YeneTube
118K subscribers
31.4K photos
485 videos
79 files
3.86K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ 12 የልማት ድርጅቶችን ወደ ግል ለማዛወር አቅጃለሁ- ብሏል ዛሬ በሰጠው መግለጫ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 6 የስኳር ፕሮጀክቶች፣ ሒልተን ሆቴል እና የላንጋኖ ሪዞርት ሆቴል እንደተካተቱ የዘገበው ሸገር ነው፡፡ መንግሥት በሒልተን አዲስ ሆቴል ካለው ድርሻ 70 በመቶውን ለግል ባለሃብቶች ለመሸጥ ታቅዷል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
የሕዝብ ቤተ መፃህፍትን ወደ ዲጂታል የመቀየርና ተደራሽ የማድረግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መፃሕፍት ኤጀንሲ አስታወቀ።

እንደ አገር የትውልዱን የንባብ ባህል ለማሳደግ ጠቃሚ የሆኑ መፃሕፍትን በዲጂታል መንገድ ለመቀየር ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሚገኝ የብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መፃሕፍት ኤጀንሲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክተር ሽመልስ ታዩ ገልጸዋል።

Via:- ኢቢሲ
@YeneTube @Fikerassefa
የሱዳን ዜግነት ያለዉ አንድ ግለሰብ ትላንት መስከረም 21/2012 1300 የክላሽ ጥይት ከሰሜን ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ ይዞ ሊገባ ሲል በጅማ ጉምሩክ አልመሀል መቆጣጠሪያ ጣቢያ በጣቢያዉ ሠራተኞች እና በፌደራል ፖሊስ ትብብር በቁጥጥር ስር ውሏል።

የኅብረተሰቡን ሰላም የሚያደፈርሱና የሚያውኩ ሕገ ወጥ መሳሪያዎችን ይዞ መንቀሳቀስ ከሕግ እንደማያስመልጥ በማሰብ ሕገወጦች ከዚህ መሰል ተግባር መታቀብ እንዳለባቸው የገቢዎች ሚኒስቴር አሳስቧል።

Via:- አዲስ ማለዳ
@YeneTube @Fikerassefa
የመጀመሪያ ቪዲዮችን የኢሬቻበዓል በሚከበርበት ቀን ይለቀቃል!

የኔቲዩብን በYouTube ላይ አሁንኑ ሰብስክራይብ ያድርጉ!!!

https://bit.ly/2pKzukZ
Forwarded from YeneTube
እንኳን አደረሳችሁ

በ አዲስ አበባ የተለያዩ እቃዎች አስመጪ
🎖ብራንድ የወንድና የሴት ሰዓቶች
🎖የሴት ቦራሳዎች
🎖የመዋቢያ እቃዎች
🎖እንዲሁም አልባሳት

የምናስመጣቸው እቃዎች ጥራት እና በቀላሉ ገበያ ላይ አለመገኘት እንዲሁም ወደ ክልል ከተሞች መላክ መቻላችን ለየት ያደርገናል ።

ቦሌ መድኃአለም ሞል
+251993014846

ከታች ባለው ሊንክ ገብተው ይጎብኙን ይምረጡ ይዘዙን
👇👇👇👇👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAENXyUTam6WMV6_hmg
ዋይት ሃውስ ቤተመንግሥት በአባይና በኅዳሴ ግድብ ላይ ማምሻውን መግለጫ አውጥቷል።

የኢትዮጵያን ታላቁን ኅዳሴ ግድብ ለመሙላትና አገልግሎቱንም ለማስኬድ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ የትብብር፣ ዘላቂነት ያለውና የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያመጣ ስምምነት ላይ ለመድረስ በግብፅ፣ በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል እየተካሄዱ ያሉትን ድርድሮች እንደምትደግፍ ዩናይትድ ስቴትስ አስታውቀች።ከዋይት ሃውስ ቤተመንግሥት የፕሬስ ኃላፊ ማምሻውን የወጣው አጭር መግለጫ ”ሁሉም የአባይ ተፋሰስ ሃገሮች የምጣኔኃብትና የብልፅግና መብት አላቸው” ይላል። በመቀጠልም “እነዚያን መብቶች የሚጠብቅና በተመሣሣይ ጊዜም በአባይ ውኃ ላይ የሁሉንም የውኃ ድርሻ እኩልነት የሚያከብር ስምምነት ላይ እንዲደርሱ የሚያስችል ቀና ጥረት እንዲያደርጉ አስተዳደሩ ለሁሉም ወገኖች ጥሪ ያደርጋል” ብሏል።

መግለጫው የወጣበት ምክንያት አልተገለፀም።

Via VOA
@YeneTube @FikerAssefa
የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት አባላት በጥቅምት ወር አጋማሽ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ ዥንዋ ዘግቧል፡፡ የልዑኩ ጉዞ ዋና ዐላማ ከአፍሪካ ኅብረት ባለስልጣናት ጋር መምከር ነው፡፡ አጀንዳዎቹ የመካከለኛው ምስራቅ ሁኔታ፣ በአፍሪካ ስላሉ የተመድ ሰላም ተልዕኮዎችና ሰላምና ጸጥታ እንደሆኑ ተጠቅሷል፡፡ ልዑኩ ወደ ደቡብ ሱዳንም ያመራል ተብሏል፡፡

ምንጭ:Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ወጣቶች ፌደሬሽን ነገ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚከበረው የእሬቻ በዓል የከተማዋን ወጣቶች በማሳተፍ በዛሬው እለት በመስቀል አደባባይ የፅዳት ፕሮግራም አካሂዷል፡፡

በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች መስቀል አደባባይና አካባቢዉን ነው ያፀዱት። የእሬቻ በዓል አስመልክተዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በተለያዩ ስፍራዎች ጽዳት በማካሄድ ላይ መሆናቸውም ታውቋል፡፡

Via EBC

@YeneTube @Fikerassefa
የ15 ሀገራት አምባሳደሮችን ያካተተ ልዑክ በትግራይ ክልል ይፋዊ የስራ ጉብኝት ሊያደርግ ነው፡፡

ልዑኩ የትግራይ ክልል የድህነት ቅነሳ ፕሮጀክቶችን፣ ቱሪዝም እና የኢንቨስትመንት ልማት እንቅቃሴዎችን ተዘዋውሮ እንደሚጎበኝ ነው የተገለጸው፡፡

የአውስትራልያ፣ አዘርባጃን ፣ ባንግላድሽ፣ ቻይና፣ ፊጂ፣ ኢንዶኖዥያ፣ ህንድ፣ ኢራን፣ ጃፖን፣ ካዛኪስታን፣ ደቡብ ኮርያ፣ ኒውዝላንድ፣ ፓኪስታን፣ ስሪላንካ እና የቱርክ አምባሳደሮች የጉብኝቶ ተሳታፊዎች ናቸው፡፡
ለዚህም አሁን ላይ የአራት ሀገራት አምባሰደሮች መቐለ ገብተዋል፡፡

እንግዶቹ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች አቀባበል ተድርጎላቸዋል፡፡

በተመሳሳይ መልኩ ሌሎች ቀሪ የልዑኩ አባላትም ዛሬ ከሰዓት ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Via:- FBC
@YeneTube @Fikerassefa
ከሲዳማ ከስልጤ እና ጉራጌ ዞን የተወጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች በጋራ በሀዋሳ ከተማ የምክክር መድረክ ትላንት አድርገዋል።

የጋራ መድረኩ አላማ የህዝቦቹን ለዘመናት አብሮ የኖረ በደም ተሳሰረ አንድነት ለማስቀጠል ያለመ ነው ተብሏል።

በመድረኩ ላይ የሶስቱም ዞን የስራ ሀላፊዎች ተገኝቷል።

Via:- SMN
@YeneTube @Fikerassefa
ET 302 - ጉዳይ ⬆️

እ.ኤ.አ በመጋቢት ወር 2019 ከአዲስ አበባ ወደ ኬንያ ናይሮቢ በረራዉን ሲያደርግ በነበረዉ ET 302 የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዉሮፕላን ቢሾፍቱ ከተማ አቅራቢያ በመከስከሱ የ35 ሀገራት መንገደኞች ህይወት ማለፉ ይታወሳል፡፡ አደጋዉ ከደረሰ ከሁለት ቀናት በኃላ ኢትዮጵያ በጠየቀችዉ ጥያቄ መሰረት ኢንተርፖል ምላሽ ሰጪ ቡድን በመላክ ምርመራዉን ሲያከናዉን ቆይቷል፡፡

ለህልፈተ ህይወት የተዳረጉትን ለመለየት እንዲረዳዉም ኢንተርፖል የተጎጂ ቤተሰቦች ዲ ኤን ኤ በማሰባሰብ ምርመራ አድርጓል፡፡ ኢንተርፖል ለአደጋዉ ምላሽ ሰጪ ቡድን በማሰማራት ስሰራ የነበረዉን ተጎጂዎችን የመለየት ስራ ከ 6 ወራት በኃላ በተሳካ ሁነታ ማጠናቀቅ መቻሉን አፍሪፖል በድህረ ገፁ ባወጣዉ መረጃ አስነብቧል፡፡

ምላሽ ሰጪ ቡድኑ በአለም አቀፍ ደረጃ የሞት አደጋ የደረሰባቸዉን የሚለዩ ህግ አስፈፃሚዎችን በማስተባበር እና በአባል ሀገራት የቀረበዉን የቅድመ ሞት መረጃን የማቀናጀት ሚና ተጫዉቷል ተብሏል፡፡

ቡድኑ የሞት አደጋ የደረሰባቸዉን የመለየት ምርመራዉ ዓለም አቀፋዊ ደረጃዉን ጠብቆ መካሄዱን ለማረጋገጥ እንዲሁም የጣት አሻራ እና የ ዲ ኤን ኤ ናሙናዎችን በማሰባሰብ እገዛ ማድረጉም ተገልጿል፡፡ በአዲስ አበባ የሚገኘዉ የኢንተርፖል ልዩ ተወካይ ፅፈት ቤትም ለህልፈተ ህይወት የተዳረጉትን የመለየት ስራን በማስተባበር ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል፡፡

ከ14 የአፍርካ ሀገራት የተዉጣጡ መቶ የሚደርሱ ባለሙያዎች እንዲሁም የአሜሪካ እና የአዉሮፓ ሀገራት ባለሙያዎች ባካሄዱት ምርመራ 48 የሚደርሱ ሟቾችን በጣት አሻራዎቻቸዉ መለየት ችለዋል ተብሏል፡፡

Via:- ፌዴራል ፓሊስ
@YeneTube @Fikerassefa
ብሔራዊ ባንክ ሶስት ምክትል ገዢዎች ተሾሙለት። በአዲስ ፎርቹን ዘገባ መሠረት ፍቃዱ ድጋፌ፣ ሰለሞን ደስታ እና እዮብ ገብረእየሱስ የባንኩ ምክትል ገዢዎች ሆነው ተሾመዋል። ፍቃዱ ድጋፌ የባንኩ ዋና ኤኮኖሚስት ሆነዋል።

Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
ነፃ የአይን ህክምና ጅማ

በጅማ ዩንቨርስቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የዐይን ክፍል ከዛሬ ጀምሮ ለ 3 ቀናት ( ከመስከረም 23 - መስከረም 25) የሚቆይ ነፃ የCataract ህክምና በስፔሻሊስት ዶክተሮች እየተሰጠ በመሆኑ ጅማ እና በአከባቢው የሚኖሩ ህሙማን ወደ ሆስፒታሉ በመምጣት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በየኔቲዩብ ቦኩል አስታውቋል ።

እንዲሁም በዚህ በ 3 ቀን ዘመቻ ከ 200-300 ለሚሆኑ ህሙማን በነፃ ቀዶ ህክምና ለመስራት ታስቧል።

@Yenetube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በኤረር ወንዝ ድልድይ ላይ ጉዳት በመድረሱ አሽከርካሪዎች በጊዜያዊ ተለዋጭ መንገድ እንድትጠቀሙ የሚያስችል ግንባታ እያከናወነ ነው።

ከሐረር ወደባቢሌ መስመር 20 ኪ.ሜ ዕርቀት ላይ የሚገኘው በኤረር ወንዝ ድልድይ ላይ በአካባቢው በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው ጎርፍ ሳቢያ ጉዳት ደርሷል። በዚህም ምክንያት ተለዋጭ መንገድ እየተሰራ ይገኛል።ተለዋጭ መንገዱ በተወሰነ ደረጃ ተሽከርካሪዎችን በማሳለፍና ግዚያዊ መፍትሄ ለመስጠት እየተስራ ሲሆን በቀጣይ ጉዳት የደረሰበትን ድልድይ በመጠገን ዘለቄታዊ አገልግሎትን እንዲቀጥል ይደረጋል። በመስመሩ ተጓዦችና አሽከርካሪዎች ለሚያጋጥማችሁ እንግልት የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ይቅርታ እየጠየቀ የተለዋጭ መንገዱ ግንባታ በአፋጣኝ እየተሰራ ሲሆን አሽከርካሪዎች በትግስት በመጠበቅና በቅደም ተከተል በመተላለፍ የበኩላችሁን አስተዋፅዖ እንድታደርጉልን በትህትና እንጠይቃልን።

ምንጭ: መንገዶች ባለስልጣን
@YeneTube @FikerAssefa
ዩንቨርስቲ መግቢያ ውል❗️

በመላው ኢትዮጵያ በ2011 የመሰናዶ ትምህርታቸውን አጠናቀው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በ2012 ለሚቀላቀሉ ተማሪዎች ከወትሮው በተለየ ተቋማት አዲስ ገቢ ተማሪዎቻቸውን ከአንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ልብስ ባለፈ ከሚኖሩበት አካባቢ ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት በኩል የፈረሙትን ውል ይዘው እንዲመጡ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። ጉዳዩ እንዲህ ነው፤ ባሳለፍናቸው ጥቂት ዓመታት በአገሪቱ የሚገኙት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የእውቀት መገቢያነታቸው ተዘንግቶ ጎራ ተለይቶ መጠፋፊያ ቀጠና ሆነው የበርካታ ተማሪዎችን ሕይወት እንዲቀጠፍ የሆነበት ነበር።

ታዲያ ያለፉትን ዓመታት አለመረጋጋቶችና ግጭቶች በከፍተኛ ተቋማት ውስጥ ጭራሽ እንዳይከሰት በሚል በዘንድሮው ማለትም 2012 የትምህርት ዘመን አዲስ እና ነባር ተማሪዎች በሚማሩበት ዩኒቨርስቲ ውስጥ አስተዳደራዊ እና አካዳሚያዊ ሥነ ስርዓቶችን አክብረው ሊማሩ እና ሕገ ደንቦችን ጥሰው ቢገኙ ደግሞ ለሚወሰድባቸው ማንኛውም ዓይነት እርምጃ ኀላፊነቱን ራሳቸው እንደሚወስዱ ውል እንዲገቡ ተደርገዋል።

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ግን በዚህ ይብቃኝ ያለ አይመስልም። ወላጆችም ለጆቻቸውን በሚሔዱበት ዩኒቨርስቲዎች ያሉትን ሕጎች እንዲያከብሩ መምከራቸውን እና ተላልፈው ቢገኙ እና ለሚወሰድባቸው እርምጃ ልጆቻቸው ኀላፊነቱን እንደሚወስዱ አስታውቀው ውል ፈርመዋል።

በማኅበራዊ ትስስር ገፆች ታዲያ በርካታ ግለሰቦች የውሉን ጠቀሜታ እያሞካሹ አስተያየታቸውን ሲሰጡ እኩል በእኩል በሆነ ቁጥር ደግሞ በተቃራኒው በመቆም ተማሪዎች የሚያስሩት ውል ፋይዳው ምንድነው? የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ትችታቸውን ሲያሰሙ ከፍ ሲልም ሲሳለቁ ነበር።

ተማሪዎች በተለይም ደግሞ አዲስ ገቢዎች ገና ከጅምሩ እንደዚህ ዓይነት ኀላፊነት ተሸክመው መግባታቸው ከትምህርት ውጪ ወደ ብጥብጥና ረብሻ የሚያመሩበት አዝማሚያ በእጅጉ ይቀንሳል፤ መንግሥት እንዲያውም ከዚህ ቀደም ያላሳየውን የኀላፊነት መንፈስ አሁን እየተገበረው ነው። ይበል የሚያሰኝ አካሔድ ነው ሲሉ ድጋፋቸውን ያለመሰሰት አስተጋብተዋል።

ከዚሁ በተቃራኒው የቆሙት ደግሞ የለም መንግሥት አሁንም ”የውሃ ቢወቅጡት” ዓይነት አካሔድ ነው እየተከተለ ያለው ዘንድሮም ለውጥ ለሌለው ጉዳይ ማወናበጃ እንጂ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሰላም እንዲህ በቀላል የሚመለስ ሳይሆን ትልቅ ፖለቲካዊ ውሳኔዎች ተላልፈው ከተቋማት ውጭ ያሉት ውዥንብሮች ሲረግቡ ተያይዞ የሚረግቡ ናቸው ይላሉ። እንዲያውም ከጎረቤት በተለይም ደግሞ ከኤርትራው ፕሬዘዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የተገኘች ምክር መሆን አለባት ሲሉም የተሳለቁ አልታጡም። ቀጥለውም በወላጆች፣ በተማሪዎችና በትምህርት ጽሕፈት ቤቶች በኩል የሚገባው ውል በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚማሩ ተማሪዎች ልብ ማሰሪያስ ይሆናል ወይ? በውል የሚመጣ ሰላም ካለስ እስካሁን መንግሥት ምነው ዘገየ እና የመሳሰሉ ጥያቄዎች ከግራም ከቀኝም ሲናፈሱ ሰንብተዋል።

Via:- Maleda
@YeneTube @Fikerassefa
አዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ የመንገድ መጨናነቅ ላይ ትገኛለች።

#ኢሬቻ2019_ሆራ ፊንፊኔ
@YeneTube @Fikerassefa