YeneTube
116K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
Protect your self from Virus⬆️
እራሳችሁን ጠብቁ ከቫይረሱ

ለወዳጆ ምልክቱን አስተላልፉ
ስለ ኮሮና ቫይረስ ኮቪድ 19 በክልሎች አገልግሎት የሚሰጡ ነጻ የስልክ መስመሮች:-

Tigray:- 6244
Oromia:- 6955
Amhara:- 6982
South N.N.P:- 6599
Dire Dawa:- 6407

#COVIDー19
@YeneTube @Fikerassefa
ለዋሽንግተን ዲ.ሲ. ነዋሪዎች የቀረቡ ጠቃሚ መረጃዎች :-

----- አምባሳደር ፍፅም አረጋ ------

አንዳንድ ዲ.ሲ. ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የኮሮና ቫይረስ መስፋፋቱን ተከትሎ አስተዳደሩ ባወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅና ሌሎች ህጎች ሰራተኞች ከስራ ተለይተው፣ የንግድ ተቋማትም ተዘግተው እቤት በመዋል የቫይረሱን ስርጭት እየተከላከሉ ቢሆንም ኑሮአቸው እንዳሳሰባቸው በገለጹት መሰረት የሚከተሉ መረጃዎች ቀረበዋል:-

1) በዲስትሪክቱ ስለበሽታው ሁኔታ ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት: https://t.co/89ZVI6ObAh ይጫኑ፣

2) በዲስትሪክቱ በልዩ ሁኔታ እስከ ኤፕሪል 27/20 ለአገልግሎት ክፍት የሚሆኑ ተቋማትን ለማወቅ: https://t.co/qWausMjqlL ይጫኑ፣ ለምሳሌ ቆሻሻ አወጋገድ በተለመደው መልኩ እንደሚቀጥል፤ የንግድ ፈቃድ ኦንላይን በ https://t.co/iuq4Sv17HL ማሳደስ እንደሚቻል፣

3) ከስራ ለተፈናቀሉ ጥቅማጥቅምና መረጃዎችን ለማግኘት: https://t.co/5AFiMeyEFR

4) የአነስተኛ ቢዝነሶችን ጉዳት ለመቀነስ የፌዴራል መንግስት ከከፈተው የብድር ዕድል ለመጠቀም: https://t.co/J100IWqjR5 መመልከትና https://t.co/DVtChsNibj ማመልከት ይችላሉ::


5) በአስቸኳይ ጊዜ አወጁ ወቅት የቤት ኪራይ፣ የኤሌክትሪክ፣ የጋዝ እና የውሃ ክፍያ መጠየቅም ሆነ ማቋረጥ የማይቻል መሆኑን፣ የዲ.ሲ. ፐብሊክ ትምህርት ቤቶቸ የነጻ ምገባ የሚሰጥ መሆኑን፣ ዝርዝሩን (202) 727 5355 በመደወዕል መጠየቅ ይቻላል፣

6) ማደሪያ የሌለው ጊዜያዊ መጠለያ ለማግኘት (202)399 7093 /311 መደወል ይቻላል፣

በሌሎች አካባቢዎች የሚገኙ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲዎች ለየአካባቢው ተስማሚ መረጃ በማቅረብ እንድታግዙ እየጠየቅሁ ከበሽታው ተጠበቃችሁ ኑሮአችሁ እንዲቃና እመኛለሁ!
በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ አንድ (1) ተጨማሪ ሰው በመገኘቱ በአጠቃላይ ቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አስራ ሁለት (12) ደርሷል፡፡ ይህ ታማሚ የ 34 ዓመት ኢትዮጵያዊ ሲሆን ከዱባይ ወደ ሀገር ውስጥ መጋቢት 10 ቀን 2012 ዓ.ም የገባ ነው፡፡

ግለሰቡ የህመም ምልክት የነበረው በመሆኑ በመጋቢት 13፣2012 ዓ.ም ወደ ጤና ተቋም የሄደ ሲሆን ተቋሙም ለህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሪፖረት በማደረግ በተደረገለት የላብራቶሪ ምርመራ በቫይረሱ መያዙ ተረጋግጧል፡፡ ታማሚውም በለይቶ ማከሚያ ውስጥ የህክምና ክትትል እየተደረገለት ሲሆን ጤንነቱ በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከታማሚው ግንኙነት የነበራቸው 15 ሰዎች በክትትል ላይ ይገኛሉ፡፡

ዶ/ር ሊያ ታደሰ
የጤና ሚኒስትር
መጋቢት 14 ፣ 2012 ዓ.ም
@YeneTube @FikerAssefa
ለኮሮና ቫይረስ ፈዋሽ ነው ተብሎ በፕሬዝዳንት ትረምፕ የተገለፀው ንጥረ ነገር ሰው ገደለ

ፕሬዝዳንት ትረምፕ ለኮሮና ቫይረስ ጥሩ ሳይሆን አይቀርም ብለው ያሉትን" ኮሎሮኮየን" የተባለ ንጥረ ነገርን የወሰዱ በ60 ዎቹ ያሉ አሜሪካዊ ባልና ሚስቶች ባልያው ትናንት ሲሞት ሚስትዬው በፅኑ ታማለች ሲል የእንግሊዙ ዲይሊ ስታር ጋዜጣ አስነብቧል። ባልና ሚስቱ ገና ኮሮና ቫይረስ ይኑርባቸው አይኑርባቸው ሳይረጋገጥ ነው የህመም ስሜት ሲሰማቸው ነበር ንጥረ ነገሩን መዋጥ የጀመሩት።

Via:- ተስፋዬ ጌትነት
@Yenetube @Fikerassefa
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር ማምረት መጀመሩ ተነገረ፡፡

ምርቱን የሚሰራው የዩኒቨርስቲው የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ነው ተብሏል፡፡የእጅ ማፅጃው የኮሮና በሽታን ለመከላከል አገልግሎት ላይ እንደሚውልም ሰምተናል፡፡ዩኒቨርስቲው በኢትዮጵያ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር እጥረት መኖሩን ከግምት በማስገባት መስራቱን የኮሌጁ የፋርማሲ ትምህርት ክፍል ኃላፊ መምህር ታምራት ባልቻ መናገራቸውን ወላይታ ታይምስ ፅፏል፡፡የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘሩ ትክክለኛ ኬሚካላዊ ኡደትን ተከትሎ የተሰራ ነውም ብለዋል፡፡ለጊዜው የኮሮና ቫይረስን ለመከላል በተቋቋመው ግብረ ኃይል ውስጥ ለሚሰሩ የህክምና ባለሞያዎች የሚከፋፈለው ይህ ምርት በቀጣይ በብዛትና በተሻለ ጥራት ይመረታል ተብሏል፡፡

Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በተለምዶ አውቶብስ ተራ ተብሎ የሚጠራው አካባቢ የሚገኘው መለስተኛ መናኸሪያ አገልግሎት ወደሌሎች መናኸሪያዎች እንዲዛወር መደረጉን የትራንስፖርት ባለሥልጣን አመለከተ።

ባለሥልጣኑ የኮሮናቫይረስ ሥርጭትን ለመቀነስ በመናኸሪያዎች የሰዎችን ጥግግት ለመቀነስ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።ባለሥልጣኑ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ የሰዎች ጥግግትን በመቀነስ ማኅበራዊ ርቀትን ለማስጠበቅ እየተሞከረ ይገኛል። መናኸሪያዎች ከፍተኛ የሕዝብ ምልልስ ያለበትና የተሳፋሪ ጥግግት በብዛት የሚታይበት በመሆኑ ማኅበራዊ ርቀት በማስጠበቅና ንክኪን በመቀነስ የኮሮና ቫይረስ ሥርጭትን ለመግታት እየሰራ እንደሚገኝ አመልክቷል።

የሰው ጥግግትን ለመቀነስ በአዲስ ከተማ መለስተኛ መናኸሪያ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ከዛሬ ጀምሮ ወደ ሌሎች መናኸሪያዎች በማዛወር አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ጠቁሟል።በዚህም መሠረት የሆሳዕና፣ ቡታጅራ፣ ቱሉቦሎ፣ ወሊሶ፣ ወልቂጤና ሰባት ቤት ጉራጌ ሥምሪቶች በአየር ጤና መናኸሪያ የሚሰጡ ሲሆን የአዳማና ቢሾፍቱ ሥምሪቶች ደግሞ በላምበረት እና በቃሊቲ መናኸሪያዎች ላልተወሰነ ጊዜ ተዛውረው አገልግሎት የሚሰጡ ይሆናል።

ባለሥልጣኑ የኮሮና ቫይረስ ሥርጭትን ለመግታት አዲስ አበባ ባሉ መናኸሪያዎች መንገደኞች እጃቸውን እንዲታጠቡ፣ የእጅ ማጽጃ ኬሚካሎችን እንዲጠቀሙና ተሽከርካሪዎች በአልኮል እንዲያጸዱ እየተደረገ መሆኑን ገልጿል። የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም የግንዛቤ ማሳደጊያ ሥራዎች ባለሥልጣኑ እያከናወነ ሲሆን ይህንን አጠናክሮ ለማስቀጠልም ኮሚቴ አቋቁሞ በሁሉም መናኸሪያዎች ክትትል እያደረገ መሆኑን አመልክቷል።

Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
አሜሪካ ሕክምና ላይ የሰነበቱት የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ ወደ ክልሉ ተመለሱ። ሕክምናቸውን አጠናቀው መመለሳቸውን የገለጸው የክልሉ ፕሬስ ሴክሬታሪያት "ከገጠማቸው የጤና እክል አገግመው በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ" ብሏል።

Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
64 ኢትዮጵያዊያን ሞዛምቢክ ውስጥ በጭነት መኮና ውስጥ ሞተው ተገኙ!

ከማላዊ ወደ ሞዘምቢክ ሲጓዝ በነበረ የጭነት መኪና ውስጥ ቢያንስ 64 ኢትዮጵያዊያን በመተፋፈን ሳቢያ ህይወታቸው ማለፉን ባለስልጣናት አስታወቁ።ዛሬ ጠዋት በሞዛምቢክ ምዕራባዊ ግዛት በምትገኘው ቴቴ በተባለችው ክፍለሃገር ውስጥ በተገኘው ተሽከርካሪ ውስጥ ከሞቱት ሰዎች በተጨማሪ 14 ሰዎች በህይወት ተገኝተዋል። "የሞዛምቢክ የኢሚግሬሽን አገልግሎት ሰራተኞች የጭነት መኪናውን ሞአትዜ በተባለችው የግዛቲቱ ከተማ ውስጥ አስቁመው ሲፈትሹ ነው ሟቾቹን ያገኙት" ሲሉ የቴቴ ክፍለ ሃገር የጤና ባለስልጣን የሆኑት ካርላ ሞሴ ተናግረዋል።

ባለስልጣኗ እንዳሉት በጭነት መኪናው ላይ የተሳፈሩት ሰዎች ህይወታቸው በምን ምክንያት ሊያልፍ እንደቻለ ምርመራ እየተደረገ ነው። ነገር ግን የኢትዮጵያዊያኑ ህይወት ያለፈው በአየር ማጣት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ጥርጣሬያቸውን ገልጸዋል።የሞዛምቢክ ብሔራዊ ኢሚግሬሽን አገልግሎት ቃል አቀባይ የሆኑት አሜሊያ ደሪዬሮ እንደተናገሩት ሟቾቹን ያሳፈረው የጭነት መኪና ሾፌር እንዲቆም ሲጠየቅ ፍላጎት አልነበረውም ብለዋል።

ጨምረውም የኢሚግሬሽን ሰራተኞቹ ከመኪናው ውስጥ ድምጽ በመስማታቸው ስደተኞች በውስጡ ሊኖሩ ይችላሉ የሚል ጥርጣሬ እንዳረባቸውና እንዲቆም እንዳረጉ ገልጸዋል።ይህ የሞዛምቢክ ክፍለ ግዛት ወደ ደቡብ አፍሪካ በሕገ ወጥ መንገድ ስደተኞች በስፋት የሚዘዋወሩበት አንዱ ቦታ መሆኑ ይታወቃል።በህይወት የተረፉት 14ቱ ሰዎች የኮሮናቫይረስ ምርመራ እንደተደረገላቸው ቃል አቀባይዋ ጨምረው ተናግረዋል።

Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
የ2020ው ኦሎምፒክ ጨዋታወዎች አስተናጋጅ ጃፓንና የአለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ውድድሩን ለሚቀጥለው አመት ለማስተላለፍ ተስማሙ።

@YeneTube @FikerAssefa
ሳንሸንግ ፓርማሲውትካል የተባለ ኩባንያ በምስራቅ የኢንዱስትሪ ፓርክ ሳኒታይዘር ማምረት ጀምሯል። በቀን 24,000 ሊትር ያመርታል የተባለ ሲሆን የCovid-19ን ወረርሽኝ ተከትሎ ያለውን ፍላጎት ለማድረስ እየተሰራ እንዳለም ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አበበ አለማየሁ የትዊተር ገፅ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

@YeneTube @FikerAssefa
የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች ከቤት ሆነው እንዲሠሩ ተወሰነ!

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ከነገ ጀምሮ ተጨማሪ ውሳኔ እስከሚተላለፍ ድረስ ሥራቸውን በቤታቸው ሆነው እንዲያከናውኑ ወስኗል።

Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
መንግሥት በምዕራብ ኦሮሚያ የጣለውን ሕጋዊ ያልሆነ የስልክ እና የኢንተርኔት ግንኙት በአፋጣኝ እንዲመልስና በአካባቢው የሚኖሩ ዜጎች መረጃ የማግኘት መብታቸው እንዲከበር፣ የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (CARD) የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት በሚል ባወጣው መግለጫ ጠይቋል።

@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ መንግስት ሰራተኞች ከነገ ጀምሮ ወሳኝ የሥራ ሂደት ሰራተኞች ከሆኑት ውጪ ላልተወሰነ ጊዜ ከቤታቸው ሆነው እንዲሠሩ ተወስኗል።

@Yenetube @Fikerassefa
ወልቂጤ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች በሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስትር በተላከው አቅጣጫ መሰረት ግቢውን ለቀችሁ እንድትወጡ ዩንቨርስቲው አሳስቧል።

ነገር ግን እኛ ባለን መረጃ መሰረት የሳይንስ እና ከፍተኛ ሚንስትር ተማሪዎች በግቢው ውስጥ እንዲቆዩ ከግቢ እንዳይወጡ እንዲሁም እንዳይገቡ ነበር ትእዛዝ ያስተላለፈው።

--አዲስ ነገር ካለ የምናሳውቅ ይሆናል!!--
@Yenetube @Fikerassefa
የኮሮና ቫይረስን ለመግታት ትምህርት ሚንስትር እና ተጠሪ ተቋማቱ ከ1544 ሰራተኞች 196(12.7%) ብቻ በማስቀረት ቀሪዎቹ ሰራተኞች ቤታቸው ሆነው ስራቸውን እንዲሰሩና መንግስት ስርጭቱን ለመከላከል በሚያደርገው ጥረት የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ መወሰኑን የትምህርት ሚንስቴር ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን መኩሪያ መውሰኑን አስታውቀዋል

ምንጭ: Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
Breaking AAU

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሁሉም የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ወደ ቤታችሁ እንድትሄዱ ተወስኗአል::

@YeneTube @Fikerassefa
በአዳማ ከተማ “በኮሮናቫይረስ ምክንያት ረዳቱን መልስ አይጠይቁ” የሚል መልዕክት ለጥፈው የትራንስፖርት አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩት አሽከርካሪ እና ረዳት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፖሊስ አስተወቀ።

Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
Breaking AAU የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሁሉም የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ወደ ቤታችሁ እንድትሄዱ ተወስኗአል:: @YeneTube @Fikerassefa
በመላው ሀገሪቱ ያሉ ዩንቨርስቲዎች ተማሪዎችን ከግቢ ለቃችሁ ውጡ የሚል ማስታወቂያ እየተለጠፈ እንደሆነ የሚደርሱን መረጃዎች ያሳያሉ።

@Yenetube @Fikerassefa
አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች በትራንስፖርት ጊዜ ችግር እንዳይፈጠር የራሱን ትራንስፖርት ስለሚያዘጋጅ ሁሉም ተማሪዎች Student Council ቢሮ እየመጣችሁ ስም እና የሚሄዱበትን ሀገር እንዲያስገባ እናሳስባለን ሲል አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ አስታውቋል ።

AAU/ EiABC
@Yenetube @Fikerassefa