እራሳቸውን ለይተው የነበሩት የራይድ አሽከርካሪዎች ከኮረናነጻ መሆናቸው ተነገረ
አዲስ አበባ ውስጥ ዘመናዊ የታክሲ አገልግሎት የሚሰጠው የራይድ ሁለት አሽከርካሪዎች የኮሮናቫይረስ ጥርጣሬ አድሮባቸው እራሳቸውን ለይተው ከቆዩ በኋላ በተደረገላቸው ምርምራ ነጻ ሆኑ ሲል ድርጅቱ አስታወቀ።
የራይድ ታክሲ መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳምራዊት ፍቅሩ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ያሳፈሩትን ሰው በመጠርጠራቸው እራሳቸውን ለይተው የቆዩት ሁለት ሾፌሮች እንደነበሩ፤ ነገር ግን ሁለቱም ተመርምረው ነጻ ሆነው መገኘታቸውን ተናግረዋል።
ራይድ አስራ አምስት ሺህ ሾፌሮችን በመያዝ አገልግሎት እንደሚሰጥ የተናገሩት ሥራ አስፈጻሚዋ፤ የኮሮናቫይረስ በአዲስ አበባ ውስጥ መገኘቱን ተከትሎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ጨምረውም ሾፌሮች ከተሳፋሪ ጋር ስለሚኖራቸው ግንኙነት እንዲሁም የእጃቸውንና የመኪናቸውን ንጽህና በጸረ ተህዋሲያን እንዴት መጠበቅ እንዳለባቸው እንደሚያስተምሩ ጠቅሰዋል።
ከዚህ ባሻገርም የተሳፋሪዎችንም ሆነ የሾፌሮችን ጤንንት ለመጠበቅ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብልና ጓንት እንዲጠቀሙ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
-BBC
@Yenetube @Fikerassefa
አዲስ አበባ ውስጥ ዘመናዊ የታክሲ አገልግሎት የሚሰጠው የራይድ ሁለት አሽከርካሪዎች የኮሮናቫይረስ ጥርጣሬ አድሮባቸው እራሳቸውን ለይተው ከቆዩ በኋላ በተደረገላቸው ምርምራ ነጻ ሆኑ ሲል ድርጅቱ አስታወቀ።
የራይድ ታክሲ መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳምራዊት ፍቅሩ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ያሳፈሩትን ሰው በመጠርጠራቸው እራሳቸውን ለይተው የቆዩት ሁለት ሾፌሮች እንደነበሩ፤ ነገር ግን ሁለቱም ተመርምረው ነጻ ሆነው መገኘታቸውን ተናግረዋል።
ራይድ አስራ አምስት ሺህ ሾፌሮችን በመያዝ አገልግሎት እንደሚሰጥ የተናገሩት ሥራ አስፈጻሚዋ፤ የኮሮናቫይረስ በአዲስ አበባ ውስጥ መገኘቱን ተከትሎ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ጨምረውም ሾፌሮች ከተሳፋሪ ጋር ስለሚኖራቸው ግንኙነት እንዲሁም የእጃቸውንና የመኪናቸውን ንጽህና በጸረ ተህዋሲያን እንዴት መጠበቅ እንዳለባቸው እንደሚያስተምሩ ጠቅሰዋል።
ከዚህ ባሻገርም የተሳፋሪዎችንም ሆነ የሾፌሮችን ጤንንት ለመጠበቅ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብልና ጓንት እንዲጠቀሙ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
-BBC
@Yenetube @Fikerassefa
ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ንግድ እና መምሪያ ቤት የተላከ ⬆️
ጭፈራ ቤቶችን በተመለከተ ይህ ደብዳቤ ከደረሳችሁ ቀን ጀምሮ ቤታችሁን እንድትዘጉ የሚል ማሳሰቢያ አስተላልፏል ምክንያቱም የአለም ስጋት የሆነውን ኮሮና ቫይረስን ለመከላከ መሆኑን በደብዳቤ ላይ ተገልጷል ።
@Yenetube @Fikerassefa
ጭፈራ ቤቶችን በተመለከተ ይህ ደብዳቤ ከደረሳችሁ ቀን ጀምሮ ቤታችሁን እንድትዘጉ የሚል ማሳሰቢያ አስተላልፏል ምክንያቱም የአለም ስጋት የሆነውን ኮሮና ቫይረስን ለመከላከ መሆኑን በደብዳቤ ላይ ተገልጷል ።
@Yenetube @Fikerassefa
የቦትስዋና ፕሬዝዳንት ኤሪክ ሞጊዚሲ ማሳሲ ለአራት ቀናት ራሳቸውን ማግለል በለይቶ ማቆያ ውስጥ ማድረግ መጀመራቸውን መንግሥት በፕሬዚዳንቱ ጽህፈት ቤት በኩል በዛሬው እለት አስታውቋል ፡፡
ራስን ማግለል ውሳኔው የመጣው ለስራ ጉዞ ወደ ጎረቤት ናሚቢያ ሄደው ከተመለሱ በኋላ ነው ፡፡ በዊንሆክ ፕሬዝዳንት ሀጌ ጂንግቦ በተደረገው ቃለ መሀላ ላይ ተገኝተዋል።
- CGTN
@YENETUBE @Fikerassefa
ራስን ማግለል ውሳኔው የመጣው ለስራ ጉዞ ወደ ጎረቤት ናሚቢያ ሄደው ከተመለሱ በኋላ ነው ፡፡ በዊንሆክ ፕሬዝዳንት ሀጌ ጂንግቦ በተደረገው ቃለ መሀላ ላይ ተገኝተዋል።
- CGTN
@YENETUBE @Fikerassefa
👍1
በአዲስ አበባ ለረዥም ጊዜ መንገድ ዳር የቆሙ ተሽከርካሪዎችን የማስነሳት ስራ ጀመረ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ለመንገድ ትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት ከሆኑ ነገሮች መካከል በየጎዳናዎቹ ላይ ያለአግባብ ለረዥም ጊዜ የሚቆሙ የንግድ ፣ በብልሽት እና በተለያዩ ምክንያቶች የሚቆሙ ተሽከርካሪዎች ተጠቃሽ ናቸው፡፡የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ችግሩን ለመቅረፍ የሚያስችል ተግባር በመጀመሩ መንገድ ዳር የቆሙ ተሽከርካሪዎችን ከመጋቢት 3/2012 ዓ.ም ጀምሮ እያስነሳ ይገኛል፡፡
ኤጀንሲው ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን እና ከከተማዋ የሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ደንብ ማስከበር አገልግሎት ዘርፍ ጋር በመተባበር ሲሆን የተሽከርካሪዎቹ ባለቤቶች ንብረቶቻቸውን ከመንገድ ዳር እንዲያስነሱ ከአምስት እስከ ሰባት ቀን ጊዜ ማስታወቂያ ከተለጠፈ በኃላ በክሬን የማስነሰቱን ስራ እየተከናወነ ነው፡፡ከየመንገዱ ዳር በክሬን የሚነሱ ተሽከርካሪዎች ለሚቆዩበት ሶስት ቦታዎች የተዘጋጁ ሲሆን እስከ አሁን ስምንት ተሽከርካሪዎች ተነስተዋል፡፡
የተሽከርካሪ ባለቤቶቹ በሚሰጣቸው የጊዜ ገደብ ተሽከርካሪዎቻቸውን የማያስነሱ ከሆነ ተሽከርካሪዎቹ በሚነሱበት ወቅት ለሚደርስባቸው ጉዳቶች ኤጀንሲው ተጠያቂ የማይሆን ሲሆን ለክሬን ማስነሻ ኪራይ ክፍያ፣ ተሽከርካሪዎቹ ለሚቆዩበት ቦታ የፓርኪንግ እና የጥበቃ አገልግሎት ክፍያን ጨምሮ ባለንብረቶች ይከፍላሉ፡፡ በቀጣይም በከተማዋ በተለያዩ ቦታዎች በተለያዩ ምክንያቶች ለረዥም ጊዜ መንገድ ዳር ቆመው የሚገኙ ተሽከርካሪዎችን የማስነሳቱ ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ተብሏል።
ምንጭ: የከ/መ/ ፕሬስ ሴክሬተሪያት
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ ለመንገድ ትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት ከሆኑ ነገሮች መካከል በየጎዳናዎቹ ላይ ያለአግባብ ለረዥም ጊዜ የሚቆሙ የንግድ ፣ በብልሽት እና በተለያዩ ምክንያቶች የሚቆሙ ተሽከርካሪዎች ተጠቃሽ ናቸው፡፡የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ችግሩን ለመቅረፍ የሚያስችል ተግባር በመጀመሩ መንገድ ዳር የቆሙ ተሽከርካሪዎችን ከመጋቢት 3/2012 ዓ.ም ጀምሮ እያስነሳ ይገኛል፡፡
ኤጀንሲው ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን እና ከከተማዋ የሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ደንብ ማስከበር አገልግሎት ዘርፍ ጋር በመተባበር ሲሆን የተሽከርካሪዎቹ ባለቤቶች ንብረቶቻቸውን ከመንገድ ዳር እንዲያስነሱ ከአምስት እስከ ሰባት ቀን ጊዜ ማስታወቂያ ከተለጠፈ በኃላ በክሬን የማስነሰቱን ስራ እየተከናወነ ነው፡፡ከየመንገዱ ዳር በክሬን የሚነሱ ተሽከርካሪዎች ለሚቆዩበት ሶስት ቦታዎች የተዘጋጁ ሲሆን እስከ አሁን ስምንት ተሽከርካሪዎች ተነስተዋል፡፡
የተሽከርካሪ ባለቤቶቹ በሚሰጣቸው የጊዜ ገደብ ተሽከርካሪዎቻቸውን የማያስነሱ ከሆነ ተሽከርካሪዎቹ በሚነሱበት ወቅት ለሚደርስባቸው ጉዳቶች ኤጀንሲው ተጠያቂ የማይሆን ሲሆን ለክሬን ማስነሻ ኪራይ ክፍያ፣ ተሽከርካሪዎቹ ለሚቆዩበት ቦታ የፓርኪንግ እና የጥበቃ አገልግሎት ክፍያን ጨምሮ ባለንብረቶች ይከፍላሉ፡፡ በቀጣይም በከተማዋ በተለያዩ ቦታዎች በተለያዩ ምክንያቶች ለረዥም ጊዜ መንገድ ዳር ቆመው የሚገኙ ተሽከርካሪዎችን የማስነሳቱ ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ተብሏል።
ምንጭ: የከ/መ/ ፕሬስ ሴክሬተሪያት
@YeneTube @FikerAssefa
አል ኢምራን መስጂድ አስተዳደር የተወሰዱ እርምጃዎች :-
-ለሰላት መስጂድ ስንመጣ በየመሃላችን ሁለት ሰው ሊያሰግድ የሚችል ቦታ ርቀት አድርገን መቆም።
-ወደ መስጂድ ስንገባ እጃችንን በሳሙና ታጥበን መግባት።
- መስጂድ ሲመጣ ህፃናትን ይዞ አለመምጣት።
-ሰላምታ በቃላት መለዋወጥ....የመሳሰሉት
እርምጃዎች ተውስደዋል ሁላችንም ብንተገብረው መልካም ነው።
@Yeneyube @FikerAssefa
-ለሰላት መስጂድ ስንመጣ በየመሃላችን ሁለት ሰው ሊያሰግድ የሚችል ቦታ ርቀት አድርገን መቆም።
-ወደ መስጂድ ስንገባ እጃችንን በሳሙና ታጥበን መግባት።
- መስጂድ ሲመጣ ህፃናትን ይዞ አለመምጣት።
-ሰላምታ በቃላት መለዋወጥ....የመሳሰሉት
እርምጃዎች ተውስደዋል ሁላችንም ብንተገብረው መልካም ነው።
@Yeneyube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 11 አራብሳ ለሚ ኮብልስቶን ማምረቻ አከባቢ ስኳር እና ኬሚካል ከቀይ አፈር ጋር በመቀላቀል ማር ነው ብሎ ለመሸጥ ሲያዘጋጅ የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።
ግለሰቡ ሙሉ መኖሪያ ግቢ ተከራይቶ ህገ - ወጥ ተግባሩን ሲፈፅም በቁጥጥር ስር ሊውል የቻለው ፖሊስ በጥርጣሬ ባደረገው ማጣራት ነው ፡፡በቦሌ አራብሳ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል መከላከል አባል ሳጅን ድንበሩ ጥላሁን እንደገለፁት ለስራ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ከፍተኛ ጭስ ከግቢው ሲወጣ ተመልክተው ሲጠይቁ እንጀራ እየጋገርን ነው የሚል ምላሽ ቢሰጣቸውም ተጠራጥረው ባደረጉት ማጣራት ህገ- ወጥ ድርጊት እየተፈፀመ መሆኑን በማረጋገጥ ለሚመለከተው የአስተዳደር አካል ሪፖርት አድርገዋል፡፡
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘም አንድ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት ይገኛል ብለዋል፡፡በቦሌ ክ/ከተማ የወረዳ 11 ንግድና ኢንዱስትሪ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ አድነው ወልዴ በበኩላቸው ግለሰቡ መርካቶን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ማር ነው ብሎ ያዘጋጀውን ባዕድ ነገር ሲሸጥ እንደቆየ ገልፀዋል፡፡
Via Addis Ababa Police Commission
@YeneTube @FikerAssefa
ግለሰቡ ሙሉ መኖሪያ ግቢ ተከራይቶ ህገ - ወጥ ተግባሩን ሲፈፅም በቁጥጥር ስር ሊውል የቻለው ፖሊስ በጥርጣሬ ባደረገው ማጣራት ነው ፡፡በቦሌ አራብሳ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል መከላከል አባል ሳጅን ድንበሩ ጥላሁን እንደገለፁት ለስራ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ከፍተኛ ጭስ ከግቢው ሲወጣ ተመልክተው ሲጠይቁ እንጀራ እየጋገርን ነው የሚል ምላሽ ቢሰጣቸውም ተጠራጥረው ባደረጉት ማጣራት ህገ- ወጥ ድርጊት እየተፈፀመ መሆኑን በማረጋገጥ ለሚመለከተው የአስተዳደር አካል ሪፖርት አድርገዋል፡፡
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘም አንድ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት ይገኛል ብለዋል፡፡በቦሌ ክ/ከተማ የወረዳ 11 ንግድና ኢንዱስትሪ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ አድነው ወልዴ በበኩላቸው ግለሰቡ መርካቶን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ማር ነው ብሎ ያዘጋጀውን ባዕድ ነገር ሲሸጥ እንደቆየ ገልፀዋል፡፡
Via Addis Ababa Police Commission
@YeneTube @FikerAssefa
በጋምቤላ ኤርፖርት እስካሁን የመንገደኞች ሙቀት እየተለካ አለመሆኑ ተገለጸ።
በቀን ሁለት ጊዜ ማለትም ከአዲስ አበባ በአሶሳ አድርጎ ወደ ጋምቤላ እና ከጋምቤላ ወደ አዲስ አበባ የሚደረገው የሃገር ውስጥ በረራ እንደቀጠለ ነው፡፡ነገር ግን ተጓዦች ከጋምቤላ ተነስተው ወደ አዲስ አበባ ሊሄዱ ሲሉ እንዲሁም ከ አዲስ አበባ ወደ ጋምቤላ የሚገቡ ተጓዞች ወደ አየር ጣቢያው ሲደርሱ ምንም አይነት የሙቀት መለኪያ እየተደረገላቸው እንዳልሆነ የክልሉ ጤና ቢሮ ሃላፊ ካን ጋሏክ ተናግረዋል፡፡ምንም እንኳን ክልሉ አምስት የሙቀት መለኪያ ማሽኖች እንዲኖሩት ቢደረግም እነዚህን ማሽኖች ከ ደቡብ ሱዳን ጋን በሚዋሰኑ አምስት ጣቢያዎች እንዲከፋፈሉ መደረጉን ነግረውናል፡፡ይሁን እንጂ ይህ መሳሪያ በ ከተማው በሚገኘው ኤርፖርት ተግባራዊ ያለመደረጉ ወረርሽኙን ለመከላከል እየተሰራ ያለውን የጥንቃቄ ስራ እንደሚያጎድል ሃላፊው ገልጸዋል። በተጨማሪም መሳሪያውን ወደ ስፍራው ለማስገባት ጥረቶች ማድረጋችን መቀጠላቸውም ሃላፊው ተናግረዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በቀን ሁለት ጊዜ ማለትም ከአዲስ አበባ በአሶሳ አድርጎ ወደ ጋምቤላ እና ከጋምቤላ ወደ አዲስ አበባ የሚደረገው የሃገር ውስጥ በረራ እንደቀጠለ ነው፡፡ነገር ግን ተጓዦች ከጋምቤላ ተነስተው ወደ አዲስ አበባ ሊሄዱ ሲሉ እንዲሁም ከ አዲስ አበባ ወደ ጋምቤላ የሚገቡ ተጓዞች ወደ አየር ጣቢያው ሲደርሱ ምንም አይነት የሙቀት መለኪያ እየተደረገላቸው እንዳልሆነ የክልሉ ጤና ቢሮ ሃላፊ ካን ጋሏክ ተናግረዋል፡፡ምንም እንኳን ክልሉ አምስት የሙቀት መለኪያ ማሽኖች እንዲኖሩት ቢደረግም እነዚህን ማሽኖች ከ ደቡብ ሱዳን ጋን በሚዋሰኑ አምስት ጣቢያዎች እንዲከፋፈሉ መደረጉን ነግረውናል፡፡ይሁን እንጂ ይህ መሳሪያ በ ከተማው በሚገኘው ኤርፖርት ተግባራዊ ያለመደረጉ ወረርሽኙን ለመከላከል እየተሰራ ያለውን የጥንቃቄ ስራ እንደሚያጎድል ሃላፊው ገልጸዋል። በተጨማሪም መሳሪያውን ወደ ስፍራው ለማስገባት ጥረቶች ማድረጋችን መቀጠላቸውም ሃላፊው ተናግረዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በኮሮናቫይረስ ስርጭት ስጋት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር-ኦነግ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ቢሮውን መዝጋቱን አስታወቀ።
ምንጭ: ቢቢሲ
@YeneTube @FikerAssefa
ምንጭ: ቢቢሲ
@YeneTube @FikerAssefa
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ እና አፍጋኒስታን የኮሮና ቫይረስ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ መቀነስ የሚያስችል ድጋፍ ሊያጸድቅ ነው!
የዓለም ባንክ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ40 ሃገራት የኮሮና ቫይረስ የሚያደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ መቀነስና መከላከል የሚያስችል የ1 ነጥብ 7 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።ድጋፉ ኢትዮጵያና አፍጋኒስታንን ጨምሮ በሃገራቱ የኮሮና ቫይረስ የሚያደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖና ጉዳት ለመቀነስ ያለመ ነው ተብሏል።
የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድም በዚህ ሳምንት ለኢትዮጵያ እና አፍጋኒስታን ድጋፍ ለማድረግ የቀረበውን ሰነድ ተመልከቶ እንደሚያጸድቅ ነው የሚጠበቀው።ድጋፉ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ባንኩ ለአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ በሚል ባለፈው ሳምንት ካጸደቀው 14 ቢሊየን ዶላር ለሃገራቱ የሚሰጥ መሆኑን የባንኩ ፕሬዚዳንት ዴቪድ ማልፓስ አስታውቀዋል።
ባንኩ ባለፈው ሳምንት ዓለም ላይ የኮሮና ቫይረስ የሚያስከትለውን ተፅዕኖ መቀነስና መከላከል የሚያስችል የ14 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ ማፅደቁ ይታወሳል።ከዚህ ባለፈም ባንኩ ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ትብብርና ከባንኩ የግሉ ሴክተር ዘርፍ ጋር በመሆን በ24 ሃገራት ተግባራዊ የሚደረግ የ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ፕሮጀክት ለመተግበር እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
የዓለም ባንክ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ40 ሃገራት የኮሮና ቫይረስ የሚያደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ መቀነስና መከላከል የሚያስችል የ1 ነጥብ 7 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።ድጋፉ ኢትዮጵያና አፍጋኒስታንን ጨምሮ በሃገራቱ የኮሮና ቫይረስ የሚያደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖና ጉዳት ለመቀነስ ያለመ ነው ተብሏል።
የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድም በዚህ ሳምንት ለኢትዮጵያ እና አፍጋኒስታን ድጋፍ ለማድረግ የቀረበውን ሰነድ ተመልከቶ እንደሚያጸድቅ ነው የሚጠበቀው።ድጋፉ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ባንኩ ለአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ በሚል ባለፈው ሳምንት ካጸደቀው 14 ቢሊየን ዶላር ለሃገራቱ የሚሰጥ መሆኑን የባንኩ ፕሬዚዳንት ዴቪድ ማልፓስ አስታውቀዋል።
ባንኩ ባለፈው ሳምንት ዓለም ላይ የኮሮና ቫይረስ የሚያስከትለውን ተፅዕኖ መቀነስና መከላከል የሚያስችል የ14 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ ማፅደቁ ይታወሳል።ከዚህ ባለፈም ባንኩ ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ትብብርና ከባንኩ የግሉ ሴክተር ዘርፍ ጋር በመሆን በ24 ሃገራት ተግባራዊ የሚደረግ የ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ፕሮጀክት ለመተግበር እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
የእርዳታ ጥሪ !
የእህታችንን ህይወት የጓጓችለትን ምርቃቷን ሳታይ እንዳትቀጠፍብን የተማሪነት ድርሻችንን እንወጣ።
ምርቃቷን በጉጉት የምትተብቀው ቤተልሄም ተስፋዬ ዛሬ ጥቁር አንበሳ ተኝታ እህት ወንድሞቼ ህይወቴን ታደጓት እያለች የ እርዳታ ጥሪ ታስተላልፋች። በቻልነው አቅም በየትምህርት ክፍላችን በመልቀቅ የ እህታችንን ህይወት እንታደግ።
ዛሬ ብቻ በ ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ጊቢ 12,921 ብር (አስራ ሁለት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሃያ አንድ ብር) መሰብሰብ ችሏል። ቀጣይ የታሰቡ ስራዎች በመላው ኢትዮጵያ ማስታወቂያ በመስራት የእህታችንን ህይወት እንታደጋለን።
በ አጠቃላይ ለህክምናው የሚያስፈልጋት ወጪ 50,000$ በ ሃገር ደረጃ 1,645,551 ማለትም አንድ ሚሊየን ስድስት መቶ አርባ አምስት ሺ አምስት መቶ ሃምሳ አንድ ብር ነው። በምንጠቀመው ማህበራዊ ሚዲያዎች በመልቀቅ እህታችን የደረሰባትን ህመም በማስተዋወቅ እንታደጋት።
ቤቲየ ተመርቀሽ ስትስቂ እናይሻለን እሺ እህት አለም። ለወገን ደራሽ ወገን ነው።
የንግድ ባንክ አካውንት
- 1000326460568
@Yenetube @Fikerassefa
የእህታችንን ህይወት የጓጓችለትን ምርቃቷን ሳታይ እንዳትቀጠፍብን የተማሪነት ድርሻችንን እንወጣ።
ምርቃቷን በጉጉት የምትተብቀው ቤተልሄም ተስፋዬ ዛሬ ጥቁር አንበሳ ተኝታ እህት ወንድሞቼ ህይወቴን ታደጓት እያለች የ እርዳታ ጥሪ ታስተላልፋች። በቻልነው አቅም በየትምህርት ክፍላችን በመልቀቅ የ እህታችንን ህይወት እንታደግ።
ዛሬ ብቻ በ ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ጊቢ 12,921 ብር (አስራ ሁለት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሃያ አንድ ብር) መሰብሰብ ችሏል። ቀጣይ የታሰቡ ስራዎች በመላው ኢትዮጵያ ማስታወቂያ በመስራት የእህታችንን ህይወት እንታደጋለን።
በ አጠቃላይ ለህክምናው የሚያስፈልጋት ወጪ 50,000$ በ ሃገር ደረጃ 1,645,551 ማለትም አንድ ሚሊየን ስድስት መቶ አርባ አምስት ሺ አምስት መቶ ሃምሳ አንድ ብር ነው። በምንጠቀመው ማህበራዊ ሚዲያዎች በመልቀቅ እህታችን የደረሰባትን ህመም በማስተዋወቅ እንታደጋት።
ቤቲየ ተመርቀሽ ስትስቂ እናይሻለን እሺ እህት አለም። ለወገን ደራሽ ወገን ነው።
የንግድ ባንክ አካውንት
- 1000326460568
@Yenetube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና የሊግ ካምፓኒ ዛሬ ከሰዓት በፌዴሬሽኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ መቋረጡን ይፋ አድርገዋል፡፡
ክለቦችም ተጫዋቾችን ለመጠበቅ በዚህ ጊዜ ልምምዶችን ማቋረጥ እንዳለባቸው የእግር ኳሱ አስተዳዳሪው አካል አሳውቋል፡፡
በደብረዘይት በሚገኘው የክቡር ይድነቃቸው ተሰማ አካዳሚ ለፕሪሚየር ሊጉ ዝግጅታቸውን ሲያደርጉ የነበሩት ቅዱስ ጊዮርጊሶች በኮሮና ስጋት ምክንያት ልምምዳቸውን ከነገ ጀምሮ እንደሚያቆሙ ከክለቡ የወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡
via:- Hatric Sport
@Yenetube @Fikerassefa
ክለቦችም ተጫዋቾችን ለመጠበቅ በዚህ ጊዜ ልምምዶችን ማቋረጥ እንዳለባቸው የእግር ኳሱ አስተዳዳሪው አካል አሳውቋል፡፡
በደብረዘይት በሚገኘው የክቡር ይድነቃቸው ተሰማ አካዳሚ ለፕሪሚየር ሊጉ ዝግጅታቸውን ሲያደርጉ የነበሩት ቅዱስ ጊዮርጊሶች በኮሮና ስጋት ምክንያት ልምምዳቸውን ከነገ ጀምሮ እንደሚያቆሙ ከክለቡ የወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡
via:- Hatric Sport
@Yenetube @Fikerassefa
በመላው ዓለም የተስፋፋውን የኮሮና ወረርሽኝ ለመግታት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ
በሀገራችን ኢትዮጵያ በገጠር፣ በከተማና በመላው ዓለም ለምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን በሙሉ!
ወቅታዊ የሰው ልጅ ሥጋት በመሆን በመላው ዓለም በፍጥነት በተስፋፋው የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ዓለም አቀፍ ሥጋት ስለተከሰተ መንግሥታት ሀገርን ከጥፋት፣ ሕዝብን ከሞት ለመጠበቅ አዋጆችን እያወጡ ይገኛሉ፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ለመታደግ እምነትና ቀኖናን ጠብቆ ሃይማኖታዊ መመሪያ የመስጠት ሐዋርያዊ ኃላፊነት አለባት፡፡
ስለዚህ ቋሚ ሲኖዶስ የጉዳዩን አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት መሠረተ እምነትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ጠብቆ ለሁሉም ካህናትና ለሕዝበ እግዚአብሔር ደኅንነት ሲባል የሚከተሉትን መመሪያዎች አስተላልፏል፡-
1. በሰሙነ ሕማማት እንደምናደርገው የእርስ በርስ መሳሳም ቀርቶ ራስን ዝቅ በማድረግ፣ እጅ በመንሳት ወይም በእማሄ ሰላምታ በማቅረብ እንዲፈጸም፣
2. ወረርሽኙ በሰዎች መሰባሰብ የሚስፋፋ ስለሆነ ማናቸውም መንፈሳዊ ጉባኤያት፣ የትምህርት ክፍለ ጊዜያት፣ ወደ ገዳማትና አድባራት የሚደረጉ ጉዞዎች እና ምዕመናን የሚሳተፉባቸው ታላላቅ መርሐ ግብሮች ለጊዜው እንዲቋረጡ፣
3. ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲገባም ሆነ አሰፈላጊ በሆነበት ጊዜ ሁሉ እጆቻንን በመታጠብና ዘርዘር ብሎ በመቆም ሥርዓተ አምልኮ እንዲፈጸም፣
4. ዓመታዊ የንግሥ ክብረ በዓላት በቅዳሴና በማኅሌት ታስበው ክብረ በዓላቱ በሌላ ጊዜ እንዲከበሩ፣
5. የጉንፋን ምልክት ያለባቸው ለሌሎች እንዳያስተላልፉ በቤታቸው በጥንቃቄ ተለይተው በጸሎትና በሕክምና እንዲቆዩ፣ ከቤተ ክርስቲያን የሚያስፈልጋቸውን መንፈሳዊ አገልግሎትም በልዩ ሁኔታ እንዲያገኙ፣
6. በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ የተቋቋመው ግብረ ኃይል የተስፋ ልዑክ በመሆን እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ተደራጅቶ ተልዕኮውን በአስቸኳይ እንዲጀምር
7. ሥርዓተ ቅዳሴን በተመለከተ፡-
• በቤተ መቅደስ ቀዳስያን በሆኑት ልዑካን ብቻ ሥርዓተ ቅዳሴው እንዲፈጸምና ሌሎች አገልጋዮች በቅድስቱ ዘርዘር ብለው በመቆም እንዲያገለግሉ፣
• በዕለቱ ለሚቆርቡ ምዕመናን ለአረጋውያን፣ ለወጣቶችና ለሕፃናት የፈረቃ ተራ በማዘጋጀት ቆራቢዎች ብቻ ወደ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ገብተው ዘርዘር ብለው በመቆም እንዲያስቀድሱ፣
• ሌሎች ምእመናን በአጸደ ቤተክርስቲያን ቢያንስ ሁለት የትልቅ ሰው እርምጃ ያህል በመራራቅ ቆመው እንዲያስቀድሱ፣
• የቅዳሴ ጠበል በየግል መጠቀሚያ ምእመናን በየቆሙበት ቦታ በጥንቃቄ እንዲሰጥ፣
• ሌሎች ከቅዳሴ ጋር የተያያዙ ዝርዝር የአፈፃፀም ጉዳዮችን ግብረ ኃይሉ አዘጋጅቶ በቅዱስ ሲኖዶስ በማጸደቅ ለአህጉረ ስብከት በሚልከው መመሪያ መሠረት ተግባራዊ እንዲደረግ፤
8. ከሥርዓተ ቅዳሴ በተጨማሪ እንደ ስብሐተ ነግሕ፣ ሰዓታት፣ ቁመተ ማኅሌት፣ ጥምቀተ ክርስትና፣ ጸሎተ ፍትሐት፣ የመሳሰሉ አገልግሎቶች ለሥርዓቱ በሚያስፈልገው ቁጥር ብቻ እና በውሱን ሊቃውንት በተራ እንዲፈፀም፣
9. ወረርሽኙ ከዓለም እንዲጠፋ ካህናት ብቻ በቤተ መቅደስ፣ በዐውደ ምኅረትና በአጸደ ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ጸሎተ እጣን በማድረስ ማዕጠንት እንዲፈጽሙ፣
10. በማኅበራዊ ግንኙነት በደስታ፣ በሐዘን፣ በእድር፣ በሥርዓተ ቀብር አፈፃፀምና በመሳሰሉት መሰባሰቦች በሽታው እንዳይሠራጭ አገልግሎቱ በውስን የሰው ቁጥር በጥንቃቄ እንዲፈፀም፤
11. ምዕመናን ራሳቸውን እየጠበቁ በቫይረሱ የተጠቁና አገግመው የወጡ ወገኖችን፣ እንዲሁም በውጭ ሀገር ዜጎች ላይ ከሃይማኖትና ከምግባር የወጣ መገለልና ጥቃት እንዳይደርስባቸው በክርስቲያናዊ ፍቅርና በኢትጵያዊ ጨዋነት እንክብካቤ እንዲደረግላቸው፣
12. ለነዳያን እና ለተቸገሩ ወገኖች አስፈላጊው ማኅበራዊ እና ቁሳዊ እገዛ በሁሉም አጥቢያዎች እንዲደረግ፣
13. ቤተ ክርስቲያንን ከማይወክሉና ቀኖናዊ ካልሆኑ አሳሳች መረጃዎች በመቆጠብ ሊቃውንት፣ ካህናት፣ መምህራን፣ ሰባክያን፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ከቅዱስ ሲኖዶስ የሚሰጡ መመሪያዎችን በየአጥቢያችሁና አስፈላጊ በሆኑ ቦታዎች ሁሉ እንድትፈጽሙ እና እንድታስፈጽሙ ተወስኗል፡፡
በአጠቃላይ በበሽታው እስካሁን ለተያዙት፣ በጊዜያዊ ማቆያ ለሚገኙት በሙሉ እግዚአብሔር አምላካችን ምህረቱን እንዲሰጥልን እንጸልያለን፤
በመላው ዓለም ዜጎቻቸውን በበሽታው ለተነጠቁ ሁሉ መጽናናቱን እንዲሰጥልን ያረፉትንም እንዲምርልን እግዚአብሔርን በጸሎት እንጠይቃለን፤
በመላው ዓለም የምትገኙ ወገኖቻችን የራሳችሁና የሌሎች ሕይወት ከወረርሽኙ እንዲጠበቅ እንዲሁም የበሽታው ሥርጭት እንዲቆም መንፈሳዊና ማኅበራዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እያሳሰብን የተሰጡት መመሪያዎች ወረርሽኙ እስኪጠፋ ድረስ የጸኑ እንዲሆኑ በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡
ልዑል እግዚአብሔር በቸርነቱና በይቅርታው ብዛት ዓለማችንን ከጥፋት የሰውን ልጅ ሁሉ ከመከራ ሞት ይጠብቅልን፡፡ አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ.ም
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በሀገራችን ኢትዮጵያ በገጠር፣ በከተማና በመላው ዓለም ለምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን በሙሉ!
ወቅታዊ የሰው ልጅ ሥጋት በመሆን በመላው ዓለም በፍጥነት በተስፋፋው የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ዓለም አቀፍ ሥጋት ስለተከሰተ መንግሥታት ሀገርን ከጥፋት፣ ሕዝብን ከሞት ለመጠበቅ አዋጆችን እያወጡ ይገኛሉ፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ለመታደግ እምነትና ቀኖናን ጠብቆ ሃይማኖታዊ መመሪያ የመስጠት ሐዋርያዊ ኃላፊነት አለባት፡፡
ስለዚህ ቋሚ ሲኖዶስ የጉዳዩን አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት መሠረተ እምነትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ጠብቆ ለሁሉም ካህናትና ለሕዝበ እግዚአብሔር ደኅንነት ሲባል የሚከተሉትን መመሪያዎች አስተላልፏል፡-
1. በሰሙነ ሕማማት እንደምናደርገው የእርስ በርስ መሳሳም ቀርቶ ራስን ዝቅ በማድረግ፣ እጅ በመንሳት ወይም በእማሄ ሰላምታ በማቅረብ እንዲፈጸም፣
2. ወረርሽኙ በሰዎች መሰባሰብ የሚስፋፋ ስለሆነ ማናቸውም መንፈሳዊ ጉባኤያት፣ የትምህርት ክፍለ ጊዜያት፣ ወደ ገዳማትና አድባራት የሚደረጉ ጉዞዎች እና ምዕመናን የሚሳተፉባቸው ታላላቅ መርሐ ግብሮች ለጊዜው እንዲቋረጡ፣
3. ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲገባም ሆነ አሰፈላጊ በሆነበት ጊዜ ሁሉ እጆቻንን በመታጠብና ዘርዘር ብሎ በመቆም ሥርዓተ አምልኮ እንዲፈጸም፣
4. ዓመታዊ የንግሥ ክብረ በዓላት በቅዳሴና በማኅሌት ታስበው ክብረ በዓላቱ በሌላ ጊዜ እንዲከበሩ፣
5. የጉንፋን ምልክት ያለባቸው ለሌሎች እንዳያስተላልፉ በቤታቸው በጥንቃቄ ተለይተው በጸሎትና በሕክምና እንዲቆዩ፣ ከቤተ ክርስቲያን የሚያስፈልጋቸውን መንፈሳዊ አገልግሎትም በልዩ ሁኔታ እንዲያገኙ፣
6. በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ የተቋቋመው ግብረ ኃይል የተስፋ ልዑክ በመሆን እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ተደራጅቶ ተልዕኮውን በአስቸኳይ እንዲጀምር
7. ሥርዓተ ቅዳሴን በተመለከተ፡-
• በቤተ መቅደስ ቀዳስያን በሆኑት ልዑካን ብቻ ሥርዓተ ቅዳሴው እንዲፈጸምና ሌሎች አገልጋዮች በቅድስቱ ዘርዘር ብለው በመቆም እንዲያገለግሉ፣
• በዕለቱ ለሚቆርቡ ምዕመናን ለአረጋውያን፣ ለወጣቶችና ለሕፃናት የፈረቃ ተራ በማዘጋጀት ቆራቢዎች ብቻ ወደ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ገብተው ዘርዘር ብለው በመቆም እንዲያስቀድሱ፣
• ሌሎች ምእመናን በአጸደ ቤተክርስቲያን ቢያንስ ሁለት የትልቅ ሰው እርምጃ ያህል በመራራቅ ቆመው እንዲያስቀድሱ፣
• የቅዳሴ ጠበል በየግል መጠቀሚያ ምእመናን በየቆሙበት ቦታ በጥንቃቄ እንዲሰጥ፣
• ሌሎች ከቅዳሴ ጋር የተያያዙ ዝርዝር የአፈፃፀም ጉዳዮችን ግብረ ኃይሉ አዘጋጅቶ በቅዱስ ሲኖዶስ በማጸደቅ ለአህጉረ ስብከት በሚልከው መመሪያ መሠረት ተግባራዊ እንዲደረግ፤
8. ከሥርዓተ ቅዳሴ በተጨማሪ እንደ ስብሐተ ነግሕ፣ ሰዓታት፣ ቁመተ ማኅሌት፣ ጥምቀተ ክርስትና፣ ጸሎተ ፍትሐት፣ የመሳሰሉ አገልግሎቶች ለሥርዓቱ በሚያስፈልገው ቁጥር ብቻ እና በውሱን ሊቃውንት በተራ እንዲፈፀም፣
9. ወረርሽኙ ከዓለም እንዲጠፋ ካህናት ብቻ በቤተ መቅደስ፣ በዐውደ ምኅረትና በአጸደ ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ጸሎተ እጣን በማድረስ ማዕጠንት እንዲፈጽሙ፣
10. በማኅበራዊ ግንኙነት በደስታ፣ በሐዘን፣ በእድር፣ በሥርዓተ ቀብር አፈፃፀምና በመሳሰሉት መሰባሰቦች በሽታው እንዳይሠራጭ አገልግሎቱ በውስን የሰው ቁጥር በጥንቃቄ እንዲፈፀም፤
11. ምዕመናን ራሳቸውን እየጠበቁ በቫይረሱ የተጠቁና አገግመው የወጡ ወገኖችን፣ እንዲሁም በውጭ ሀገር ዜጎች ላይ ከሃይማኖትና ከምግባር የወጣ መገለልና ጥቃት እንዳይደርስባቸው በክርስቲያናዊ ፍቅርና በኢትጵያዊ ጨዋነት እንክብካቤ እንዲደረግላቸው፣
12. ለነዳያን እና ለተቸገሩ ወገኖች አስፈላጊው ማኅበራዊ እና ቁሳዊ እገዛ በሁሉም አጥቢያዎች እንዲደረግ፣
13. ቤተ ክርስቲያንን ከማይወክሉና ቀኖናዊ ካልሆኑ አሳሳች መረጃዎች በመቆጠብ ሊቃውንት፣ ካህናት፣ መምህራን፣ ሰባክያን፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ከቅዱስ ሲኖዶስ የሚሰጡ መመሪያዎችን በየአጥቢያችሁና አስፈላጊ በሆኑ ቦታዎች ሁሉ እንድትፈጽሙ እና እንድታስፈጽሙ ተወስኗል፡፡
በአጠቃላይ በበሽታው እስካሁን ለተያዙት፣ በጊዜያዊ ማቆያ ለሚገኙት በሙሉ እግዚአብሔር አምላካችን ምህረቱን እንዲሰጥልን እንጸልያለን፤
በመላው ዓለም ዜጎቻቸውን በበሽታው ለተነጠቁ ሁሉ መጽናናቱን እንዲሰጥልን ያረፉትንም እንዲምርልን እግዚአብሔርን በጸሎት እንጠይቃለን፤
በመላው ዓለም የምትገኙ ወገኖቻችን የራሳችሁና የሌሎች ሕይወት ከወረርሽኙ እንዲጠበቅ እንዲሁም የበሽታው ሥርጭት እንዲቆም መንፈሳዊና ማኅበራዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እያሳሰብን የተሰጡት መመሪያዎች ወረርሽኙ እስኪጠፋ ድረስ የጸኑ እንዲሆኑ በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡
ልዑል እግዚአብሔር በቸርነቱና በይቅርታው ብዛት ዓለማችንን ከጥፋት የሰውን ልጅ ሁሉ ከመከራ ሞት ይጠብቅልን፡፡ አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ.ም
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በጣሊያን እስካሁን የተመዘገበው የሟቾች ቁጥር 6077 ደርሷል። የ24 ሰዐት ሪፖርቱ እንደሚያሳየው ከሆነ ደግሞ 4,789 አዲስ ተጠቂዎች የተመዘገቡ ሲሆን 602 ሰዎች ደግሞ ሞተዋል። በአጠቃላይ በሀገሪቱ የተመዘገቡ ተጠቂዎች ቁጥር ደግሞ 63,927 ደርሷል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
የጀርመኗ መራሄተ መንግሥት አንጌላ መርክል በምርመራ ከኮሮና ቫይረስ ነጻ መሆናቸው መረጋገጡን የጀርመን መንግሥት ቃል አቀባይ ተናገረ!
አርብ ዕለት ለመርክል የፀረ-ኒሞኒያ አምጪ ተህዋስ ክትባት የሰጣቸው ዶክተር በኮሮና መያዙን ተከትሎ፣ መራሄተ መንግስቷ ራሳቸውን አግልለው ነበር፡፡የ65 ዓመቷ መርክል በቀጣይ ቀናትም በተደጋጋሚ ይመረመራሉ ተብሏል፡፡
Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
አርብ ዕለት ለመርክል የፀረ-ኒሞኒያ አምጪ ተህዋስ ክትባት የሰጣቸው ዶክተር በኮሮና መያዙን ተከትሎ፣ መራሄተ መንግስቷ ራሳቸውን አግልለው ነበር፡፡የ65 ዓመቷ መርክል በቀጣይ ቀናትም በተደጋጋሚ ይመረመራሉ ተብሏል፡፡
Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
ዛሬ ከምሽቱ 2:00 ሳሪስ አከባቢ ባቡር ሰው መግጨቱን ሰምተናል።
የተገጨው ግለሰብ በአንቡላንስ ወደ ሆስፒታል መወሰዱን ተነግሮናል።
@Yenetube @Fikerassefa
የተገጨው ግለሰብ በአንቡላንስ ወደ ሆስፒታል መወሰዱን ተነግሮናል።
@Yenetube @Fikerassefa
በማስታወቂያ የሚገኝ ገንዘብ ለእርዳታ ስለ ማዋል :-
የኔቲዩብ ፈጣን እና ወቅታዊ ሚዛናዊ መረጃዎች ስናደርስ አመታትን ያሳለፈ ድርጅት መሆኑን እናንተው ቤተሰቦቻችን የምትመሰክሩት እውነት ነው።
አለም አቀፍ ወረርሽኝ እንደሆነ በአለም የጤና ድርጅት የታወጀው የኮቪድ-19ን ለአለም ብሎም ለሀገራችን ስጋት መሆኑን ተከትሎ፣ መረጃዎችን ብቻ እንድናደርስና ማስታወቂያ እንድናቆም የተለያዩ ሰዎች መልዕክቶች እየደረሱን ይገኛሉ የኔቲዩብም የእናንተን ጥያቄ በመቀበል እንዲሁም የደንበኞቻችን ፍላጎት ጋር በማስታረቅ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ኮሮና ቫይረስ ከተጠቂ ከተገኘበት ቀን ጀምሮ የሚታሰብ ለየኔቲዩብ ለማስታወቂያ የተከፈሉ/የሚከፈሉ ክፍያዎችን አቅም ለሌላቸው ለክልል ነዋሪዎች፣ የንፅህና መጠበቂያ መግዣ እንዲውል ይደረጋል።
በመጀመርያ እቅዳችን የያዝነው በሀዋሳና አካባቢዋ ለሚገኙት ለማዳረስ ሲሆን እኛ ከምናደርገው እርዳታ በተጨማሪ መርዳት የምትፈልጉ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም የንግዱ ማህበረሰብ በ @Fikerassefa ማናገር ትችላላችሁ።
ሀዋሳ የምትገኙ በዚህ ተግባር ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲህም መርዳት የምትፈልጉ በነዚህ አካውንቶች ማናገር ትችላላችሁ።
- በቴሌግራም t.me/Fikerassefa
- በስልክ +251991467259
እናመሰግናለን!
የኔቲዩብ ፈጣን እና ወቅታዊ ሚዛናዊ መረጃዎች ስናደርስ አመታትን ያሳለፈ ድርጅት መሆኑን እናንተው ቤተሰቦቻችን የምትመሰክሩት እውነት ነው።
አለም አቀፍ ወረርሽኝ እንደሆነ በአለም የጤና ድርጅት የታወጀው የኮቪድ-19ን ለአለም ብሎም ለሀገራችን ስጋት መሆኑን ተከትሎ፣ መረጃዎችን ብቻ እንድናደርስና ማስታወቂያ እንድናቆም የተለያዩ ሰዎች መልዕክቶች እየደረሱን ይገኛሉ የኔቲዩብም የእናንተን ጥያቄ በመቀበል እንዲሁም የደንበኞቻችን ፍላጎት ጋር በማስታረቅ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ኮሮና ቫይረስ ከተጠቂ ከተገኘበት ቀን ጀምሮ የሚታሰብ ለየኔቲዩብ ለማስታወቂያ የተከፈሉ/የሚከፈሉ ክፍያዎችን አቅም ለሌላቸው ለክልል ነዋሪዎች፣ የንፅህና መጠበቂያ መግዣ እንዲውል ይደረጋል።
በመጀመርያ እቅዳችን የያዝነው በሀዋሳና አካባቢዋ ለሚገኙት ለማዳረስ ሲሆን እኛ ከምናደርገው እርዳታ በተጨማሪ መርዳት የምትፈልጉ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም የንግዱ ማህበረሰብ በ @Fikerassefa ማናገር ትችላላችሁ።
ሀዋሳ የምትገኙ በዚህ ተግባር ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲህም መርዳት የምትፈልጉ በነዚህ አካውንቶች ማናገር ትችላላችሁ።
- በቴሌግራም t.me/Fikerassefa
- በስልክ +251991467259
እናመሰግናለን!