#የደሜ ዜመኞች
ክፍል - ፩
ጲላጦስ ነኝ - የጀግና አዝማሪ የሙዚቀኛ ልጅ ነኝ
ዜማ እስካሁን በመጣሁበት የህይወት ጎዳና ያልተለየኝ የኔ የምለው ቀረኝ የምለው ወዳጄ ነው
ብዙ ነገር ስላጣሁ ነው ዜማን አሁን ላይ ቀረኝ ያልኩት
ኑ እስቲ በውብ ሙዚቃዎች የህይወቴን ውብ ትዝታዎች ላጋራችሁ
መቼም በትዝታ አድማስ ወደ ኀላ ልወስዳችሁም አይደል
ውሎ አድሮ ነበረ ከተወኝ ፍቅርሽ
አስቸገረኝ እንጂ ዛሬ ትዝታሽ
በትዝታ አትጋርጂኝ አይኔን ልግለጥበት
ፍቅርሽን አንሺልኝ አልጨነቅበት
ሙሉቀን መለሰ ነው
ለመጀመሪያ ማጫወቺያዬን ከፍቼላቹሀለሁ አቤት ድምፅ እኔም በሱ ልሳን ወደ ኀላ ተመለስኩ
ዜማውን እያጣጣማችሁ
ይህ ነው የሚባል የህይወት ታሪክ ስለሌለኝ ለኔ ውድ ስለሆነው የፍቅር ታሪኬ ላጫውታችሁ
ለካስ ታሪክ የሚባለው በኖርንበት አለም ውስጥ አንስተን ምንሰጠው ስያሜ ነው
እኔ የኖርኩበትን ምዕራፍ ታሪኬ አልለውም ብቻ ዳሽ በዳሽ አድርጌዋለሁ
ኑ ለማንኛው ከትዝታዬ ጋር የኀሊት እንፍሰስ
የሙዚቃዋን ስንኝ አትርሷት
ውሎ አዳድሮብኛል አረ ሰነባብቶም ከርሞብኛል
ያው እንደ ዘፈኑ ፍቅርሽ አሁን ላይ ለቆኛል ብያለሁ እንግዲህ
ግና ትዝታዋ ሙሉ ትውስታዬን ተቆጣጥሮት የመርሳት በሽታ እንደገጠመው ሰው እሷ የገባችበትን ህይወቴን ብቻ ነው የማውቀው ሌላው ከትውስታ ማህደሬ ተሰርዟል
ሁሉም .......
በአካል መታ ከምደነግጠው በላይ ትዝታዋ ይበልጥ ያስደነግጠኛል ለምን እንደሆነ እንጃ
ሙልዬ እኮ መዝፈኑን ቀጥሏል ቆይ ጨመር ላድርግላችሁ
እኔም ፋታ ልውሰድ ሁሉን ሳስታውስ የማይቆም ነስር ስላለብኝ ከአፍንጫዬ ሚንጠባጠበውን ደም ልጥረገው
በስቃይ.....
ቀኑን እያቃዠ
ሌት የሚያባንነኝ
ትዝታሽ መሆኑ
ዛሬ ነው የገባኝ
ሙዚቃዋ ቀጥላለች እያጣጣማችሁ እኔም ይህን የደም ጠብታዬን አፅድቼ ተመልሻለሁ ሌላ ጠብታ እስኪመጣ እቀጥላለሁ
ስለ አፈቅርኩዋት ጉብል ትንሽ ልበላችሁ......
በየቦታው እየተንከላወሱ እያቀነቀኑ ከመዞር ሌላ ምንም ስራ የለኝም ሀሳብ አላማ ነገን የሚሉ ነገሮች ከህይወት መዝገቤ ላይ በጭራሽ የሉም ነበር
አረ እንደውም ግምሹ የእድሜ ዘመኔን በመዞር ነው ያለፈው ማለት ይቻላል
ግን እንዲ ስል ነፍፍፍፍፍ አመት የኖርኩ አይመስልም እድሜይንም ላስጠጣ ሆነ እኮ
ስለሷ ላወራ ብዬ ሌላ ነገር ምቀባጥረው ባሰብኳት ቁጥር ትልቅ ሀይል ያለው ነገር አናቴን ስለሚነድለኝ ነው መቆጣጠር ስለማልችል ቦታዬ ከመሬት ነው እራሴን እስክስት ድረስ ምቱ አይምረኝም
ለነገሩ ይበለኝ.....
በመዞሬ ጎዳኝ የምለው አንድም ነገር የለም ብዙ ነገር አትርፌበታለሁና ከምላችሁ በላይ ብዙ ነገር አይቼበታለሁ
ተፈጥሮን መርምሬበታለሁ እግሬ መሄድ ብቻ አይደለም ጭንቅላቴም ብዙ አይሽሬ ትዝታዎችን ስለያዘበት
አሁን ይህን ምፅፈው ትውስታዬን ለመመለስ ነው
...........
ስንከላወስ ብዙ ማልጠግባቸው ጓደኞች አጊቻለሁ
ፍቅሬን ግን ከህይወት ትልቁ ሰአታችንን ከምናሳልፍበት ት /ቤት ነው ያገኘሁዋት
ፊያሜታ.......
የበአሉ ግርማዋን የኦሮማይ ድምቀት ፊያሜታ ጊላይ እናንተ እሷን ይሆናል የምታውቁት አይደል
እኔ ስለኔዋ ፊያሜታ ላወራችሁ ነው ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ ነው በጀብድ የተሞሉ የጥቁር አሜርካኖችንና የኮሎምቢያ የእፅ አዘዋዋሪዎችን ፊልም መመልከት የጀመርኩት
ቆይ አንዴ ዘፈኑን ልቀይርላችሁ
ቀዘብዬ የኔ ቀዘባ
ቀዘብዬ የኔ ቀዘባ
ስልሽ ጥላዬ የማለዳ ሲሳይ
የጠዋት እጣዬ ነይ ወለባዬ
ቴድዬ ነፍሴ መቶላቹሀል እኔም ጠብታዎቼን ላፅዳ እናንተም .....
ቀዘብዬን የከፈትኩት ለፊያዬ ለመጀመሪያ ጊዜ ያቀነቀንኩላት ዘፈን ነበር አሁንም እሷው ናት ብዬ ነው
አይ ፍቅር አሁን ድረስ ፊያዬ ነው የምላት እና ትውስታዬን መላሾች እናንተ በሰማችሁኝ ቁጥር ነው ትውስታዬን ምመልሰው
ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ ስኮመኩመው የነበረው ነገር ሙሉ ለሙሉ ጭንቅላቴን ተቆጣጥረው በቃ ሀሳቤ ሁሉ Drug diller መሆን ሆነ እንደ እነሱ የራሴን ቡድን አቋቁሜ ሁሉን መስራት አማረኝ
ሀሳቤ አይሎ አይሎ የፈነዳው 11ኛ ክፍል ከገባን በኋላ ነው
ምን እንዳረኩ አሁን ትዝ ባይለኝም በሆነ ነገር ከነበርኩበት ትምህርት ቤት ወጥቼ ፊያዬን ወዳገኘሁበት አዲሱ ት/ቤት የገባሁት
እንግዲህ አዲስ የህይወት ጅማሬ ጀመርኩ በዚች ትንሽ ትውስታዬ ማረሳው አንድ ሀቅ በጣም ደስተኛ እንደነበርኩኝ ነው
ጀንበር ተሰናብታ ሰማዩም ጠቆረ
ደሞ እንደ ልማዴ ይጨንቀኝ ጀመረ
ሙዚቃው ቀጥሏል
ለኔ ደስታ የፈጠረለኝ የመሰለኝ ነገር ለካ የህይወቴን ሰማይ እያጠለሸው እያጠቆረው ነበር
ይሄን የምላችሁ ካለሁበት የሰመመን ህይወትና ከንሰሀው መንገዴ ላይ ሆኜ ነው
ኑዛዜ አይደለም ግን ስም ያልሰጠሁትን ዳሽ በዳሽ ያልኩት ምዕራፌን እያወጋዋችሁ ነው
እቀጥላለሁ......
✍ብላቴናው በደም ቀለም
@wegoch
@wegoch
@wegoch
ክፍል - ፩
ጲላጦስ ነኝ - የጀግና አዝማሪ የሙዚቀኛ ልጅ ነኝ
ዜማ እስካሁን በመጣሁበት የህይወት ጎዳና ያልተለየኝ የኔ የምለው ቀረኝ የምለው ወዳጄ ነው
ብዙ ነገር ስላጣሁ ነው ዜማን አሁን ላይ ቀረኝ ያልኩት
ኑ እስቲ በውብ ሙዚቃዎች የህይወቴን ውብ ትዝታዎች ላጋራችሁ
መቼም በትዝታ አድማስ ወደ ኀላ ልወስዳችሁም አይደል
ውሎ አድሮ ነበረ ከተወኝ ፍቅርሽ
አስቸገረኝ እንጂ ዛሬ ትዝታሽ
በትዝታ አትጋርጂኝ አይኔን ልግለጥበት
ፍቅርሽን አንሺልኝ አልጨነቅበት
ሙሉቀን መለሰ ነው
ለመጀመሪያ ማጫወቺያዬን ከፍቼላቹሀለሁ አቤት ድምፅ እኔም በሱ ልሳን ወደ ኀላ ተመለስኩ
ዜማውን እያጣጣማችሁ
ይህ ነው የሚባል የህይወት ታሪክ ስለሌለኝ ለኔ ውድ ስለሆነው የፍቅር ታሪኬ ላጫውታችሁ
ለካስ ታሪክ የሚባለው በኖርንበት አለም ውስጥ አንስተን ምንሰጠው ስያሜ ነው
እኔ የኖርኩበትን ምዕራፍ ታሪኬ አልለውም ብቻ ዳሽ በዳሽ አድርጌዋለሁ
ኑ ለማንኛው ከትዝታዬ ጋር የኀሊት እንፍሰስ
የሙዚቃዋን ስንኝ አትርሷት
ውሎ አዳድሮብኛል አረ ሰነባብቶም ከርሞብኛል
ያው እንደ ዘፈኑ ፍቅርሽ አሁን ላይ ለቆኛል ብያለሁ እንግዲህ
ግና ትዝታዋ ሙሉ ትውስታዬን ተቆጣጥሮት የመርሳት በሽታ እንደገጠመው ሰው እሷ የገባችበትን ህይወቴን ብቻ ነው የማውቀው ሌላው ከትውስታ ማህደሬ ተሰርዟል
ሁሉም .......
በአካል መታ ከምደነግጠው በላይ ትዝታዋ ይበልጥ ያስደነግጠኛል ለምን እንደሆነ እንጃ
ሙልዬ እኮ መዝፈኑን ቀጥሏል ቆይ ጨመር ላድርግላችሁ
እኔም ፋታ ልውሰድ ሁሉን ሳስታውስ የማይቆም ነስር ስላለብኝ ከአፍንጫዬ ሚንጠባጠበውን ደም ልጥረገው
በስቃይ.....
ቀኑን እያቃዠ
ሌት የሚያባንነኝ
ትዝታሽ መሆኑ
ዛሬ ነው የገባኝ
ሙዚቃዋ ቀጥላለች እያጣጣማችሁ እኔም ይህን የደም ጠብታዬን አፅድቼ ተመልሻለሁ ሌላ ጠብታ እስኪመጣ እቀጥላለሁ
ስለ አፈቅርኩዋት ጉብል ትንሽ ልበላችሁ......
በየቦታው እየተንከላወሱ እያቀነቀኑ ከመዞር ሌላ ምንም ስራ የለኝም ሀሳብ አላማ ነገን የሚሉ ነገሮች ከህይወት መዝገቤ ላይ በጭራሽ የሉም ነበር
አረ እንደውም ግምሹ የእድሜ ዘመኔን በመዞር ነው ያለፈው ማለት ይቻላል
ግን እንዲ ስል ነፍፍፍፍፍ አመት የኖርኩ አይመስልም እድሜይንም ላስጠጣ ሆነ እኮ
ስለሷ ላወራ ብዬ ሌላ ነገር ምቀባጥረው ባሰብኳት ቁጥር ትልቅ ሀይል ያለው ነገር አናቴን ስለሚነድለኝ ነው መቆጣጠር ስለማልችል ቦታዬ ከመሬት ነው እራሴን እስክስት ድረስ ምቱ አይምረኝም
ለነገሩ ይበለኝ.....
በመዞሬ ጎዳኝ የምለው አንድም ነገር የለም ብዙ ነገር አትርፌበታለሁና ከምላችሁ በላይ ብዙ ነገር አይቼበታለሁ
ተፈጥሮን መርምሬበታለሁ እግሬ መሄድ ብቻ አይደለም ጭንቅላቴም ብዙ አይሽሬ ትዝታዎችን ስለያዘበት
አሁን ይህን ምፅፈው ትውስታዬን ለመመለስ ነው
...........
ስንከላወስ ብዙ ማልጠግባቸው ጓደኞች አጊቻለሁ
ፍቅሬን ግን ከህይወት ትልቁ ሰአታችንን ከምናሳልፍበት ት /ቤት ነው ያገኘሁዋት
ፊያሜታ.......
የበአሉ ግርማዋን የኦሮማይ ድምቀት ፊያሜታ ጊላይ እናንተ እሷን ይሆናል የምታውቁት አይደል
እኔ ስለኔዋ ፊያሜታ ላወራችሁ ነው ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ ነው በጀብድ የተሞሉ የጥቁር አሜርካኖችንና የኮሎምቢያ የእፅ አዘዋዋሪዎችን ፊልም መመልከት የጀመርኩት
ቆይ አንዴ ዘፈኑን ልቀይርላችሁ
ቀዘብዬ የኔ ቀዘባ
ቀዘብዬ የኔ ቀዘባ
ስልሽ ጥላዬ የማለዳ ሲሳይ
የጠዋት እጣዬ ነይ ወለባዬ
ቴድዬ ነፍሴ መቶላቹሀል እኔም ጠብታዎቼን ላፅዳ እናንተም .....
ቀዘብዬን የከፈትኩት ለፊያዬ ለመጀመሪያ ጊዜ ያቀነቀንኩላት ዘፈን ነበር አሁንም እሷው ናት ብዬ ነው
አይ ፍቅር አሁን ድረስ ፊያዬ ነው የምላት እና ትውስታዬን መላሾች እናንተ በሰማችሁኝ ቁጥር ነው ትውስታዬን ምመልሰው
ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ ስኮመኩመው የነበረው ነገር ሙሉ ለሙሉ ጭንቅላቴን ተቆጣጥረው በቃ ሀሳቤ ሁሉ Drug diller መሆን ሆነ እንደ እነሱ የራሴን ቡድን አቋቁሜ ሁሉን መስራት አማረኝ
ሀሳቤ አይሎ አይሎ የፈነዳው 11ኛ ክፍል ከገባን በኋላ ነው
ምን እንዳረኩ አሁን ትዝ ባይለኝም በሆነ ነገር ከነበርኩበት ትምህርት ቤት ወጥቼ ፊያዬን ወዳገኘሁበት አዲሱ ት/ቤት የገባሁት
እንግዲህ አዲስ የህይወት ጅማሬ ጀመርኩ በዚች ትንሽ ትውስታዬ ማረሳው አንድ ሀቅ በጣም ደስተኛ እንደነበርኩኝ ነው
ጀንበር ተሰናብታ ሰማዩም ጠቆረ
ደሞ እንደ ልማዴ ይጨንቀኝ ጀመረ
ሙዚቃው ቀጥሏል
ለኔ ደስታ የፈጠረለኝ የመሰለኝ ነገር ለካ የህይወቴን ሰማይ እያጠለሸው እያጠቆረው ነበር
ይሄን የምላችሁ ካለሁበት የሰመመን ህይወትና ከንሰሀው መንገዴ ላይ ሆኜ ነው
ኑዛዜ አይደለም ግን ስም ያልሰጠሁትን ዳሽ በዳሽ ያልኩት ምዕራፌን እያወጋዋችሁ ነው
እቀጥላለሁ......
✍ብላቴናው በደም ቀለም
@wegoch
@wegoch
@wegoch
#የደሜ ዜመኞች
ክፍል - ፪
ቀጥያለሁ......
team jungle boyz በትምህርት ቤታችን ታዋቂ ሆነናል
በስራችን ውስጥ የሌለ ተማሪ የለም ሁሉንም በኔትወርካችን ስር አድርገን ተደራሽነታችንን እስከ አስተማሪ ድረስ አድርሰነዋል በቃ ሁሉም ነገር ጭስ በጭስ ሆኑአል በኛ ምክንያት
አላማዬ መሉ በሙሉ ወደ ምፈልገው ቦታ ሄዶልኛል በዚ ዘመን ላለምነው አላማ መሳካት ያለምነው ነገር ሰውን ጎጂ መሆን አለበት
ሁሉም በር ካለምንም ልፋት ስለሚከፈትልን
ስለኛ ማያወራ ስለኛ ማያነሳ በኛ ስራ ማይቀና ሰው የለም
እኔም ከልጅነቴ ጀምሮ ሳየው የነበረው ነገር በተግባር በመፈጸሜ ከኔ በላይ የጀግንነት ስሜት የሚሰማው ሰው አልነበረም
በቃ ጀግና ነኝ....
ባለሁበት ትምህርት ቤት ውስጥ ካለው የተማሪ ብዛት 60% በላይ የሚህኑት ሴቶች ነበሩ በኔ የስራ አለም ውስጥ ፆታ ቀለም የሚባል ነገር የለም ሁሉንም ተደራሽ ማድረግ ነው ፍላጎቴ
ግን አብዛኛዎቹ ወንዶች በመሆናቸው ያን ያህል ተደራሽ እንዳሎንኩኝ ውስጤ በተደጋጋሚ ለጀግናው ስሜቴ ይነግረዋል
ሄዋንስ........
ሄዋንን ወደኔ ለማምጣት ሌላ ብልህ ሄዋን በጣም ታስፈልገኛለች እሷም ነይ ሳትባል ነው የመጣችው
ነገሩ ወዲህ ነው
አንድም ቀን ከጆሮዬ ኤርፎን ተለይቶኝ አያቅም #ኢስኮባር መጣ ኢስኮባር እንዲህ ሆነ ...
ኢስኮባር ነበር የሚሉኝ
ኢስኮባር ታዋቂ የኮሎምቢያ ሀሺሽ ነጋዴ ነው ኢስኮባር እሹ እራሱ አንድ መንግስት ነው ማለት ይቻላል
እኔም በሱ ስም በመጠራቴ ከፍ ያለ ስሜት ነበር የሚሰማኝ
አዎ ኢስኮባር ነበርኩ ትንሹ ኢስኮባር
አባቴ በአዝማሪነቱ የማያውቀው ሰው ያላካለለው ሀገር ያልዞረበት የባህል ቤት የለም
እኔም የማያውሸኝ ሰው በስራዬ ሙሉ የአዲስ አበባን ትምህርት ቤቶች እና ኩታራው የሚዝናናባቸውን ክለቦች በጠቅላላ ተቆጣጥሬ ነበር
የአዝማሪ ልጅ መሆኔን ለማሳወቅ ነው ሁሌ በሄድኩበት ሙዚቃ ማይለየኝ
በሄድኩበት ቦታ ሁሉ ሲሰማ የነበረው ሙዚቃ ይቀየራል ሁሉም ነገር ወደ ድሮ ይመለሳል
አንድም ሰው አያጉረመርምም
ፀጥ ረጭ ...... ኢስኮ ነኛ
ከአባቴ ቀጥሎ ያለኝ ነገር ሙዚቃ ነው አባቴም ከባቲ እና አምባሰል ካንቺሆዬን ትዝታ ቀጥሎ የምሰማው እሱ እራሱ አንዱ ሙዚቃዬ ነው
አባት አለሜ ለኔ የሰጠኝ ትልቁ ሀብት ሙዚቃ ነው
ሙዚቃ ህይወቴ አለ ቴዲዬ ነፍሴ
ወደ ፊያሜታ ልመልሳችሁ (ማንም ሳይጠራት መጣች)
አንዳንዴ ፍቅርን ከየት እንደምናገኝ አናውቀውም ስንዳክር ለኛ ባልተሰራ ሰው ስነንደክም ቆይተን ባላሰብነው ሰአት የኛ ሰው ከጎናችንን እናገኘዋለን
የኔ ...... ባትሆንም የኔ ነበረች
ትዝ ይለኛል መማር ያለመደው ጎኔ ዛሬም በተለመደችው ቦታ ቁጭ ብያለሁ ለምን እንደሆነ ባላውቅም ብቻዬን ነበርኩኝ
ገና ስመጣ ወደዚች ምድር
አሳደገችኝ ቀብታ ፍቅር
በልጅነቴ ከእቅፋ ሰርቃ
ነፍሴን ወሰደች ያቺ ሙዚቃ
ሳሚ ዳን ነው ብዙ አወጋዋችሁ እኔም የምፅፍበት ሉኬን ያበላሸውን ጠብታዬን ለፅዳ ድምጿን ጨመር አርጉት እኔም አንዴ ሰላም ያለው አየር ልውሰድ .......
ሰላም በሌለው ክፉ ትዝታ ውስጥ አፋኝ አየር እንጂ ንፁ ነገር የለም
ስቃይ ........
ለምን እንዲህ እንደሆንኩ አላቅም ጥግ ድረስ የልባችንን በራፍ ወገግ አርገን ስንከፍት የከፈትንለት ሰው ብቻውን መግባት ይፈራል መሰል ብዙ የልብ ምት አዋኪ ነገሮች ከልባችን ስር ይቀመጣሉ
ደም መዘዋወሩን አቁሞ በገባው ነገር ተደናግጥ እዛው ባለበት ይረጋል
ሌላ ደም ስለማይመጣ ልባችን ትቀዘቅዛል እራሷ ከፍታ ያስገባችውን አካል መልሳ ለማስወጣት ቅዝቃዜው ያስቸግራታል ለመሞቅ የትዝታዋን እሳት ስለለኩስ የረጋው ደም መፍላት ይጀምራል ይበልጥ ስቃይ
ትነቱ አእምሮ ጋ ሄዶ ይደልቀዋል ያኔ ያ ህመም ከህመሞች ሁሉ የባሰው ይሆናል
ምክንያቱም........
ማሰብ ቆሞ ልብ የምትሰጠንን ምስል ብቻ ማውጠንጠን ስለምንጀምር
ማሰብ ማቆም ነው የህመም ሁሉ ህመም
ልብ ሲተክዝ ሰወነት ይቆማል
ሰውነትም ሲቆም ማሰቡ የጠፋል
የኔ ሀሳብ ባንቺ ፍቅር ተመርዞ
ቢያስቸግረኝ ፍፁም ልቤን አስተክዞ
ተረታሁኝ ባንቺ ፍቅር ተይዤ
አሃ አሃ አሀሀሀሀሀሀሀሀሀሀ
ቁጭ ብዬ ቀረሁልሽ ተክዤ
አሃ አሃ አሀሀሀሀሀሀሀሀ
ሀሳብ ብቻ በልቤ ውስጥ ተመርኩዤ
ግርማ ነጋሽ ቀጥሏል ከዚ ዜማ በላይ ሊገልፀኝ የሚችለው ነገር የለም
የልብ ስብራት እንደ ጉልበት ስለማይታሽ እንደ ፀባዩ መያዝ ነው
አቃተኝ እናነተዬ ደምና እንባ እየጠከስኩ ነው ምፅፈው አቅሙ አጥሮኛል እጄ ተንቀጥቅጦ ቃላቱን በአንዱ ቃል ላይ እየደረበ ነው
ስቃይ.....
እቀጥላለሁ
✍ብላቴናው በደም ቀለም
@wegoch
@wegoch
@wegoch
ክፍል - ፪
ቀጥያለሁ......
team jungle boyz በትምህርት ቤታችን ታዋቂ ሆነናል
በስራችን ውስጥ የሌለ ተማሪ የለም ሁሉንም በኔትወርካችን ስር አድርገን ተደራሽነታችንን እስከ አስተማሪ ድረስ አድርሰነዋል በቃ ሁሉም ነገር ጭስ በጭስ ሆኑአል በኛ ምክንያት
አላማዬ መሉ በሙሉ ወደ ምፈልገው ቦታ ሄዶልኛል በዚ ዘመን ላለምነው አላማ መሳካት ያለምነው ነገር ሰውን ጎጂ መሆን አለበት
ሁሉም በር ካለምንም ልፋት ስለሚከፈትልን
ስለኛ ማያወራ ስለኛ ማያነሳ በኛ ስራ ማይቀና ሰው የለም
እኔም ከልጅነቴ ጀምሮ ሳየው የነበረው ነገር በተግባር በመፈጸሜ ከኔ በላይ የጀግንነት ስሜት የሚሰማው ሰው አልነበረም
በቃ ጀግና ነኝ....
ባለሁበት ትምህርት ቤት ውስጥ ካለው የተማሪ ብዛት 60% በላይ የሚህኑት ሴቶች ነበሩ በኔ የስራ አለም ውስጥ ፆታ ቀለም የሚባል ነገር የለም ሁሉንም ተደራሽ ማድረግ ነው ፍላጎቴ
ግን አብዛኛዎቹ ወንዶች በመሆናቸው ያን ያህል ተደራሽ እንዳሎንኩኝ ውስጤ በተደጋጋሚ ለጀግናው ስሜቴ ይነግረዋል
ሄዋንስ........
ሄዋንን ወደኔ ለማምጣት ሌላ ብልህ ሄዋን በጣም ታስፈልገኛለች እሷም ነይ ሳትባል ነው የመጣችው
ነገሩ ወዲህ ነው
አንድም ቀን ከጆሮዬ ኤርፎን ተለይቶኝ አያቅም #ኢስኮባር መጣ ኢስኮባር እንዲህ ሆነ ...
ኢስኮባር ነበር የሚሉኝ
ኢስኮባር ታዋቂ የኮሎምቢያ ሀሺሽ ነጋዴ ነው ኢስኮባር እሹ እራሱ አንድ መንግስት ነው ማለት ይቻላል
እኔም በሱ ስም በመጠራቴ ከፍ ያለ ስሜት ነበር የሚሰማኝ
አዎ ኢስኮባር ነበርኩ ትንሹ ኢስኮባር
አባቴ በአዝማሪነቱ የማያውቀው ሰው ያላካለለው ሀገር ያልዞረበት የባህል ቤት የለም
እኔም የማያውሸኝ ሰው በስራዬ ሙሉ የአዲስ አበባን ትምህርት ቤቶች እና ኩታራው የሚዝናናባቸውን ክለቦች በጠቅላላ ተቆጣጥሬ ነበር
የአዝማሪ ልጅ መሆኔን ለማሳወቅ ነው ሁሌ በሄድኩበት ሙዚቃ ማይለየኝ
በሄድኩበት ቦታ ሁሉ ሲሰማ የነበረው ሙዚቃ ይቀየራል ሁሉም ነገር ወደ ድሮ ይመለሳል
አንድም ሰው አያጉረመርምም
ፀጥ ረጭ ...... ኢስኮ ነኛ
ከአባቴ ቀጥሎ ያለኝ ነገር ሙዚቃ ነው አባቴም ከባቲ እና አምባሰል ካንቺሆዬን ትዝታ ቀጥሎ የምሰማው እሱ እራሱ አንዱ ሙዚቃዬ ነው
አባት አለሜ ለኔ የሰጠኝ ትልቁ ሀብት ሙዚቃ ነው
ሙዚቃ ህይወቴ አለ ቴዲዬ ነፍሴ
ወደ ፊያሜታ ልመልሳችሁ (ማንም ሳይጠራት መጣች)
አንዳንዴ ፍቅርን ከየት እንደምናገኝ አናውቀውም ስንዳክር ለኛ ባልተሰራ ሰው ስነንደክም ቆይተን ባላሰብነው ሰአት የኛ ሰው ከጎናችንን እናገኘዋለን
የኔ ...... ባትሆንም የኔ ነበረች
ትዝ ይለኛል መማር ያለመደው ጎኔ ዛሬም በተለመደችው ቦታ ቁጭ ብያለሁ ለምን እንደሆነ ባላውቅም ብቻዬን ነበርኩኝ
ገና ስመጣ ወደዚች ምድር
አሳደገችኝ ቀብታ ፍቅር
በልጅነቴ ከእቅፋ ሰርቃ
ነፍሴን ወሰደች ያቺ ሙዚቃ
ሳሚ ዳን ነው ብዙ አወጋዋችሁ እኔም የምፅፍበት ሉኬን ያበላሸውን ጠብታዬን ለፅዳ ድምጿን ጨመር አርጉት እኔም አንዴ ሰላም ያለው አየር ልውሰድ .......
ሰላም በሌለው ክፉ ትዝታ ውስጥ አፋኝ አየር እንጂ ንፁ ነገር የለም
ስቃይ ........
ለምን እንዲህ እንደሆንኩ አላቅም ጥግ ድረስ የልባችንን በራፍ ወገግ አርገን ስንከፍት የከፈትንለት ሰው ብቻውን መግባት ይፈራል መሰል ብዙ የልብ ምት አዋኪ ነገሮች ከልባችን ስር ይቀመጣሉ
ደም መዘዋወሩን አቁሞ በገባው ነገር ተደናግጥ እዛው ባለበት ይረጋል
ሌላ ደም ስለማይመጣ ልባችን ትቀዘቅዛል እራሷ ከፍታ ያስገባችውን አካል መልሳ ለማስወጣት ቅዝቃዜው ያስቸግራታል ለመሞቅ የትዝታዋን እሳት ስለለኩስ የረጋው ደም መፍላት ይጀምራል ይበልጥ ስቃይ
ትነቱ አእምሮ ጋ ሄዶ ይደልቀዋል ያኔ ያ ህመም ከህመሞች ሁሉ የባሰው ይሆናል
ምክንያቱም........
ማሰብ ቆሞ ልብ የምትሰጠንን ምስል ብቻ ማውጠንጠን ስለምንጀምር
ማሰብ ማቆም ነው የህመም ሁሉ ህመም
ልብ ሲተክዝ ሰወነት ይቆማል
ሰውነትም ሲቆም ማሰቡ የጠፋል
የኔ ሀሳብ ባንቺ ፍቅር ተመርዞ
ቢያስቸግረኝ ፍፁም ልቤን አስተክዞ
ተረታሁኝ ባንቺ ፍቅር ተይዤ
አሃ አሃ አሀሀሀሀሀሀሀሀሀሀ
ቁጭ ብዬ ቀረሁልሽ ተክዤ
አሃ አሃ አሀሀሀሀሀሀሀሀ
ሀሳብ ብቻ በልቤ ውስጥ ተመርኩዤ
ግርማ ነጋሽ ቀጥሏል ከዚ ዜማ በላይ ሊገልፀኝ የሚችለው ነገር የለም
የልብ ስብራት እንደ ጉልበት ስለማይታሽ እንደ ፀባዩ መያዝ ነው
አቃተኝ እናነተዬ ደምና እንባ እየጠከስኩ ነው ምፅፈው አቅሙ አጥሮኛል እጄ ተንቀጥቅጦ ቃላቱን በአንዱ ቃል ላይ እየደረበ ነው
ስቃይ.....
እቀጥላለሁ
✍ብላቴናው በደም ቀለም
@wegoch
@wegoch
@wegoch
#የደሜ ዜመኞች
ክፍል - ፫
ቀጥያሉ.....
ከታፈንኩበት አየር ተመልሻለሁ ትንጋዬንም ጠረግ ጠረግ አድርጌዋለሁ
ቅድም ከተሰቃየሁት በላይ ስቃይ መሰቃየት ልጀምር ነው መሰለኝ
ማብቂያ የሌለው ስቃይ የእቶን ቃጠሎ ከበርባሮስ በጠለቀ ፅልመት ውስጥ ነኝ
ፊያ.....
ኢስኮ ኢስኮ አለቺኝ ሰምቻታለሁ ግን እንደሌሎቹ ወይ ሰላም ለማለት ወይ እንደተለመደው .......
መጣራቱ ቆሞ ከአጠገቤ መታ ጀርባዬን ደለቀቺኝ
ምን አይነት ድፍረት ነው ደሜ ፈላ ብዙ ነገር ልናገር የተነሳሁት ልጅ አፌ ፀጥ ረጭ አለ
አነሳሴ አስደንግጡአት ነው መሰለ ትናንሽ እጆቹአን ቀሚሷ ላይ አርጋ አንገቱአን ደፋች
ያ የደለቀኝ ድፍረቷ የት ገባ
እእእእእእእእ ምድነው አልኳት
ቀና ብላ አየቺኝ ረጅሙ ፀጉሯ አንድ አይኗን እስከ ግማሽ ከንፈሯ ሸፍኖታል
የጎደለ የፊት ገፅታ ግን ምንኛ ታምራለች በአባባ ሞት
ፈጠን ብላ
እኔ ካንተ ጋ መቀላለቀል እፈልጋለሁ ምንም አታስብ ጭራሽ ሀሳብ አይግባህ የሰጠኸኝን ዛሬውኑ
አየር እንኳ አቶስድም ስታወራ ከንፈሯ ላይ የተጣበቀው ፀጉሯ ለማውራት ስላዳገታት ሙሉ ጸጉሯን በአለንጋ ጣቶቹአ ወደ ኀላ አሸሸችው
ያ ግማሽ ውበት አሁን በሙሉ ሆኖ ደሜን ያራውጠው ጀመር
እእእእእ በናትህ ኢስኮ ቃጭል ድምጿ ከሀሳቤ አነቃኝ
ምን አለ በደንብ በሀሳቤ ብከትሽ
ምንም ሳላቅማማ ከቀኑ የቢዝነስ ስራ የተረፈውን 5 ክርታስ ሰጠሁዋት
ዘላ ተጠመጠቺብኝ ትንፋሿ ይፋጃል ገና ከመመሰጤ ጥላኝ ሄደች ......
ከመሄዷ አይኔን አንከራተተችው ልፍለፋዋ ዝም ብሎ ይታወሰኝ ገባ
ለነገ የሰጠሁዋትን ትሽጥም አትሽጥም እሷን ማግኘት ለኔ ከብሩ በላይ አጓጊ ሆኑአል
አዳሬን ሙሉ እሷን ማሰብ ሆነ ከዚ በፊት ለብዙ ሴቶች እንዲ አይነት ስሜት ተሰምቶኝ ያውቃል ይሄም ስሜቴም ብዙ እንግዳ አሎነብኝም
መጣ መሄዷ ስለማይቀር......
ይገርማል ቁመናና ዛላ
ልዩ ነው የፀጉሯ ዘለላ
ጥርሶቿ አቀማመጣቸው
ይገርማል አቤት ንፃታቸው
ጥልዬ ደሞ መቷል በተራው በጣም ይገልፃታል ይሄ ዜማ በሉ በምናባችሁ የኔ ፀጉረ ዘለላ ምን እንደምትመስል እየሳላችሁ ጠብቁኝ
እኔም እንደለመደብኝ ...........
አይነጋ የለ አዲሷ የቢዝነስ አጋሬ ስታቃዠኝ አድራ ከመኝታ ቤቴ ከምተገባው ጮራ ጋ ውብ ፊቷ ድቅን ይል ጀመረ
ገና በጠዋቱ ....
አባቴ ተነስቶ ወዲ ወዲያ ይላል እንደለመደው ሬዲዮኗ ተከፍታ ጥዑም ዜማ እያደረሰችን ነው
ማለዳ ፀሀይ ስቶጣ ደማምቃ
ከእንቅልፌ ድንገት ባንኜ ስነቃ
ፈጣሪን በቀኝ አውለኝ እላለሁ
አምላኬን ስሙን ሳነሳ እውላለሁ
ቴዎድሮስ ታደሰ ነው አባቴ ነፍሱ እስኪወጣ ነው ሚወደው
ዘፈኑ ለአመስጋኝ እንጂ ለኔ አይነቱ ተራሰው እንደማይሆን ባውቅም ቀኑን ሙሉ ምለሴ ላይ ዋለ
መማርን አላማ አድርጌ ወደ ምማርበት ቦታ ሄጄ አላውቅም
ዛሬም ማለዳ ከምላሴ ያቺ ውብ ደሞ ከጭንቅላቴ ተጣበቀው ዋሉ
ዛሬ ከመጣችልኝ ቀኔ ነው በቃ ምን አልባትም ዜማው ሳይረዳኝ አልቀረም መሰል
ፊያሜታ ከፊት ለፊቴ .........
እቀጥላለሁ
✍ብላቴናው በደም ብዕር
@wegoch
@wegoch
@wegoch
ክፍል - ፫
ቀጥያሉ.....
ከታፈንኩበት አየር ተመልሻለሁ ትንጋዬንም ጠረግ ጠረግ አድርጌዋለሁ
ቅድም ከተሰቃየሁት በላይ ስቃይ መሰቃየት ልጀምር ነው መሰለኝ
ማብቂያ የሌለው ስቃይ የእቶን ቃጠሎ ከበርባሮስ በጠለቀ ፅልመት ውስጥ ነኝ
ፊያ.....
ኢስኮ ኢስኮ አለቺኝ ሰምቻታለሁ ግን እንደሌሎቹ ወይ ሰላም ለማለት ወይ እንደተለመደው .......
መጣራቱ ቆሞ ከአጠገቤ መታ ጀርባዬን ደለቀቺኝ
ምን አይነት ድፍረት ነው ደሜ ፈላ ብዙ ነገር ልናገር የተነሳሁት ልጅ አፌ ፀጥ ረጭ አለ
አነሳሴ አስደንግጡአት ነው መሰለ ትናንሽ እጆቹአን ቀሚሷ ላይ አርጋ አንገቱአን ደፋች
ያ የደለቀኝ ድፍረቷ የት ገባ
እእእእእእእእ ምድነው አልኳት
ቀና ብላ አየቺኝ ረጅሙ ፀጉሯ አንድ አይኗን እስከ ግማሽ ከንፈሯ ሸፍኖታል
የጎደለ የፊት ገፅታ ግን ምንኛ ታምራለች በአባባ ሞት
ፈጠን ብላ
እኔ ካንተ ጋ መቀላለቀል እፈልጋለሁ ምንም አታስብ ጭራሽ ሀሳብ አይግባህ የሰጠኸኝን ዛሬውኑ
አየር እንኳ አቶስድም ስታወራ ከንፈሯ ላይ የተጣበቀው ፀጉሯ ለማውራት ስላዳገታት ሙሉ ጸጉሯን በአለንጋ ጣቶቹአ ወደ ኀላ አሸሸችው
ያ ግማሽ ውበት አሁን በሙሉ ሆኖ ደሜን ያራውጠው ጀመር
እእእእእ በናትህ ኢስኮ ቃጭል ድምጿ ከሀሳቤ አነቃኝ
ምን አለ በደንብ በሀሳቤ ብከትሽ
ምንም ሳላቅማማ ከቀኑ የቢዝነስ ስራ የተረፈውን 5 ክርታስ ሰጠሁዋት
ዘላ ተጠመጠቺብኝ ትንፋሿ ይፋጃል ገና ከመመሰጤ ጥላኝ ሄደች ......
ከመሄዷ አይኔን አንከራተተችው ልፍለፋዋ ዝም ብሎ ይታወሰኝ ገባ
ለነገ የሰጠሁዋትን ትሽጥም አትሽጥም እሷን ማግኘት ለኔ ከብሩ በላይ አጓጊ ሆኑአል
አዳሬን ሙሉ እሷን ማሰብ ሆነ ከዚ በፊት ለብዙ ሴቶች እንዲ አይነት ስሜት ተሰምቶኝ ያውቃል ይሄም ስሜቴም ብዙ እንግዳ አሎነብኝም
መጣ መሄዷ ስለማይቀር......
ይገርማል ቁመናና ዛላ
ልዩ ነው የፀጉሯ ዘለላ
ጥርሶቿ አቀማመጣቸው
ይገርማል አቤት ንፃታቸው
ጥልዬ ደሞ መቷል በተራው በጣም ይገልፃታል ይሄ ዜማ በሉ በምናባችሁ የኔ ፀጉረ ዘለላ ምን እንደምትመስል እየሳላችሁ ጠብቁኝ
እኔም እንደለመደብኝ ...........
አይነጋ የለ አዲሷ የቢዝነስ አጋሬ ስታቃዠኝ አድራ ከመኝታ ቤቴ ከምተገባው ጮራ ጋ ውብ ፊቷ ድቅን ይል ጀመረ
ገና በጠዋቱ ....
አባቴ ተነስቶ ወዲ ወዲያ ይላል እንደለመደው ሬዲዮኗ ተከፍታ ጥዑም ዜማ እያደረሰችን ነው
ማለዳ ፀሀይ ስቶጣ ደማምቃ
ከእንቅልፌ ድንገት ባንኜ ስነቃ
ፈጣሪን በቀኝ አውለኝ እላለሁ
አምላኬን ስሙን ሳነሳ እውላለሁ
ቴዎድሮስ ታደሰ ነው አባቴ ነፍሱ እስኪወጣ ነው ሚወደው
ዘፈኑ ለአመስጋኝ እንጂ ለኔ አይነቱ ተራሰው እንደማይሆን ባውቅም ቀኑን ሙሉ ምለሴ ላይ ዋለ
መማርን አላማ አድርጌ ወደ ምማርበት ቦታ ሄጄ አላውቅም
ዛሬም ማለዳ ከምላሴ ያቺ ውብ ደሞ ከጭንቅላቴ ተጣበቀው ዋሉ
ዛሬ ከመጣችልኝ ቀኔ ነው በቃ ምን አልባትም ዜማው ሳይረዳኝ አልቀረም መሰል
ፊያሜታ ከፊት ለፊቴ .........
እቀጥላለሁ
✍ብላቴናው በደም ብዕር
@wegoch
@wegoch
@wegoch
#የደሜ ዜመኞች
ክፍል - ፬
ቀጥያለሁ ......
የዛሬዋ ማለዳ ምንኛ ትለያለች ካየሁዋቸው ማለዳዎች ይቺ ለየት ሳትል አትቀርም
በማለዳ ዜማ ገና በማለደው እንደ ማለዳዋ ጮራ የፈካችው ልጅ ከፊት ለፊቴ ቆማለች
ዛሬም ያ እረጅም ፀጉር ይበልጥ አምሮበታል ከለበሰችው ጥቁር ጃኬት ጋ በቃ ዝም ነው
በዛች ትንሽ ንግግር ውስጥ እኔጋ ብዙ ስሜቶች ገብተዋል እኔም እንደመጣች ከእቅፌ አስገባሁዋት
ሌላ ስሜት ወደ ውስጤ ሲገባ ተሰማኝ
እቅፍ አደረኩዋት
ጠረኗ ዛሬም አልተቀየረም እራሷ ተጠምጥማ ያሸተትኩትን ጠረን ዛሬ እኔ ተጠምጥሜባት መልሼ እያሸተትኩት ነው
በጣቶቹአ የያዘችውን ብር ከደረት ኪሰ ከተተችልኝ
መተቃቀፉ አበቃ
ኤጭ.....
እየው ኮሚሽኔ ከዛሬ ጀምሮ ይታሰብልኝ ደሞ ወደህ ነው ማታስብልኝ እኔ በአንድ ስራ ብቻ ትንሽ ነገር መውሰድ ስለማልፈልግ ነው እሺ ሙሉ ብሩን የሰጠሁህ
ያ የማውራት ፍጠነቱአ ዛሬም አልቆመም
አይኔ ከንፈሯ ላይ ነው
እና አጋሮች ሆነናላ ተስማምተናል አይደል
አፌን ምን እንደለጎመኝ አላውቅም አይኔን ከከንፈሯ ነቅዬ አይኗ ላይ ተከልኩት ትክ ብዬ እያየሁዋት አንገቴን በአዎንታ ነቀነኩላት
በኔ ዝምታ ውስጥ ትልቅ ጩኸት አለ
መልሴ አስደሰታት መሰለኝ ደስ የሚል ትንሽዬ ፈገግታ ሰታኝ ቻው አለቺኝ
እቅፉአን ናፈኩት
ድንገት ከሄደችበት ተንደርድራ መታ ከንፈሯን ጉንጮቼ ላይ አሳረፈቻቸው
ኡፋ በአባባ ሞት
በዚች ማለዳ ውስጤን ያጠልቀለቀ ሀሴት ሲገባ ተሰማኝ
እርቃ ሳቴድ ታድያ ምሳ ልጋብዝሽ አልኩዋት
ቡና ይሁንልኝ ..... መለሰችልኝ
አቤት ፍጥነቷ
ፍጥነቷን ተጠቅማ ሳይሆን አይቀርም ከስሜቴ ዘላ እንዲህ በፍጥነት የገባችው
እጄ ከንፈሯ ያረፈበት ጉንጬ ላይ ነው አጣብቄው ቀርቻለው
ፍዝዝ ድንዝዝ ........
የልቤ በራፍ ሰተት ብሎ ሲከፈት ተሰማኝ በልቤ አዳራሽ እንድትገባ እኔም ፈቀድኩላት
በሩን ቶሎ አልዘጋሁትም
ምን ልበላችሁ በቃ ልዩ ሆነቺብኛ ምን አባቴ ላርግ
በፍላጎቴ ሰው ለመውደድ ስሞክር ታወቀኝ
ብዙ ጊዜ ፍቅር ሲይዘን ሁሌ ሳናስበውና ሳናስተውለው ስለሆነ ፍቅር እሱ እራሱ ሚታዘበን ይመስላል
እንዲህ ደሞ በፍላጎት ሲሆን በረከቱ እራሱ ሚበዛ ይመስለኛል
እናንተዬ ብዙ አሶራችሁኝ እኮ
እስቲ እቺን ጀባ ልበላችሁ እኔም ጠብታዎቼን ላፅዳ
የልቤን አዳራሽ መኖሪያ አርገዋለች
ወይስ የምሯን ነው ወይ ትቀልዳለች
ከልቤ አዳራሽ ውስጥ ሰተት ብላ ገብታ
ውስጥ የነበሩን በሙሉ አሶጥታ
መልካሙ ተበጀ ነው በፍላጎቴ አዳራሼን ከፍቼ ልቤን ልበላ ነው
ከትዝታዬ ተመልሻለሁ
ትንሽ የሙዚቃዋን ድምፅ ቀነስ አድርጉአት
ልቤም የአዳራሹን በር መክፈቱን እንጂ በየትኛው ቁልፍ ተዘግቶ ቁልፉን ከየት እንደጣለው ማያውቀው
ለዛም ነው በዘህ አሁን ባለሁበት ሁኔታ የልቤን አዳራሽ ከፍቼ ውስጡ ያለችውን ሰው ጎትቼ ማውጣት ያቃተኝ
ምክንያቱም ቁልፉ እኔጋ ስለሌ
አንዴ ከተዘጋ የልብን በር መክፈቻ ቁልፍ ማግኘት ይከብዳል
ቁልፉም አንዴ ብቻ ነው መሰል ለመክፈቻነት ሚያገለግለው
ለዛም ነው ብዙ ከፋቾች ወደ በራችን በር ሲመጡ በሩን መክፈት ሚከብዳቸው
የዘጋው መልሶ ከፍቶ ካልወጣ ከውጪ ሆኖ ማንም ሊከፍተው አይችልም
እሷም መልሳ እንዳቶጣ ከዚ ዘንድ የለችም
እሷ ግን የት ናት ወደትዝታዬ ስመለስ አወጋቹሀለሁ
እመለሳለሁ.....
✍ብላቴናው በደም ቀለም
@wegoch
@wegoch
@wegoch
ክፍል - ፬
ቀጥያለሁ ......
የዛሬዋ ማለዳ ምንኛ ትለያለች ካየሁዋቸው ማለዳዎች ይቺ ለየት ሳትል አትቀርም
በማለዳ ዜማ ገና በማለደው እንደ ማለዳዋ ጮራ የፈካችው ልጅ ከፊት ለፊቴ ቆማለች
ዛሬም ያ እረጅም ፀጉር ይበልጥ አምሮበታል ከለበሰችው ጥቁር ጃኬት ጋ በቃ ዝም ነው
በዛች ትንሽ ንግግር ውስጥ እኔጋ ብዙ ስሜቶች ገብተዋል እኔም እንደመጣች ከእቅፌ አስገባሁዋት
ሌላ ስሜት ወደ ውስጤ ሲገባ ተሰማኝ
እቅፍ አደረኩዋት
ጠረኗ ዛሬም አልተቀየረም እራሷ ተጠምጥማ ያሸተትኩትን ጠረን ዛሬ እኔ ተጠምጥሜባት መልሼ እያሸተትኩት ነው
በጣቶቹአ የያዘችውን ብር ከደረት ኪሰ ከተተችልኝ
መተቃቀፉ አበቃ
ኤጭ.....
እየው ኮሚሽኔ ከዛሬ ጀምሮ ይታሰብልኝ ደሞ ወደህ ነው ማታስብልኝ እኔ በአንድ ስራ ብቻ ትንሽ ነገር መውሰድ ስለማልፈልግ ነው እሺ ሙሉ ብሩን የሰጠሁህ
ያ የማውራት ፍጠነቱአ ዛሬም አልቆመም
አይኔ ከንፈሯ ላይ ነው
እና አጋሮች ሆነናላ ተስማምተናል አይደል
አፌን ምን እንደለጎመኝ አላውቅም አይኔን ከከንፈሯ ነቅዬ አይኗ ላይ ተከልኩት ትክ ብዬ እያየሁዋት አንገቴን በአዎንታ ነቀነኩላት
በኔ ዝምታ ውስጥ ትልቅ ጩኸት አለ
መልሴ አስደሰታት መሰለኝ ደስ የሚል ትንሽዬ ፈገግታ ሰታኝ ቻው አለቺኝ
እቅፉአን ናፈኩት
ድንገት ከሄደችበት ተንደርድራ መታ ከንፈሯን ጉንጮቼ ላይ አሳረፈቻቸው
ኡፋ በአባባ ሞት
በዚች ማለዳ ውስጤን ያጠልቀለቀ ሀሴት ሲገባ ተሰማኝ
እርቃ ሳቴድ ታድያ ምሳ ልጋብዝሽ አልኩዋት
ቡና ይሁንልኝ ..... መለሰችልኝ
አቤት ፍጥነቷ
ፍጥነቷን ተጠቅማ ሳይሆን አይቀርም ከስሜቴ ዘላ እንዲህ በፍጥነት የገባችው
እጄ ከንፈሯ ያረፈበት ጉንጬ ላይ ነው አጣብቄው ቀርቻለው
ፍዝዝ ድንዝዝ ........
የልቤ በራፍ ሰተት ብሎ ሲከፈት ተሰማኝ በልቤ አዳራሽ እንድትገባ እኔም ፈቀድኩላት
በሩን ቶሎ አልዘጋሁትም
ምን ልበላችሁ በቃ ልዩ ሆነቺብኛ ምን አባቴ ላርግ
በፍላጎቴ ሰው ለመውደድ ስሞክር ታወቀኝ
ብዙ ጊዜ ፍቅር ሲይዘን ሁሌ ሳናስበውና ሳናስተውለው ስለሆነ ፍቅር እሱ እራሱ ሚታዘበን ይመስላል
እንዲህ ደሞ በፍላጎት ሲሆን በረከቱ እራሱ ሚበዛ ይመስለኛል
እናንተዬ ብዙ አሶራችሁኝ እኮ
እስቲ እቺን ጀባ ልበላችሁ እኔም ጠብታዎቼን ላፅዳ
የልቤን አዳራሽ መኖሪያ አርገዋለች
ወይስ የምሯን ነው ወይ ትቀልዳለች
ከልቤ አዳራሽ ውስጥ ሰተት ብላ ገብታ
ውስጥ የነበሩን በሙሉ አሶጥታ
መልካሙ ተበጀ ነው በፍላጎቴ አዳራሼን ከፍቼ ልቤን ልበላ ነው
ከትዝታዬ ተመልሻለሁ
ትንሽ የሙዚቃዋን ድምፅ ቀነስ አድርጉአት
ልቤም የአዳራሹን በር መክፈቱን እንጂ በየትኛው ቁልፍ ተዘግቶ ቁልፉን ከየት እንደጣለው ማያውቀው
ለዛም ነው በዘህ አሁን ባለሁበት ሁኔታ የልቤን አዳራሽ ከፍቼ ውስጡ ያለችውን ሰው ጎትቼ ማውጣት ያቃተኝ
ምክንያቱም ቁልፉ እኔጋ ስለሌ
አንዴ ከተዘጋ የልብን በር መክፈቻ ቁልፍ ማግኘት ይከብዳል
ቁልፉም አንዴ ብቻ ነው መሰል ለመክፈቻነት ሚያገለግለው
ለዛም ነው ብዙ ከፋቾች ወደ በራችን በር ሲመጡ በሩን መክፈት ሚከብዳቸው
የዘጋው መልሶ ከፍቶ ካልወጣ ከውጪ ሆኖ ማንም ሊከፍተው አይችልም
እሷም መልሳ እንዳቶጣ ከዚ ዘንድ የለችም
እሷ ግን የት ናት ወደትዝታዬ ስመለስ አወጋቹሀለሁ
እመለሳለሁ.....
✍ብላቴናው በደም ቀለም
@wegoch
@wegoch
@wegoch
#የደሜ ዜመኞች
ክፍል - ፭
ቀጥያለሁ.....
ወደ ትዝታዬ ሚገፋኝ እህህህ ብሎ ሚሰማኝ ስለሆን አብራችሁኝ ፍሰሱ
ከዚ ዘንድ የሌለችው የኔ አለም ከየትኛው ቦታ ወደ የትኛው ሌላ አለም እንደገባች በደንብ አውቃለሁ
አዎ ከኔ አለም ወደ ሌላ አለም
እሷ ያለችበትን አለም ቶሎ መናገር አልፈልግም የሷን አለም መገኛውን ምነግራችሁ እኔም ወደዛ ለመሄድ መንገድ ስጀምር ነው
ለጊዜው ብዙ ምነግራችሁ ውብ ትዝታዎች አሉኝ
ወደ ትዝታዬ ተመልሻለሁ
ቅደም የተለያየንበት ቦታ ሁለታችንም እኩል ተገናኝተናል እሷም ወደ እኔ እኔም ወደ እሷ በፍቅር መላእክቶች ጠሪነት
ቁጥብ ፈገግታዋና ችኩልነቷ ተደምረው በቃ መፍዘዝ ሆኑአል ስራዬ
ወደ ቡናችን እንሂድ ፈጠን ብላ አነቃቺኝ
የቅደሚ እጄን ወደ ፊት ዘረጋሁላት ግድ የለም ቅደም ወደ ፊት ገፋችኝ
ታስገርመኝ ጀምሯል አይኔ አይኗ ላይ ነው
ጀርባዬን ትመታኛለች ከደረጃዎቹ ስንወርድ እጆቼን ትጎትተኛለች በቃ
ደስ የሚል ስቃይ.......
ባለፍንበት መንገድ ሁሉ ኢስኮና ፊያሜታ ሆኑአል ወሬው
እስከ ዚች ሰአት ድረስ ስሟን አልጠየኩዋትም ፊያሜታ መሆኑአን ያወኩት ጓደኛዬ ጠበቅ አርጋት የወንዱ ሁሉ አይን እሷ ላይ ብሎ የነገረኝ ሰአት ነው
ቡናችንን አዘን ቁጭ ብለን ደስ የሚል ጨዋታ ላይ ነን
ቆንጆ የቡና ሱሰኛ ናት ለነገሩ እኔም ካልጠጣሁ አይሆንልኝም
ስምሽ ግን ማነው በወሬያችን መሀል እንዳላወቀ ሆኜ ጥያቄዬን ወረወርኩላት
ፊያሜታ እባላለሁ ችኩል ብላ ተነስታ እጇን ዘረጋችልኝ
ምን አይነት እብደት ነው በጣም አሳቀቺኝ
ደስ አለኝ በቃ
እጄን ዘርግቼ ሰላምታዬን ስሰጣት መልሳ ከጎኔ ተቀመጠች
አይኖች ሁሉ ወደ እኛ ናቸው በቃ
የተማሪው አፍ በእኛ ወሬ ተጠምዶ ቡናው በስቅታ ነው የጨረስነው
እኔ ምልህ አይኗን ወደ አይኔ ተክላ እንዲህ ታዋቂ ነህ እንዴ ደሞ ተወዳጅ በዛ ላይ ቆንጆ
አቤት አቤት አረ አታሽኮርምሚኝ ጨዋታችን ሳቅ ብቻ ሆነ
ይልቅ አሁን ወደ ስራ በል ተነስ ተነስ የጠጣንበትን ሲኒ መልሰን ተነስተን ሄድን
ወደ ክፍሏ ይዛኝ ሄደች
ገባን በሩን ጥርቅም አደረገችው
ቡናው አስክሯት ነው መሰል ዝም ብላ ትስቃለች
ቁጥብ ፈገግታዋ ተቀይሮ እንዲህ ስትስቅ ሳያት ማላውቀው ስሜት ይነዝረኝ ጀመር
ዴስኮቹ ላይ ተቀመጥን በስራዬ ቀልጣፋና ፈጣን መሆኔን በባለፈው ስራዬ ተረድተሀል አይደል
ምንም እንደታስብ ጭራሽ በቃ 60% የትምህርት ቤቱን ሴት በእቅድህ አስገባልሀለሁ
በባለፈው የሰገሁሽ ሙሉ በሴቶች ነው ያለቀው ገርሞኝ ጥያቄዬን ወረወርኩላት
አዎና አለቺኝ.....
አንተ ከላይ አለክ ከበታችህ ብዙ ሰዎች እኔ ግን ከሁሉም በላይ አስፈልግሀለሁ በራስ መተማመኗ አስገረመኝ
ስለዚህ ሀሳብ አይግባህ ኢስኮዬ የሸሚዜን ኮሌታ ጨምድዳ ይዛ ይበልጥ ተጠጋችኝ ከመቀራረባችን የተነሳ በአይኗ ብሌን መልኬን አየሁት አይኗ ውብ ነው የሆነ ሀይል ያለው አካል
ትንፋሿ አጋለኝ ይበልጥ ተጠጋጋን አፍንጫዎቻችን እስኪነካኩ ድረስ መጠጋጋታችን አላቆመም ቀይ ፊቷ እዛው እያየሁት በርበሬ መሰለ እጆቼን ወደ አንገቷ ላኩት
እንቅ አደረኩዋት
አየር ሳንስብ ሁለታችንም አየር ተሰጣጠን ትንፋሽ የለም ቆዳዬን ትኩሱ ትንፋሿ ይገርፈው ጀመር
ያንን ከንፈር በቃ.......
እናንተዬ ኑ ተመለሱ በቃ ስቃዬን አበዛችሁት እኮ ትንሽ ዜማ እንስማ እንጂ እኔም ጠብታዎቼን እንደተለመደው ላፅዳ
ድንቅ ልጅ ድንቅ ነው ውበትሽ
ከዋክብት ናቸው አይኖችሽ
አቤት ቅርፀ ስራው የከናፍርሽ
ፈገግማ ስትይ ሌላ ነው ጥርስሽ
መሀሙድን ከፈትኩላችሁ
አዎና ማንም ምንም ብዬ ባልሰየምኩአት ልጅ የማላውቀው ስሜት ውስጥ ተወርውሬያለሁ
ማን ምን ብለን ሳንጠይቅ ሚሰማን ፍቅር ነው ሌላ ልዩ አለም ውስጥ ሚከተን በቃ እኔም እዛ ልዩ አለም ውስጥ ነበርኩኝ እንዲህ ትዝታን ብቻ ታቅፌ ከመቀመጤ በፊት
አሁንማ ልዩ አለም ውስጥ ሳልሆን ልዩ ስቃይ ውስጥ ነኝ
ወደ ትዝታዬ እመለሳለሁ ......
እቀጥላለሁ
✍ብላቴናው በደም ቀለም
@Wegoch
@wegoch
@wegoch
ክፍል - ፭
ቀጥያለሁ.....
ወደ ትዝታዬ ሚገፋኝ እህህህ ብሎ ሚሰማኝ ስለሆን አብራችሁኝ ፍሰሱ
ከዚ ዘንድ የሌለችው የኔ አለም ከየትኛው ቦታ ወደ የትኛው ሌላ አለም እንደገባች በደንብ አውቃለሁ
አዎ ከኔ አለም ወደ ሌላ አለም
እሷ ያለችበትን አለም ቶሎ መናገር አልፈልግም የሷን አለም መገኛውን ምነግራችሁ እኔም ወደዛ ለመሄድ መንገድ ስጀምር ነው
ለጊዜው ብዙ ምነግራችሁ ውብ ትዝታዎች አሉኝ
ወደ ትዝታዬ ተመልሻለሁ
ቅደም የተለያየንበት ቦታ ሁለታችንም እኩል ተገናኝተናል እሷም ወደ እኔ እኔም ወደ እሷ በፍቅር መላእክቶች ጠሪነት
ቁጥብ ፈገግታዋና ችኩልነቷ ተደምረው በቃ መፍዘዝ ሆኑአል ስራዬ
ወደ ቡናችን እንሂድ ፈጠን ብላ አነቃቺኝ
የቅደሚ እጄን ወደ ፊት ዘረጋሁላት ግድ የለም ቅደም ወደ ፊት ገፋችኝ
ታስገርመኝ ጀምሯል አይኔ አይኗ ላይ ነው
ጀርባዬን ትመታኛለች ከደረጃዎቹ ስንወርድ እጆቼን ትጎትተኛለች በቃ
ደስ የሚል ስቃይ.......
ባለፍንበት መንገድ ሁሉ ኢስኮና ፊያሜታ ሆኑአል ወሬው
እስከ ዚች ሰአት ድረስ ስሟን አልጠየኩዋትም ፊያሜታ መሆኑአን ያወኩት ጓደኛዬ ጠበቅ አርጋት የወንዱ ሁሉ አይን እሷ ላይ ብሎ የነገረኝ ሰአት ነው
ቡናችንን አዘን ቁጭ ብለን ደስ የሚል ጨዋታ ላይ ነን
ቆንጆ የቡና ሱሰኛ ናት ለነገሩ እኔም ካልጠጣሁ አይሆንልኝም
ስምሽ ግን ማነው በወሬያችን መሀል እንዳላወቀ ሆኜ ጥያቄዬን ወረወርኩላት
ፊያሜታ እባላለሁ ችኩል ብላ ተነስታ እጇን ዘረጋችልኝ
ምን አይነት እብደት ነው በጣም አሳቀቺኝ
ደስ አለኝ በቃ
እጄን ዘርግቼ ሰላምታዬን ስሰጣት መልሳ ከጎኔ ተቀመጠች
አይኖች ሁሉ ወደ እኛ ናቸው በቃ
የተማሪው አፍ በእኛ ወሬ ተጠምዶ ቡናው በስቅታ ነው የጨረስነው
እኔ ምልህ አይኗን ወደ አይኔ ተክላ እንዲህ ታዋቂ ነህ እንዴ ደሞ ተወዳጅ በዛ ላይ ቆንጆ
አቤት አቤት አረ አታሽኮርምሚኝ ጨዋታችን ሳቅ ብቻ ሆነ
ይልቅ አሁን ወደ ስራ በል ተነስ ተነስ የጠጣንበትን ሲኒ መልሰን ተነስተን ሄድን
ወደ ክፍሏ ይዛኝ ሄደች
ገባን በሩን ጥርቅም አደረገችው
ቡናው አስክሯት ነው መሰል ዝም ብላ ትስቃለች
ቁጥብ ፈገግታዋ ተቀይሮ እንዲህ ስትስቅ ሳያት ማላውቀው ስሜት ይነዝረኝ ጀመር
ዴስኮቹ ላይ ተቀመጥን በስራዬ ቀልጣፋና ፈጣን መሆኔን በባለፈው ስራዬ ተረድተሀል አይደል
ምንም እንደታስብ ጭራሽ በቃ 60% የትምህርት ቤቱን ሴት በእቅድህ አስገባልሀለሁ
በባለፈው የሰገሁሽ ሙሉ በሴቶች ነው ያለቀው ገርሞኝ ጥያቄዬን ወረወርኩላት
አዎና አለቺኝ.....
አንተ ከላይ አለክ ከበታችህ ብዙ ሰዎች እኔ ግን ከሁሉም በላይ አስፈልግሀለሁ በራስ መተማመኗ አስገረመኝ
ስለዚህ ሀሳብ አይግባህ ኢስኮዬ የሸሚዜን ኮሌታ ጨምድዳ ይዛ ይበልጥ ተጠጋችኝ ከመቀራረባችን የተነሳ በአይኗ ብሌን መልኬን አየሁት አይኗ ውብ ነው የሆነ ሀይል ያለው አካል
ትንፋሿ አጋለኝ ይበልጥ ተጠጋጋን አፍንጫዎቻችን እስኪነካኩ ድረስ መጠጋጋታችን አላቆመም ቀይ ፊቷ እዛው እያየሁት በርበሬ መሰለ እጆቼን ወደ አንገቷ ላኩት
እንቅ አደረኩዋት
አየር ሳንስብ ሁለታችንም አየር ተሰጣጠን ትንፋሽ የለም ቆዳዬን ትኩሱ ትንፋሿ ይገርፈው ጀመር
ያንን ከንፈር በቃ.......
እናንተዬ ኑ ተመለሱ በቃ ስቃዬን አበዛችሁት እኮ ትንሽ ዜማ እንስማ እንጂ እኔም ጠብታዎቼን እንደተለመደው ላፅዳ
ድንቅ ልጅ ድንቅ ነው ውበትሽ
ከዋክብት ናቸው አይኖችሽ
አቤት ቅርፀ ስራው የከናፍርሽ
ፈገግማ ስትይ ሌላ ነው ጥርስሽ
መሀሙድን ከፈትኩላችሁ
አዎና ማንም ምንም ብዬ ባልሰየምኩአት ልጅ የማላውቀው ስሜት ውስጥ ተወርውሬያለሁ
ማን ምን ብለን ሳንጠይቅ ሚሰማን ፍቅር ነው ሌላ ልዩ አለም ውስጥ ሚከተን በቃ እኔም እዛ ልዩ አለም ውስጥ ነበርኩኝ እንዲህ ትዝታን ብቻ ታቅፌ ከመቀመጤ በፊት
አሁንማ ልዩ አለም ውስጥ ሳልሆን ልዩ ስቃይ ውስጥ ነኝ
ወደ ትዝታዬ እመለሳለሁ ......
እቀጥላለሁ
✍ብላቴናው በደም ቀለም
@Wegoch
@wegoch
@wegoch
#የደሜ ዜመኞች
ክፍል - ፮
ቀጥያለሁ....
በትዝታ ንጉደት ህመሜን ታማችሁ ኋላዬ ነውና አሁን ላለሁበት ምክንያት
አሁንም ከጎኔ ሁኑ በደም ዜማዬን እየሰማችሁ
ትዝታ ከፉ ነው መቼም ያሰቃያል የኔ ስቃይ ሲበዛ ከፍ ያለ ንዝረት በአካሌ ላይ ሀይለኛ ምት ያደርሳል ነርቬን ነክቶ የንዝረቱን መልስ በአፍንጫዬ ቀዳዳዎች ይመለሱልኛል መልሶቹም ጠብታዎቼ ናቸው ንዝረቱ ክፉ የሆነነ ህመም ውስጥ ስለሚከተኝ ፋታ ለመውሰድ ዜማን እከፍታለሁ ስቃዬም በረድ ሲል ዜማውን ቀነስ አድርጌ በትዝታዬ እጮሀለሁ
ወደ ትዝታዬ ተመልሻለሁ .....
ፍቅሯ በመቅሰፍቱ እየመታኝ ይገኛል ሁሉ ነገሬን ነጥቃ እሷ ዘንዳ አስቀምጣዋለች ስትመጣልኝ ነው እራሴን ማገኘው
ፊያሜታዬ ነፍሴ ሆናለች....
በቃ ከሚከተሉኝ ጓደኞቼ የበለጠ እሷን ከጎኔ አድርጌ መንቀሳቀስ ጀምሬያለሁ እኔ ካለሁ እሷ አለች ባለሁበት ቦታ ሁሉ ከጎኔ አድርጌ ይዣት መዞር ጀምሬያለሁ
ተማሪውም አውርቶ አውርቶ ሰለቸው መሰል አሁን ስለ እኔ እና ስለሷ መወራቱ ቆሟል ተለምደናል እኔ እና እሷም ተላምደናል
ብዙ ቀናቶች ሆኑን አሁንም ከኔ ዘንድ ነች
ፊያዬ እንዴት እንደሆነ ባልነገረቺኝ ሁኔታ ቢዝነሱን ተቆጣጥራዋለች
ሙሉ በሙሉ በሚቻል መልኩ ሴት ተማሪዎች በእቅዴ ውስጥ አስገብታልኛለች
ከኔ ጋ ከሚሰሩት ወንዶች ሁሉ ብዙ ገቢ ምታስገባልኝ እሷ ሆናለች
ካፒታሌም በደንብ ጨመር ብሏል ....
ለሷ ምቆርጥላትን ነገር ሙሉ ለሙሉ ትቼዋለሁ አሁን ላይ እኔ ማለት እሷ ስለሆነች የኔ የሆነው ሁሉ የሷ ሆኑአል በቃ
ምታመጣልኝን ገንዘብ ለራሷ እንድትጠቀመው ነግሬያታለሁ በቃ ግድ የለኝም ገንዘቡ አሁን ላይ ለኔ ምንም ነው እሷ ደሞ ብዙ ነገሬ ናት
ኑሮዬን ከቤተሰቤ ጋ ቢሆንም የራሴ የምላት ቆንጅዬ ቤት ነበረቺኝ ብዙ ነገሮቼን ማስቀምጠው በቤቴ ነው ምቆዝምባት ትንሽ መሸሸጊያ ቤት ነበረቺኝ
ፊያሜታዬን እዛ ይሻት ለመሄድ ወሰንኩ ቀኑን እኔ እና እሷ ብቻ እንድናሳልፈው ከሰዉ አይን እራቅ ብለን በትንሿ ቤቴ ትልቅ ፍቅር ውስጥ ለመግባት አሰብኩ
ከሷ ጋ.....
ወደ ማታ ደወልኩላት ዛሬ አኩርፋብኛለች ትንሽ ደብሮኝ ነው ኘለቺኝ
ቶሎ ለመናገር ወስኜ አፈነዳሁት ምንም ሳታቅማማ ተስማማች
ግን ምን አባህ አስበህ ነው ብላ በጣም አሳቀቺኝ ጥያቄው ስለገባኝ እኔም ያን ያህል መፍጠን እንደማልፈልግ ነግሬ ቃል ገብቼ ለነገው የፍቅር የድግስ ቀኔ ማሰብ ጀምርኩኝ
ምን ማድረግ እንዳለብኝ ባላውቅም ቤቴ ባለችበት ንፁህና ቆንጆ ስለሆነች ስለ ቤቴ ማሰቡ አላደከመኝም
ብቻ እስኪነጋ ቋምጫለሁ በእቅፌ እስካሞቃት ጓጉቻለሁ እኔ እና እሷ ብቻ
በቃ አይኔ ላይ ነው.....
ትንሽ ዜማ ልክፈት ወደ ንፁህ ቤት ከመግባቴ በፊት ትንሽ ጠብታዎቼን ላፅዳ
ትናንትናን ጥሶ ዛሬን ተንተርሶ
ነገንም ተውሶ አምናንም አድሶ
ይመጣል ትዝታሽ ጓዙን አግበስብሶ
አዎን በትናንት ጥሰት ውስጥ ዛሬን ተንተርሼ ትውስታ መመለሻዬን ዛሬ በትናንቱ ትዝታዬ ከትቼ ነገዬን ማስተካከል ስለምፈልግ ነው እንዲህ በስቃይ ውስጥ ያለሁት
ትንሽ ትዝታዋን ስሻ ጓዙን ጠቅልሎ መቶ ያሰቃየኛል
በቃ ትዝታ ስቃይ ነው አቦ
እመለሳለሁ......
እቀጥላለሁ....
✍ብላቴናው በደም ቀለም
@wegoch
@wegoch
@wegoch
ክፍል - ፮
ቀጥያለሁ....
በትዝታ ንጉደት ህመሜን ታማችሁ ኋላዬ ነውና አሁን ላለሁበት ምክንያት
አሁንም ከጎኔ ሁኑ በደም ዜማዬን እየሰማችሁ
ትዝታ ከፉ ነው መቼም ያሰቃያል የኔ ስቃይ ሲበዛ ከፍ ያለ ንዝረት በአካሌ ላይ ሀይለኛ ምት ያደርሳል ነርቬን ነክቶ የንዝረቱን መልስ በአፍንጫዬ ቀዳዳዎች ይመለሱልኛል መልሶቹም ጠብታዎቼ ናቸው ንዝረቱ ክፉ የሆነነ ህመም ውስጥ ስለሚከተኝ ፋታ ለመውሰድ ዜማን እከፍታለሁ ስቃዬም በረድ ሲል ዜማውን ቀነስ አድርጌ በትዝታዬ እጮሀለሁ
ወደ ትዝታዬ ተመልሻለሁ .....
ፍቅሯ በመቅሰፍቱ እየመታኝ ይገኛል ሁሉ ነገሬን ነጥቃ እሷ ዘንዳ አስቀምጣዋለች ስትመጣልኝ ነው እራሴን ማገኘው
ፊያሜታዬ ነፍሴ ሆናለች....
በቃ ከሚከተሉኝ ጓደኞቼ የበለጠ እሷን ከጎኔ አድርጌ መንቀሳቀስ ጀምሬያለሁ እኔ ካለሁ እሷ አለች ባለሁበት ቦታ ሁሉ ከጎኔ አድርጌ ይዣት መዞር ጀምሬያለሁ
ተማሪውም አውርቶ አውርቶ ሰለቸው መሰል አሁን ስለ እኔ እና ስለሷ መወራቱ ቆሟል ተለምደናል እኔ እና እሷም ተላምደናል
ብዙ ቀናቶች ሆኑን አሁንም ከኔ ዘንድ ነች
ፊያዬ እንዴት እንደሆነ ባልነገረቺኝ ሁኔታ ቢዝነሱን ተቆጣጥራዋለች
ሙሉ በሙሉ በሚቻል መልኩ ሴት ተማሪዎች በእቅዴ ውስጥ አስገብታልኛለች
ከኔ ጋ ከሚሰሩት ወንዶች ሁሉ ብዙ ገቢ ምታስገባልኝ እሷ ሆናለች
ካፒታሌም በደንብ ጨመር ብሏል ....
ለሷ ምቆርጥላትን ነገር ሙሉ ለሙሉ ትቼዋለሁ አሁን ላይ እኔ ማለት እሷ ስለሆነች የኔ የሆነው ሁሉ የሷ ሆኑአል በቃ
ምታመጣልኝን ገንዘብ ለራሷ እንድትጠቀመው ነግሬያታለሁ በቃ ግድ የለኝም ገንዘቡ አሁን ላይ ለኔ ምንም ነው እሷ ደሞ ብዙ ነገሬ ናት
ኑሮዬን ከቤተሰቤ ጋ ቢሆንም የራሴ የምላት ቆንጅዬ ቤት ነበረቺኝ ብዙ ነገሮቼን ማስቀምጠው በቤቴ ነው ምቆዝምባት ትንሽ መሸሸጊያ ቤት ነበረቺኝ
ፊያሜታዬን እዛ ይሻት ለመሄድ ወሰንኩ ቀኑን እኔ እና እሷ ብቻ እንድናሳልፈው ከሰዉ አይን እራቅ ብለን በትንሿ ቤቴ ትልቅ ፍቅር ውስጥ ለመግባት አሰብኩ
ከሷ ጋ.....
ወደ ማታ ደወልኩላት ዛሬ አኩርፋብኛለች ትንሽ ደብሮኝ ነው ኘለቺኝ
ቶሎ ለመናገር ወስኜ አፈነዳሁት ምንም ሳታቅማማ ተስማማች
ግን ምን አባህ አስበህ ነው ብላ በጣም አሳቀቺኝ ጥያቄው ስለገባኝ እኔም ያን ያህል መፍጠን እንደማልፈልግ ነግሬ ቃል ገብቼ ለነገው የፍቅር የድግስ ቀኔ ማሰብ ጀምርኩኝ
ምን ማድረግ እንዳለብኝ ባላውቅም ቤቴ ባለችበት ንፁህና ቆንጆ ስለሆነች ስለ ቤቴ ማሰቡ አላደከመኝም
ብቻ እስኪነጋ ቋምጫለሁ በእቅፌ እስካሞቃት ጓጉቻለሁ እኔ እና እሷ ብቻ
በቃ አይኔ ላይ ነው.....
ትንሽ ዜማ ልክፈት ወደ ንፁህ ቤት ከመግባቴ በፊት ትንሽ ጠብታዎቼን ላፅዳ
ትናንትናን ጥሶ ዛሬን ተንተርሶ
ነገንም ተውሶ አምናንም አድሶ
ይመጣል ትዝታሽ ጓዙን አግበስብሶ
አዎን በትናንት ጥሰት ውስጥ ዛሬን ተንተርሼ ትውስታ መመለሻዬን ዛሬ በትናንቱ ትዝታዬ ከትቼ ነገዬን ማስተካከል ስለምፈልግ ነው እንዲህ በስቃይ ውስጥ ያለሁት
ትንሽ ትዝታዋን ስሻ ጓዙን ጠቅልሎ መቶ ያሰቃየኛል
በቃ ትዝታ ስቃይ ነው አቦ
እመለሳለሁ......
እቀጥላለሁ....
✍ብላቴናው በደም ቀለም
@wegoch
@wegoch
@wegoch
#የደሜ ዜመኞች
ክፍል - ፯
ቀጥያለሁ......
አይነጋ የለ እንደ መንፈቅ የረዘመብኝ ሌሊት ነግቶልኛል
በአይነ ህሊናዬ ስስለው የነበረውን ነገር ከፊያዬ ጋ ለማድረግ ጓጉቻለሁ
ዛሬ ለኔ የፍቅር ቀን ነው
አንድ ነገር አብዝተን በጓጓንለት ቁጥር ላሰብነው ሁኔታ ማድረግ የምንፈልጋቸው ነገሮች ይበዛሉ
እኔም በላፈልኝ ሌሊት ውስጥ አይደለም በአንድ ቀን በሳምንታት እድሜ አድርገን ማንጨርሳቸውን ነገር ሳብሰለስልና ስመኝ ነበር ........ ፍቅር ነዋ ነገሩ
እሷ ያለችበት አለም ይሁን እንጂ የትም እደርሳለሁ
ተመስገን...
ፈጣሪ ምወደውን ቀዝቀዝ ያለ አየር በቅዝቃዜው ወላጆች በደመና ልኮልኛል
መሬቱንም ለማረስረስ ካፊያ ይጥል ጀምሯል
ዝናብ ከመምጣቱ በፊት ብዙ ሚሰሙን ነጎድጓዶች አሉ
በኔም ስሜት ነጎድጓዱን በተሰመኝ ትላልቅ ስሜቶች ወክዬዋለሁ ዝናቡም ቀስ እያለ ይመጣ ይሆናል ልቤን ዘንባ በፍቅሯ ካረሰረሰችልኝ
ወጣ አልኩና የፍቅሯ ዝናብ የልቤን ሀገር እንዲያረሰረስልኝ ተማፀንኩ
ፊቴን ቀና አድርጌ ሌት ያልተኛውን አይኔን በዝናብ ኣራስኩት
ጠብታዎቹ የሆነ ደስ የሚል ስሜት ወደ ውስጤ ሲያስገቡ ተሰማኝ
በጠብታው ምት ውስጥ ከዝናቡ በፊት ካፊያ ነው ሚመጣው
ፊያም ባትዘንብልኝ እያካፋችልኝ በመሆኑ ተመስገን አልኩኝ
ወደ ፊያ ተፈተለኩ.....
እጇን ከደረቷ ከታ ኩምሽሽ ብላ ቆማለች ዝናቡ ፀጉሯን አርጥቦ በለበሰችው ጃኬት ይንፎለፎላል
ጉርዷም በስብሷል
እዛ እረጅም ፀጉር ላይ ዝናቡ የሙጢኝ ብሏል የብዙ ኮረዶችን ፀጉር ያረጠበው ዝናብ በፊያ ፀጉር ላይ በማረፉ ደስ ሳይለው አይቀርም
ሌላ እኮ ናት ልጅቷ
ከፀጉሯ እየተንሸራተቱ በሚወድቁት ጠብታዎች የረጠበው ግንባሯን ጠጋ ብዬ ሳምኩት
አሙቀኝ ብላ አቀፈቺኝ ስላስጠበኩአት ተናዳ እኔን ለማርጠብ ፈልጋ ነው
ከላይ ብትቀዘቅዝም ከውስጡአ ሚወጣው ሙቀት አንገቴን ፈጀው
የያዝኩትን ጥላ ዘረጋሁት
እጆቻችንን አጥብቀን አቆላለፍናቸው ....
የሷን ባላውቅም የደም ዝውውሯ እስኪሰማኝ እጄን አጥብቃ ይዛኛለች ... ፍቅር ነዋ
ወደ ትንሿ ቤቴ መክነፍ ጀመርን
እንግዳዋ በሬን በራሷ እጅ ከፍታ ገባች
ባላሰብኩት ፍጥነት ጃኬቷን እስከ ጉርዷ አውልቃ ከፍሬሼ ገብታ በብርድ ልብሱ ተጠቀለለች
ቤቴን ዙሪያዋን እየቃኘችው ነው
ጨለምለም ካለችው ቤቴ ቤት ለእንቦሳ ሳትል ዘው ብላ ገብታለች
ደማቋ ብርሀኔ ከፍራሼ ውስጥ ገብታ ቤቴን አብርታልኛለች
ቤቴን ስትቃኝ እኔም በተራዬ የብርሀኗ ምንጭ ከየትኛው ውበቷ ላይ እንዳለ ስቃኛት ነበር
አትገባም እንዴ አለቺኝ
እኔም በራሴ ቤት ና ግባ ተብዬ በመግባቴ ደስ ብሎኛል
ለፀጉሯ ሚድረቂያ ፎጣና እረዘም ያለ ሹራብ ሳቀብላት እጄን ጎተት አርጋ ከጀርባዋ እንድሆን አዘዘቺኝ
እኔም ጉብ አልኩባት
በብርድ ልብስ በሞቀው አየር ውስጥ እግሬን ወደ ውስጥ ሰደርኩት
እግሯ እግሮቼን ሲነኩት ቅዝቃዜዋ ጣቶቼን አስደነገጡአቸው
ወገቧ ከሆዴ ጋ የሙጢኝ ተጣብቋል
ከላይ ከለበሰችው ሸሚዝና ከውስጥ ሱሪዋ በቀር ምንም የለም
እኔም ወደ ትእዛዟ ገባሁ...
ፀጉሯን በፎጣው ማድረቅ ጀመርኩ ዳሌዋ ጋ ሊደረስ ትንሽ የቀረው ፀጉሯን አፍተለትለው ገባሁ
ፎጣው በዝናቡ ውሀ ይደርቃል እኔም ማላውቀው ነገር ትንፋሼን ያደረቅው ጀምሯል
የቀዘቀዘ ሞቃት ሆነቺብኝ እዛው መሞቅ ጀመረች
እኔም በአንገቶቿ ስር ጭምር እየገባሁ ፀጉሯን እየያወጣሁ ተያያዝኩት
በዙ ነገሮች የልቤን ምት ጨመሩት
እግሮቻችን ተጠባብቀዋል
ዳሌዋ ከወገቤ በታች የሙጥኝ ተጣብቋል እጆቼ በሳሱ ገላዉቿ ላይ ስልጣን አጊተዋል
ቤቴ ወሬ ናፈቃት ምትሰማው የሁለት ሰዎች ፈጣን ትንፋሾችን ነው
ከወገቤ በታች ጭንቀት ወጠረ
ፀጉሯ እስኪበቃው ደረቀ ወደዛ ወረወርኩት ለስ
እጆቼን መሰስ አድርጌ ከጀርባዋ ላይ ጣልኩት ጀርባዋ ሙቅ ነው ለስላሳ መዳፎቼ ትልግ ግዳጅ ላይ ናቸወቀ
ኋላዋ አስፈራኝ እኔም ፈራሁ ጀርባዋ ከበደኝ ለሆነ ፈተና ዝምታዋ እንደመጣ ገባኝ
አልቻልኩም እናንተዬ በጣም የበዛ ደም እየፈሰሰኝ ነው አሁን ላይ ትንሽ ዜማ ላጫውትላችሁ
ውብ አለም የሌለሽ እንደው ይጨንቀኛል
ይህ ፍቅርሽ ስንቴ ገሎ ስንቴ አድኖኛል
ጎሳዬ ነው ትንሽ ፋታ እንውሰድ እንጂ
አዎ በገሎ ማዳን ውስጥ ነው ብዙ ሞቶች ከብዙ ድህነቶች ጋ ትግል የሚያደርጉት
መተ ተብዬ ዛሬም እየኖርኩ ነው አሁንም ተመልሼ መሞቴ አይቀርም ግን ከእንግዲህ ከሞቴ ሚያስነሳኝ ሰው ስለሌለ በዛው መቅረቴ ነው
አዳኜ እሷ ስለነበረች ከእንግዲህ ሞት እንጂ መዳን በኔ ዘንድ የለም ስቃይ ብቻ
እመለሳለሁ......
✍ብላቴናው በደም ቀለም
@wegoch
@wegoch
@wegoch
ክፍል - ፯
ቀጥያለሁ......
አይነጋ የለ እንደ መንፈቅ የረዘመብኝ ሌሊት ነግቶልኛል
በአይነ ህሊናዬ ስስለው የነበረውን ነገር ከፊያዬ ጋ ለማድረግ ጓጉቻለሁ
ዛሬ ለኔ የፍቅር ቀን ነው
አንድ ነገር አብዝተን በጓጓንለት ቁጥር ላሰብነው ሁኔታ ማድረግ የምንፈልጋቸው ነገሮች ይበዛሉ
እኔም በላፈልኝ ሌሊት ውስጥ አይደለም በአንድ ቀን በሳምንታት እድሜ አድርገን ማንጨርሳቸውን ነገር ሳብሰለስልና ስመኝ ነበር ........ ፍቅር ነዋ ነገሩ
እሷ ያለችበት አለም ይሁን እንጂ የትም እደርሳለሁ
ተመስገን...
ፈጣሪ ምወደውን ቀዝቀዝ ያለ አየር በቅዝቃዜው ወላጆች በደመና ልኮልኛል
መሬቱንም ለማረስረስ ካፊያ ይጥል ጀምሯል
ዝናብ ከመምጣቱ በፊት ብዙ ሚሰሙን ነጎድጓዶች አሉ
በኔም ስሜት ነጎድጓዱን በተሰመኝ ትላልቅ ስሜቶች ወክዬዋለሁ ዝናቡም ቀስ እያለ ይመጣ ይሆናል ልቤን ዘንባ በፍቅሯ ካረሰረሰችልኝ
ወጣ አልኩና የፍቅሯ ዝናብ የልቤን ሀገር እንዲያረሰረስልኝ ተማፀንኩ
ፊቴን ቀና አድርጌ ሌት ያልተኛውን አይኔን በዝናብ ኣራስኩት
ጠብታዎቹ የሆነ ደስ የሚል ስሜት ወደ ውስጤ ሲያስገቡ ተሰማኝ
በጠብታው ምት ውስጥ ከዝናቡ በፊት ካፊያ ነው ሚመጣው
ፊያም ባትዘንብልኝ እያካፋችልኝ በመሆኑ ተመስገን አልኩኝ
ወደ ፊያ ተፈተለኩ.....
እጇን ከደረቷ ከታ ኩምሽሽ ብላ ቆማለች ዝናቡ ፀጉሯን አርጥቦ በለበሰችው ጃኬት ይንፎለፎላል
ጉርዷም በስብሷል
እዛ እረጅም ፀጉር ላይ ዝናቡ የሙጢኝ ብሏል የብዙ ኮረዶችን ፀጉር ያረጠበው ዝናብ በፊያ ፀጉር ላይ በማረፉ ደስ ሳይለው አይቀርም
ሌላ እኮ ናት ልጅቷ
ከፀጉሯ እየተንሸራተቱ በሚወድቁት ጠብታዎች የረጠበው ግንባሯን ጠጋ ብዬ ሳምኩት
አሙቀኝ ብላ አቀፈቺኝ ስላስጠበኩአት ተናዳ እኔን ለማርጠብ ፈልጋ ነው
ከላይ ብትቀዘቅዝም ከውስጡአ ሚወጣው ሙቀት አንገቴን ፈጀው
የያዝኩትን ጥላ ዘረጋሁት
እጆቻችንን አጥብቀን አቆላለፍናቸው ....
የሷን ባላውቅም የደም ዝውውሯ እስኪሰማኝ እጄን አጥብቃ ይዛኛለች ... ፍቅር ነዋ
ወደ ትንሿ ቤቴ መክነፍ ጀመርን
እንግዳዋ በሬን በራሷ እጅ ከፍታ ገባች
ባላሰብኩት ፍጥነት ጃኬቷን እስከ ጉርዷ አውልቃ ከፍሬሼ ገብታ በብርድ ልብሱ ተጠቀለለች
ቤቴን ዙሪያዋን እየቃኘችው ነው
ጨለምለም ካለችው ቤቴ ቤት ለእንቦሳ ሳትል ዘው ብላ ገብታለች
ደማቋ ብርሀኔ ከፍራሼ ውስጥ ገብታ ቤቴን አብርታልኛለች
ቤቴን ስትቃኝ እኔም በተራዬ የብርሀኗ ምንጭ ከየትኛው ውበቷ ላይ እንዳለ ስቃኛት ነበር
አትገባም እንዴ አለቺኝ
እኔም በራሴ ቤት ና ግባ ተብዬ በመግባቴ ደስ ብሎኛል
ለፀጉሯ ሚድረቂያ ፎጣና እረዘም ያለ ሹራብ ሳቀብላት እጄን ጎተት አርጋ ከጀርባዋ እንድሆን አዘዘቺኝ
እኔም ጉብ አልኩባት
በብርድ ልብስ በሞቀው አየር ውስጥ እግሬን ወደ ውስጥ ሰደርኩት
እግሯ እግሮቼን ሲነኩት ቅዝቃዜዋ ጣቶቼን አስደነገጡአቸው
ወገቧ ከሆዴ ጋ የሙጢኝ ተጣብቋል
ከላይ ከለበሰችው ሸሚዝና ከውስጥ ሱሪዋ በቀር ምንም የለም
እኔም ወደ ትእዛዟ ገባሁ...
ፀጉሯን በፎጣው ማድረቅ ጀመርኩ ዳሌዋ ጋ ሊደረስ ትንሽ የቀረው ፀጉሯን አፍተለትለው ገባሁ
ፎጣው በዝናቡ ውሀ ይደርቃል እኔም ማላውቀው ነገር ትንፋሼን ያደረቅው ጀምሯል
የቀዘቀዘ ሞቃት ሆነቺብኝ እዛው መሞቅ ጀመረች
እኔም በአንገቶቿ ስር ጭምር እየገባሁ ፀጉሯን እየያወጣሁ ተያያዝኩት
በዙ ነገሮች የልቤን ምት ጨመሩት
እግሮቻችን ተጠባብቀዋል
ዳሌዋ ከወገቤ በታች የሙጥኝ ተጣብቋል እጆቼ በሳሱ ገላዉቿ ላይ ስልጣን አጊተዋል
ቤቴ ወሬ ናፈቃት ምትሰማው የሁለት ሰዎች ፈጣን ትንፋሾችን ነው
ከወገቤ በታች ጭንቀት ወጠረ
ፀጉሯ እስኪበቃው ደረቀ ወደዛ ወረወርኩት ለስ
እጆቼን መሰስ አድርጌ ከጀርባዋ ላይ ጣልኩት ጀርባዋ ሙቅ ነው ለስላሳ መዳፎቼ ትልግ ግዳጅ ላይ ናቸወቀ
ኋላዋ አስፈራኝ እኔም ፈራሁ ጀርባዋ ከበደኝ ለሆነ ፈተና ዝምታዋ እንደመጣ ገባኝ
አልቻልኩም እናንተዬ በጣም የበዛ ደም እየፈሰሰኝ ነው አሁን ላይ ትንሽ ዜማ ላጫውትላችሁ
ውብ አለም የሌለሽ እንደው ይጨንቀኛል
ይህ ፍቅርሽ ስንቴ ገሎ ስንቴ አድኖኛል
ጎሳዬ ነው ትንሽ ፋታ እንውሰድ እንጂ
አዎ በገሎ ማዳን ውስጥ ነው ብዙ ሞቶች ከብዙ ድህነቶች ጋ ትግል የሚያደርጉት
መተ ተብዬ ዛሬም እየኖርኩ ነው አሁንም ተመልሼ መሞቴ አይቀርም ግን ከእንግዲህ ከሞቴ ሚያስነሳኝ ሰው ስለሌለ በዛው መቅረቴ ነው
አዳኜ እሷ ስለነበረች ከእንግዲህ ሞት እንጂ መዳን በኔ ዘንድ የለም ስቃይ ብቻ
እመለሳለሁ......
✍ብላቴናው በደም ቀለም
@wegoch
@wegoch
@wegoch
#የደሜ ዜመኞች
ክፍል - ፱
ቀጥያለሁ......
ቤቴ በውብ ንግስት ጣፋጭ በሆነች ሽሮ ከምርጥ ወይን ጋር ከምሰማው ጥዑም ዜማ ጋ ሌላ ሆነናለች
የሁሉም መሰረት ደሞ እሷ ናት
ባማሩ እጆች የተሰራውን ምግብ በወይኑ እያወራረድን በውብ ዜማ ተመስጠን በልተን ጨረሰን
ዛሬ ሁሉም ነገር ደስታ ብቻ ነው
ከትዝታዬ መለስ ልበል አንዴ ብቻ ስሙኝ አደራ እንዳታዝኑብኝ እሺ
ባሰብኩት ሁኔታ በጣም ህመሜ ብሶብኛል ይህን ምፅፍላችሁ ቃሌ ድምፅ ሆኑአችሁ እንድትሰሙኝ ብቻ ሳይሆን ወደ ትዝታዬ ለመመለስ የማደረግው ፍቱኑ መዳኒቴም ጭምር ነበር
ከአፍንጫዬ ሚወጣው የደም ጠብታ ዛሬ መልሱን አገኘ አባቴ ሀዘኑን እንኳ ሊደብቅ አልተቻለውም
ፊት ለፊቴ ተንበርክኮ ከተራመዱ ብዙ ጊዜ የሆናቸውን እግሮቼን በእንባው አራሳቸው
እንባው መዳኒት ሆኖኝ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ከጉልበቴ ስር ባነሳው ምንኛ ሀሴት ባደረኩ
ላተርፍህ ብችል.... ሊጨርሰው አልቻለም ነፍሴን ልስጥህ... በሀዘን ሳግ ሆኖ እንባ እየቀደመው ምንም ሊያወራኝ አልቻለም
የኔ አባት አለኝ በእንባው የራሳቸውን ጉልበቶቼን ይዞ
ያ አዝማሪ ጀግና የስንኞች አባት ስንት ዜማ ባንቆረቆረበት ልሳኑ አፉ ለኔ እንዲህ ቃል ሲያጥረው ማየት ምንኛ ህመም ነው
ለስቃይ የፈጠረኝ ሰው.....
ልጅህ የደም መርጋት በሽታ አለበት ብለውታል ሲመስለኝ ምሄድበትንም ቀን አያይዘው ሳይነግሩት አልቀሩም
ማንባት የለመደው አይኔ ዛሬ ሲቃ በሌለው ድምፅ ዘለላውን ብቻ ዱብዱብ ያደርገው ጀምሯል
ለምን እንደማለቅስ አላውቅም ምን አልባት ለአባቴ ስል ይሆናል እንጂማ እኔ ወደ ማርፍበት አለም ልጓዝ ነው ከዚ ካለሁበት ከስቃይ ምድር ለቅቄ
አድሎኝና ብዙ ጊዜ ኖሮኝ ከዚ በባሰ ስቃይ ውስጥ ሆኜ እንኩዋ ውብ ትዝታዎቼን ብነግራችሁ ምንኛ ደስ ባለኝ ነበረ
ግን በቃ ምን አባቴ ላድርግ......
ግን ምነግራቹ ነገር አለኝ
ዛሬ ይሄን ምፅፍላችሁ በደም ቀለም ብቻ አይደለም
በደምና በእንባ ዘለላዎቼ እየጠቀስኩ ነው ማጫውታችሁ
እንባዬ ለአባቴ ነው ደሜ ደሞ ለፊያዬ
ደሞ አልፈራሁም
ስሞት እኮ ለዘላለማዊ ህይወቴ ውልደቴን እያበሰርኩ ነው
አልቅሼ ነው የመጣሁት አልቅሼ ነው ምሄደው ለዛም ነው እንባዬ
ደሞ እጅግ ደስ ብሎኛል ወደ እሷ እየሄድኩ ነዋ እዚ በትዝታ ከምዋትት እዛ በፍቅር መላእክት እርዳታ ብፈልጋት ይሻለኛል
መንገዱ ላይ ነኝ አዎ መንገድ ላይ ነኝ
ሞት እንደ ንፋስ ሽው ሲል እየተሰማኝ ነው መልአከ ሞት ለቀም ሊያደርገኝ አሰፍስፎ ቆሙአል
እኔም ከሱ እጅ ለመግባት እየዳዳሁ ነው ወደ እሷ ለመጓዝ
ውልብ ትልብኝ ገባች እኮ እናንተዬ
አረ እስቅላችሁ ጀመር አለም ነው
እዛ እንገናኝ እንጂ እናንተ ሳመጡ ሰራግችን አይደገሰም በእውነት ስላችሁ
ሀዘን ደስታ ስቃይ ምን አይነት ስሜት ነው እናንተዬ
እዚ የጀመርኩትን ውብ ትዝታዎቼን እዛው ስትመጡ ከእሷ ጋ እንጨርስላቹሀለን
መቼም ከዛ አይቀር
ለመጨረሻ ጊዜ ሁለት ዜማዎችን አጫውታላቹሀለሁ
አንደኛውን አሁኑኑ ሁለተኛውን እሷን ፍለጋ ልሄድ ስለሆነ የዛን ሰአት አካፍላቹሀለሁ
ስወለድ አባቴ 15 አዝማሪ አምጥቶ ድል ባለ ዜማ ነው የተቀበለኝ ሲዜምልኝ እንደመጣው እያዜምኩ ነው ምሄደው
ስሞት አዝማሪዎች ባይኖሩም
በምከፍተው ዜማ አዝያሚው ሲያዜም እኔ እና መልአከ ሞት እዝማቹን እየተቀበልን ጉዞአችንን እንቀጥላለን
ኋላ ሳታመሰግነን እንዳትሉኝ ደሞ በጣም እወዳቹሀለሁ
ሰማይ ቤት አባቴ በጣም ስለሚናፍቀኝ እዛ ለማገኛቸው አዳዲስ ጓደኞቼ ደሞ የሱን ትዝታ ከመላእክት በምዋሰው ብዕር አወጋቸዋለሁ
ልዩነቱ እዛ ምንም ስቃይ የለም
በጸአዳ ባጌጠ ደስታ ውስጥ ሆኜ ነው አባቴን እና እናንተን ምጠብቀው
ግን
ይሄ የደሜ ዜማ ነው ባማሩ ትዝታዎች በስቃይ ምፅፈው
አልፈራሁም ደሞ ማርያምን
ዜማውን ተጋበዙልኝ
ልምጣ ወይ ልቅር ምን ይሻለኛል
ከፍቅርሽ ሚያስጥል ማን ዘንድ ይገኛል
ስለት አለብኝ ከርቤ እና እጣና
ለመተያየት እንዲያበቃን
ማ ዘንድ ይደር ሄዶ ጎኔ ሰው አልሆንም ካላንቺ እኔ
ቴዲ ነፍሴን ስሙልኝ አቦ
አዎ ማድርበት ምሸሸግበት ጥግ አጥቻለሁ ሁሉም አንቺን በማጣቴ የሆነ ነው
ልምጣ ወይስ ልቅር እያልኩ ስባዝን ይኸው በጊዜው እራሱ ከተፍ ብሎልኛል
ፀሎቴም ተሰምቶ ስለቴን እዛው ለመላእክት እሰጣለሁ ካንቺ ላገናኘኝ ፈጣሪ እንዲሰጡልኝ
ሊፈፀም ሰአቱ ደርሷል
እቀጥላለሁ....
✍ብላቴናው በእንባ ዘለላ ከደም ቀለምጋ
@wegoch
@wegoch
@wegoch
ክፍል - ፱
ቀጥያለሁ......
ቤቴ በውብ ንግስት ጣፋጭ በሆነች ሽሮ ከምርጥ ወይን ጋር ከምሰማው ጥዑም ዜማ ጋ ሌላ ሆነናለች
የሁሉም መሰረት ደሞ እሷ ናት
ባማሩ እጆች የተሰራውን ምግብ በወይኑ እያወራረድን በውብ ዜማ ተመስጠን በልተን ጨረሰን
ዛሬ ሁሉም ነገር ደስታ ብቻ ነው
ከትዝታዬ መለስ ልበል አንዴ ብቻ ስሙኝ አደራ እንዳታዝኑብኝ እሺ
ባሰብኩት ሁኔታ በጣም ህመሜ ብሶብኛል ይህን ምፅፍላችሁ ቃሌ ድምፅ ሆኑአችሁ እንድትሰሙኝ ብቻ ሳይሆን ወደ ትዝታዬ ለመመለስ የማደረግው ፍቱኑ መዳኒቴም ጭምር ነበር
ከአፍንጫዬ ሚወጣው የደም ጠብታ ዛሬ መልሱን አገኘ አባቴ ሀዘኑን እንኳ ሊደብቅ አልተቻለውም
ፊት ለፊቴ ተንበርክኮ ከተራመዱ ብዙ ጊዜ የሆናቸውን እግሮቼን በእንባው አራሳቸው
እንባው መዳኒት ሆኖኝ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ከጉልበቴ ስር ባነሳው ምንኛ ሀሴት ባደረኩ
ላተርፍህ ብችል.... ሊጨርሰው አልቻለም ነፍሴን ልስጥህ... በሀዘን ሳግ ሆኖ እንባ እየቀደመው ምንም ሊያወራኝ አልቻለም
የኔ አባት አለኝ በእንባው የራሳቸውን ጉልበቶቼን ይዞ
ያ አዝማሪ ጀግና የስንኞች አባት ስንት ዜማ ባንቆረቆረበት ልሳኑ አፉ ለኔ እንዲህ ቃል ሲያጥረው ማየት ምንኛ ህመም ነው
ለስቃይ የፈጠረኝ ሰው.....
ልጅህ የደም መርጋት በሽታ አለበት ብለውታል ሲመስለኝ ምሄድበትንም ቀን አያይዘው ሳይነግሩት አልቀሩም
ማንባት የለመደው አይኔ ዛሬ ሲቃ በሌለው ድምፅ ዘለላውን ብቻ ዱብዱብ ያደርገው ጀምሯል
ለምን እንደማለቅስ አላውቅም ምን አልባት ለአባቴ ስል ይሆናል እንጂማ እኔ ወደ ማርፍበት አለም ልጓዝ ነው ከዚ ካለሁበት ከስቃይ ምድር ለቅቄ
አድሎኝና ብዙ ጊዜ ኖሮኝ ከዚ በባሰ ስቃይ ውስጥ ሆኜ እንኩዋ ውብ ትዝታዎቼን ብነግራችሁ ምንኛ ደስ ባለኝ ነበረ
ግን በቃ ምን አባቴ ላድርግ......
ግን ምነግራቹ ነገር አለኝ
ዛሬ ይሄን ምፅፍላችሁ በደም ቀለም ብቻ አይደለም
በደምና በእንባ ዘለላዎቼ እየጠቀስኩ ነው ማጫውታችሁ
እንባዬ ለአባቴ ነው ደሜ ደሞ ለፊያዬ
ደሞ አልፈራሁም
ስሞት እኮ ለዘላለማዊ ህይወቴ ውልደቴን እያበሰርኩ ነው
አልቅሼ ነው የመጣሁት አልቅሼ ነው ምሄደው ለዛም ነው እንባዬ
ደሞ እጅግ ደስ ብሎኛል ወደ እሷ እየሄድኩ ነዋ እዚ በትዝታ ከምዋትት እዛ በፍቅር መላእክት እርዳታ ብፈልጋት ይሻለኛል
መንገዱ ላይ ነኝ አዎ መንገድ ላይ ነኝ
ሞት እንደ ንፋስ ሽው ሲል እየተሰማኝ ነው መልአከ ሞት ለቀም ሊያደርገኝ አሰፍስፎ ቆሙአል
እኔም ከሱ እጅ ለመግባት እየዳዳሁ ነው ወደ እሷ ለመጓዝ
ውልብ ትልብኝ ገባች እኮ እናንተዬ
አረ እስቅላችሁ ጀመር አለም ነው
እዛ እንገናኝ እንጂ እናንተ ሳመጡ ሰራግችን አይደገሰም በእውነት ስላችሁ
ሀዘን ደስታ ስቃይ ምን አይነት ስሜት ነው እናንተዬ
እዚ የጀመርኩትን ውብ ትዝታዎቼን እዛው ስትመጡ ከእሷ ጋ እንጨርስላቹሀለን
መቼም ከዛ አይቀር
ለመጨረሻ ጊዜ ሁለት ዜማዎችን አጫውታላቹሀለሁ
አንደኛውን አሁኑኑ ሁለተኛውን እሷን ፍለጋ ልሄድ ስለሆነ የዛን ሰአት አካፍላቹሀለሁ
ስወለድ አባቴ 15 አዝማሪ አምጥቶ ድል ባለ ዜማ ነው የተቀበለኝ ሲዜምልኝ እንደመጣው እያዜምኩ ነው ምሄደው
ስሞት አዝማሪዎች ባይኖሩም
በምከፍተው ዜማ አዝያሚው ሲያዜም እኔ እና መልአከ ሞት እዝማቹን እየተቀበልን ጉዞአችንን እንቀጥላለን
ኋላ ሳታመሰግነን እንዳትሉኝ ደሞ በጣም እወዳቹሀለሁ
ሰማይ ቤት አባቴ በጣም ስለሚናፍቀኝ እዛ ለማገኛቸው አዳዲስ ጓደኞቼ ደሞ የሱን ትዝታ ከመላእክት በምዋሰው ብዕር አወጋቸዋለሁ
ልዩነቱ እዛ ምንም ስቃይ የለም
በጸአዳ ባጌጠ ደስታ ውስጥ ሆኜ ነው አባቴን እና እናንተን ምጠብቀው
ግን
ይሄ የደሜ ዜማ ነው ባማሩ ትዝታዎች በስቃይ ምፅፈው
አልፈራሁም ደሞ ማርያምን
ዜማውን ተጋበዙልኝ
ልምጣ ወይ ልቅር ምን ይሻለኛል
ከፍቅርሽ ሚያስጥል ማን ዘንድ ይገኛል
ስለት አለብኝ ከርቤ እና እጣና
ለመተያየት እንዲያበቃን
ማ ዘንድ ይደር ሄዶ ጎኔ ሰው አልሆንም ካላንቺ እኔ
ቴዲ ነፍሴን ስሙልኝ አቦ
አዎ ማድርበት ምሸሸግበት ጥግ አጥቻለሁ ሁሉም አንቺን በማጣቴ የሆነ ነው
ልምጣ ወይስ ልቅር እያልኩ ስባዝን ይኸው በጊዜው እራሱ ከተፍ ብሎልኛል
ፀሎቴም ተሰምቶ ስለቴን እዛው ለመላእክት እሰጣለሁ ካንቺ ላገናኘኝ ፈጣሪ እንዲሰጡልኝ
ሊፈፀም ሰአቱ ደርሷል
እቀጥላለሁ....
✍ብላቴናው በእንባ ዘለላ ከደም ቀለምጋ
@wegoch
@wegoch
@wegoch
#የደሜ ዜመኞች
ክፍል - ፲
ቀጥያለሁ...
(የሞቴ መምጣት ደርሳለችና የፍቅሬን ንሰሀ ስሙልኝ)
ቀጥያለሁ.....
የፍቅሬ ሀገር ድንበር ስለሌለው መሰረትና አጥር ሳይከልለው ወደ አርያም ሊፈረጥጥነው
ተጠርቷላ
መልአከ ምትም ከፊቴ ተገትሮ ና እንጂ እየጠበቀችህ ብሎ እጁን ዘርግቶልኛል
እኔም ከእጁ ለመግባት ቸኩያለሁ ግን ንሰሀዬን ልነግራችሁ ወደድኩኝ
ማ ዘንድ ይደር
ሰው አሳዝኖ ሰው ላይሆን ነገር
ምን አስጀመረው የማይሆን ነገር
ልቤ አንቺን ትቶ ከማን ዘንድ ይደር
ልማልልሽ ወይ በቶ መስቀሌ
ከራሴ ጋር ነው ብጣላሽ ጥሌ
ትዝ ይለኛል የፊያሜታዬ ልደት ሰኔ 19 ነበር ምን አድርጌ እንደማከብርላት ግራ ግብት ብሎኝ ነበር ብዙ ጊዜ ፈጣን ትሁን እንጂ ፀጥታ ነፍሱአ ነው ልደቷን እኔ እና እሷ ብቻ እንድናከብረው ፈለኩኝ በምቶደው በፀጥታ አለም ውስጥ ሆነን
ትምህርቱ ሊያልቅ የ1 ሳምንት ጊዜ ብቻ ነበር የቀረው እናም ሁሉም ነገር መለየት መለየት ብቻ ነው ሚሸተው
የኛም ቢዝነስ ከምላችሁ በላይ አድጓል ግን በዛው ልክ ማላውቃቸው ሰዎች ቢዝነሴን እንድተውና ከስራቸው ገለል እንድል እየነገሩኝ ነበር
አልሰማም ብያለሁ እኔም
ሰኔ 18 ላይ ነኝ ነገ የንግስቴ የውልደቷ ቀን ነው ማንንም ሳላማክር ሁሉን ነገር በራሴ ለማድረግ ወስኛለሁ
ገና በጠዋቱ ፊያዬ እየሮጠች መታ ከእቅፌ ውስጥ ገባች ጊዮርጊስ ሄጄ ፀሎት አድርጌ መጣሁ አለቺኝ ምን ታየሽ ባክሽ አልኩአት ትናንሽ አይኖቹአን አንስታ ገላመጠቸኝ
ሁሌ ሳናዳት እንዲህ ነው ምታደርገው
ይሄን ደሞ ላንተ ብላ ከወደ አንገቷ እጆቹአን አስገባች የሚያምር ቶ መስቀል ወደ አንገቴ አስጠጋችልኝ እንዳይጠፋብኝ አስሬው እኮ ነው አለቺኝ
መስቀሉን ስማ አሰረቺልኝ መቼም ላልየህ ቃሌ ነው የኔ አባት ቃሏ ሰርስሮኝ ወደ ውስጤ ዘለቀ
እንባ ቀረሽ ስሜት ውስጥ ገብታ እኔንም ይዛኝ ዘለቀች
ዛሬ ስሜቷ ሁሉ ዝብርቅርቅ ሆኑአል
ሁሌ ወደ ምንቀምጥባት ቦታ ወስጄ አወራት ጀመር
ትዝ ይለኛል ይሄን ዜማ ከሰጠችኝ መስቀል ጋር አያይዤ እዘፍንላት ጀመር
ልቤ አንቺን ትቶ ከማዘንድ ይደር
ልማልልሽ ወይ በ ቶ መስቀሌ
ከራሴ ጋር ነው ብጣላሽ ጥሌ
የሰጠችኝን መስቀል እየዳበሰች ከእቅፌ ውስጥ ገብታለች
ደሞ ነገ የንግስቴ ልደት ነው
ሁሌ ደስ ሲለኝ በደስታዬ ሀይል ዳመናውን ማዘው ይመስል ዛሬም ስሜቴን ተረድቶ በነጎድጓዱ መጣው ይለኝ ጀምሯል
ካፊያ ከሰማዩ ሲጀምር ይዣት ልነሳ ተነሳሁ አይሆንም አለቺኝ ምወደው ዝናብ ከላይ ከእቅፌ ስር ደሞ ንግስቴ ተኝታለች
በእቅፌ ስር ነች ቶ መስቀሌን በጣቶቿ እየዳሰሰች በትንፋሿ አንገቴን ታሞቀው ጀምራለች
ምን ቁር ምን ብርድ ምን ዶፍ አሁን በኔ ላይ ስሜት አያመጡም የሷ ትንሽ ትንፋሽ የልቤን እሳት ይለኩሰዋል
ያ ውብ ፀጉር በዝናቡ ጠብታዎች ውበቱ ጨምሯል ጠብታዎቹ ቁጭ ቁጭ ብለው ለፀጉሯ ማጌጫ የተቀመጡ ጌጦች መስለዋል ሁሉ ነገራች በስብሷል ዝንቡ ክፉኛ ቢያረጥበንም በፍቅር እቅፍ ውስጥ ሙቅ ቤት ሰርተናል
ፈራሁ አለቺኝ ዝም ብለሽ እቀፊኝ አልኩአት ለካ
እንባዋን ከዝናቡ ጠብታውች እጋ እኩል እያፈሰሰቸቻው ነው
ስቅ ሲላት ሳግ ወደ ላይ ስሜቷን ሲያወጣው እኔም ማልቀሷን አወኩኝ
ምድነው የሆነሽቢኝ ፈራሁ ፈራሁ ብቻ ነው መልሷ
ከፊቴ የማላውቃቸው ሁለት ልጆች ኢስኮ ታች ሜዳ ላይ በጣም ተፈልገሀል አሉኝ መጣሁ አልኳቸው ከሁኔታቸው የግዴት ትዕዛዝ ነው ሚመስለው
ደርሼ ልምጣ አልኩአት አትሂድ አለቺኝ አሁን ነው ምመለሰው ብላትም እባክህ ሆነ መማፀኑአ ተነሺ እሺ አብረን ሄደን እንመለሳለን አልኩአት
ዛሬ ከበስተጀርባዬ ሚቆም ማንም ሰው አልነበረም ሚከተለኝ ህዝብ ዛሬ ከኋላዬ የለም አጆቹአን ይዤ አለሜን እያስከተለኩኝ ወረድኩ
በጨቀየው ሜዳ ወደ 12 የሚጠጉ ልጆች ተሰብስው ቆመዋል በዛ ዝናብ እኔን ቀመው እየጠበቁ ነው አንድማ ማውቀው ፊት የለም
እኔ ከጨቀየው መሬት አለሜን አስከትዬ ጭቃው እየዛኩ ወደ ነሱ ተጠጋው ፎቁ ላይ ያለው ተማሪ ከሜዳው ሚደረገውን ድርጊት ተገርሞ ይመለከታል እጇን አጥብቄ ይዤዋለሁ
ድንገት ከወደ ጭንቅላቴ ከፍ ያለ ምት ተሰማኝ እጆቹአን ለቅቄ ከመሬት ወደኩኝ ጩኸቷ ከጆሮዬ ያቃጭላል ሰውነቴ ብዙ ምቶችን እያስተናገደ ነው ዝናቡ ከላይ የነሱ ቡጢ ከሰውነቴ ይወርድ ጀመረ ኢስኮ እያለች የነበረችው ፊያዬ ዋይ ዋይታዋ ቀነሰብኝ ድምጿ ከጆሮዬ ሲጠፋ የተማሪው ጩኸት ሲያስተጋባ ተሰማኝ ዱላው እየቀነሰ ዝናቡ ሀይሉን ጨምሯል
ደም የሞሏው ፊቴ በዝናቡ እየታጠበ ይነፃ ጀመር ከምንም በላይ የጭንቅላቴ ህመም አይሎብኛል አይኔን ከሜዳው ላይ ጥዬ ብዥታዬን አጠራ ጀመር እሷን መፈለግ ጀመርኩ
ከፊቴ ውድቅ ብላለች ያ ውብ ገላ ከጨቀየው ሜዳ ላይ ተንጋሎ ወድቋል
በተሰባበሩት እጆቼ አይኔን እጠርግ ገባሁ እየዳሁ አጠገቧ ደረስኩ ቅድም ስዳብሰው የነበረው ፀጉር በጭቃ ተለውሷል
በእጆቿ ሆዶአን ይዛዋላች አሁንም ይበልጥ ተጠጋሁዋት
ከዝናቡ አልፍ አንድ ዘለላ እንባ ከአይኗ ስትፈስ አየሁ
ሆዷ ደም ለብሷል ሆድ እቃዋ ተገልብጧል
ኢ ኢ ኢ ስስስኮ አለቺኝ ምድነው እናቴ እጆቼ ግንባሮቿ ላይ ጣልኩት
ቶሎ እንድትመጣ እሺ አባቴ አለቺኝ በደም እጇ ከአንገቴ የተንጠለጠለውን የሰጠችን መስቀል በደም ለወሰቻቸው
ተማሪው ሜዳው ላይ ደርሷል ወዴት እንደምመጣ ባላቅም እሺ እንኩአን ሳልላት አፋፍሰው ወሰዱአት
እኔም በተማሪዎቹ ድጋፍ ተነስቼ እከተላት ጀመረ በታክሲ ተጭኜ ዝም ብዬ መጓዝ ጀመርኩ የተማሪዎቹን የለቅሶና የሀዘን ድምፅ እየሰማሁ ከአንድ ሆስፒታል ደጃፍ ደረስኩ
በነሱ ድጋፍ ከውስጥ ዘለኩ የት እንዳስገቡአት እንጃ ብቻ ሁለት ነርሶች ወደ እኔ መጡ ሊወስዱኝ ፈለጉ አይሆንም አልኩኝ ቶሎ ና እሺ ቶሎ ና የመጨረሻ ድምጿ ከጆሮዬ ያስተጋባል ቃናዋ በህሊናዬ ያንሻብብ ጀመር
ነርሶቹ እንደያዙኝ እሪታና ጩኸት ሲበዛ የአለሜ ቃና በድምፃቸው ተዋጠ ነርሶቹ በሰሙት ጩኸት ለቀቁኝ
ሞታለች የሚል ድምፅ ስሰማ እኔም ሌላ ምት ወደ ጭንቅላቴ ሲመጣ ታወቀኝ ከመሬት ወደኩ ጭንቅላቴ ሲከፈል የጎን አጥንቴ ሲደቅ ተሰማኝ
እናንተዬ ልቤ እየቀነሰችብኝ ትንፋሽ እያጠረኝ ነው እጆቼ ንዝረታቸው ጨምሮ ምፅፈው ሁሉ እየተደለዘ ነው እፍን ምልስ እፍን ምልስ
ሞቷን ስነግራችሁ እኔም ልሄድ ነው መሰለኝ
ደሜ ወረቄትን ሸፍኖታል ድምፅ አልባው እንባዬ እየወረደ ነው ልሄድ ነው በቃ ልሄድ ነው ልቤ እየያዘገመች ነው እጆቼም ዝለውብኛል
እይኔ መስለምለም ጀምሯል ብዥ ብዥ ሆኖብኝ መስመሬን እየሳትኩ ነው ምፅፈው
ከዚ ወዲ ፋታ ለመውሰድ ብዬ ዜማ ስለማላጫውትላችሁ እቺን ብቻ ስሙልኝ እሺ ወደ እኔ ቶሎ ኑ እሺ እናንተም እዛ ስንገናኝ ብዙ ነገር ነው ማጫውታችሁ
መልአከ ሞት መጨረሴን አውቋል መሰል ቀኝ እጄን ለቀም አድርጎ ይዞኛል
በግማሽ ሞት እና በግማሽ ሂወት ውስጥ ነኝ
በግራው አይኔ ካለሁበት አለም ወጥቼ አዲስ ነገርች እያየሁ ነው
በቀኜ ደሞ በደም የተጨማለቀውን ገፄን
እቺን ስሙልኝ አደራ ቶሎ ኑ በሷ ቃል ነው እኔም ምሰናበታችሁ
ዜማዋ ልትጀምር ነው
የት ነው የምትኖሪው ያለሽበት ቦታ
ምንኛ ሀያል ነው ይህ ያንቺ ትዝታ
ደቂቃዎች ሴኮንድ እንዴት ልለይሽ
የትዝታዬ ምንጭ ውሀ
ውሀ ጥሜ ነ
ክፍል - ፲
ቀጥያለሁ...
(የሞቴ መምጣት ደርሳለችና የፍቅሬን ንሰሀ ስሙልኝ)
ቀጥያለሁ.....
የፍቅሬ ሀገር ድንበር ስለሌለው መሰረትና አጥር ሳይከልለው ወደ አርያም ሊፈረጥጥነው
ተጠርቷላ
መልአከ ምትም ከፊቴ ተገትሮ ና እንጂ እየጠበቀችህ ብሎ እጁን ዘርግቶልኛል
እኔም ከእጁ ለመግባት ቸኩያለሁ ግን ንሰሀዬን ልነግራችሁ ወደድኩኝ
ማ ዘንድ ይደር
ሰው አሳዝኖ ሰው ላይሆን ነገር
ምን አስጀመረው የማይሆን ነገር
ልቤ አንቺን ትቶ ከማን ዘንድ ይደር
ልማልልሽ ወይ በቶ መስቀሌ
ከራሴ ጋር ነው ብጣላሽ ጥሌ
ትዝ ይለኛል የፊያሜታዬ ልደት ሰኔ 19 ነበር ምን አድርጌ እንደማከብርላት ግራ ግብት ብሎኝ ነበር ብዙ ጊዜ ፈጣን ትሁን እንጂ ፀጥታ ነፍሱአ ነው ልደቷን እኔ እና እሷ ብቻ እንድናከብረው ፈለኩኝ በምቶደው በፀጥታ አለም ውስጥ ሆነን
ትምህርቱ ሊያልቅ የ1 ሳምንት ጊዜ ብቻ ነበር የቀረው እናም ሁሉም ነገር መለየት መለየት ብቻ ነው ሚሸተው
የኛም ቢዝነስ ከምላችሁ በላይ አድጓል ግን በዛው ልክ ማላውቃቸው ሰዎች ቢዝነሴን እንድተውና ከስራቸው ገለል እንድል እየነገሩኝ ነበር
አልሰማም ብያለሁ እኔም
ሰኔ 18 ላይ ነኝ ነገ የንግስቴ የውልደቷ ቀን ነው ማንንም ሳላማክር ሁሉን ነገር በራሴ ለማድረግ ወስኛለሁ
ገና በጠዋቱ ፊያዬ እየሮጠች መታ ከእቅፌ ውስጥ ገባች ጊዮርጊስ ሄጄ ፀሎት አድርጌ መጣሁ አለቺኝ ምን ታየሽ ባክሽ አልኩአት ትናንሽ አይኖቹአን አንስታ ገላመጠቸኝ
ሁሌ ሳናዳት እንዲህ ነው ምታደርገው
ይሄን ደሞ ላንተ ብላ ከወደ አንገቷ እጆቹአን አስገባች የሚያምር ቶ መስቀል ወደ አንገቴ አስጠጋችልኝ እንዳይጠፋብኝ አስሬው እኮ ነው አለቺኝ
መስቀሉን ስማ አሰረቺልኝ መቼም ላልየህ ቃሌ ነው የኔ አባት ቃሏ ሰርስሮኝ ወደ ውስጤ ዘለቀ
እንባ ቀረሽ ስሜት ውስጥ ገብታ እኔንም ይዛኝ ዘለቀች
ዛሬ ስሜቷ ሁሉ ዝብርቅርቅ ሆኑአል
ሁሌ ወደ ምንቀምጥባት ቦታ ወስጄ አወራት ጀመር
ትዝ ይለኛል ይሄን ዜማ ከሰጠችኝ መስቀል ጋር አያይዤ እዘፍንላት ጀመር
ልቤ አንቺን ትቶ ከማዘንድ ይደር
ልማልልሽ ወይ በ ቶ መስቀሌ
ከራሴ ጋር ነው ብጣላሽ ጥሌ
የሰጠችኝን መስቀል እየዳበሰች ከእቅፌ ውስጥ ገብታለች
ደሞ ነገ የንግስቴ ልደት ነው
ሁሌ ደስ ሲለኝ በደስታዬ ሀይል ዳመናውን ማዘው ይመስል ዛሬም ስሜቴን ተረድቶ በነጎድጓዱ መጣው ይለኝ ጀምሯል
ካፊያ ከሰማዩ ሲጀምር ይዣት ልነሳ ተነሳሁ አይሆንም አለቺኝ ምወደው ዝናብ ከላይ ከእቅፌ ስር ደሞ ንግስቴ ተኝታለች
በእቅፌ ስር ነች ቶ መስቀሌን በጣቶቿ እየዳሰሰች በትንፋሿ አንገቴን ታሞቀው ጀምራለች
ምን ቁር ምን ብርድ ምን ዶፍ አሁን በኔ ላይ ስሜት አያመጡም የሷ ትንሽ ትንፋሽ የልቤን እሳት ይለኩሰዋል
ያ ውብ ፀጉር በዝናቡ ጠብታዎች ውበቱ ጨምሯል ጠብታዎቹ ቁጭ ቁጭ ብለው ለፀጉሯ ማጌጫ የተቀመጡ ጌጦች መስለዋል ሁሉ ነገራች በስብሷል ዝንቡ ክፉኛ ቢያረጥበንም በፍቅር እቅፍ ውስጥ ሙቅ ቤት ሰርተናል
ፈራሁ አለቺኝ ዝም ብለሽ እቀፊኝ አልኩአት ለካ
እንባዋን ከዝናቡ ጠብታውች እጋ እኩል እያፈሰሰቸቻው ነው
ስቅ ሲላት ሳግ ወደ ላይ ስሜቷን ሲያወጣው እኔም ማልቀሷን አወኩኝ
ምድነው የሆነሽቢኝ ፈራሁ ፈራሁ ብቻ ነው መልሷ
ከፊቴ የማላውቃቸው ሁለት ልጆች ኢስኮ ታች ሜዳ ላይ በጣም ተፈልገሀል አሉኝ መጣሁ አልኳቸው ከሁኔታቸው የግዴት ትዕዛዝ ነው ሚመስለው
ደርሼ ልምጣ አልኩአት አትሂድ አለቺኝ አሁን ነው ምመለሰው ብላትም እባክህ ሆነ መማፀኑአ ተነሺ እሺ አብረን ሄደን እንመለሳለን አልኩአት
ዛሬ ከበስተጀርባዬ ሚቆም ማንም ሰው አልነበረም ሚከተለኝ ህዝብ ዛሬ ከኋላዬ የለም አጆቹአን ይዤ አለሜን እያስከተለኩኝ ወረድኩ
በጨቀየው ሜዳ ወደ 12 የሚጠጉ ልጆች ተሰብስው ቆመዋል በዛ ዝናብ እኔን ቀመው እየጠበቁ ነው አንድማ ማውቀው ፊት የለም
እኔ ከጨቀየው መሬት አለሜን አስከትዬ ጭቃው እየዛኩ ወደ ነሱ ተጠጋው ፎቁ ላይ ያለው ተማሪ ከሜዳው ሚደረገውን ድርጊት ተገርሞ ይመለከታል እጇን አጥብቄ ይዤዋለሁ
ድንገት ከወደ ጭንቅላቴ ከፍ ያለ ምት ተሰማኝ እጆቹአን ለቅቄ ከመሬት ወደኩኝ ጩኸቷ ከጆሮዬ ያቃጭላል ሰውነቴ ብዙ ምቶችን እያስተናገደ ነው ዝናቡ ከላይ የነሱ ቡጢ ከሰውነቴ ይወርድ ጀመረ ኢስኮ እያለች የነበረችው ፊያዬ ዋይ ዋይታዋ ቀነሰብኝ ድምጿ ከጆሮዬ ሲጠፋ የተማሪው ጩኸት ሲያስተጋባ ተሰማኝ ዱላው እየቀነሰ ዝናቡ ሀይሉን ጨምሯል
ደም የሞሏው ፊቴ በዝናቡ እየታጠበ ይነፃ ጀመር ከምንም በላይ የጭንቅላቴ ህመም አይሎብኛል አይኔን ከሜዳው ላይ ጥዬ ብዥታዬን አጠራ ጀመር እሷን መፈለግ ጀመርኩ
ከፊቴ ውድቅ ብላለች ያ ውብ ገላ ከጨቀየው ሜዳ ላይ ተንጋሎ ወድቋል
በተሰባበሩት እጆቼ አይኔን እጠርግ ገባሁ እየዳሁ አጠገቧ ደረስኩ ቅድም ስዳብሰው የነበረው ፀጉር በጭቃ ተለውሷል
በእጆቿ ሆዶአን ይዛዋላች አሁንም ይበልጥ ተጠጋሁዋት
ከዝናቡ አልፍ አንድ ዘለላ እንባ ከአይኗ ስትፈስ አየሁ
ሆዷ ደም ለብሷል ሆድ እቃዋ ተገልብጧል
ኢ ኢ ኢ ስስስኮ አለቺኝ ምድነው እናቴ እጆቼ ግንባሮቿ ላይ ጣልኩት
ቶሎ እንድትመጣ እሺ አባቴ አለቺኝ በደም እጇ ከአንገቴ የተንጠለጠለውን የሰጠችን መስቀል በደም ለወሰቻቸው
ተማሪው ሜዳው ላይ ደርሷል ወዴት እንደምመጣ ባላቅም እሺ እንኩአን ሳልላት አፋፍሰው ወሰዱአት
እኔም በተማሪዎቹ ድጋፍ ተነስቼ እከተላት ጀመረ በታክሲ ተጭኜ ዝም ብዬ መጓዝ ጀመርኩ የተማሪዎቹን የለቅሶና የሀዘን ድምፅ እየሰማሁ ከአንድ ሆስፒታል ደጃፍ ደረስኩ
በነሱ ድጋፍ ከውስጥ ዘለኩ የት እንዳስገቡአት እንጃ ብቻ ሁለት ነርሶች ወደ እኔ መጡ ሊወስዱኝ ፈለጉ አይሆንም አልኩኝ ቶሎ ና እሺ ቶሎ ና የመጨረሻ ድምጿ ከጆሮዬ ያስተጋባል ቃናዋ በህሊናዬ ያንሻብብ ጀመር
ነርሶቹ እንደያዙኝ እሪታና ጩኸት ሲበዛ የአለሜ ቃና በድምፃቸው ተዋጠ ነርሶቹ በሰሙት ጩኸት ለቀቁኝ
ሞታለች የሚል ድምፅ ስሰማ እኔም ሌላ ምት ወደ ጭንቅላቴ ሲመጣ ታወቀኝ ከመሬት ወደኩ ጭንቅላቴ ሲከፈል የጎን አጥንቴ ሲደቅ ተሰማኝ
እናንተዬ ልቤ እየቀነሰችብኝ ትንፋሽ እያጠረኝ ነው እጆቼ ንዝረታቸው ጨምሮ ምፅፈው ሁሉ እየተደለዘ ነው እፍን ምልስ እፍን ምልስ
ሞቷን ስነግራችሁ እኔም ልሄድ ነው መሰለኝ
ደሜ ወረቄትን ሸፍኖታል ድምፅ አልባው እንባዬ እየወረደ ነው ልሄድ ነው በቃ ልሄድ ነው ልቤ እየያዘገመች ነው እጆቼም ዝለውብኛል
እይኔ መስለምለም ጀምሯል ብዥ ብዥ ሆኖብኝ መስመሬን እየሳትኩ ነው ምፅፈው
ከዚ ወዲ ፋታ ለመውሰድ ብዬ ዜማ ስለማላጫውትላችሁ እቺን ብቻ ስሙልኝ እሺ ወደ እኔ ቶሎ ኑ እሺ እናንተም እዛ ስንገናኝ ብዙ ነገር ነው ማጫውታችሁ
መልአከ ሞት መጨረሴን አውቋል መሰል ቀኝ እጄን ለቀም አድርጎ ይዞኛል
በግማሽ ሞት እና በግማሽ ሂወት ውስጥ ነኝ
በግራው አይኔ ካለሁበት አለም ወጥቼ አዲስ ነገርች እያየሁ ነው
በቀኜ ደሞ በደም የተጨማለቀውን ገፄን
እቺን ስሙልኝ አደራ ቶሎ ኑ በሷ ቃል ነው እኔም ምሰናበታችሁ
ዜማዋ ልትጀምር ነው
የት ነው የምትኖሪው ያለሽበት ቦታ
ምንኛ ሀያል ነው ይህ ያንቺ ትዝታ
ደቂቃዎች ሴኮንድ እንዴት ልለይሽ
የትዝታዬ ምንጭ ውሀ
ውሀ ጥሜ ነ