ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.4K subscribers
68 photos
69 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
በሥመላህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

96፥1 አንብብ በዚያ ሁሉን "በ-"ፈጠረው ጌታህ ስም"፡፡ اقْرَأْ بِاسْمِ رَبِّكَ الَّذِي خَلَقَ

ቁርኣን ሲጀምር የሚነበበው ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም ነው፥ ከአንድ ሡራህ በስተቀር እያንዳንዱ ሡራህ ሲጀምር “በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው” በሚል ነው። አንድ ሡራህ ከሌላው ሡራህ የሚለየው “በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው” በሚል ቃል ነው፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 398
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ "ነቢዩ”ﷺ” ሁለት ሡራዎች አይለያዩ በመካከላቸው “በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው” የሚለው ቃል ወደ እርሳቸው ቢወርድላቸው እንጂ"። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ كَانَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم لاَ يَعْرِفُ فَصْلَ السُّورَةِ حَتَّى تُنَزَّلَ عَلَيْهِ ‏{‏ بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ ‏}

አምላካችን አላህ በጂብሪል ለነቢያችን”ﷺ” “ኢቅራ” اقْرَأْ ማለትም “አንብብ” ብሎ አዟቸዋል፦
18፥27 ከጌታህም መጽሐፍ ወደ አንተ የተወረደውን አንብብ፡፡ وَاتْلُ مَا أُوحِيَ إِلَيْكَ مِن كِتَابِ رَبِّكَ
29፥45 ከመጽሐፍ ወደ አንተ የተወረደውን አንብብ፡፡ اتْلُ مَا أُوحِيَ إِلَيْكَ مِنَ الْكِتَابِ
96፥1 አንብብ በዚያ ሁሉን "በ-"ፈጠረው ጌታህ ስም"፡፡ اقْرَأْ بِاسْمِ رَبِّكَ الَّذِي خَلَقَ

"አንብብ በዚያ ሁሉን "በ-"ፈጠረው ጌታህ ስም" የሚለው ይሰመርበት! "በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው" የሚለው ቃል እኛ ሁሉን "በ-"ፈጠረው ጌታህ ስም እንድናነበው የወረደው ነው፥ "በሥመላህ" بَسْمَلَة የሚለው ቃል “በሥመለ” بَسْمَلَ‎ ማለትም “ጠራ” ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “የአላህን ስም መጥራት” ማለት ነው። ይህም ተዝኪራህ "በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው" የሚል ነው፦
1፥1 በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيم

ሡረቱል ፋቲሓህ ሰባት አናቅጽ የያዘች እንደሆነች በቁርኣን እና በሐዲስ ተገልጿል፦
15፥87 ከሚደጋገሙ የኾኑን ሰባትን እና ታላቁንም ቁርኣን በእርግጥ ሰጠንህ፡፡ وَلَقَدْ آتَيْنَاكَ سَبْعًا مِّنَ الْمَثَانِي وَالْقُرْآنَ الْعَظِيمَ
ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3415
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "አል ሐምዱሊሏህ የቁርኣን "እናት"፣ የመጽሐፉ "እናት" እና ሰባት የተደጋገሙ ናት። عَنِ ابْنِ أَبِي ذِئْبٍ، عَنِ الْمَقْبُرِيِّ، عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْحَمْدُ لِلَّهِ أُمُّ الْقُرْآنِ وَأُمُّ الْكِتَابِ وَالسَّبْعُ الْمَثَانِي ‏

"ሡረቱል ፋቲሓህ ሰባት አንቀጽ ያላት በሥመላህን ጨምሮ ነው ወይስ ሳይጨምር " ለሚለው ጥያቄ መልሱ የሐፍሥ ቂርኣህ በሥመላህን የመጀመሪያው አንቀጽ አርጎ በዚህ መልኩ ያስቀምጧል፦
1፥1 "በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَـٰنِ الرَّحِيمِ
1፥2 ምስጋና ለአላህ ይገባው የዓለማት ጌታ ለኾነው። الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ
1፥3 እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ። الرَّحْمَـٰنِ الرَّحِيمِ
1፥4 የፍርዱ ቀን ባለቤት ለኾነው፡፡ مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ
1፥5 አንተን ብቻ እናመልካለን፤ አንተንም ብቻ እርዳታን እንለምናለን፡፡ إِيَّاكَ نَعْبُدُ وَإِيَّاكَ نَسْتَعِينُ
1፥6 ቀጥተኛውን መንገድ ምራን፡፡ اهْدِنَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ
1፥7 የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን፥ በእነርሱ ላይ ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትን ሰዎች መንገድ ምራን" በሉ፡፡ صِرَاطَ الَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلَا الضَّالِّينَ
የወርሽ ቂርኣህ በሥመላህን መግቢያ አርጎ ተሕሚድን የመጀመሪያው አንቀጽ አርጎ በዚህ መልኩ ያስቀምጧል፦
"በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَـٰنِ الرَّحِيمِ
1፥1 ምስጋና ለአላህ ይገባው የዓለማት ጌታ ለኾነው። الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ
1፥2 እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ። الرَّحْمَـٰنِ الرَّحِيمِ
1፥3 የፍርዱ ቀን ንጉሥ ለኾነው፡፡ مَلِكِ يَوْمِ الدِّينِ
1፥4 አንተን ብቻ እናመልካለን፤ አንተንም ብቻ እርዳታን እንለምናለን፡፡ إِيَّاكَ نَعْبُدُ وَإِيَّاكَ نَسْتَعِينُ
1፥5 ቀጥተኛውን መንገድ ምራን፡፡ اهْدِنَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ
1፥6 የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን። صِرَاطَ الَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ
1፥7 በእነርሱ ላይ ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን" በሉ፡፡  غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلَا الضَّالِّينَ

በሥመላህ የቁርኣን ክፍል ነው፥ በአንዱ ቂርኣህ በአንቀጽ መልኩ መቀመጡ እና በሌላው ቂርኣህ በአንቀጽ መልኩ አለመቀመጡ ከተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" የመጣ የአነባነብ ስልት"mode of recitation" ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 66, ሐዲስ 13
ኢብኑ ዐባሥ”ረ.ዐ.” እንደተረከው የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ጂብሪል ለእኔ በአንድ ሐርፍ አቀራር ይቀራልኝ ነበር፥ ከዚያም እኔ በሌላ ሐርፍ እንዲያስቀራኝ ጠየኩት። በተደጋጋሚ ስጠይቀው በሰባት አሕሩፍ በመቅራት ጨመረልኝ። أَنَّ ابْنَ عَبَّاسٍ ـ رضى الله عنهما ـ حَدَّثَهُ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ أَقْرَأَنِي جِبْرِيلُ عَلَى حَرْفٍ فَرَاجَعْتُهُ، فَلَمْ أَزَلْ أَسْتَزِيدُهُ وَيَزِيدُنِي حَتَّى انْتَهَى إِلَى سَبْعَةِ أَحْرُفٍ ‏”‌‏.‏

የሐፍሥ ሪዋያህ፣ የወርሽ ሪዋያህ፣ የቃሉን ሪዋያህ፣ የዱሪ ሪዋያህ ወዘተ ሲባል ከአሏህ በጂብሪል ለተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" የተወረደ ግልጠተ መለኮት እንጂ ሰዎች የፈጠሩት ልዩነት አይደለም። ይህንን ከተረዳን ዘንዳ በስመላህ የቁርኣን ክፍል ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 4 ሐዲስ 56
አነሥ እንደተረከው፦ "በመካከላችን የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" ሆነው ነበርና ተኙ፥ ከዚያም በፈገግታ እራሳቸውን አነሱ። እኛም፦ "የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! ለምን ፈገግ አሉ? አልን፥ እርሳቸውም፦ "ሡራህ ወደ እኔ ተወርዶልኛል" አሉ። እርሳቸው፦ "በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡
እኛ በጣም ብዙ በጎ ነገሮችን ሰጠንህ፣
ስለዚህ ለጌታህ ስገድ፤ በስሙ ሰዋም፣
ጠይህ እርሱ በእርግጥ የተቆረጠው ነው" የሚለውን ቀሩ"። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ بَيْنَا رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ذَاتَ يَوْمٍ بَيْنَ أَظْهُرِنَا إِذْ أَغْفَى إِغْفَاءَةً ثُمَّ رَفَعَ رَأْسَهُ مُتَبَسِّمًا فَقُلْنَا مَا أَضْحَكَكَ يَا رَسُولَ اللَّهِ قَالَ ‏"‏ أُنْزِلَتْ عَلَىَّ آنِفًا سُورَةٌ ‏"‏ ‏.‏ فَقَرَأَ ‏"‏ بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ ‏{‏ إِنَّا أَعْطَيْنَاكَ الْكَوْثَرَ فَصَلِّ لِرَبِّكَ وَانْحَرْ إِنَّ شَانِئَكَ هُوَ الأَبْتَرُ‏}‏ ‏"‏

አያችሁ በሥመላህ የቁርኣን ክፍል ነው። በስመላህ ያለ አንቀጽ መቀመጥ እንደሚችል ደግሞ ይህ ሐዲስ ያሳያል፦
ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 33, ሐዲስ 131
አቢ ሁረይራህ”ረ. ዐ.” እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “እስከሚያስምር ድረስ ለሚቀራው ወዳጁ የሚያማልድ ሠላሳ አናቅጽ የያዘ ሡራህ በቁርኣን ውስጥ አለ፥ እርሱም፦ “ያ ንግሥና በእጁ የኾነው አምላክ የተባረከ(ተመሰገነ) ይሁን” የሚለው ሡራህ ነው”። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ ـ صلى الله عليه وسلم ـ قَالَ ‏”‏ إِنَّ سُورَةً فِي الْقُرْآنِ ثَلاَثُونَ آيَةً شَفَعَتْ لِصَاحِبِهَا حَتَّى غُفِرَ لَهُ ‏{تَبَارَكَ الَّذِي بِيَدِهِ الْمُلْكُ}‏ ‏”‏

ሠላሳ አናቅጽ የያዘ ሡራህ ሡረቱል ሙልክ ሠላሳ የተባለው በስመላህን ሳያካትት ነው። ስለዚህ ሡረቱል ፋቲሓህ ላይ በሥመላህ በአንቀጽ መምጣት እና አለመምጣት ኢሥቲሥናዕ ሆኖ በተለያየ ሪዋያህ መምጣቱ ምንም የትርጉም ልዩነት አያመጣምና እዛ ሰፈር አቧራ ከማስነሳት ይልቅ በመታቀብ "ተሰተሩ" እንላለን። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ቀጥተኛው መንገድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

36፥4 "በቀጥታም መንገድ ላይ ነህ"፡፡ عَلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ

"ሲሯጥ" صِرَٰط ማለት በመነሻ እና በመዳረሻ መካከል ያለ "መንገድ" ማለት ሲሆን እዚህ ዐውድ ላይ "መንገድ" እያልን የምንጦምረው እማሬአዊ የሆነውን የአስፋት መንገድ ሳይሆን ወደ ጀነት የሚያደርሰውን ፍካሬአዊ የሆነውን መንገድ ነው። አምላካችን አሏህን በብቸኝነት ማምለክ ወደ ጀነት የሚያደርስ "ቀጥተኛው መንገድ" ነው፦
36፥61 "አምልኩኝ! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው" በማለትም አላዘዝኩምን? وَأَنِ ٱعْبُدُونِى ۚ هَٰذَا صِرَٰطٌۭ مُّسْتَقِيمٌۭ

"ይህ" የሚለው አመልካች ተውላጠ ስም "አምልኩኝ" የሚለውን ቃል አመላካች ነው። ዒሣም በተልኮው አሏህን በብቸኝነት ማምለክ "ቀጥተኛ መንገድ" እንደሆነ አበክሮ እና አዘክሮ ነግሮናል፦
3፥51 አላህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነዉ፥ ስለዚህ "አምልኩት! ይህ "ቀጥተኛ መንገድ" ነዉ" አላቸዉ። إِنَّ ٱللَّهَ رَبِّى وَرَبُّكُمْ فَٱعْبُدُوهُ ۗ هَٰذَا صِرَٰطٌۭ مُّسْتَقِيمٌۭ

እዚህም አንቀጽ ላይ "ይህ" የሚለው አመልካች ተውላጠ ስም "አምልኩት" የሚለውን ቃል አመላካች ነው። ይህ አንዱን አምላክ በብቸንነት ማምለክ ለኢብራሂም የተገለጠ የኢብራሂም መንገድ ነው፥ አምላካችን አሏህ የኢብራሂምን መንገድ መርቶናል፦
6፥161 «እኔ ጌታዬ ወደ "ቀጥተኛው መንገድ" ትክክለኛን ሃይማኖት ወደ እውነት አዘንባይ ሲኾን የአብርሃምን መንገድ መራኝ፡፡ እርሱም ከአጋሪዎቹ አልነበረም» በል፡፡ قُلْ إِنَّنِى هَدَىٰنِى رَبِّىٓ إِلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ دِينًۭا قِيَمًۭا مِّلَّةَ إِبْرَٰهِيمَ حَنِيفًۭا ۚ وَمَا كَانَ مِنَ ٱلْمُشْرِكِينَ

አሁንም "ቀጥተኛው መንገድ" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! አንድ ሙሥሊም በቀጥተኛው መንገድ ላይ ስለሆነ አምላካችን አሏህ፦ "በቀጥታም መንገድ ላይ ነህ" ብሏል፦
36፥4 "በቀጥታም መንገድ ላይ ነህ"፡፡ عَلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ
43፥43 ያንንም ወደ አንተ የተወረደልህን አጥብቀህ ያዝ! አንተ "በቀጥተኛው መንገድ ላይ ነህና"።فَاسْتَمْسِكْ بِالَّذِي أُوحِيَ إِلَيْكَ ۖ إِنَّكَ عَلَىٰ صِرَاطٍ مُّسْتَقِيمٍ

አንድ ሙሥሊም ቁርኣንን አጥብቆ ከያዘ በቀጥተኛው መንገድ ነው። ከላይ በቁና ጥቅስ እንደተጠቀሰው ሙሥሊም በቀጥተኛ መንገድ ስለሆነ እና ይህም ቀጥተኛ መንገድ አሏህን በብቸኝነት ማምለክ እንደሆነ ተረድቶ አንድ ዳዒ ሰዎችን ወደ ቀጥተኛው መንገድ ይጣራል፦
23፥73 አንተም ወደ "ቀጥተኛው መንገድ" በእርግጥ ትጠራቸዋለህ። وَإِنَّكَ لَتَدْعُوهُمْ إِلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ
16፥125 "ወደ ጌታህ መንገድ" በጥበብ እና በመልካም ግሳጼ ጥራ፡፡ ادْعُ إِلَىٰ سَبِيلِ رَبِّكَ بِالْحِكْمَةِ وَالْمَوْعِظَةِ الْحَسَنَةِ

አንድ ሙሥሊም በቀጥተኛ መንገድ ላይ ባይሆን ኖሮ ወደ ቀጥተኛ መንገድ መጥራቱ ትርጉም አልባ ይሆን ነበር። ቅሉ እና ጥቅሉ ግን ሙሥሊም በቀጥተኛ መንገድ ነው።
ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ታዲያ ለምንድን ነው "ቀጥተኛውን መንገድ ምራን" የምንለው? ይህንን ለመረዳት ይህንን ምሳሌ አጢኑት! ለምሳሌ፦ እኔ ፒያሳ መሄድ ፈልጌ የፒያሳን መንገድ መነሻውን ከጦ ሃይሎች ሰፈር አንድ ሰው ከመራኝ በኃላ መንገዱ በጉዞ ልደታ ጋር ስደርስ ወይም ብሔራዊ ጋር ስደርስ መንገድ እንዳልስት እስከመጨረሻው ምሪት ያስፈልገኛል፥ በተመሳሳይ ይህ ቀጥተኛ መንገድ መነሻውን አሏህ ከመራን በኃላ በጉዞ ላይ እያለን ከመንገዱ እንዳንወጣ ምሪት እስከመጨረሻው ለማግኘት አሏህን በቀን 17 ጊዜ ሶላት ላይ ስንቆም በሱረቱል ፋቲሓህ ላይ "ቀጥተኛውን መንገድ ምራን" እንድንል ነግሮናል፦
1፥6 "ቀጥተኛውን መንገድ ምራን። ٱهْدِنَا ٱلصِّرَٰطَ ٱلْمُسْتَقِيمَ

ምክንያቱም ከአይሁዳውያን ብዙኃኑ ከቀጥተኛው መንገድ ወጥተው አሏህ ተቆጥቷቸዋል፥ ከክርስቲያኖች ብዙኃኑ ከቀጥተኛው መንገድ ወጥተው ተሳስተዋል፦
ጃምዒ አት-ተርሚዚይ መጽሐፍ 47 ሐዲስ 3212
ዐዲይ ኢብኑ ሓቲም እንደተረከው ነብዩም”ﷺ” አሉ፦ "አይሁዳውያን የተቆጣባቸው ናቸው፥ ክርስቲያኖች የተሳቱተት ናቸው"። عَنْ عَدِيِّ بْنِ حَاتِمٍ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ الْيَهُودُ مَغْضُوبٌ عَلَيْهِمْ وَالنَّصَارَى ضُلاَّلٌ ‏”‏ ‏.‏

ነገር ግን በጽናት ከአይሁዳውያን ጥቂት ያልተቆጣቸው እንዲሁ ከክርስቲያኖች ጥቂት ያልተሳሳቱ ሙዋሒዲን ነበሩ፥ እኛም ሳንጸና ከመንገዱ እንዳንስት የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋለላቸውን መንገድ ምራን ብለን እንቀራለን፦
1፥7 የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን፣ በእነርሱ ላይ ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን"በሉ። صِرَٰطَ ٱلَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ غَيْرِ ٱلْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلَا ٱلضَّآلِّينَ

አምላካችን አሏህ ሰዎችን ወደ ቀጥተኛው መንገድ የምንጠራ ያርገን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ንጽጽር በስልጢኛ ለምትፈልጉ ይህንን ሊንክ ያስፈንጥሩ፦ https://tttttt.me/wahidcomselitiy
የውሻ ልጋግ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

7፥176 ብጤውም ብታባርረው ምላሱን አውጥቶ የሚያለከልክ ወይም ብትተወው ምላሱን አውጥቶ የሚያለከልክ እንደ ኾነ ውሻ ነው፡፡ فَمَثَلُهُ كَمَثَلِ الْكَلْبِ إِن تَحْمِلْ عَلَيْهِ يَلْهَثْ أَوْ تَتْرُكْهُ يَلْهَث

"ልጋግ" ማለት "ላጭ" ማለት ሲሆን ከውሻ አፍ የሚወጣው ልጋግ ሰውን የሚጎዱ ጀርሞችን ስለያዘ ነጃሣህ ነው፥ "ነጃሣህ" نَجَاسَة‎ የሚለው ቃል "ነጀሠ" نَجُسَ‎ ማለትም "አረከሰ" "አቆሸሸ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ርኩስ" "ቆሻሻ" ማለት ነው። የውሻ ልጋግ ስለሚነጅሥ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" በቅዱስ ንግግራቸው፦ "ከእናንተ አንዳችሁ ከዕቃው ውስጥ ውሻ ከጠጣ ዕቃውን ሰባት ጊዜ ይጠበው" ያሉን፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 1 ሐዲስ 98
አቢ ሁረይራ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ከእናንተ አንዳችሁ ከዕቃው ውስጥ ውሻ ከጠጣ ዕቃውን ሰባት ጊዜ ይጠበው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ قَالَ ‏ "‏ إِذَا شَرِبَ الْكَلْبُ فِي إِنَاءِ أَحَدِكُمْ فَلْيَغْسِلْهُ سَبْعَ مَرَّاتٍ ‏"‏ ‏.‏

ከታች የለቀኩላችሁ ሁለት ቪድዮ የውሻ ልጋግ እና ከጸጉሩ የሚወጣው ነገር ምን ያህል እንደሚነጅሥ የምርምር ጥናቱ ያሳያል።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የሰንበት ጌታ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

16፥124 ሰንበት የተደረገው በእነዚያ በእርሱ በተለያዩበት ሰዎች ላይ ብቻ ነው፡፡ إِنَّمَا جُعِلَ السَّبْتُ عَلَى الَّذِينَ اخْتَلَفُوا فِيهِ

"ሠብት" سَّبْت የሚለው ቃል "ዕረፍት" ሲሆን "ሰንበት" የሚለው የግዕዙ ቃል በራሱ "እረፍት" ማለት ነው፥ "ሠብዓህ" سَبْعَة ማለት እራሱ "ሰባት" ማለት ነው። በዚህ በሰባተኛው ቀን እረፍት የተደረገው በእስራኤል ልጆች ብቻ ነው፦
16፥124 ሰንበት የተደረገው በእነዚያ በእርሱ በተለያዩበት ሰዎች ላይ ብቻ ነው፡፡ إِنَّمَا جُعِلَ السَّبْتُ عَلَى الَّذِينَ اخْتَلَفُوا فِيهِ

ወደ ባይብንም ስንገባ "ሰንበት" ማለት "እረፍት" ማለት ሲሆን ሰው ስድስት ቀን ሠርቶ በሰባተኛው ቀን ግን የዕረፍት ቀኑ ነው፦
ዘሌዋውያን 23፥3 ስድስት ቀን ሥራ ይሠራል፥ በሰባተኛው ቀን ግን የዕረፍት ሰንበት ነው።

ሰው የተፈጠረው አምላኩን እንዲያመልክ ሲሆን አምላኩ ለሰው ሰንበትን የፈጠረለት እንዲያርፍበት ነው፥ ሰንበት ለሰው ተፈጥሮአል እንጂ ሰው ለሰንበት አልተፈጠረም፦
ማርቆስ 2፥27-28 ደግሞ አላቸው፦ ሰንበት ለሰው ተፈጥሮአል እንጂ ሰው ለሰንበት አልተፈጠረም። እንዲሁም የሰው ልጅ ለሰንበት እንኳ ጌታዋ ነው።

በባይብል ዐውድ "ሰው" እና "የሰው ልጅ" ተብሎ ተያይዞ ከመጣ አጠቃላይ የሰው ልጆችን ያመላክታል፦
ኢዮብ 25፥6 ይልቁንስ ብስብስ የሆነ "ሰው"፥ ትልም የሆነ "የሰው ልጅ" ምንኛ ያንስ!
መዝሙር 144፥3 አቤቱ እርሱን ታውቀው ዘንድ "ሰው" ምንድር ነው? ታስብለት ዘንድ "የሰው ልጅ" ምንድር ነው?
ኢሳይያስ 51፥12 የሚሞተውን "ሰው" እንደ ሣርም የሚጠወልገውን "የሰው ልጅ" ትፈራ ዘንድ አንተ ማን ነህ?
ዘኍልቍ 23፥19 ሐሰትን ይናገር ዘንድ አምላክ "ሰው" አይደለም፥ ይጸጸትም ዘንድ "የሰው ልጅ" አይደለም።

አምላክ ሰው እና የሰው ልጅ አይደለም፥ እንግዲህ ሰው" እና "የሰው ልጅ" አጠቃላይ የሰው ልጆችን ካመለከተ ሰንበት የተፈጠረው ለሰው ማረፊያ ስለሆነ የሰው ልጅ ለሰንበት እንኳ ጌታዋ ነው። ሴት “ለ”-ወንድ ተፈጠረች እንጂ ወንድ “ለ”-ሴት አልተፈጠረምና፥ ወንድ የሴት ጌታዋ ነው፦
1 ቆሮንቶስ 11፥9 ሴት “ለ”-ወንድ ተፈጠረች እንጂ ወንድ “ለ”-ሴት አልተፈጠረምና።
ዘፍጥረት 3፥16 ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፥ እርሱም "ገዥሽ" ይሆናል።
1ኛ ጴጥሮስ 3፥5 ቅዱሳት ሴቶች ደግሞ ለባሎቻቸው ሲገዙ ተሸልመው ነበርና፥ እንዲሁም ሣራ ለአብርሃም፦ ጌታ" ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት።
ዘፍጥረት18፥12 ሣራም በልብዋ እንዲህ ስትል ሳቀች። ካረጀሁ በኋላ በውኑ ፍትወት ይሆንልኛልን? "ጌታዬም" ፈጽሞ ሸምግሎአል።

ሴት ለወንድ ስለተፈጠረች እና ወንድ የሴት ጌታዋ ስለሆነ "ወንድ የባሕርይ ጌታ ነው" እንደማንል ሁሉ ሰንበት ለሰው ስለተፈጠረች እና የሰው ልጅ የሰንበት ጌታዋ ስለሆነ "የሰው ልጅ የባሕርይ ጌታ ነው" አንልም።
ሲቀጥል ኢየሱስ "የሰንበት ጌታ ነው" ቢባል እንኳን ከዐውዱ አንጻር ሰንበትን የሰጠ ነው ተብሎ በፍጹም አይተረጎምም፥ ከዚያ ይልቅ በሰንበት ቀን መልካም በማድረጉ በሰንበት ላይ የበላይ መሆኑን የሚያሳይ ነው።
ሢሠልስ "የጌታችን አምላክ" የሚለው ቃል የሰንበት ጌታ የተባለው ኢየሱስ አምላክ እንዳለው ያሳብቃል፦
ኤፌሶን 1፥17 የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ἵνα ὁ Θεὸς τοῦ Κυρίου ἡμῶν Ἰησοῦ Χριστοῦ,

ዐማርኛ ግልጽ ባይሆንም ግሪኩ "ሆ ቴዎስ ቱ ኩሪዩ ሄሞን" ὁ Θεὸς τοῦ Κυρίου ἡμῶν ማለትም "የጌታችን አምላክ"the God of our Lord" ይላልና። "ጌታችን" ብዙ ቦታ ለፍጡራን ሰዎች ማዕረግ ሆኖ ጥቅም ላይ ውሏል፥ ለምሳሌ፦ ዮሴፍ፣ ሙሴ፣ ዳዊት "ጌታችን" ተብለዋል፦
ዘፍጥረት 44፥9 እኛም ደግሞ "ለ-"ጌታችን ባሪያዎች እንሁን።
ዘኁልቅ 36፥2 እግዚአብሔር አንተን "ጌታችንን" አዘዘህ።
1ኛ ነገሥት 1፥43 በእውነት "ጌታችን" ንጉሥ ዳዊት ሰሎሞንን አነገሠው።

አንድ ሰው ተነስቶ፦ "የእኛ ጌታ አምላክ አለው" ቢልህ ጌታቸው ማእረግ እንጂ እውን ለጌታ የፈጠረው አምላክ አለውን? አሏህ ይቅር ይበለን! ኢየሱስን የባሕርይ ጌታ ለማድረግ የምትፍጨረጨሩት መፍጨርጭ እንዲህ ድባቅ ይገባል። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
አዳም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

32፥7 ያ የፈጠረውን ነገር ሁሉ ያሳመረው የሰውንም ፍጥረት ከጭቃ የጀመረው ነው፡፡ الَّذِي أَحْسَنَ كُلَّ شَيْءٍ خَلَقَهُ ۖ وَبَدَأَ خَلْقَ الْإِنسَانِ مِن طِينٍ

"አዳም" אָדָם ማለት በዕብራይስጥ "ሰው" ማለት ሲሆን የመጀመሪያው ሰው ማንነት እና ምንነት ነው፦
ዘፍጥረት 2፥7 ያህዌህ አምላክ "ሰውን" ከምድር አፈር አበጀው። וַיִּיצֶר֩ יְהוָ֨ה אֱלֹהִ֜ים אֶת־הָֽאָדָ֗ם עָפָר֙ מִן־הָ֣אֲדָמָ֔ה

እዚህ አንቀጽ ላይ "ሰው" ለሚለው የገባው ቃል "ሃ አዳም" הָֽאָדָ֗ם ነው፥ "ሃ" הָֽ አመልካች ውስን መስተአምር ሲሆን በኢ-አመልካች አመልካች "አዳም" אָדָם የመጀመሪያው ሰው የተጸውዖ ስም ነው፦
ዘፍጥረት 5፥5 "አዳም" የኖረበት ዘመን ሁሉ ዘጠኝ መቶ ሠላሳ ዓመት ሆነ፤ ሞተም። וַיִּֽהְי֞וּ כָּל־יְמֵ֤י אָדָם֙ אֲשֶׁר־חַ֔י תְּשַׁ֤ע מֵאֹות֙ שָׁנָ֔ה וּשְׁלֹשִׁ֖ים שָׁנָ֑ה וַיָּמֹֽת׃ ס

"አዳም" אָדָם ለመጀመሪያው ሰው የምንነቱ እና የማንነቱ የተጸውዖ ስሙ ነው። ነገር ግን ይህ አዳም ብቻውን በነበረበት ጊዜ ከጎኑ እረዳት ሌላ ሰው ተፈጠረለት፦
ዘፍጥረት 2፥18 ያህዌህ አምላክ አለ፦ "ሰው" ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፥ የሚመቸውን ረዳት ልፍጠርለት"። וַיֹּ֙אמֶר֙ יְהוָ֣ה אֱלֹהִ֔ים לֹא־טֹ֛וב הֱיֹ֥ות הָֽאָדָ֖ם לְבַדֹּ֑ו אֶֽעֱשֶׂהּ־לֹּ֥ו עֵ֖זֶר כְּנֶגְדֹּֽו׃

እዚህ አንቀጽ ላይ "ሰው" ለሚለው የገባው ቃል "ሃ አዳም" הָֽאָדָ֗ם ሲሆን ይህ አንዱ አዳም አንድ ነጠላ ማንነት ነበረ፥ ከጎኑ አንዲት አጥንት ወስዶ ሔዋን የምትባል ሴት ፈጠረ። በዚያን ቀን ወንዱ አዳም እና ሴቷ ሔዋን በጋራ "አዳም" אָדָ֔ם ተብለዋል፦
ዘፍጥረት 5፥2 ወንድ እና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፥ ባረካቸውም። ስማቸውንም በፈጠረበት ቀን "አዳም" ብሎ ጠራቸው። זָכָ֥ר וּנְקֵבָ֖ה בְּרָאָ֑ם וַיְבָ֣רֶךְ אֹתָ֗ם וַיִּקְרָ֤א אֶת־שְׁמָם֙ אָדָ֔ם בְּיֹ֖ום הִבָּֽרְאָֽם׃ ס

ግን ሔዋን "አዳም" אָדָ֔ם ናት ወይ? ስንል የመጀመሪያው አዳም ባትሆንም ሌላዋ አዳም ናት። ሁለቱ ሰዎች ተራክቦ አርገው ሲዋለዱ ብዙ ሰዎች በዙ፦
ዘፍጥረት 6፥1 እንዲህም ሆነ "ሰዎች" በምድር ላይ መብዛት በጀመሩ ጊዜ ሴቶች ልጆች ተወለዱላቸው። וַֽיְהִי֙ כִּֽי־הֵחֵ֣ל הָֽאָדָ֔ם לָרֹ֖ב עַל־פְּנֵ֣י הָֽאֲדָמָ֑ה וּבָנֹ֖ות יֻלְּד֥וּ לָהֶֽם׃

እዚህም አንቀጽ ላይ "ሰዎች" ለሚለው የገባው ቃል "ሃ አዳም" הָֽאָדָ֗ם እንደሆነ ልብ አድርግ! በዓለም ላይ ዛሬ በጥናት 7.8 ቢልዮን ሰዎች አሉ፥ ሰውን ብዙ ያረገው ማንነቱ እንደሆነ እሙን እና ቅቡል ነው።
ሁሉን የፈጠረ አንድ አምላክ ግን በማንነት ሆነ በምንነት አንድ ስለሆነ የምንነቱ ስም እና የማንነቱ ስም "አሏህ" ይባላል። ሰዎች ይህንን ምንነት እና ማንነት በዕውቀት እየመረመሩ ፈልገው ያገኙት ዘንድ ሰዎችን ሁሉ ከአዳም ፈጠራቸው፦
የሐዋርያት ሥራ 17፥26 ምናልባትም እየመረመሩ ያገኙት እንደ ሆነ አምላክን ይፈልጉ ዘንድ በምድር ሁሉ ላይ እንዲኖሩ የሰውን ወገኖች ሁሉ "ከ-"አንድ" ፈጠረ። ἐποίησέν τε ἐξ ἑνὸς πᾶν ἔθνος ἀνθρώπων κατοικεῖν ἐπὶ παντὸς προσώπου τῆς γῆς,

"አምላክን ይፈልጉ ዘንድ" የሚለው ይሰመርበት! እዚህ አንቀጽ ላይ "አንድ" የተባለው የመጀመሪያው ሰው አዳም ሲሆን እርሱ አንድ ምንነት እና ማንነት እንደነበረ ካወቅን ዘንዳ ሁላችንን የፈጠረ አንድ አምላክ አንድ ማንነት እንደሆነ መርምረን መረዳት ችለናል፦
ሚልክያስ 2፥10 አንድ አምላክስ የፈጠረን አይደለምን? הֲלֹ֛וא אֵ֥ל אֶֽחָ֖ד בְּרָאָ֑נוּ

አዳም ከጎኑ ሴት የምትባል ሰው ባትገኝ እና በመዋለድ ባይባዛ ኖሮ በማንነት እና በምንነት አንድ የሆነ ሰው እና ስሙም አንድ የሆነ ሰው ብቻ ይኖር ነበር፥ ነገር ግን ሰው በዓለም ላይ ብዙ ስለሆነ እከሌ ወይም እከሊት የሚል የተጻውዖ ስም ለእያንዳንዱ ሰው ወቶለታል።

ፈጣሪ ግን አንድ አምላክ ስለሆነ የምንነቱ ስም እና የማንነቱ ስም "አሏህ" ሲሆን ከእርሱ ውጪ ሌላ አምላክ ስለሌለ ብዙ አሏህ የለም፥ ምንነቱን የሚያሳዩ የባሕርያት ስሞች ቢኖሩትም የእርሱ ኢሥሙል ዐለም እና ኢሥሙዝ ዛት “አሏህ” ٱللَّه ነው። “ኢሥሙል ዐለም” اِسْم العَلَم ማለት “የተጸውዖ ስም”proper name” ማለት ሲሆን "ኢሥሙዝ ዛት" اِسْم الذَات ማለት "የምንነት ስም" ማለት ነው፥ “አሏህ” ٱللَّه ማለት ትርጉሙ “አምልኮ የሚገባው” ማለት ሲሆን ከጥንትም ቁርኣን ከመውረዱ በፊት በሴማዊ ዳራ ደግሞ ከሁሉ በላይ የሆነው አንዱ አምላክ ሲጠራበት የነበረ ስም እንደነበር የተለያየ መድብለ ዕውቀቶች"encycolopedias" ያትታሉ፦
1. የሃይማኖት መድብለ-ዕውቀት 1987: “አሏህ የሚለው ስም ሥረ መሠረት የጋራ በሆኑ በተለያዩ ጥንታዊ የሴም ቋንቋዎች ይገኛል” ገጽ 27.
Encycolopedia of religion 1987: “the orgin of Allah is found in a root common to various ancient semetic languages” p27.

2. የክርስትና መድብለ-ዕውቀት 2001: “ቅድመ-ቁርኣን ዐረብ ተናጋሪ ክርስቲያን እና አይሁድ እንዲሁ አሏህ ለታላቁ አምላክ ይጠቀሙበት ነበር” ገጽ 101.
Encyclopedia of Christianity 2001: “before Quran Arabic-speaking Christians and Jews also refer to supreme God as Allāh” page 101.

3. የኢሥላም መድብለ-ዕውቀት 1913: “ዐረቦች ቅድመ-ነቢዩ ሙሐመድ በነበሩት ዘመናት አሏህ የሚባል ታላቅ አምላክ ያመልኩ ነበር” ገጽ 302.
Encyclopedia of Islam 1913: “Before prophet Muhammad Arabian was worshiping supreme God who is Allah” page 302.

4. የብሪታኒካ መድብለ-ዕውቀት 1996: “ቅድመ-ቁርኣን በነበሩት ዐረቢያን መጻሕፍት ውስጥ አላህ የሚለው ቃል ይገኛል” ገጽ 106.
Encyclopedia of britannica 1996: “Before Quran The word Allah was in the Arabic books” page 106.

የአዳምን አፈጣጠር አይታችሁ የአሏህ ስም የምትረዱ ያርጋችሁ! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የሁሉ ጌታ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

6፥164 በላቸው «እርሱ አላህ የሁሉ ነገር ጌታ ሲሆን ከአላህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን? ነፍስም ሁሉ በራሷ ላይ እንጅ ክፉን አትሠራም፡፡ قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْءٍۢ ۚ وَلَا تَكْسِبُ كُلُّ نَفْسٍ إِلَّا عَلَيْهَا

አምላካችን አሏህ ስለ ራሱ በሦስተኛ መደብ "የሁሉ ነገር ጌታ" እንደሆነ ይናገራል፦
6፥164 በላቸው «እርሱ አላህ የሁሉ ነገር ጌታ ሲሆን ከአላህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን? ነፍስም ሁሉ በራሷ ላይ እንጅ ክፉን አትሠራም፡፡ قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْءٍۢ ۚ وَلَا تَكْسِبُ كُلُّ نَفْسٍ إِلَّا عَلَيْهَا

ሚሽነሪዎች ይህንን አንቀጽ ይዘው "በባይብል ኢየሱስ "የሁሉ ጌታ" ተብሏልና የእርሱ ጌትነት የባሕርይ ነው" በማለት ይህንን ጥቅስ ይጠቅሳሉ፦
የሐዋርያት ሥራ 10፥36: "የሁሉ ጌታ በሚሆን" በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምን እየሰበከ ይህን ቃል ወደ እስራኤል ልጆች ላከ። Tὸν λόγον ὃν ἀπέστειλεν τοῖς υἱοῖς Ἰσραήλ, εὐαγγελιζόμενος εἰρήνην διὰ Ἰησοῦ χριστοῦ― οὗτός ἐστιν πάντων κύριος―

ሲጀመር "የሁሉ ጌታ በሚሆን"he is Lord of all" የሚለው ኃይለ-ቃል በ 400 ድኅረ ልደት በተዘጋጀው ኮድ በፊደል D በቁጥር 05 በሆነው ኮዴክስ ቤዛይ ላይ በቅንፍ የተቀመጠ ነው፦
― οὗτός ἐστιν πάντων κύριος―

ለማመሳከሪያ ኦርጅናሉ ስለሌለ የተለያዩ ቨርዥኖች "he is Lord of all" የሚለውን በቅንፍ አስቀምጠውታል፥ ለምሳሌ፦
1. English Standard Version
2. King James Bible
3. New American Standard Bible
4. American Standard Version
5. Literal Standard Version
6. Young's Literal Translation
ተጠቃሾ ናቸው።

ልክ ሉቃስ 3፥23 "እንደመሰላቸው"as was supposed" የሚለው ኮዴክስ ቤዛይ ላይ በቅንፍ እንደተቀመጠው ማለት ነው፦
ሉቃስ 3፥23 ― ὡς ἐνομίζετο―

ሲቀጥል ጥቅሱ ላይ "የሁሉ" የሚለው ገላጭ ቅጽል "ፓንቶን" πάντων አይሁድ እና አሕዛብ ለማሳየት የገባ አንጻራዊ እንጂ ፍጹማዊ አይደለም። ለምሳሌ፦ "ፓንቶን" የሚለው ቃል በአንጻራዊ ደረጃ ይመጣል፦
1 ቆሮንቶስ 4፥13 እስከ አሁን ድረስ የዓለም ጥራጊ "የሁሉም" ጉድፍ ሆነናል። δυσφημούμενοι παρακαλοῦμεν· ὡς περικαθάρματα τοῦ κόσμου ἐγενήθημεν, πάντων περίψημα ἕως ἄρτι.

ጳውሎስ "የሁሉም" ሰው ጉድፍ ሆነናል" ሲል በአንጻራዊ እንጂ ጳውሎስ የማያውቁት ሁሉንም ያጠቃልላል ማለት አይደለም። በተመሳሳይም ኢየሱስ "የሁሉ ጌታ" የተባለው በአንጻራዊ ደረጃ ነው፥ ምክንያቱም አንደኛ ጌትነቱ መነሻ አለው፣ ሁለተኛ ከእርሱ በላይ ያለውን ጌታውን "ጌታዬ" እያለ ተናግሯል፣ ሦስተኛ የእርሱ ጌታ አብ እርሱን "ባሪያዬ" ብሎታል፣ አራተኛ ከበላዩ ራስ አለው።
ሢሠልስ አማኞች "የሁሉ ጌታ" ተብለዋል፦
ገላትያ 4፥1 ነገር ግን እላለሁ ወራሹ ሕፃን ሆኖ ባለበት ዘመን ሁሉ ምንም "የሁሉ ጌታ" ቢሆን ከቶ ከባሪያ አይለይም። Λέγω δέ, ἐφ’ ὅσον χρόνον ὁ κληρονόμος νήπιός ἐστιν, οὐδὲν διαφέρει δούλου κύριος πάντων ὤν,

"ወራሹ ሕፃን ሆኖ ባለበት ዘመን ሁሉ ምንም "የሁሉ ጌታ" ቢሆን ከቶ ከባሪያ አይለይም" የተባለው ሕፃን አማንያንን እንደሆነ ዐውደ ንባቡ"contextual passage" ይናገራል፦
ገላትያ 4፥2-3 ነገር ግን አባቱ እስከ ቀጠረለት ቀን ድረስ ከጠባቂዎችና ከመጋቢዎች በታች ነው። እንዲሁ እኛ ደግሞ ሕፃናት ሆነን ሳለን ከዓለም መጀመሪያ ትምህርት በታች ተገዝተን ባሪያዎች ነበርን።
ገላትያ 4፥7 ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲህ ልጅ ነህ እንጂ ባሪያ አይደለህም፤ ልጅም ከሆንህ ደግሞ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ወራሽ ነህ።

ዮሴፍ በአንጻራዊ ደረጃ በግሪክ ሰፕቱአጀንት "የሁሉ ጌታ" ተብሏል፦
ዘፍጥረት 45፥9 "አምላክ" በግብፅ ምድር ላይ "የሁሉ ጌታ" አደረገኝ። τάδε λέγει ὁ υἱός σου ᾿Ιωσήφ· ἐποίησέ με ὁ Θεὸς κύριον πάσης γῆς Αἰγύπτου·

ዮሴፍ በመደረግ "የሁሉ ጌታ" ከተባለ ኢየሱስም በመደረግ "የሁሉ ጌታ" ቢባል ያንስበታልን? ወይስ ይበዛበታል? ፈጣሪ አምላክ ዮሴፍን ጌታ ስላረገው ዮሴፍ፦ "አምላክ" በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ "ጌታ" አደረገኝ" ብሎአል፦
ዘፍጥረት 45፥9 "አምላክ" በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ "ጌታ" አደረገኝ። שָׂמַ֧נִי אֱלֹהִ֛ים לְאָדֹ֖ון לְכָל־מִצְרָ֑יִם

"ጌታ አደረገኝ" ሲል የዓለማቱ ጌታ ሆነ ማለት ሳይሆን በጸጋ እና በስጦታ ያገኘው እንጂ የባሕርይ ጌትነት በፍጹም አይደለም። በተመሳሳይም የኢየሱስ ጌትነት በመደረግ ላይ የተመሠረተ መነሾ ያለው ስለሆነ የባሕርይ ጌትነት በፍጹም አይደለም፦
የሐዋርያት ሥራ 2፥36 ኢየሱስን አምላክ ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው የእስራኤል ወገን ሁሉ በእርግጥ ይወቅ። ἀσφαλῶς οὖν γινωσκέτω πᾶς οἶκος Ἰσραὴλ ὅτι καὶ Κύριον αὐτὸν καὶ Χριστὸν ἐποίησεν ὁ Θεός, τοῦτον τὸν Ἰησοῦν.

እዚህ አንቀጽ ላይ "አምላክ" ባለቤት ሲሆን "ኢየሱስ" ተሳቢ ነው፥ በባለቤት እና በተሳቢ መካከል "እንዳደረገው" የሚል ተሻጋሪ ግሥ አለ። ጌታ አድራጊ አንዱ አምላክ ሲሆን ጌታ ተደራጊ ኢየሱስ ነው፥ አምላክ ኢየሱስን ጌታ ካረደገው የኢየሱስ ጌትነት መነሾ ያለው ስለሆነ ጌታ ከመደረጉ በፊት በባዶነት ስለሚቀደም ጌትነቱ ሥልጣን እና ሹመት ወይም እልቅና እና ማዕረግን ብቻ ያሳያል እንጂ የባሕርይ ገንዘቡ መሆኑን በፍጹም አያሳይም።
ስለዚህ ኢየሱስ "የሁሉ ጌታ" የተባለው ልክ አማኞች እና ዮሴፍ በተባሉበት ሒሣብ አንጻራዊ ነው፥ የኢየሱስ ጌታ አሏህ ግን በጌትነቱ ባርነት የሌለበት የሁሉም አንድ ጌታ አምላክ ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
በስሜ ብትለምኑ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

5፥75 የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልእክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልእክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ

የተለያዩ ሰዎች በአንድ ጊዜ በተለያየ ሥፍራ ሆነውን የሚለምኑትን ልመና የሚሰማ አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ ልመና የአምልኮ ክፍል ስለሆነ ልመናን የሚቀበል እና የሚሰማ ኢየሱስን የላከው አንዱ አምላክ አብ ብቻ ነው፦
ማቴዎስ 7፥11 በሰማያት ያለው አባታችሁ "ለሚለምኑት" እንዴት አብልጦ መልካም ነገርን ይሰጣቸው? πόσῳ μᾶλλον ὁ Πατὴρ ὑμῶν ὁ ἐν τοῖς οὐρανοῖς δώσει ἀγαθὰ τοῖς αἰτοῦσιν αὐτόν.

"በሰማያት ያለው አባታችሁ ለሚለምኑት" የሚለው ኃይለ ቃል ተለማኝ አብ ለማኝ ፍጡራን እንደሆኑ ቁልጭ አርጎ ያሳያል። ኢየሱስ እራሱ አንዱን አምላክ ጠይቆ መልስ የሚጠብቅ ለማኝ ነበር፦
ዮሐንስ 11፥22 አሁንም ከአምላክ የምትለምነውን ሁሉ አምላክ እንዲሰጥህ አውቃለሁ አለችው። καὶ νῦν οἶδα ὅτι ὅσα ἂν αἰτήσῃ τὸν Θεὸν δώσει σοι ὁ Θεός.

ኢየሱስ አምላክን ለምኖ የሚሰጠው ከሆነ እርሱ ለማኝ ነቢይ እንጂ ተለማኝ አምላክ በፍጹም አይደለም፥ ኢየሱስ ይህንን አንድ አምላክ ሌሊቱን ሙሉ ሲለምን በአምልኮ አሳልፏል፦
ሉቃስ 6፥12 በነዚህም ወራት ይጸልይ ዘንድ ወደ ተራራ ወጣ፥ ሌሊቱንም ሁሉ ወደ አምላክ ሲጸልይ አደረ። Ἐγένετο δὲ ἐν ταῖς ἡμέραις ταύταις ἐξελθεῖν αὐτὸν εἰς τὸ ὄρος προσεύξασθαι, καὶ ἦν διανυκτερεύων ἐν τῇ προσευχῇ τοῦ Θεοῦ.

ኢየሱስ በጸሎት የሚለምን ለማኝ ከሆነ ጸሎቱን ሰምቶ የሚመልስለት አምላኩ ተለማኝ ነው። ሰዎችም የእርሱ ፈለግ ተከትለው አምላኩን ቢለምኑ ልመናቸውን ይሰማል፦
ዮሐንስ 15፥16 አብም በስሜ "የምትለምኑትን" ሁሉ ይሰጣችኃል። ἵνα ὅ τι ἂν αἰτήσητε τὸν Πατέρα ἐν τῷ ὀνόματί μου δῷ ὑμῖν.

"በስሜ" የሚለው ይሰመርበት! በኢየሱስ ስም አብ ሲለመን ልመናውን ሰምቶ አብ ይሰጣል። አብን በኢየሱስ ስም ሲለመን ኢየሱስ ደግሞ አብን አማላጅ ሆኖ ይለምናል፦
ዮሐንስ 14፥14 ማናቸውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ እኔ አደርገዋለሁ። ἐάν τι αἰτήσητε ἐν τῷ ὀνόματί μου, ἐγὼ ποιήσω.

"አደርጋው"I will do" የሚለው መጻኢ ግሥ "ፓኤሶ" ποιήσω ሲሆን ምን እንደሚያደርግ ዐውዱ ላይ ተገልጿል፦
ዮሐንስ 14፥15 እኔም አብን "እለምናለሁ"፥ κἀγὼ ἐρωτήσω τὸν Πατέρα

"እለምናለሁ"I will pray" በማለት "አደርጋለው" የሚለው ድርጊት ጸሎት እንደሆነ እንቅጩን ፍርጥ አርጎ ተናግሯል። ኢየሱስ ለማኝ እንዲሁ አምላክ ደግሞ ተለማኝ ከሆነ ኢየሱስ በአምላክ ቀኝ አብን ስለ አማኞች ይለምናል፦
ሮሜ 8፥34 በአምላክ ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ "የሚማልደው" ክርስቶስ ኢየሱስ ነው። ὅς ἐστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ Θεοῦ, ὃς καὶ ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.

"ኢንቱካኖ" ἐντυγχάνω ማለት "ጠራ" "ማለደ" "አማለደ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ ለማኝ መሆኑን አምላክ ተለማኝ መሆኑን ፍንትው አርጎ ያሳያል፥ በቋንቋ ደረጀ "ማለደ" ማለት "ለመነ" "ደጅ ጠና" ማለት ነው። ኢየሱስ አማላጅ ስለመሆኑ ከዚህ ቀደም የጻፍኩትን ያንብቡ፦ https://tttttt.me/Wahidcom/3374

ኢየሱስ ለሐዋርያቱ፦"አብም በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ ይሰጣችኃል" ባለው መሠረት ሐዋርያት አብን በተግባር ለምነውታል፦
የሐዋርያት ሥራ 4፥29 አሁንም ጌታ ሆይ! ወደ ዛቻቸው ተመልከት! ባሪያዎችህ በፍጹም ግልጥነት ቃልህን እንዲናገሩ ስጣቸው።
የሐዋርያት ሥራ 4፥30 ለመፈወስም እጅህን ስትዘረጋ በቅዱስ ባሪያ በኢየሱስ ስም ምልክት እና ድንቅ ይደረግ። ἐν τῷ τὴν χεῖρά ἐκτείνειν σε εἰς ἴασιν καὶ σημεῖα καὶ τέρατα γίνεσθαι διὰ τοῦ ὀνόματος τοῦ ἁγίου Παιδός σου Ἰησοῦ.

"ፓይዶስ" Παιδός ማለት "ባሪያ" "አገልጋይ" ማለት ነው፥ በዚህ ባሪያ ስም የሚለመነው ጌታ አብ እንደሆነ በቂ ማሳያ ነው። ኢየሱስ ሰማይ ላይ እንደ አምላክ ተገልጋይ ሳይሆን አገልጋይ ነው፦
ዕብራውያን 8፥2 እርሱም የመቅደስ እና የእውነተኛይቱ ድንኳን "አገልጋይ" ነው፥ እርስዋም በሰው ሳይሆን በጌታ የተተከለች ናት።
"በኢየሱስ ስም" ማለት ደግሞ "ኢየሱስ እንዴት መጸለይ እንዳለባቸው ባዘዛቸው መሠረት ወደ አብ መጸለይ በኢየሱስ ስም መጸለይ" ማለት ነው፥ "በ" የሚል መስተዋድድ ባለበት ቃል ላይ "ስም" የሚል ቃላት አንዳንድ ናሙና እንመልከት፦
1ኛ ስሙኤል 25፥9  የዳዊትም ጕልማሶች መጡ፥ ይህንም ቃል ሁሉ "በዳዊት ስም" ለናባል ነግረው ዝም አሉ።

"በዳዊት ስም" የሚለው ይሰመርበት! የዳዊትም ጕልማሶች ለናባል "በዳዊት ስም" ነገሩት ማለት "በዳዊት ትእዛዝ" ነገሩት ከሆነ እንግዲያውስ "በኢየሱስ ስም" አብን መለመን ማለት "በኢየሱስ ትእዛዝ" አብን መለመን ማለት ነው። ሌላ ናሙና እንመልከት፦
ማቴዎስ 10፥42 ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ "በደቀ መዝሙር ስም" የሚያጠጣ እውነት እላችኋለሁ ዋጋው አይጠፋበትም።

"በደቀ መዝሙር ስም" የሚለው ይሰመርበት! "በደቀ መዝሙር ስም" ጽዋ ውኃ ለታናናሾች ማጠጣት ዋጋ እንደሚያሰጥ ሁሉ "በኢየሱስ ስም" ጽዋ ውኃ ማጠጣት ዋጋ ያሰጣል፦
ማርቆስ 9፥41 የክርስቶስ ስለ ሆናችሁ "በስሜ" ጽዋ ውኃ የሚያጠጣችሁ ሁሉ ዋጋው እንዳይጠፋበት እውነት እላችኋለሁ።

እንደ እናንተ ስሑት ሙግት "በኢየሱስ ስም" ማለት ልክ "በአሏህ ስም" እንደ ማለት ከሆነ "በዳዊት ስም" "በደቀ መዝሙር ስም" ማለት "በአምላክ ስም" ማለት ነው ብላችሁ ለምን አልተረዳችሁትም? ዳዊት እና ኢየሱስ ነቢያት ሲሆኑ ሐዋርያቱ ደግሞ ጻድቃን ናቸው፥ ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል፦
ማቴዎስ 10፥41 ነቢይን "በነቢይ ስም" የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም "በጻድቅ ስም" የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።

"በነቢይ ስም" እና "በጻድቅ ስም" የሚለው ይሰመርበት! ያ ማለት ነቢይን እንደ ነቢይ የሚቀበል ጻድቅን እንደ ጻድቅ የሚቀበል ዋጋ አለው፥ ዐውደ ንባቡ ላይ "እናንተን የሚቀበል" በማለት ሐዋርያትን እንደ ጻድቅ መቀበል እንዲሁ "እኔን የሚቀበል" በማለት መልእክተኛውን ኢየሱስን እንደ ነቢይ መቀበል ምንዳ እና ትሩፋት አለው፦
ማቴዎስ 10፥40 እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።

ስለዚህ "በኢየሱስ ስም" የተባለው "በዳዊት ስም" "በደቀ መዝሙር ስም" "በነቢይ ስም" "በጻድቅ ስም" በተባለበት ስሌት እና ቀመር ነው። “በ” የሚለውን “ለ” ብሎ ከተረዱት እንግዲያውስ “በ”-ጽዮን” የሚለውን “ለ”-ጽዮን” ብለው መረዳት ይኖርባቸዋል፦
መዝሙር 65፥1 አቤቱ “በ”-ጽዮን ለአንተ ምስጋና ይገባል።  לַמְנַצֵּ֥חַ מִזְמֹ֗ור לְדָוִ֥ד שִֽׁיר׃ לְךָ֤ דֻֽמִיָּ֬ה תְהִלָּ֓ה אֱלֹ֘הִ֥ים בְּצִיֹּ֑ון

ስለዚህ “ኢየሱስ ይመለካል” ብሎ ኲታ ገጠም ርእስ አርጎ በደምሳሳው መሞገት ወትሮም ቢሆን ዘንድሮም የሚያዋጣ ሙግት አይደለም፥ የሚለምንን ለማኝ መለመን በራሱ ሺርክ ነው። በኢሥላም ግን የመርየም ልጅ ኢየሱስ ከእርሱ በፊት እንዳሉት መልእክተኞች የሆነ መልእክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፦
5፥75 የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልእክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልእክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ

አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የዘላለም ሕይወት መልእክት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

4፥71 የመርየም ልጅ አል-መሢሕ ዒሣ የአላህ መልእክተኛ ብቻ ነው። إِنَّمَا الْمَسِيحُ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ رَسُولُ اللَّهِ

"ረሡል" رَسُول የሚለው ቃል "አርሠለ" أَرْسَلَ ማለትም "ላከ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "መልእክተኛ" ማለት ነው፥ "ሪሣላህ" ማለት "መልእክት" ማለት ሲሆን "ሙርሢል” مُرْسِل ማለት ደግሞ "ላኪ" ማለት ነው። አምላካችን አሏህ "ሙርሢል" ሲሆን ዒሣ ኢብኑ መርየም ደግሞ "ረሡል" ነው፦
4፥71 የመርየም ልጅ አል-መሢሕ ዒሣ የአላህ መልእክተኛ ብቻ ነው። إِنَّمَا الْمَسِيحُ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ رَسُولُ اللَّهِ

አሏህ ለዒሣ እንዲያስተላልፍ የሰጠው "ሪሣላህ" ኢንጂል ነው፥ መልእክተኛ የራሱ ሙሉ ዕውቀት ስለሌለው የላከው ዕውቀት የሚያስለላልፍ ነው።
ወደ ባይብል ስንመጣ ኢየሱስ የአንዱ አምላክ መልእክተኛ ስለሆነ አንዱ አምላክ ለኢየሱስ እንዲያስተላልፍ መልእክት ሰቶታል፦
ዮሐንስ 17፥8 የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና።

"የሰጠኸኝን ቃል" የሚለው ይሰመርበት! ኢየሱስ የዘላለም ሕይወት ቃል አለው፥ ይህን የዘለዓለም ሕይወት ቃል የሚሰጠው አብ እንዲሰጥ ሥልጣን ስለሰጠው እንጂ እርሱ ከራሱ ምንም ማድረግ አይችልም፦
ዮሐንስ 6፥68 አንተ "የዘላለም ሕይወት ቃል" አለህ።
ዮሐንስ 12፥49 እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም "ትእዛዝ ሰጠኝ"።
ዮሐንስ 12፥50 "ትእዛዙም የዘላለም ሕይወት እንደ ሆነች" አውቃለሁ። ስለዚህ እኔ የምናገረውን አብ እንደ ነገረኝ እንዲሁ እናገራለሁ።

ኢየሱስ የሚለው እና የሚናገረው ከራሱ ካልሆነ እና የሚለው እና የሚናገረው ትእዛዙ የላከው ከሰጠው ያ የተሰጠው ትእዛዝ የዘላለም ሕይወት ነው። የዘላለም ሕይወትን የሆነውን ይህንን ትእዛዝ ለአማኞች እንዲሰጥ ሥልጣን የሰጠው አብ ነው፦
ዮሐንስ 17፥2 በሥጋም ሁሉ ላይ ሥልጣን እንደ ሰጠኸው፥ ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ልጅህን አክብረው።

የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ሥልጣን ከተሰጠው ይህም የዘላለም ሕይወት ዕውቀት እንደሆነ ዐውደ ንባቡ ይናገራል፦
ዮሐንስ 17፥3 እውነተኛ አምላክ ብቻህን የሆንህ አንተን እና የላክኸውን ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት። αὕτη δέ ἐστιν ἡ αἰώνιος ζωή, ἵνα γινώσκωσιν σὲ τὸν μόνον ἀληθινὸν θεὸν καὶ ὃν ἀπέστειλας Ἰησοῦν Χριστόν.
1ኛ ዮሐንስ 5፥20 የአምላክም ልጅ እንደ መጣ፥ እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ መረዳት እንደ ሰጠን እናውቃለን። οἴδαμεν δὲ ὅτι ὁ Υἱὸς τοῦ Θεοῦ ἥκει, καὶ δέδωκεν ἡμῖν διάνοιαν ἵνα γινώσκομεν τὸν ἀληθινόν·

"ይህቺ" ተብሎ በአምልካች ተውላጠ ስም የተቀመጠው የዘላለም ሕይወት አብን ብቻውን እውነተኛ አምላክ መሆኑን እና ኢየሱስ የእውነተኛው አምላክ መልእክተኛ መሆኑን "ማወቅ" ነው። በዚህም መልእክተኛው ወልድ እውነተኛ አምላክን የሆነውን አብን ለማወቅ መረዳት(ዕውቀት) ሰጥቷል፥ "እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ መረዳት እንደ ሰጠን እናውቃለን" የሚለው ይህንኑ ነው። ኢየሱስ ከአብ የሰማውን ዕውቀት አስታውቋል፦
ዮሐንስ 15፥15 ከአባቴ የሰማሁትን ሁሉ ለእናንተ አስታውቄአችኋለሁና።

ኢየሱስ፦ "ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ" በሚል ኃይለ ቃል ውስጥ "ለሰጠኸው" ሲል ከአብ ለወልድ የተሰጡት አማኞች ናቸው፦
ዮሐንስ 10፥29 "የሰጠኝ" አባቴ ከሁሉ ይበልጣል።
ዮሐንስ 17፥6 ከዓለም "ለሰጠኸኝ ሰዎች" ስምህን ገለጥሁላቸው። የአንተ ነበሩ ለእኔም "ሰጠሃቸው"።

ኢየሱስ ከአብ የተሰጠውን ቃል፣ ትእዛዝ፣ ዕውቀት ለአማኞችም ስለሚሰጥ "ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ" ማለቱ ይህንን ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው፦
ዮሐንስ 10፥28 እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ።

"ለበሬ ሁሉ ነገር ጭድ ይመስለዋል" ለየት ያለ ጥቅስ ሲገኝ ጎትጉቶ እና ጎትቶ ለኢየሱስ አምላክነት መደረብ ሚሽነሪዎች ዋንጫ የወስዱበት ጉዳይ ነው፥ በድፍ ቅል ጉሳንጉስ የሥነ መለኮት ቅመራ ከመቀመር ይልቅ ማጥናት ይገባል። "የዘላለም ሕይወት" የተባለው ቃል፣ ትእዛዝ፣ ዕውቀት እንደሆነ ከተረዳን ዘንዳ ይህንን የዘላለም ሕይወት እንዲሰጥ ሥልጣን ተሰቶታል እንጂ ኢየሱስ ከራሱ ምንም ነገር ማድረግ አይችልም፦
ዮሐንስ 5፥30 እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም።

"እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም" "እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና" ካለ እርሱ የዘላለምን ሕይወት የሆነውን መልእክት ከላኪው ከአብ እንዲያስተላልፍ ሥልጣን የተሰጠው መልእክተኛ ብቻ ነው፥ ኢየሱስ "እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ" ብሎ የተናገውን ንግግር ይዞ ለአምላክነት መሞገት ዛብ የሌለው ፈረሰኛ ምሳ የሌለው ኮሰኛ ነውና ሙግቱ ያልፋፋ እና ያልዳበረ ሙግት ነው። ይህንን ሰው የሆነ መልእክተኛ የምታመልኩ አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
መተካከል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ

አምላካችን አሏህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል የራሱ ባሕርያት አሉት፥ እርሱን የሚመስል ምንም ነገር የለም፦
42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ሚስል" مِثْل በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ የገባው "ከ" كَ የሚል መስተዋድድ "በጭራሽ" ማለት ነው፥ "ነገር" በሚለው ቃል ውስጥ ሁሉም ፍጡራን የሚካተቱ ሲሆኑ ከፍጡራን መካከል እርሱን የሚመስል ብጤ እና ምክሼ በጭራሽ የለም፦
112፥4 «ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም፡፡» وَلَمْ يَكُن لَّهُ كُفُوًا أَحَدٌ
19፥65 እርሱ የሰማያት እና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነው እና አምልከው! እርሱን በአምልኮ ላይ ታገስ! ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን?። رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا فَاعْبُدْهُ وَاصْطَبِرْ لِعِبَادَتِهِ ۚ هَلْ تَعْلَمُ لَهُ سَمِيًّا

እዚህ አንቀጽ ላይ "ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን" ሲል አሏህን የሚተካከው ብጤ እና ሞክሼ እንደሌለው በቂ ማሳያ ነው።
ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ኢየሱስ በአምላክ ኃይል በሕይወት ይኖራል፦
2 ቆሮንቶስ 13፥4 ነገር ግን "በ"-አምላክ ኃይል በሕይወት ይኖራል። ἀλλὰ ζῇ ἐκ δυνάμεως Θεοῦ.

"በ" የሚለው መስተዋድድ መነሻ ላይ ያለው "የአምላክ ኃይል" እና ክርስቶስ ሁለት ለየቅል የሆኑ ነገሮች ናቸው፥ በተመሳሳይ "ኃይል" የሚለው "መልክ" በሚል ተዋዋጭ ቃል መጥቷል፦
ፊልጵስዩስ 2፥6 እርሱ "በ-"አምላክ መልክ" ሲኖር ሳለ ከአምላክ ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም። ὃς ἐν μορφῇ Θεοῦ ὑπάρχων οὐχ ἁρπαγμὸν ἡγήσατο τὸ εἶναι ἴσα Θεῷ,

"በ" የሚለው መስተዋድድ መነሻ ላይ ያለው "የአምላክ መልክ" እና ክርስቶስ ሁለት ለየቅል የሆኑ ነገሮች ናቸው፥ "ሲኖር"being" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ሃይፓርኮን" ὑπάρχων ሲሆን ቀጣይነት ያለው የአሁኑ ግሥ ስለሚያመለክት ከመወለዱ በፊት ያለውን ቅድመ ህልውና በጭራሽ አያሳያም፥ ለዚያን ነው በእንግሊዝኛ በአላፊ ግሥ "Who, was in the form of God" ሳይሆን Who, being in the form of God" ብለው ቀጣይነት ባለው አሁኗዊ ግሥ"present participle" ያስቀመጡት። አየሱስ እራሱ ከአምላክ ጋር በስምምነት ያስተካከለው በአገልግሎት ዘመኑ እንደሆነ ቅቡል ነው፦
ዮሐንስ 5፥18 ነገር ግን ደግሞ ራሱን ከአምላክ ጋር አስተካክሎ፦ "አምላክ አባቴ ነው" ስላለ፥ ἀλλὰ καὶ Πατέρα ἴδιον ἔλεγεν τὸν Θεόν, ἴσον ἑαυτὸν ποιῶν τῷ Θεῷ.

"ሳለ" የሚለው ጊዜን ለማመልከት የመጣ ሲሆን በአምላክ ኃይል በሚኖርበት ጊዜ ራሱን ከአምላክ ጋር አስተካክሎ፦ "አምላክ አባቴ ነው" ብሎ ተናገረ። "መተካከል" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ኢሱስ" ἴσος ሲሆን "መስማማት"agreement" ማለት ነው፦
ማርቆስ 14፥56 ብዙዎች በሐሰት ይመሰክሩበት ነበርና፥ ምስክርነታቸው ግን "አልተሰማማም"። πολλοὶ γὰρ ἐψευδομαρτύρουν κατ’ αὐτοῦ, καὶ ἴσαι αἱ μαρτυρίαι οὐκ ἦσαν.

እዚህ አንቀጽ ላይ ያለ አፍራሽ ስናስቀምጥ "መስማማት" ለሚለው የግሥ መደብ የተጠቀመበት በተመሳሳይ "ኢሱስ" ἴσος ነው፥ አምላክ አንድ ከሆነ እና ኢየሱስ ከአንድ አምላክ ጋር መስማማትን እንደ መቀማት አልቆጠረም። "ኢሱስ" ἴσος ገላጭ ቅጽል በተውሳከ ግሥ "ኡስ" ως ሲሆን "ልክ እንደ"as" ማለት ነው፦
ዘካሪያስ 12፥8 የዳዊትም ቤት በፊታቸው "እንደ" አምላክ እንደ ጌታ መልአክ ይሆናል። ὁ δὲ οἶκος Δαυὶδ ὡς οἶκος Θεοῦ, ὡς ἄγγελος Κυρίου ἐνώπιον αὐτῶν.

የዳዊት ቤት(ቤተሰብ) እንደ አምላክ እና እንደ የጌታ መልአክ ይሆናል ሲባል በባሕርይ ይስተካከላል ማለት ነውን? አምላክ፣ መልአክ እና የዳዊት ቤተሰብ በምንነት እንደሚለያዩ ሁሉ ክርስቶስ እና አምላክ በምንነት ይለያያሉ። ኢየሱስን የላከው አብ ከማንም ጋር በባሕርይ አይስተካከልም፦
ኢሳይያስ 46፥5 በማን ትመስሉኛላችሁ? ከማንስ ጋር ታስተካክሉኛላችሁ? τίνι με ὡμοιώσατε; ἴδετε, τεχνάσασθε, οἱ πλανώμενοι.

ይህ አንድ ነጠላ ማንነት "ከምን ጋር" ሳይሆን "ከማን ጋር" ማለቱ አብን በምንነት የሚስተካከል ማንነት እንደሌለ ቁልጭ አርጎ ያሳያል። "ሜጋስ" μέγας ማለት "ታላቅ" ማለት ሲሆን ገላጭ ቅጽል"Adjective" ነው፥ የሜጋስ አንጻራዊ ገላጭ ቅጽል "ሜይዞን" μεῖζόν ሲሆን ይህም አንጻራዊ ገላጭ ቅጽል የባሕርይ መበላለጥን ለማመልከት አገልግሎት ላይ ውሏል፦
ማቴዎስ 12፥6 ነገር ግን እላችኋለሁ ከመቅደስ "የሚበልጥ" ከዚህ አለ። λέγω δὲ ὑμῖν ὅτι τοῦ ἱεροῦ μεῖζόν ἐστιν ὧδε.

እዚህ አንቀጽ ላይ "የሚበልጥ" ለሚለው የገባው ቃል "ሜይዞን" μεῖζόν ሲሆን በላጩ ኢየሱስ ሰው ሲሆን ተበላጩ መቅደስ ደግሞ ድንጋይ በድንጋይ ላይ የተነባበረ ግዑዝ ነገር ነው፥ ይህ የባሕርይ መበላለጥን ያሳያል። ሰው፣ እንስሳ፣ እጽዋት፣ ማዕድናት በባሕርይ የተለያዩ ናቸው፥ የሰው ኑባሬ"being" ሰው ብቻ ነው። እዚህ ድረስ ከተግባባን ከሁሉ በላይ ሁሉን የፈጠረ አንድ አምላክ አብ ከሁሉ ይበልጣል፦
ዮሐንስ 10፥29 የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል። ὁ Πατήρ μου ὃ δέδωκέν μοι πάντων μεῖζόν ἐστιν
እዚህ አንቀጽ ላይ "ይበልጣል" ለሚለው የገባው ቃል "ሜይዞን" μεῖζόν ሲሆን በላጩ አብ ሲሆን ተበላጩ ደግሞ ሁሉም ነው፥ ኢየሱስ አብ ስላልሆነ "ሁሉ" በሚል ቃላት ውስጥ ኢየሱስ ስለሚካተት አብ ኢየሱስን በባሕርይ ይበልጠዋል። ኢየሱስ፦ "ከ"እኔ" አብ ይበልጣል" ብሏል፦
ዮሐንስ 14፥28 "ከ"እኔ" አብ ይበልጣልና። ὁ Πατὴρ μείζων μού ἐστιν.

እዚህ አንቀጽ ላይ "ይበልጣል" ለሚለው የገባው ቃል "ሜይዞን" μείζων ሲሆን በላጩ አብ ሲሆን ተበላጩ ደግሞ ኢየሱስ ነው፥ "ከ" የሚለው መስተዋድድ መነሻ ቅጥያ የሆነለት "እኔ" የሚለው ተሳቢ ተውላጠ ስም የኢየሱስ ሙሉ "እኔነትን" ቁልጭ አርጎ ያሳያል፦
ዕብራውያን 2፥7 ከመላእክት ይልቅ በጥቂት አሳነስኸው። ἠλάττωσας αὐτὸν βραχύ τι παρ’ ἀγγέλους,

"ኤላሶን" ἐλάσσων ማለት "ማነስ" ማለት ሲሆን "ሜይዞን" μείζων ለሚለው ተቃራኒ ነው፥ ኢየሱስ ከመላእክት ያነሰው በባሕርይ ከሆነ ይልቁኑ ከአብ በባሕርይ ምንኛ ያንስ ይሆን?
"ኬኖሲስ" κένωσις የሚለው የግሪክ ኮይኔ ቃል "ኬኖ" κενόω ማለትም "ባዶ አደረገ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ከንቱነት" "ባዶነት"emptiness" ማለት ነው፦
ፊልጵስዩስ 2፥7 ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን "ባዶ አደረገ"። ἀλλὰ ἑαυτὸν ἐκένωσεν μορφὴν δούλου λαβών, ἐν ὁμοιώματι ἀνθρώπων γενόμενος· καὶ σχήματι εὑρεθεὶς ὡς ἄνθρωπος

እዚህ አንቀጽ ላይ "ባዶ አደረገ" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ኤኬኖሴን" ἐκένωσεν ሲሆን ሥርወ-ቃሉ "ኬኖ" κενόω ነው፥ "ባዶ አደረገ" የሚለውን አንዳንድ የፕሮቴስታንት አንጃ እና ጎጥ፦ "አምላክነቱን ትቶ መጣ" በሚል ይረዱታል። አምላክነት የሆነ ቦታ አስቀምጠህ የምትመጣበት ጃኬት አይደለም፥ መጨመር እና መጉደል የፍጡር እንጂ የመለኮት ባሕርይ አይደለም። ነገር ግን እንደ ጳውሎስ ትምህርት ኢየሱስ ሕይወቱን በመስጠት ለሰው ልጆች ሲል ድሀ ሆነ ይለናል፦
2 ቆሮንቶስ 8፥9 የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቸር ስጦታ አውቃችኋልና ሀብታም ሲሆን እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ።

"ቸር ስጦታ" የተባለው ሕይወቱን መስጠቱን እንደሆነ ብዙ ቦታ ተናግሯል፦ ገላትያ 1፥4 ቲቶ 2፥14 ተመልከት! "ራሱን ባዶ አደረገ" ማለት "ራሱን አሳልፎ ሰጠ" ማለት ነው፥ ሕይወትን አሳልፎ ከሰጠ ትልቁ ድህነት(ባዶነት) ነው።
"የባሪያ መልክ" ማለት "ባርነት" ማለት ነው፥ ለምሳሌ "የአምልኮ መልክ" ማለት "አምልኮት" ማለት ነው፦
2 ጢሞቴዎስ 3፥5 የአምልኮት "መልክ" አላቸው ኃይሉን ግን ክደዋል፤ ከእነዚህ ደግሞ ራቅ። ἔχοντες μόρφωσιν εὐσεβείας τὴν δὲ δύναμιν αὐτῆς ἠρνημένοι· καὶ τούτους ἀποτρέπου.

"ሞርፎሲስ" μόρφωσις ወይም "ሞርፌ" μορφή የሚሉት ቃላት "ሞርፎ" μορφόω ከሚል ግሥ መደብ የመጣ ሲሆን "መልክ"form" ማለት ነው፥ ኢየሱስ ባርነት ይዞ እራሱን አዋረደ፦
ፊልጵስዩስ 2፥8 በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ። ἐταπείνωσεν ἑαυτὸν γενόμενος ὑπήκοος

ኢየሱስ፦ "ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ይላል" ብሎ ባስተማረው መሠረት ራሱን በትህትና በማዋረዱ አምላክ ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፦
ማቴዎስ 23፥12 ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ይላል። καὶ ὅστις ταπεινώσει ἑαυτὸν ὑψωθήσεται.
ፊልጵስዩስ 2፥9 በዚህ ምክንያት ደግሞ አምላክ ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው። διὸ καὶ ὁ Θεὸς αὐτὸν ὑπερύψωσεν,

ከመላእክት ያሳነሰው እና እራሱን በማዋረዱ ከፍ ከፍ ያደረገው አንዱ አምላክ ከሆነ አንዱ አምላክ እና ኢየሱስ ሁለት ለየቅል ማንነት እና ምንነት ይሆናሉ፥ በምንነት ከተለያዩ ኢየሱስ ከአምላኩ ጋር በባሕርይ ሊስተካከል አይችልም። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የመለኮት ሙላት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

43፥59 እርሱ በእርሱ ላይ የለገስንለት እና ለእስራኤል ልጆች ተአምር ያደረግነው የኾነ ባሪያ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ إِنْ هُوَ إِلَّا عَبْدٌ أَنْعَمْنَا عَلَيْهِ وَجَعَلْنَاهُ مَثَلًا لِّبَنِي إِسْرَائِيلَ

ነገርን መጠምዘዝ የሚቀናቸው ሚሽነሪዎች ያልተፈለገ መባልን ሲሉና "አሃ! እንዲህ ለማለት እኮ ነው!" እያሉ መለኮት በትስብእት እንደተገለጠ አርገው ከሚጠቅሷቸው ቅሰራዊ እና ቅየጣዊ ጥቅሶች መካከል ቆላይስይስ 2፥9 ነው። ባይብል ላይ ኢየሱስ መሢሕ፣ ነቢይ፣ መልእክተኛ መሆኑት በክብር ተቀምጦ ሳለ መለኮትን ለማላበስ በመሞከር የአህያ ሥጋ አልጋ ሲሉት ዐመድ ነገር ሆነዋል። ቆላይስይስ 2፥9 ላይ ያለውን ዐውድ "ውኃን ከጥሩ ነገርን ከሥሩ" የሚለውን አገርኛ ብሒል ይዘን እንሞግት!
"ሶማ" σῶμα ማለት "አካል" ማለት ሲሆን በጳውሎስ ትምህርት ውስጥ ቤተክርስቲያን የክርስቶስ አካል ስለሆነች "ሶማ" σῶμα ተብላለች፦
ቆላስይስ 1፥18 እርሱም የአካሉ ማለት የቤተ ክርስቲያን ራስ ነው። καὶ αὐτός ἐστιν ἡ κεφαλὴ τοῦ σώματος, τῆς ἐκκλησίας·

እነዚ አንቀጽ ላይ "ቤተ ክርስቲያን" ለሚለው የገባው ቃል "ኤክሌሲያ" ἐκκλησία ሲሆን ትርጉሙ "ጉባኤ" "ማኅበር" "ስብስብ" ማለት ነው፥ የምእመናን ስብስብ "ኤክሌሲያ" ይባላል። የመለኮት ሙላት ሁሉ በክርስቶስ በኤክሌሲያ ተገልጦ ይኖራል፦
ቆላስይስ 2፥9 "በ-"እርሱ" የመለኮት ሙላት ሁሉ በአካል ይኖራልና። ὅτι ἐν αὐτῷ κατοικεῖ πᾶν τὸ πλήρωμα τῆς Θεότητος σωματικῶς,

"በ-"እርሱ" የሚለው ይሰመርበት! "እርሱ" የሚለው ተውላጠ ስም "ክርስቶስ" የሚለውን የሚተካ ነው፥ አብ ሙላቱን ሁሉ በክርስቶስ በኩል እንዲኖር ፈቅዷልና፦
ቆላስይስ 1፥19 ሙላቱ ሁሉ በእርሱ እንዲኖር ፈቅዷልና። ὅτι ἐν αὐτῷ εὐδόκησεν πᾶν τὸ πλήρωμα κατοικῆσαι

ዐማርኛ ላይ "እግዚአብሔር" ወይም ኪንግጀምስ ቨርዢን ላይ "አብ" ብለው ያስቀመጡት በውስጠ ታዋቂነት አብን ወይም እግዚአብሔርን ስለሚያመለክት ነው፥ አብ መለኮት ሲሆን ሙላቱን በክርስቶስ በኩል ለቤተክርስቲያን ይገልጣል። በቆላስይ 2፥9 ላይ "አካል" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ሶማቲኮስ" σωματικῶς ሲሆን በጳውሎስ ትምህርት ውስጥ "አንድ አካል አለ" ብሎ የሚናገርላት ቤተክርስቲያን ናት፦ ቆላስይስ 1፥24 ኤፌሶን 4፥4 ሮሜ 12፥4-5 1ኛ ቆሮንቶስ 12፥12 ቆላስይስ 3፥15 ተመልከት!

"መለኮት" የተባለው አብ ሲሆን ሙላቱ ደግሞ ሰዎች የሚሞሉት ጸጋ ነው፥ እዛው ዐውድ ላይ በክርስቶስ በኩል አማኞች ይህንን ሙላት እንደሚሞሉ ይናገራል፦
ቆላስይስ 2፥10 ለአለቅነትና ለሥልጣንም ሁሉ ራስ በሆነ በእርሱ ሆናችሁ "ተሞልታችኋል"። καὶ ἐστὲ ἐν αὐτῷ πεπληρωμένοι, ὅς ἐστιν ἡ κεφαλὴ πάσης ἀρχῆς καὶ ἐξουσίας,

"ተሞልታችኋል" የሚለው ይሰመርበት! "የመለኮት ሙላት" ማለት እና "መለኮት" ማለት ይለያያል፥ መለኮት አብ ሲሆን ሙላቱ ጸጋው ነው። ይህንን ስታውቁ ሙግቱ እግረ ሰረሰር እንደሚሆንባችሁ እሙን እና ቅቡል ነው፥ ቢመራችሁም ዋጡት። መለኮትን ሰው አይሞላም፥ ነገር ግን ጸጋውን ይሞላሉ፦
ኤፌሶን 3፥19 እስከ አምላክም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ ነው። ἵνα πληρωθῆτε εἰς πᾶν τὸ πλήρωμα τοῦ θεοῦ.

ጋንጩር እንዳለበት ክልው ክልው የሚያደርጋቸው ሚሽነሪዎች ነገርን አቅሎ ማርገብ እና አጃምሎ ማራገብ ስለሚወዱ እንጂ እዚህ አንቀጽ ላይ አማኞች የአምላክ ፍጹም ሙላት እንደሚሞሉ በግልጽ ይናገራል። በክርስቶስ በኩል የአብን ሙላት የሚሞሉት ሰዎች ከሆኑ የመለኮት ሙላት በክርስቶስ በኩል የሚኖረው ቤተክርስቲያን ውስጥ ነው፥ ስለዚህ ቆላስይስ 2፥9 "መለኮት በትስብእት ተገለጠ" ለሚል የክርስትና ተሠግዎት"Incarnation" ትምህርት ማስረጃም መረጃም መሆን አይችልም። እኛ ሙሥሊሞች አይሁዳውያን የሚጠብቁት መሢሕ ኢየሱስ ነው ብለን እናምናለን፥ ኢየሱስ አሏህ መጽሐፍ እና ነቢይነት የለገሰው ባሪያ እና ያለ አባት በመወለድ ለእስራኤልም ልጆች ተአምር የተደረገ ባሪያ ነው፦
43፥59 እርሱ በእርሱ ላይ የለገስንለት እና ለእስራኤል ልጆች ተአምር ያደረግነው የኾነ ባሪያ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ إِنْ هُوَ إِلَّا عَبْدٌ أَنْعَمْنَا عَلَيْهِ وَجَعَلْنَاهُ مَثَلًا لِّبَنِي إِسْرَائِيلَ

ለኢየሱስ ነቢይነትን እና መጽሐፍን የሰጠውን አንዱን አምላክ አሏህን እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ኢንጂል

ክፍል አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

57፥27 ከዚያም በዱካዎቻቸው ላይ መልክተኞቻችንን አስከታተልን፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሣንም አስከተልን፥ ኢንጂልንም ሰጠነው፡፡ ثُمَّ قَفَّيْنَا عَلَىٰ آثَارِهِم بِرُسُلِنَا وَقَفَّيْنَا بِعِيسَى ابْنِ مَرْيَمَ وَآتَيْنَاهُ الْإِنجِيلَ

ኢየሱስ ከአምላኩ ግልጠተ መለኮት በተቀበለበት በዐረማይስጥ ቋንቋ "ኢዋንገሊዎን" ܐܘܢܓܠܝܘܢ ማለት "ብሥራት" "የምስራች" "መልካም ዜና" ማለት ሲሆን "ኢዋንገሊዎን" ܐܘܢܓܠܝܘܢ ወደ ዐረቢኛ ሙዐረብ ሆኖ ሲገባ "ኢንጂል" إِنْجِيل ሲባል፣ ወደ ግሪክ ሲገባ "ዩአንጌሎስ" εὐάγγελος ሲባል፣ ወደ ግዕዝ ሲገባ ደግሞ "ወንጌል" ተባለ። አምላካችን አሏህ ለዒሣ ኢንጂልን በመስጠት መልእክተኛ አርጎ ልኮታል፦
57፥27 ከዚያም በዱካዎቻቸው ላይ መልክተኞቻችንን አስከታተልን፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሣንም አስከተልን፥ ኢንጂልንም ሰጠነው፡፡ ثُمَّ قَفَّيْنَا عَلَىٰ آثَارِهِم بِرُسُلِنَا وَقَفَّيْنَا بِعِيسَى ابْنِ مَرْيَمَ وَآتَيْنَاهُ الْإِنجِيلَ

በባይብልም ቢሆን ኢየሱስ ከላከው ከአምላክ መልእክት እየሰማ የሚያስተላለፍ መልእክተኛ ነበር፦
ዮሐንስ 8፥26 የላከኝ እውነተኛ ነው እኔም ከእርሱ "የሰማሁትን" ይህን ለዓለም እናገራለሁ።
ዮሐንስ 8፥40 ነገር ግን አሁን ከአምላክ "የሰማሁትን" እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ። νῦν δὲ ζητεῖτέ με ἀποκτεῖναι, ἄνθρωπον ὃς τὴν ἀλήθειαν ὑμῖν λελάληκα, ἣν ἤκουσα παρὰ τοῦ Θεοῦ·

እዚህ አንቀጽ ላይ "አምላክ" አሰሚ ባለቤት ሲሆን "ሰው" ሰሚ ተሳቢ ነው፥ በአምላክ እና በሰው መካከል "የሰማሁት" የሚል አጫፋሪ ግሥ"transitive verb" አለ። መልእክተኛው ኢየሱስ የሚናገረው የላከው እንደነገረው እንጂ ከራሱ ምንም አልተናገረም፦
ዮሐንስ 12፥50 ስለዚህ እኔ የምናገረውን አብ እንደ ነገረኝ እንዲሁ እናገራለሁ።
ዮሐንስ 12፥49 እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን "የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ"።

"ትእዛዝ ሰጠኝ" የሚለው ይሰመርበት! ይህቺም ትእዛዝ ታላቂቱ እና ፊተኛይቱ ትእዛዝ "ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው" የምትል ተውሒድ ስትሆን የዘላለም ሕይወት ናት፦
ዮሐንስ 12፥50 "ትእዛዙም የዘላለም ሕይወት እንደ ሆነች" አውቃለሁ።
ማቴዎስ 22፥38 ታላቂቱ እና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።
ማርቆስ 12፥29 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ፦ "እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው"..የምትል ናት።

ጥንትም በቅዱሳን ነቢያት ቀድሞ የተባለውን ቃል እና በሐዋርያትም ከኢየሱስ የተገኘው ትእዛዝ "ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው" የሚል ጭብጥ ነው፦
2 ጴጥሮስ 3፥2 በቅዱሳን ነቢያትም ቀድሞ የተባለውን ቃል እና በሐዋርያቶቻችሁም ያገኛችኋትን የጌታን እና የመድኃኒትን ትእዛዝ እንድታስቡ በሁለቱ እያሳሰብኋችሁ ቅን ልቡናችሁን አነቃቃለሁ።

ኢየሱስ "የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ" ሲል ይህንን የአምላክ ትእዛዝ ከአምላክ ተቀብሎ ለሐዋርያት የሰጠው ቃል የአምላክ ቃል ነው፦
ዮሐንስ 17፥8 "የሰጠኸኝን ቃል" ሰጥቻቸዋለሁና።
ዮሐንስ 17፥14 እኔ "ቃልህን" ሰጥቻቸዋለሁ።

ኢየሱስ ወደ አምላኩ ሲጸልይ በሁለተኛ መደብ "ቃልህን" ማለቱ በራሱ የተሰጠው "ቃል" የአምላክ ቃል ነው፥ ሕዝቡም ሲሰማ የነበረው ቃል የላከው የአምላክ ቃል እንጂ የመልእክተኛው የራሱ ቃል አይደለም፦
ዮሐንስ 7፥16 ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አላቸው፦ "ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከእኔ አይደለም"።
ዮሐንስ 14፥24 "የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም"።
ሉቃስ 5፥1 ሕዝቡም "የአምላክን ቃል" እየሰሙ ሲያስጠብቡት ሳሉ፥ እርሱ ራሱ በጌንሳሬጥ ባሕር ዳር ቆሞ ነበር።
ዮሐንስ 8፥47 ከአምላክ የሆነ "የአምላክን ቃል" ይሰማል።
ዮሐንስ 3፥34 አምላክ የላከው የአምላክንን ቃል ይናገራልና።

ኢየሱስ መልእክተኛ ነቢይ ሆኖ ከአምላኩ የተሰጠውን የአምላክን ቃል ይናገር ከነበረ እና ከራሱ ምንም ካልተናገረ ኢየሱስ ሙሉ ዕውቀት የለውም፥ ምክንያቱም ከአምላኩ የሚሰማው እርሱ ጋር ከሌለ እና ከአምላኩ ሰምቶ ከተናገረ ከላከው ዕውቀት ጋር እኩል ዕውቀት አይሆንም። እንግዲህ ኢየሱስ ከአምላኩ እየሰማ የተሰጠው የአምላክ ቃል ወንጌል ይባላል፥ ኢንሻላህ በክፍል ሁለት ስለዚህ ወንጌል እናያለን........

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ኢንጂል

ክፍል ሁለት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

57፥27 ከዚያም በዱካዎቻቸው ላይ መልክተኞቻችንን አስከታተልን፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሣንም አስከተልን፥ ኢንጂልንም ሰጠነው፡፡ ثُمَّ قَفَّيْنَا عَلَىٰ آثَارِهِم بِرُسُلِنَا وَقَفَّيْنَا بِعِيسَى ابْنِ مَرْيَمَ وَآتَيْنَاهُ الْإِنجِيلَ

ኢየሱስ ከራሱ ምንም ካልተናገረ፣ ከላከው ሲሰማ የነበረው ቃል የላከው እንጂ የራሱ ካልሆነ፣ እርሱ ሲናገር የነበረው ከላከው እየሰማ ከነበረ፣ እርሱ ለሐዋርያት የሰጠው ቃል ከላከው አምላክ የተሰጠው ትእዛዝ እና ቃል ከነበረ ከላከው እየሰማ ሲያስተላልፍልን የነበረው መመሪያ ወንጌል ይባላል፦
ሉቃስ 4፥18 ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና።

"ኽሪስቶስ" χριστός የሚለው የማዕረግ ስም ትርጉሙ "የተቀባ" "ቅቡዕ" "መሢሕ" "ክርስቶስ" ማለት ሲሆን አንዱ አምላክ የናዝሬቱ ኢየሱስን ነቢይ እና መልእክተኛ አርጎ የቀባው ወንጌልን እንዲሰብክ ነው፦
ማርቆስ 1፥1 የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ። Ἀρχὴ τοῦ εὐαγγελίου Ἰησοῦ Χριστοῦ,

ኮዴክስ ሲናቲከስ ላይ፦ "የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ" αρχη του ευαγγελιου ιυ  χυ  በሚል ተቀምጧል እንጂ "ሁዩ ቴዉ" υἱοῦ θεοῦ የሚለው የለውም፥ "ሁዩ ቴዉ" υἱοῦ θεοῦ ማለት "የአምላክ ልጅ" ማለት ሲሆን "ሁዩ ቴዉ" የሚለውን በቅንፍ ያስቀመጡ እደ ክታባት አሉ። New American Bible እትምም፦ "The beginning of the gospel of Jesus Christ [the Son of God]. በማለት [the Son of God] የሚለውን በቅንፍ አስቀምጦታል፥ እንደ የኢትዮጵያ ኦርቶዶስ ተዋሕዶ አቆጣጠር በ 1993 ድኅረ ልደት የተዘጋጀው አዲሱ መደበኛ ትርጉም፦ "አንዳንድ ቅጂዎች የእግዚአብሔር ልጅ የሚለውን ሐረግ የላቸውም" በማለት ሐቁን አስቀምጧል።
ይህንን በግርድፍ እና በሌጣው ካየን ዘንዳ የኢየሱስ ወንጌል የሚጀምረው የአምላክን ወንጌል መስበክ ከጀመረበት ነው፦
ማርቆስ 1፥14 ዮሐንስም አልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የአምላክን ወንጌል እየሰበከ ወደ ገሊላ መጣ። Καὶ μετὰ τὸ παραδοθῆναι τὸν Ἰωάνην ἦλθεν ὁ Ἰησοῦς εἰς τὴν Γαλιλαίαν κηρύσσων τὸ εὐαγγέλιον τοῦ Θεοῦ

ግሪኩ ላይ አብዛኛው እደ ክታባት "የአምላክን ወንጌል" እንጂ "የአምላክ መንግሥት ወንጌል" አይሉትም፥ ይህ የአምላክ ወንጌል አንዱ አምላክ ለመልእክተኛው ለኢየሱስ የሰጠው ወንጌል ነው፦
ማርቆስ 1፥15 ዘመኑ ተፈጸመ የአምላክም መንግሥት ቀርባለች፤ ንስሐ ግቡ፡ "በወንጌልም እመኑ" አለ። καὶ λέγων ὅτι Πεπλήρωται ὁ καιρὸς καὶ ἤγγικεν ἡ βασιλεία τοῦ Θεοῦ· μετανοεῖτε καὶ πιστεύετε ἐν τῷ εὐαγγελίῳ.

ኢየሱስ፦ "በወንጌል እመኑ" ሲል ከአምላክ ለእርሱ በተሰጠው በአንድ ወንጌል እንጂ ከኢየሱስ ዕርገት በኃላ የተጻፉትን ብዙ ወንጌሎች አይደለም፥ ኢየሱስ፦ "በወንጌል እመኑ" ሲል ያኔ የማቴዎስ፣ የማርቆስ፣ የሉቃስ፣ የዮሐንስ፣ የበርተሎሜዎስ፣ የይሁዳ፣ የበርናባስ ወንጌላት አልነበሩም። የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ ማስተማር ከጀመረበት የጀመረ ሲሆን ማስተማር ሲጀምር ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ያህል ሆኖት ነበር፦
ሉቃስ 3፥23 ኢየሱስም "ሊያስተምር ሲጀምር" ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ያህል ሆኖት ነበር።

ስለዚህ ከኢየሱስ ማስተማር በፊት የነበረው የኢየሱስ የትውልድ ትረካ ወንጌል ሳይሆን የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ ነው፦
ማቴዎስ 1፥1 የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ "የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ"።

እከሌ እከሌን ወለደ እየተባለ የተዘገበው ዘገባ በአምላክ ወንጌል ላይ የተጨመረ ታሪክ ነው፥ ታሪክ ቢያስፈልግም በአምላክ ቃል ላይ ግን መጨመሩ አግባብ አይደለም። የአምላክ ወንጌል ላይ የተጨመሩት ታሪኮች ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ሞክረዋል፦
ሉቃስ 1፥1-4 የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ።
፨ሉቃስ ቴዎፍሎስ ለሚባለው ጓደኛው የጻፋለት ደብዳቤ እንጂ ወንጌል አይደለም፥ ለጓደኛው የጻፈው ደግሞ ጓደኛው ስለ ተማረው ቃል እርግጡን እንዲያውቅ መልካም ሆኖ ስለታየው እንጂ በመንፈስ ቅዱስ ተነድቶ አይደለም።
፨ማቴዎስ ደግሞ በ 50 ድኅረ ልደት ለዕብራውያን በዕብራይስጥ ደብዳቤ ጽፎ ሳለ ይህ ደብዳቤ ሲጠፋ በማቴዎስ ስም ማንነቱ የማይታወቅ ሰው የማርቆስን ትርክት መሠረት አድርጎ የማቴዎስ ወንጌልን አዘጋጀ።
፨የዮሐንስን ወንጌል የጻፈው ሽማግሌ ዮሐንስ"John the Presbyter" ሲሆን ከሐዋርያው ዮሐንስ ይለያል።
፨ሉቃስ እና ማርቆስ ደግሞ የጳውሎስ ጓደኞች ናቸው እንጂ የኢየሱስ ሐዋርያት አይደለም።

ሆነም ቀረ የመጀመሪያዎቹ የማቴዎስ፣ የማርቆስ፣ የሉቃስ፣ የዮሐንስ ወንጌላት ጠፍተዋል፥ ከአንዱ አምላክ ለኢየሱስ የተሰጠው ወንጌል አንድ ሆኖ ሳለ የኢየሱስን ወንጌል ከሠራው ተአምር ጋር ታሪክን ብዙዎች ሲያዘጋጁ ወደ 47 የሚደርሱ ወንጌላት ደርሰው ነበር።
ከእነዚህ ወንጌላት ሄለናዊ ክርስትና"hellenistic christianity" ስለ ህማማት(ስቅለት እና ግድለት) የሚናገረው አራት ወንጌላት መርጦ ሌሎችን ወንጌላት ሳይቀበል ቀርቷል፥ እነዚህ አራት ወንጌላት ከመጻፋቸው በፊት አንድ ወንጌል እንደነበረ እና ያ ወንጌል እንደጠፋ ምሁራን እንዳስቀመጡ አዲሱ መደበኛ ትርጉም የአዲስ ኪዳን መግቢያ ላይ ተቀምጧል።
ስለዚህ ሄለናዊ ክርስትና ከአሏህ ዘንድ ለዒሣ በተሰጠው ኢንጂል ላይ ታሪክን በመጨመር "ከአሏህ የሆነ ግልጠተ መለኮት ነው" ብለው ዋሽተዋል፦
2፥79 ለነዚያም መጽሐፉን በእጆቻቸው ለሚጽፉ እና ከዚያም በእርሱ ጥቂትን ዋጋ ሊገዙበት «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» ለሚሉ ወዮላቸው፡፡ فَوَيْلٌ لِّلَّذِينَ يَكْتُبُونَ الْكِتَابَ بِأَيْدِيهِمْ ثُمَّ يَقُولُونَ هَـٰذَا مِنْ عِندِ اللَّهِ لِيَشْتَرُوا بِهِ ثَمَنًا قَلِيلًا ۖ
3፥71 «የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! እውነቱን በሐሰት ለምን ትቀላቅላላችሁ? እውነቱንም እናንተ የምታውቁ ስትኾኑ ለምን ትደብቃላችሁ?» يَا أَهْلَ الْكِتَابِ لِمَ تَلْبِسُونَ الْحَقَّ بِالْبَاطِلِ وَتَكْتُمُونَ الْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ

"እውነቱን በሐሰት ለምን ትቀላቅላላችሁ" የሚለው ይሰመርበት! ሄለናዊ ክርስትና ከአሏህ ዘንድ ለዒሣ በተሰጠው ኢንጂል ላይ ታሪክን መጨመር ብቻ ሳይሆን ከተሰጠው ኢንጂል ላይ እውነትን በመደበቅ ቀንሰዋል፥ ከተቀነሱት መካከል ስለ ነቢያችን"ﷺ" መምጣት የሚናገረው የምስራች ነው፦
7፥157 ለእነዚያ ያንን እነሱ ዘንድ በተውራት እና በኢንጂል ተጽፎ የሚያገኙትን የማይጽፍ እና የማያነብ ነቢይ የኾነውን መልእክተኛ የሚከተሉ ለኾኑት በእርግጥ እጽፍለታለሁ፡፡ الَّذِينَ يَتَّبِعُونَ الرَّسُولَ النَّبِيَّ الْأُمِّيَّ الَّذِي يَجِدُونَهُ مَكْتُوبًا عِندَهُمْ فِي التَّوْرَاةِ وَالْإِنجِيلِ
61፥6 የመርየም ልጅ ዒሣም፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! እኔ ከተውራት በፊቴ ያለውን የማረጋግጥ እና ከእኔ በኋላ በሚመጣው መልእክተኛ ስሙ አሕመድ በኾነው የማበስር ስኾን ወደ እናንተ የተላክሁ የአላህ መልእክተኛ ነኝ» ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ وَإِذْ قَالَ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ يَا بَنِي إِسْرَائِيلَ إِنِّي رَسُولُ اللَّهِ إِلَيْكُم مُّصَدِّقًا لِّمَا بَيْنَ يَدَيَّ مِنَ التَّوْرَاةِ وَمُبَشِّرًا بِرَسُولٍ يَأْتِي مِن بَعْدِي اسْمُهُ أَحْمَدُ

"የማበስር" የሚለው ይሰመርበት! "ከእኔ በኋላ በሚመጣው መልእክተኛ ስሙ አሕመድ" የሚለው የምስራች አራቱ ወንጌላት ላይ ከሌለ እንግዲያውስ አምላካችን አሏህ ኢንጅል እያለ የሚነግረን ከእርሱ ዘንድ ወርዶ ለዒሣ የተሰጠው ስለ ነቢያችን"ﷺ" መምጣት የሚናገረው ነው፦
3፥3 ተውራትን እና ኢንጂልን አውርዷል፡፡ وَأَنزَلَ التَّوْرَاةَ وَالْإِنجِيلَ
3፥4 ከቁርኣን በፊት ለሰዎች መሪ አድርጎ አወረዳቸው፡፡ "ፉርቃንንም አወረደ"፡፡ مِن قَبْلُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَأَنزَلَ الْفُرْقَانَ

"ፉርቃን" فُرْقَان የሚለው ቃል "ፈረቀ" فَرَقَ ማለትም "ለየ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "እውነትን ከሐሰት የሚለይ" ማለት ነው፥ አሏህ ስለ ተውራት እና ኢንጅል መውረድ ከነገረን በኃላ በእነርሱ ላይ የተጨመረውን ሐሰት ከአሏህ ዘንድ ከወረደው እውነት የምንለይበትን ፉርቃን በባሪያው በሙሐመድ"ﷺ" ላይ አውርዷል፦
25፥1 ያ ፉርቃንን በባሪያው ላይ ለዓለማት አስጠንቃቂ ይኾን ዘንድ ያወረደው አምላክ ክብር እና ጥራት ተገባው፡፡ تَبَارَكَ الَّذِي نَزَّلَ الْفُرْقَانَ عَلَىٰ عَبْدِهِ لِيَكُونَ لِلْعَالَمِينَ نَذِيرًا
5፥48 ወደ አንተ መጽሐፉን ከበፊቱ ያለውን መጽሐፍ አረጋጋጭ እና በእርሱ ላይ ተጠባባቂ ሲኾን በእውነት አወረድን፡፡ وَأَنزَلْنَا إِلَيْكَ الْكِتَابَ بِالْحَقِّ مُصَدِّقًا لِّمَا بَيْنَ يَدَيْهِ مِنَ الْكِتَابِ وَمُهَيْمِنًا عَلَيْهِ

ቁርኣን ከበፊቱ ከአሏህ ዘንድ የወረደውን 4፥136 "ከበፊቱ ባወረደው መጽሐፍ እመኑ" በማለት መለኮታዊ ቅሪትን የሚያረጋግጥ ስለሆነ "ሙሶዲቅ" مُصَدِّق ተብሏል፥ በእርሱ ላይ የጨመሩትን የሚያርም እና የሚቆጣጠር ስለ ሆነ ደግሞ "ሙሀይሚን" مُهَيْمِن ተብሏል። ቁርኣንን ፉርቃን፣ ሙሶዲቅ፣ ሙሀይሚን አርጎ ለሰጠን ለዓለማቱ ጌታ ለአሏህ ክብር እና ምስጋና ይሁን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም