YeneTube
117K subscribers
31.5K photos
485 videos
79 files
3.88K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
በካታር ዶሃ የአትሌቲክስ ቡድናችንን ለመደገፍ ወደ ስቴድዮም የገቡ ኢትዮጵያውያንን ልዩ ድባብ IAAF በአድናቆት በትዊተር ገፁ አጋርቶታል!

@YeneTube @FikerAssefa
በታደሉ ዩኒፎርሞች ላይ ቅሬታ ያለው ማንኛውም ግለሰብ እንዲያሳውቅና አፋጣኝ ማስተካከያ እንደሚወስድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሳውቋል።

"ከዩኒፎርም ስርጭት ጋር በተያያዘ መጠነኛ ቅሬታዎች እየቀረቡልን ይገኛሉ።
የከተማ አስተዳደሩ ዋነኛ አላማው ተማሪዎች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ትምህርታቸውን እንዳያቋርጡ ማድረግና እንዲሁም ወላጆችን ከጭንቀት ለማዳን ነው።የከተማ አስተዳደሩ የየትኛውንም ሀይማኖት አስተምህሮትም ይሁን ስርአት ያከብራል።ለተማሪዎች በነጻ የዩኒፎርም ስናዘጋጅም ይህን ባገናዘበ መልኩ ነው።
ነገር ግን አሁን እየተነሱ ያሉ ጥያቄዎች በስርጭት ወቅት የተፈጠሩ በመሆናቸው መስተካከል ይችላሉ።ከዩኒፎርም አቅራቢ ድርጅቶች ጋር ስምምነት ያለን በመሆኑ ለተማሪዎች በታደሉ ዩኒፎርሞች ላይ ቅሬታ ያለው ማንኛውም ግለሰብ እንዲያሳውቅና አፋጣኝ ማስተካከያ የምንወስድ መሆኑን እናስታውቃለን።"
- የከንቲባው ጽ/ቤት

@YeneTube @FikerAssefa
ከመንግሥት ልማት ድርጅቶች መካከል አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ባዮፊዩል ኮርፖሬሽን የሚያስተዳድረው የቀንጢቻ ታንታለም ፋብሪካ ላለፉት ኹለት ዓመታት ሥራ በማቆሙ ለሠራተኞቹ ደሞዝ እንዲሁም ለሥራ ማስጀመርያ የሚሆን 132 ሚሊዮን ብር ከገንዘብ ሚኒስቴር እርዳታ ጠየቀ።

በኮርፖሬሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ቡልቲ ወዳጆ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት፣ ፋብሪካው ከተዘጋ አንስቶ ምንም ዓይነት ገቢ ባለማግኘቱ ላለፉት ስድስት ወራት ከመንግሥት በተገኛ 47 ሚሊዮን ብር የሠራተኞቹን ደሞዝ ሲከፍል የቆየ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ለሠራተኞቹ የሚከፍለው ገንዘብ የለውም።

ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የኤካ ኮተቤ አጠቃላይ ሆስፒታል እና የኢትዮጵያ የአእምሮ ጤና ምርመር ኢንስቲትዩት ህንፃን በይፋ መርቀው ከፍተዋል።

#DPMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
የባህል መድሃኒት ጥናትና ምርምር ፍኖተ- ካርታ ይፋ ሆነ፡፡

የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የባህል መድሃኒት ጥናትና ምርምር ፍኖተ ካርታ ይፋ አድርገዋል፡፡የፍኖተ-ካርታው ዋና አላማ ሃገር በቀል ዕዉቀትን በመሰነድና በመጠበቅ የተጠናከረ ጥናትና ምርምር ማከናወን፣ እንዲሁም ደረጃውን የጠበቀ የባህል ህክምና አገልግሎት በአገሪቱ እንዲሰጥ ለማድረግ የተዘጋጀ ተብላል፡፡ዶክተር ኤባ አባተ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር እንደገለጹት በአገራችን በአማካይ ወደ 80 በመቶ የሚሆነው ህዝብ የባህል መድሃኒት ተጠቃሚ ቢሆንም ለዘርፉ የተሰጠው ትኩረት ግን እምብዛም ነው ብለዋል፡፡

የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን በበኩላቸው ኢትዮጵያ ከ6 ሺህ 500 በላይ ፈዋሽ እጸዋት ቢኖራትም መጠቀም ግን አልተቻለም ብለዋል፡፡በመሆኑም ፍኖተ ካርታው በባህላዊ መድሃኒቶች ዙሪያ ጥናትና ምርምር እንዲደረግ ለባህላዊ መድሃኒት ቀማሚዎች ድጋፍ ለማድረግና ሌሎች ዘርፉን ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች እንዲከናወኑ ያስችላል ተብሏል።በቀጣይ በባህል መድሃኒቶች ላይ የተለያዩ ጥናትና ምርምር በጋራ ለማድረግ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከሁሉም የሃገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎችና ከምርምር ተቋማት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡፡ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ፍኖተ ካርታው ተግባራዊ ለማድረግ 90 ሚሊዮን ብር እንደመደበ ነው የተገለጸው፡፡

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ለጎንደር ዮኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ፦

የ2012 የትምህርት ዘመን መግቢያ ቀናት ለነባር ተማሪዎች መስከረም 22 እና 23/2012ዓም እና ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች ተማሪዎች መስከረም 28 እና 29/2012ዓ.ም እንደሆነ ማሳወቃችን ይታወሳል።

ነገር ግን በወቅታዊ ችግሮች ምክንያት የመግቢያ ቀናትን ማራዘም አስፈልጓል። ስለሆነም የነባር ተማሪዎች መግቢያ ቀናት ወደ መስከረም 29 እና 30/2012ዓ.ም እንዲሁም የአዲስ ገቢ ተማሪዎች መግቢያ ወደ ጥቅምት 6 እና 7 ቀን 2012ዓ.ም የተቀየረ መሆኑን ከይቅርታ ጋር እናሳውቃለን።

Via:- የጎንደር ዮኒቨርሲቲ

@YeneTube @Fikerassefa
የሴቶች አልባሣት እና ኮስሞቲክስ ማዘዝ ምትፈልጉ ገፃችን ላይ ያገኛሉ ከታች ባለው ሊንክ መርጠው ይላኩልን

የአውሮፓ ስታዳርድ
Imported from England
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAFW3ZmuRfJiwNyWX7g
ኒውዮርክ ታይምስ የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎችን ጠቅሶ ያወጣው ዘገባ:

"የኢትዮጵያው ገዢ ፓርቲ የሶሻል ሚድያ ንግግሮች ራሱን እንዲደግፉ ለማድረግ ሰዎችን ቀጥሮ ያሰራል/ያሰራ ነበር።"

Via:- elias meseret
@YeneTube @Fikerassefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ አረንጓዴ ልማት ፕሮጀክትን በይፋ አስጀመሩ።በቻይና መንግሥት ድጋፍ የሚገነባው የአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ አረንጓዴ ልማት ፕሮጀክት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።

ምንጭ:ETV
@YeneTube @FikerAssefa
የሩስያ ልዑክ ጎንደርን እየጎበኘ ነው

የሩስያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክስርቲያን የውጪ ጉዳይ ኃላፊዎችና የሩሲያ የሚዲያ አባላትን ያካተተ የአገሪቱ ልዑክ ጎንደርን እና በውስጧ የሚገኙ ቅርሶችን እየጎበኙ ነው።
ዘጠኝ የሚደርሱት የልዑካን ቡድኑ አባላት ዛሬ ረፋድ ላይ ደብረ ብርሃን ሥላሴን እና የዓፄ ፋሲል አብያተ-መንግሥትን ጎብኝተዋል።

ለሁለት ቀናት በጎንደር ከተማ በሚኖራቸው ቆይታም የአብነት ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ በኢትዮጵያ ብቸኛ የሆነውን የባታ ደብረ ኃይል ወደብረ ጥበብ ባሕታ ለማሪያም ካቴድራል የአቋቋም ትምህርት ቤትን ይጎበኛሉ፡፡
በጎንደር ከተማ የሚገኙ የመንበረ መድኃኒዓለም እና የቁስቋም ጥንታዊ አብያተ ክርስቲያንንም እንደሚጎበኙ ታውቋል።

ምንጭ፡- አብመድ
@YeneTube @Fikerassefa
በአውሮፓውያኑ 2030 የሴት ልጅ ግርዛትን ሙሉ በሙሉ ከኢትዮጵያ ለማጥፋት ከእስካሁኑ በሰባት እጥፍ ፍጥነት መስራት ያስፈልጋል ተባለ፡፡

አሁን ባለው ፍጥነት ግን ኢትዮጵያ በዘላቂ የልማት ግቦች የሴት ልጅ ግርዛትን በ2030 ሙሉ ለሙሉ ለማጥፋት ያቀደችውን ማሳካት እንደማትችል ተነግሯል፡፡

አምሬስ ኸልዝ አፍሪካ ድንበር ተሻጋሪ የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም በአምስት የምስራቅ አፍሪካ አገራት መካከል የተገባውን ቃል ኪዳን አስመልክቶ ከባለድርሻዎች ጋር እየተወያየ ነው፡፡
በውይይቱ የተገኙት የሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ስመኝ ውቤ ኢትዮጵያ ድንበር ተሻጋሪ የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም የተገባውን ቃል ኪዳን ለመፈፀም እየሰራች ነው ብለዋል፡፡

ይሁንና ከአንዱ አገር ወደ ሌላው እየተዘዋወሩ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት የሚፈፅሙትን ለማስቆም በርካታ ስራዎች መሰራት እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡

ኬኒያ፣ ኡጋንዳ፣ ሶማሊያ፣ ታንዛኒያና ኢትዮጵያ ስምምነቱን ፈራሚ አገራት ሲሆኑ ኬኒያ ዋነኛዋ የድንበር ተሻጋሪ የሴት ልጅ ግርዛት የሚፈፀምባት አገር መሆኗ ተጠቅሷል፡፡
ከአራቱ የምስራቅ አፍሪካ አገራት በርካቶች ወደ ኬኒያ በመሄድ የሴት ልጅ ግርዛትን ይፈፅማሉ ተብሏል፡፡

የአገራቱ የህግና የቁጥጥር ሁኔታ የተለያየ መሆን፣ የዋጋ ዝቅተኝነትና ሌሎች ምክንያቶች ለድንበር ተሻጋሪ የሴት ልጅ ግርዛት መበራከት ምክንያት መሆናቸው ተነግሯል፡፡

በተለይም በአገራቸው ድርጊቱን መፈፀም የሚያስከትለውን ህጋዊ እርምጃ በመሸሽ ኬኒያን የሚጎበኙት ቁጥር በርካታ ናቸውም ተብሏል፡፡
በአምስቱ የምስራቅ አፍሪካ አገራት ከ48 ሚሊዮን በላይ ሴቶች በተለያየ ጊዜ የሴት ልጅ ግርዛት የተፈፀመባቸው ናቸው መባሉን ከውይይቱ ሰምተናል፡፡

Via:- Shager FM
@YeneTube @Fikerassefa
ጅቡቲ ወደብ ላይ ተከማችቶ ለመንፈቅ ያህል ፀሀይ ሲፈራረቅበት የቆየው ከውጭ ተገዝቶ የመጣ ስንዴ በቅርቡ ወደ ሃገር እንዲገባ ስምምነት ላይ መደረሱ ተሰማ፡፡

የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ድርጅትም ለማጓጓዣ መኪና ለመመደብ እየሰራሁ ነው ብሏል፡፡ለገበያ ማረጋጊያ የተገዛው ስንዴ አንዴ የማጓጓዣ ችግር አለ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ነቀዝ ታይቶበታል በሚል ሰበብ ከፍተኛ ሙቀት ባለበት የጅቡቲ ወደብ ላይ ተከማችቶ ፀሀይ ሲቀጠቅጠው መክረሙን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል፡፡አሁን ወደብ ላይ የቀረው 2 ሺህ 300 ሜትሪክ ቶን ስንዴ ነቀዝ ታይቶበት ከሆነ በድጋሜ ታክሞ በቅርቡ ወደ ሃገር እንዲገባ በገዥው በኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ድርጅትና ከውጭ ባስገባው በፕሮሚሲንግ ኢንተርናሽናል መካከል ስምምነት ላይ መደረሱን ከሁለቱም ወገን ሸገር አረጋግጧል፡፡

Via Sheger
@YeneTube @FikerAssefa
ከቦሌ መስቀል አደባባይ ወደ የሚወስደው መንገድ ፍላሚንጎ አከባቢ ( ኢግዚብሽን ማዕከል ጀርባ) እሳት አደጋ ተነስቷል አሁን እሳት አደጋ መኪኖች ደርሰዋል ለማጥፍት እየተረባረቡ ነው።

እንዲሁም እየጣለ ያለው ዝናብ እያገዛቸው ይገኛል።

📌ምን ያህል ውድመት አስከተለ የሚለሁን የሚመለከተውን አካል አናግረን እንቀርባለን።

Via:- Ab Kaza #YeneTube
@YeneTube @Fikerassefa
Forwarded from YeneTube
የሴቶች አልባሣት እና ኮስሞቲክስ ማዘዝ ምትፈልጉ ገፃችን ላይ ያገኛሉ ከታች ባለው ሊንክ መርጠው ይላኩልን

የአውሮፓ ስታዳርድ
Imported from England
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAFW3ZmuRfJiwNyWX7g
የአዲስ አበባ አስተዳደር በከባድ ጭነት ተሸከርካሪዎች በከተማዋ እንዳይንቀሳቀሱ ጥሎት የነበረውን ማሻሻሉን ካፒታል አስነብቧል፡፡ ማንኛውም የጭነት መጠን ያለው የጭነት ተሸከርካሪዎች ቅዳሜ ቅዳሜ በቀን ብቻ እንዲንቀሳቀሱ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ የትራፊክ ፍሰትን ለመቀነስ ሲባል አስተዳደሩ እገዳውን የጣለው በሐምሌ ነበር፡፡

-ዋዜማ
@YeneTube @FikerAssefa
የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የጥብቅና ፈቃድ መስጫ ፈተና የለመፈተን ምዝገባ ጊዜ ማራዘሙን ከላይ በፎቶ በሚታየው ማስታወቂያ አሳውቋል።

@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን የፑሽኪን አደባባይ ጎፋ ማዞሪያ -ጎተራ ማሳለጫ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታን በዛሬ መስከረም 20/2012 በይፋ አስጀምራል።

ፕሮጀክቱ 3 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር ርዝመትና ከ30 እስከ 45 ሜትር የሚሆን የጎን ስፋት ያለው ሲሆን የመንገድ ግንባታውን ቻይና ፈርስት ሀይ ዌይ ኢንጂነሪንግ የተባለ የስራ ተቋራጭ የሚያከናውነው መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ገልጿል።

@YeneTube @Fikerassefa
የወልድያ-ቆቦ መንገድ በደለል ምክንያት መዘጋቱ ተገለፀ!

ከወልዲያ ቆቦ የሚወስደው ዋና የአስፓልት መንገድ በጎርፍ ምክንያት በተደጋጋሚ የሚዘጋ ነው። ዛሬም በጣለው ዝናብ ከቀላል እስከ ከባድ ተሽከርካሪዎች መንቀሳቀስ አልቻሉም። መንገዱ የተዘጋው ከተራራማ ቦታዎች የሚወርድ ደለልን መከላከል የሚያስችል ደጋፊ የግንብ አጥር ባለመኖሩ ነው። በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የኮምቦልቻ መንገድ ዝርጋታ ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ተስፋዬ ‹‹ችግር በተፈጠረባቸው አካባቢዎች የመንገድ ጠረጋ እየተከናወነ ነው፤ በዘላቂነት ችግሩን ለመፍታት ደግሞ ከሰባት ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ የጎርፍ መከላከያ ደጋፊ ግንብ ይሠራል›› ብለዋል፡፡ የጎርፍ መከላከያ ደጋፊ ግንቡ ከደሴ ዋጃ ያለውን መንገድም ተመሳሳይ ችግር እንዳይገጥመው ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የወልድያ ቆቦ መንገድ ከአዲስ አበባ በደሴ-ወልድያ-ቆቦ- መቀሌ የሚገባ ነው፡፡ መንገዱ ክልል ከክልል የሚያገናኝና በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የሚተዳደር ነው፡፡

Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
የኢሬቻ በዓል ኤግዚቢሽንና ባዛር በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ትናንት ተከፍቷል።

በዚሁ የግብይት መርሃ ግብር ልዩ ልዩ አልባሳት ፣ መዋቢያ ባህላዊ ቁሳቁሶች ፣ ጌጣጌጦችና ሌሎችም ምርቶች ቀርበው ግብይት እየተካሄደ ይገኛል።
@YeneTube @Fikerassefa