሞ በ1500 ሜትር የመሰናክል ሩጫ ለሜቻ ግርማን አስከትሎ በመግባት ሌላ አንጸባራቂ ድል አስመዝግቧል።
አትሌት ጌትነት ዋለ 1500 ሜትሩን በ3:35.54 ጊዜ ሲጨርስ ፣ አትሌት ለሜቻ ግርማ ደግሞ 3:35.60 በሆነ ጊዜ ሁለተኛ ሆኖ በማጠናቀቅ የሳምንቱን ድል ለኢትዮጵያ ያማረ እንዲሆን አድርጎታል።
Via: EBC
@Yenetube @Fikerassefa
አዲስ አበባ እና ድሬዳዋን ጨምሮ በአራት ክልሎች የዕጩዎች ምዝገባ ዛሬ ይጀመራል
አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ኦሮሚያ እና ሐረሪ ክልሎች የዕጩዎች ምዝገባ ዛሬ ይጀመራል።
ምዝገባው የሚከናወነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለዕጩዎች ምዝገባ ባወጣው ከየካቲት 08 እስከ የካቲት 21 ቀን 2013 ዓ.ም የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ነው።
የምርጫ ክልሎቹ በተጠቀሱት ጊዜያት የዕጩዎች ምዝገባ የሚያከናውኑት ለምርጫ ክልል እና ለዞን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሊያገለግሉ የሚችሉ ቢሮዎችን በማዘጋጀታቸው መሆኑን ቦርዱ ገልጿል።
በአፋር፣ አማራ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ እና ሶማሌ ክልሎች ከየካቲት 05 እስከ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ለዕጩዎች ምዝገባ የሚውሉ ቁሳቁሶች እንደሚጓጓዙ እና የዕጩዎች ምዝገባ አስፈጻሚዎች ሥልጠና እንደሚሰጥም ቦርዱ አመልክቷል።
ከየካቲት 15 እስከ 26 ቀን 2013 ዓ.ም ደግሞ የዕጩዎች ምዝገባ እንደሚከናወን ቦርዱ ባለፈው ሳምንት መወሰኑ ይታወሳል።
Via:- EBC
@Yenetube @Fikerassefa
አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ኦሮሚያ እና ሐረሪ ክልሎች የዕጩዎች ምዝገባ ዛሬ ይጀመራል።
ምዝገባው የሚከናወነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለዕጩዎች ምዝገባ ባወጣው ከየካቲት 08 እስከ የካቲት 21 ቀን 2013 ዓ.ም የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ነው።
የምርጫ ክልሎቹ በተጠቀሱት ጊዜያት የዕጩዎች ምዝገባ የሚያከናውኑት ለምርጫ ክልል እና ለዞን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሊያገለግሉ የሚችሉ ቢሮዎችን በማዘጋጀታቸው መሆኑን ቦርዱ ገልጿል።
በአፋር፣ አማራ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ እና ሶማሌ ክልሎች ከየካቲት 05 እስከ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ለዕጩዎች ምዝገባ የሚውሉ ቁሳቁሶች እንደሚጓጓዙ እና የዕጩዎች ምዝገባ አስፈጻሚዎች ሥልጠና እንደሚሰጥም ቦርዱ አመልክቷል።
ከየካቲት 15 እስከ 26 ቀን 2013 ዓ.ም ደግሞ የዕጩዎች ምዝገባ እንደሚከናወን ቦርዱ ባለፈው ሳምንት መወሰኑ ይታወሳል።
Via:- EBC
@Yenetube @Fikerassefa
ጊኒ የኢቦላ ወረርሽኝ መከሰቱን ይፋ አደረገች
ጊኒ በኢቦላ ወረርሽኝ የሶስት ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ ቫይረሱ በወረርሽኝ ደረጃ መከሰቱን ይፋ አደረገች።
በጊኒ ደቡብ ምስራቅ በተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ለህልፈት ከተዳረጉት ሰዎች ባሻገር አራት ሰዎች ደግሞ ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ተነግሯል።
በደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል በምትገኘው ጎዋኬ በአንድ የቀብር ስነ ስርዓት ላይ የተሳተፉ 7 ሰዎች የማስመለስ፣ የመድማት እና ማስቀመጥ እንዳጋጠማቸው ተጠቁሟል።
የኢቦላ ቫይረስ የተገኘባቸው እነዚህ ሰዎች አሁን ላይ በለይቶ ማቆያ እንደሚገኙ የጊኒ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
የጤና ሚኒስትሩ ሬሜይ ላማህ የሀገሪቱ ባለስልጣናት በኢቦላ ተከሰተው ሞት በእጅጉ እንዳሳሰባቸው መናገራቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።
Via:- FBC
@YeneTube @Fikerassefa
ጊኒ በኢቦላ ወረርሽኝ የሶስት ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ ቫይረሱ በወረርሽኝ ደረጃ መከሰቱን ይፋ አደረገች።
በጊኒ ደቡብ ምስራቅ በተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ለህልፈት ከተዳረጉት ሰዎች ባሻገር አራት ሰዎች ደግሞ ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ተነግሯል።
በደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል በምትገኘው ጎዋኬ በአንድ የቀብር ስነ ስርዓት ላይ የተሳተፉ 7 ሰዎች የማስመለስ፣ የመድማት እና ማስቀመጥ እንዳጋጠማቸው ተጠቁሟል።
የኢቦላ ቫይረስ የተገኘባቸው እነዚህ ሰዎች አሁን ላይ በለይቶ ማቆያ እንደሚገኙ የጊኒ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
የጤና ሚኒስትሩ ሬሜይ ላማህ የሀገሪቱ ባለስልጣናት በኢቦላ ተከሰተው ሞት በእጅጉ እንዳሳሰባቸው መናገራቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።
Via:- FBC
@YeneTube @Fikerassefa