ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.3K subscribers
68 photos
69 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
ሥነ-ፅንስ

ክፍል አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

31:34 አላህ የሰዓቲቱ እውቀት እርሱ ዘንድ ብቻ ነው፤ ዝናምንም ያወርዳል፤ #በማሕፀኖችም #ውስጥ #ያለን #ሁሉ #ያውቃል

መግቢያ
ሥነ-ፅንስ ጥናት ኢምብሪዮሎጂይ”Embryology” ሲባል “ኢምብሮ” ἔμβρυον “ያልተወለደ” እና “ሎጂአ” λογία, “ጥናት” ከሚል ሁለት የግሪክ ቃል የተዋቀረ ነው፤ ይህንን ፅንስ እናቱ ማህፀን ውስጥ በሚፈልገው መልኩ የሚቀርፀው አንዱ አምላክ አላህ ነው፦
3:6 እርሱ ያ “በማሕፀኖች” ዉሰጥ እንደሚሻ አድርጎ “የሚቀርጻችሁ” ነዉ፤ ከእርሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፤

ይህ ፅንስ ማህፀን ውስጥ እንዴት እንደሚፈጠር ሙሉ እውቀት ያለው የዓለማቱ ጌታ አላህ ብቻ ነው፦
31:34 አላህ የሰዓቲቱ ዕውቀት እርሱ ዘንድ ብቻ ነው፤ ዝናምንም ያወርዳል፤ “በማሕፀኖችም ውስጥ ያለን ሁሉ ያውቃል”፤
53:32 ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ “ማሕፀኖች” ውስጥ ሽሎች በሆናችሁ ጊዜ እርሱ በእናንተ ሁኔታ “አዋቂ” ነው።
13:8 አላህ ሴት ሁሉ የምታረግዘውን ያውቃል፤ “ማሕፀኖችም የሚያጐድሉትን የሚጨምሩትንም፥ ያውቃል”፤ ነገሩም ሁሉ እርሱ ዘንድ በልክ የተወሰነ ነው።

በማሕፀኖችም ውስጥ ያለውን ሁሉ የሚያውቀ አምላክ የሥነ-ፅንስ እውቀት ወደፊት እንደሚያሳየና እንደሚያሳውቀን ለማመልከት፦ “በራሶቻችሁ ውስጥ ያሉትም ታምራት ወደፊት ያሳያችኋል፤ ታውቁታላችሁ” በማለት ቃል ገብቷል፦
41፥53 እርሱም ቁርአን እውነት መሆኑ ለነርሱ እስከሚገለጽላቸው ድረስ፣ በአጽናፎቹ ውስጥ እና #በራሶቻቸውም ውስጥ ያሉትን #ታምራቶቻችንን በእርግጥ #እናሳያቸዋለን፤ ጌታህም እርሱ በነገሩ ሁሉ ላይ አዋቂ መሆኑ አይበቃቸውምን?
27:93 ምስጋና ለአላህ ነው፤ #ታምራቶቹን #ወደፊት #ያሳያችኋል#ታውቁታላችሁ በላቸው።

አላህ ይህንን እውቀት በራሳችን አካላት ከማሳየቱ በፊት በቁርአን አንድ ሽል በማህፀን ውስጥ እንዴት የተለያየ ደረጃዎችን”stages” እንደሚያሳልፍ በተከበረ ቃሉ ይነግረናል፦
23:12 በእርግጥም ሰውን ከነጠረ ጭቃ ፈጠርነው፤ ከዚያም በተጠበቀ መርጊያ ውስጥ “የፍትወት ጠብታ” النُّطْفَةَ አደረግነው፤ ከዚያም ጠብታዋን “የረጋ ደም” عَلَقَةً አድርገን ፈጠርን፤ የረጋውንም ደም “ቁራጭ ሥጋ” مُضْغَةً አድርገን ፈጠርን፤ ቁራጯንም ሥጋ “አጥንቶች” عِظَامًا አድርገን ፈጠርን፤ አጥንቶቹንም ሥጋን لَحْمًا አለበስናቸው፤ ከዚያም “ሌላ ፍጥረትን” خَلْقًا آخَرَ አድርገን “አስገኘነው” أَنْشَأْنَاهُ፤ ከሰዓሊዎችም ሁሉ በላጭ የሆነው አላህ ላቀ፡፡
ደረጃ አምስት
“ለህም”
“ለህም” لَحْم ማለት “ስጋ” ማለት ሲሆን ይህ ስጋ ጠንካራ ጡንቻ ያለው ስጋ ነው፤ ከ 35-38 ቀናት የአጥንት ሂደት ሲሆን ከመቅፅበት በ 38ኛው ቀን ልብ፣ አንጎል፣ ቆዳ፣አይን፣ አፍንጫ ወዘተ የሚፈጠርበት ሂደት ነው፦
23:12 አጥንቶቹንም “ሥጋን” لَحْمًا አለበስናቸው፤

በዚህ ጊዜ ሩህ ይነፋል፦
ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 46, ሐዲስ 1:
ዓብደላህ ኢብን መስዑድ እንዲህ አለ። እውነት ተናጋሪ እና እውነት የተነገራቸው የአላህ መልእክተኛ እንዲህ አሉ፦
إِنَّ أَحَدَكُمْ يُجْمَعُ خَلْقُهُ فِي بَطْنِ أُمِّهِ أَرْبَعِينَ يَوْمًا نُطْفَةً، ثُمَّ يَكُونُ عَلَقَةً مِثْلَ ذلِكَ، ثُمَّ يَكُونُ مُضْغَةً مِثْلَ ذلِكَ، ثمَّ يُرْسَلُ إلَيْهِ الْمَلَكُ فَيَنْفُخُ فيهِ الرُّوحَ، وَيُؤمَرُ بأرْبَعِ كَلِمَاتٍ: بِكَتْبِ رِزْقِهِ وَأَجَلِهِ وَعَمَلِهِ وَشَقِيٌّ أوْ سَعِيدٌ.
እያንዳንዳቹህ በእናቱ ሆድ ውስጥ ፍጥረቱ ይሰበሰባል፤ አርባ ቀን የፍትወት ጠብታ ይሆናል፤ ከዛም በተመሳሳይ የረጋ ደምን ይሆናል፤ ከዛም በተመሳሳይ የታኘከን ስጋ ይሆናል፤ ከዛም መልአክ ይላክና ሩሕ ይነፋበታል፤ መልአኩም አራት ነገሮች ላይ ይታዘዛል፦ ሲሳዩን፣ ፍጻሜውን፣ ስራውን፣ የተከፋ ወይንም ደስተኛ መሆኑን እንዲጽፍ ይታዘዛል።

ደረጃ ስድስት
“ነሽአ”
“ነሽአ” نَّشْأَة የሚለው ቃል “አንሸአ” أَنشَأَ “አስገኘ” ከሚለው ቃል የመጣ ሲሆን “ግኝት”production” ማለት ነው፤ አላህም “አንሸናሁ” أَنْشَأْنَاهُ “አስገኘነው” ይለናል፤ ይህም ፅንስ እስከ መወለድ ጊዜ ያለው ሽልን የሚያመለክት ሲሆን “ሌላ ፍጥረትን” ይለዋል፤ በዚህ ጊዜ ከንፈር፣ ጥፍር፣ ፀጉር ወዘተ የሚገኘበት ጊዜ ነው፤ ይህን እረጅም ደረጃ ለማመልከት “ሱምሙ” ثُمَّ “ከዚያም” የሚል መስተፃምር ይጠቀማል፦
23፥12 ከዚያም “ሌላ ፍጥረትን” خَلْقًا آخَرَ አድርገን “አስገኘነው” أَنْشَأْنَاهُ ፤ ከሰዓሊዎችም ሁሉ በላጭ የሆነው አላህ ላቀ፡፡

መደምደሚያ
አላህ ከራሳችን ጥንድ እንድንረካ መፍጠሩ፣ በመካከላችን መተዛዘንና ፍቅር መኖሩ በመርካትም ማህፀን ውስጥ የሚፈሱት የፍትወት ጠብታ ሰው መሆኑ ለሚያስውሉ ሕዝቦች ከአስደናቂ ታምራቶቹ ተጠቃሽ ነው፦
30:21 ለእናንተም ከራሳችሁ “ጥንዶችን” أَزْوَاجًا “mates” ወደ እነርሱ ትረኩ ዘንድ መፍጠሩ፤ በመካከላችሁም ፍቅርንና እዝነትን ማድረጉ ከአስደናቂ “ታምራቶቹ” آيَاتِهِ ነው፤ በዚህ ውስጥ ለሚያስውሉ ሕዝቦች “ታምራቶች” አሉ።

ይህንን ታምር አላህ በሥነ-ፅንስ እውቀት በራሳችን ያሉትን የአላህ ታምራት በዘመናችን አሳይቶናል፤ ከዚህ የሚበልጥ ምን መታደል አለ? ምስጋና ሁሉ ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ ይሁን፦
41፥53 እርሱም ቁርአን እውነት መሆኑ ለነርሱ እስከሚገለጽላቸው ድረስ፣ በአጽናፎቹ ውስጥ እና #በራሶቻቸውም ውስጥ ያሉትን #ታምራቶቻችንን በእርግጥ #እናሳያቸዋለን፤ ጌታህም እርሱ በነገሩ ሁሉ ላይ አዋቂ መሆኑ አይበቃቸውምን?

ዋቢ መጽሐፍት ይመልከቱ፦
1. The Developing Human ( Prof. Keith Moor & Prof. T. Persaud) Edition 6 – 1998
2. Clinical Anatomy . By Richard Snell ( 3ed edition) published in 1986 – Little, Brown
3. A Scientist’s Interpretation of References to Embryology in the Quran (Prof. Keith Moor) Journal of the Islamic Medical Association, 1986: vol.18, Page 15-16

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም