ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.4K subscribers
68 photos
69 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በዛሬው እለት በአሶሳ ከተማ ሦስት ፕሮቴስታንት ወደ ዲኑል ኢሥላም በሸሀደተይን ገብተዋል። አል-ሓምዱሊሏህ!
ተክቢር
አሏሁ አክበር
አሏሁ አክበር
አሏሁ አክበር
አድዋ

ተረታችን አያልቅም! "የአድዋ ጦርነት ላይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ተዋግቷል" ይሉናል። የአድዋ ጦርነት የተካሔደው በ 1888 ድኅረ-ልደት ነው። ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት የሆነው በዱዲያኖስ ዘመነ-መንግሥት በ 393 ድኅረ-ልደት ልዳ በሚባለው አገር ነው። የዛሬ 1,627 ዓመት ልዳ ላይ ሰማዕት የሆነው ሰው አድዋ ላይ በ 1888 ኅረ-ልደት ላይ እንዴት ሊዋጋ ቻለ? መረጃችሁስ ምንድን ነው? "አሞኛችሁ ዘንድ አይናችሁን ጨፍኑ!" አትበሉን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
መስካሪ እና ተመስካሪ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

85፥3 *"በመስካሪ እና በተመስካሪ እምላለሁ"*፡፡ وَشَاهِدٍ وَمَشْهُودٍ

በቁርኣን አናቅጽ ላይ "ሻሂድ" شَاهِد ማለት የሚመሰክር "መስካሪ" ማለት ሲሆን "መሽሁድ" مَشْهُود ማለት ደግሞ የሚመሰከርበት "ተመስካሪ" ማለት ነው። በተቀጠረው ቀን መስካሪ በተመስካሪ ላይ ይመሰክራሉ፦
85፥2 *"በተቀጠረው ቀንም እምላለው"*። وَالْيَوْمِ الْمَوْعُودِ
85፥3 *"በመስካሪ እና በተመስካሪ እምላለሁ"*፡፡ وَشَاهِدٍ وَمَشْهُودٍ

ኢንግሊሹ ከዐረቢኛው ጋር በተመሳሳይ "And by the witness and the witnessed" ይላል። አምላካችን አሏህ በቁርኣን የማለባቸው ነገሮችን ሁሉ ጉዳዩን አጽንዖትና አንክሮት መስጠቱን የሚያመላክት ነው፥ ያ የተቀጠረው ቀን ደግሞ ሙታን የሚቀሰቀሱበት የትንሳኤ ቀን ነው፦
34፥30 *«ለእናንተ ከእርሱ አንዲትንም ሰዓት የማትዘገዩበት የማትቀድሙበትም "የቀጠሮ ቀን" አላችሁ»* በላቸው፡፡ قُل لَّكُم مِّيعَادُ يَوْمٍ لَّا تَسْتَأْخِرُونَ عَنْهُ سَاعَةً وَلَا تَسْتَقْدِمُونَ
36፥52 *«ወይ ጥፋታችን! ከመኝታችን ማን ቀሰቀሰን? "ይህ ያ አዛኙ ጌታ በእርሱ የቀጠረን" እና መልክተኞቹም እውነትን የነገሩን ነው»* ይላሉ፡፡ قَالُوا يَا وَيْلَنَا مَن بَعَثَنَا مِن مَّرْقَدِنَا ۜ ۗ هَـٰذَا مَا وَعَدَ الرَّحْمَـٰنُ وَصَدَقَ الْمُرْسَلُونَ
11፥103 በዚህ ውስጥ የመጨረሻውን ቀን ቅጣት ለሚፈሩ ሁሉ መገሰጫ አለ፡፡ *"ይህ የትንሣኤ ቀን ሰዎች በእርሱ የሚሰበሰቡበት ቀን ነው፡፡ ይህም የሚጣዱት ቀን ነው"*፡፡ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً لِّمَنْ خَافَ عَذَابَ الْآخِرَةِ ۚ ذَٰلِكَ يَوْمٌ مَّجْمُوعٌ لَّهُ النَّاسُ وَذَٰلِكَ يَوْمٌ مَّشْهُودٌ

የተቀጠረው ቀን የመሽሁድ ቀን ነው። አሏህ፦ "በመስካሪው እና በሚመሰከርባቸው እምላለው" ብሏል፥ "መስካሪ" የተባሉት "ነቢያት" ሲሆኑ "የሚመሰከርባቸው" ደግሞ "ኡማቸው" ናቸው፦
16፥84 *"ከየሕዝቡም ሁሉ መስካሪን የምንቀሰቅስበትን ቀን አስታውስ"*፡፡ وَيَوْمَ نَبْعَثُ مِن كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا
4፥41 *"ከሕዝቦችም ሁሉ መስካሪን ባመጣን ጊዜ አንተንም በእነዚህ ሕዝብ ላይ መስካሪ አድርገን በምናመጣህ ጊዜ የከሓዲዎች ኹኔታ እንዴት ይኾን?"* فَكَيْفَ إِذَا جِئْنَا مِن كُلِّ أُمَّةٍ بِشَهِيدٍ وَجِئْنَا بِكَ عَلَىٰ هَـٰؤُلَاءِ شَهِيدًا
16፥89 *"በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ ከራሳቸው በእነርሱ ላይ መስካሪን የምንቀሰቅስበትን አንተንም በእነዚህ ሕዝብ ላይ መስካሪ አድርገን የምናመጣህን ቀን አስታውስ"*፡፡ وَيَوْمَ نَبْعَثُ فِي كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا عَلَيْهِم مِّنْ أَنفُسِهِمْ ۖ وَجِئْنَا بِكَ شَهِيدًا عَلَىٰ هَـٰؤُلَاء
28፥75 *"ከሕዝቦችም ሁሉ መስካሪን እናወጣለን፡፡ ያን ጊዜ እውነተኛውም አምላክነት ለአላህ ብቻ መኾኑን ያውቃሉ፡፡ ይቀጣጥፉት የነበሩትም ከእነርሱ ይጠፋቸዋል"*፡፡ وَنَزَعْنَا مِن كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا فَقُلْنَا هَاتُوا بُرْهَانَكُمْ فَعَلِمُوا أَنَّ الْحَقَّ لِلَّهِ وَضَلَّ عَنْهُم مَّا كَانُوا يَفْتَرُونَ

“ኡማህ” أُمَّة ማለት “ሕዝብ” ማለት ሲሆን በአንድ ነቢይ ዘመነ-መግቦት"dispensation" የሚቆዩትን "ሰዎች" ያመለክታል። እያንዳንዱ ነቢይ በራሱ ኡማህ ላይ በትንሳኤ ቀን ይመሰክራሉ። ይህ ሙግት “የተዛማች ሙግትን”textual approach” ታሳቢና ዋቢ ያደረገ ሙግት ነው።

ነገር ግን "ተጣጅ" እና "ሚጣዱት" የሚለው እንደ ኢትዮጵያ ክርስትና አቆጣጠር በ 1961 ዓመተ-ልደት በተዘጋጀው የሐጅ ሣኒ ሐቢብ የዐማርኛ የቁርኣን ትርጉም ላይ ተቀምጧል። አንዳንዶች፦ "የወሎ አማርኛ ነው" ቢሉም ምን ለማስተላለፍ እንደፈለጉ እኔ በቅጡ አልገባኝም፥ አሏሁ አዕለም ሁሉን። ነገር ግን የኢንግሊሹ የቁርኣን ትርጉም እና እራሱ ኦርጅናሉ ቁርኣን "ሻሂድ" شَاهِد "መስካሪ" "the witness" እና "መሽሁድ" مَشْهُود "ተመስካሪ" "the witnessed" ብሎ ጥልልና ጥንፍፍ አርጎ አስቀምጦታል። የአገራችን ሚሽነሪዎች ጭረው ተፍጨርጭረው ስለ ድስት መጣድ ለማስመሰል ቢዳዱም ከላይ ባለው የቋንቋ ሙግት”linguistical approach” ድባቅ ይገባሉ።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ዐድዋ በዓል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

7፥3 *ከጌታችሁ ወደ እናንተ የተወረደውን ተከተሉ*። اتَّبِعُوا مَا أُنزِلَ إِلَيْكُم مِّن رَّبِّكُمْ

ዐድዋ የሚባል በዓል በኢሥላም ውስጥ የለም። ሙሥሊም ያሉት ዓመታዊ በዓል ሁለት ብቻ ናቸው፥ እነርሱም ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓ ናቸው፦
ሡነን አቢ ዳዉድ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 745
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፤ የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” መዲና ሲገቡ የመዲና ሠዎች የሚደሰቱባቸው ሁለት በዓላት እንዳሏቸው አወቁ። እርሳቸውም እነዚህ ሁለቱ ቀናት ምንድን ናቸው? በማለት ጠየቁ፤ ሰዎችም በጃሂሊያ ጊዜ እንጫወትባቸው የነበሩ በዓላት ናቸው አሏቸው። የአላህ መልእክተኛም”ﷺ”፦ *”አላህ ከእነርሱ የተሻሉ ሁለት ዒዶችን ሠጥቷችኋል፤ እነርሱም፦ ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓን። አሏቸው”*። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ قَدِمَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم الْمَدِينَةَ وَلَهُمْ يَوْمَانِ يَلْعَبُونَ فِيهِمَا فَقَالَ ‏”‏ مَا هَذَانِ الْيَوْمَانِ ‏”‏ ‏.‏ قَالُوا كُنَّا نَلْعَبُ فِيهِمَا فِي الْجَاهِلِيَّةِ ‏.‏ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏”‏ إِنَّ اللَّهَ قَدْ أَبْدَلَكُمْ بِهِمَا خَيْرًا مِنْهُمَا يَوْمَ الأَضْحَى وَيَوْمَ الْفِطْرِ ‏”‏ ‏.‏
ጃሚዒ አት-ቲርሚዚህ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 121
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *“ዒዱል ፈጥር ሰዎች ጾም የሚፈቱበት ነው፤ ዒዱል አደሐ ደግሞ መስዋዕት የሚያቀርቡበት ቀን ነው”*። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْفِطْرُ يَوْمَ يُفْطِرُ النَّاسُ وَالأَضْحَى يَوْمَ يُضَحِّي النَّاسُ ‏”‏
ጃሚዒ አት-ቲርሚዚህ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 91
አቡ ሰዒደል ኹድሪይ እንደተረከው፥ የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” *”በሁለቱ በዓል በዒደል አደሐ እና ዒደል ፈጥር መጾም ከልክለዋል”*። عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيِّ، قَالَ نَهَى رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم عَنْ صِيَامَيْنِ يَوْمِ الأَضْحَى وَيَوْمِ الْفِطْرِ ‏.

“ዒድ” عِيد የሚለው ቃል “ዓደ” عَادَ ማለትም “ተመላለሰ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ምልሰት” ማለት ነው፥ ይህ “መደሰቻ” ወይም “በዓል” በየዓመቱ ስለሚመላለስ ይህንን ስያሜ አግኝቷል። ስለዚህ ከአላህ የወረዱትን ቁርኣን እና ሐዲስ ብቻ መከተል አለብን፦
7፥3 *ከጌታችሁ ወደ እናንተ የተወረደውን ተከተሉ*። اتَّبِعُوا مَا أُنزِلَ إِلَيْكُم مِّن رَّبِّكُمْ

“ተከተሉ” የሚለው ቃል “ኢተቢዑ” اتَّبِعُوا ሲሆን “ኢትባዕ” إِتْبَاع‎ ማለት ከአላህ ወደ ነቢያችን”ﷺ” የተወረደውን ብቻ መከተል ማለት ነው። ሙሥሊም የተወረደውን ብቻ ሲከተል ሁለት ብቻ ዒድ ያከብራል። ከዚህ ውጪ በዓል እያሉ ማክበር ቢድዓህ ነው፥ “ቢድዓህ” بِدْعَة ደግሞ “በደዐ” بَدَّعَ ማለትም “ፈጠረ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ፈጠራ” ማለት ነው። ቢድዓህ የኢትባዕ ተቃራኒ ነው። “ቢድዓህ” ማለት አላህ ሳያዘን እና ሳይፈቅድልን ዝንባሌአችንን ተከትለን የምናደርገው አዲስ አምልኮ ማለት ነው፦
ኢማም ቡኻርይ : መጽሐፍ 53, ሐዲስ 7
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ማንኛውም ሰው ከትእዛዛችን ያልሆነ አንድ ነገር ቢፈጥር ተቀባይነት የለውም عَنْ عَائِشَةَ ـ رضى الله عنها ـ قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ مَنْ أَحْدَثَ فِي أَمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ فِيهِ فَهُوَ رَدٌّ ‏”‌‏.‏
ሡነን ኢብኑ ማጃህ : መጽሐፍ 1, ሐዲስ 210
ከሲር ኢብኑብ ዐብደላህ እንደተረከው አባቱ ከአያቱ የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ ሲሉ ሰማው ያለው፦ “ማንኛውም ሰው የእኔን ሡናህ ሱናህ ያደረገ ከእኔ በኃላ የእኔን ፈለግ የሚከተሉትን ሰዎች የሚያገኙትን አጅር ከእነርሱ ላይ ሳይቀነስና ሳይጨመር ያገኛል፤
ማንም ሰው አላህ እና መልእክተኛው ያልደነገጉትን ቢድዓን ያስተዋወቀ ያንን ፈለግ የተከተሉትን ሰዎች የሚያገኙትን ኀጢአት ከእነርሱ ላይ ሳይቀነስና ሳይጨመር ይሸከማል። حَدَّثَنِي كَثِيرُ بْنُ عَبْدِ اللَّهِ، عَنْ أَبِيهِ، عَنْ جَدِّهِ، قَالَ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ يَقُولُ ‏ “‏ مَنْ أَحْيَا سُنَّةً مِنْ سُنَّتِي قَدْ أُمِيتَتْ بَعْدِي فَإِنَّ لَهُ مِنَ الأَجْرِ مِثْلَ أَجْرِ مَنْ عَمِلَ بِهَا مِنَ النَّاسِ لاَ يَنْقُصُ مِنْ أُجُورِ النَّاسِ شَيْئًا وَمَنِ ابْتَدَعَ بِدْعَةً لاَ يَرْضَاهَا اللَّهُ وَرَسُولُهُ فَإِنَّ عَلَيْهِ مِثْلَ إِثْمِ مَنْ عَمِلَ بِهَا مِنَ النَّاسِ لاَ يَنْقُصُ مِنْ آثَامِ النَّاسِ شَيْئًا ‏”‏ ‏.‏
ሡነን ነሣኢ : መጽሐፍ 19, ሐዲስ 23
ጃቢር ኢብኑ ዐብደላህ እንደተረከው፦ የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ሑጥባቸው ላይ እንደተናገሩት፦ “አላህ የመራውን ማንም አያጠመውም፤ አላህ ያጠመመውን ማንም አያቀናውም። ከንግግር ሁሉ በላጩ የአላህ መጽሐፍ ነው፤ ከመመሪያ ሁሉ በላጩ የሙሐመድ መመሪያ ነው። ከሁሉ የተጠላ ነገር ቢድዓህ ነው፤ ቢድዓህ ሁሉ ጥመት ነው፤ ጥመት ሁሉ የእሳት ነው። عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ قَالَ كَانَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ فِي خُطْبَتِهِ يَحْمَدُ اللَّهَ وَيُثْنِي عَلَيْهِ بِمَا هُوَ أَهْلُهُ ثُمَّ يَقُولُ مَنْ يَهْدِهِ اللَّهُ فَلَا مُضِلَّ لَهُ وَمَنْ يُضْلِلْهُ فَلَا هَادِيَ لَهُ إِنَّ أَصْدَقَ الْحَدِيثِ كِتَابُ اللَّهِ وَأَحْسَنَ الْهَدْيِ هَدْيُ مُحَمَّدٍ وَشَرُّ الْأُمُورِ مُحْدَثَاتُهَا وَكُلُّ مُحْدَثَةٍ بِدْعَةٌ وَكُلُّ بِدْعَةٍ ضَلَالَةٌ وَكُلُّ ضَلَالَةٍ فِي النَّارِ .

ከሁሉ የተጠላ ነገር ቢድዓህ ነው፤ ቢድዓህ ሁሉ ጥመት ነው፤ ጥመት ሁሉ የእሳት ከሆነ ካየን ቢድዓህ የሚያራምድ ማንኛውም ሰው “ሙብተዲዕ” مبتدئ ይባላል። አሏህ ከሙብተዲዕ ፈሣድ ይጠብቀን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሥነ-ፍጥረት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

39፥62 *አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው*፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡ اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ ۖ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ

“ሥነ-ፍጥረት”creatinology” ማለት ስለ ፍጥረት የሚያጠና የዕውቀት ዘርፍ ነው፤ አምላካችን አላህ የሁሉ ነገር ፈጣሪ ነው፤ “ሸይዕ” شَىْء ማለት “ነገር’thing” ማለት ሲሆን ሁሉንም ነገራት ሁሉ ማስገኘት በሻ ጊዜ ለእርሱ የሚለው፡- «ኹን ነው» ወዲያውም ይኾናል፦
2፥117 ሰማያትንና ምድርን ያለብጤ ፈጣሪ ነው፤ *ነገርንም ማስገኘት በሻ ጊዜ ለእርሱ የሚለው፡- «ኹን ነው» ወዲያውም ይኾናል*፡፡ بَدِيعُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۖ وَإِذَا قَضَىٰ أَمْرًا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُ كُن فَيَكُونُ

አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው፤ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፤ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፦
39፥62 *አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው*፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡ اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ ۖ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ
6፥102 ይህ ጌታችሁ አላህ ነው፡፡ ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፡፡ *ነገርን ሁሉ ፈጣሪ ነው*፤ ስለዚህ ተገዙት፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ተጠባባቂ ነው፡፡ ذَٰلِكُمُ اللَّهُ رَبُّكُمْ ۖ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ فَاعْبُدُوهُ ۚ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ
13፥16 *አላህ ሁሉንም ነገር ፈጣሪ ነው*፤ እርሱም አንዱ አሸናፊው ነው፤ በል፡፡ قُلِ اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ وَهُوَ الْوَاحِدُ الْقَهَّارُ
40፥62 ይሃችሁ ጌታችሁ አላህ ነው፤ *የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው*፤ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፤ ታዲያ ከእምነት ወዴት ትመለሳላችሁ፡፡ ذَٰلِكُمُ اللَّهُ رَبُّكُمْ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ لَّا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ فَأَنَّىٰ تُؤْفَكُون

ነጥብ አንድ
“ፍጥረት”
አላህ የፈጠራቸው ፍጥረታት ህልቆ-መሳፍርት ናቸው፤ ከአጽናፍ እስከ አድማስ ያሉትን ትልቅ እና ደቂቅ ፍጥረታት ቢዘረዘሩ አያልቁም፤ እነዚህን ፍጥረታት አላህ በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ ነው፦
50፥38 ሰማያትንና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ ፈጠርን፡፡ ድካምም ምንም አልነካንም፡፡ وَلَقَدْ خَلَقْنَا السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ وَمَا بَيْنَهُمَا فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ وَمَا مَسَّنَا مِن لُّغُوبٍ
25፥59 ያ ሰማያትና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ፣ ከዚያም በዐርሹ ላይ የተደላደለ አልረሕማን ነው፡፡ ከእርሱም ዐዋቂን ጠይቅ፡፡ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ وَمَا بَيْنَهُمَا فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ ثُمَّ اسْتَوَىٰ عَلَى الْعَرْشِ ۚ الرَّحْمَـٰنُ فَاسْأَلْ بِهِ خَبِيرًا

ይህ ጥቅላዊ ገለጻ ሲሆን በተናጥል አስፈላጊ የሆነው አፈጠጠሩ እንዲህ ይገልጻል፦
41፥9 በላቸው «እናንተ በዚያ ምድርን በሁለት ቀኖች ውስጥ በፈጠረው አምላክ በእርግጥ ትክዳላችሁን? ለእርሱም ባለንጣዎችን ታደርጋላችሁን? ያ ይህንን የሠራው የዓለማት ጌታ ነው፡፡ قُلْ أَئِنَّكُمْ لَتَكْفُرُونَ بِٱلَّذِى خَلَقَ ٱلْأَرْضَ فِى يَوْمَيْنِ وَتَجْعَلُونَ لَهُۥٓ أَندَادًۭا ۚ ذَٰلِكَ رَبُّ ٱلْعَٰلَمِينَ

ከመጀመሪያው ቀን እስከ አራተኛው ቀናት ባሉት በአራት ቀናት ውስጥ በምድር ላይ የረጉ ጋራዎችን፣ በውስጧም ምግቦችዋን ለጠያቂዎች ትክክል ሲኾኑ ወሰነ፦
42፥10 በእርሷም ከበላይዋ የረጉ ጋራዎችን አደረገ፡፡ በእርሷም በረከትን አደረገ፡፡ በውስጧም ምግቦችዋን በአራት ቀናት ውሰጥ ለጠያቂዎች ትክክል ሲኾኑ ወሰነ፡፡ وَجَعَلَ فِيهَا رَوَٰسِىَ مِن فَوْقِهَا وَبَٰرَكَ فِيهَا وَقَدَّرَ فِيهَآ أَقْوَٰتَهَا فِىٓ أَرْبَعَةِ أَيَّامٍۢ سَوَآءًۭ لِّلسَّآئِلِينَ

“ጭስ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ዱኻን” دُخَانٌۭ ሲሆን “ጋዝ” ማለት ነው፤ ሰማይ በጋዝ ደረጃ እያለች አላህ ለእርሷም ለምድርም «ወዳችሁም ኾነ ወይም ጠልታችሁ ኑ» አላቸው፡፡ «ታዛዦች ኾነን መጣን» አሉ፦
42፥11 ከዚያም ወደ ሰማይ እርሷ ጭስ ኾና ሳለች አሰበ፡፡ ለእርሷም ለምድርም «ወዳችሁም ኾነ ወይም ጠልታችሁ ኑ» አላቸው፡፡ «ታዛዦች ኾነን መጣን» አሉ፡፡ ثُمَّ ٱسْتَوَىٰٓ إِلَى ٱلسَّمَآءِ وَهِىَ دُخَانٌۭ فَقَالَ لَهَا وَلِلْأَرْضِ ٱئْتِيَا طَوْعًا أَوْ كَرْهًۭا قَالَتَآ أَتَيْنَا طَآئِعِينَ

“ሱመ” ثُمَّ ማለት አያያዥ መስተጻምር ሲሆን “ከዚያም” ወይም “እንዲሁ” ማለት ነው፤ አያያዥነቱ “ተርቲቢያህ” ማለትም “ቅድመ-ተከተል” ነው፤ ይህም ቅድመ-ተከተል በሁለት ይከፈላል፦ አንዱ “ተርቲበቱል ከላም” ማለት “የንግግር ቅድመ-ተከተል” ሲሆን ሁለተኛው “ተርቲበቱል ዘመን” ማለት የጊዜ ቅድመ-ተከተል ናቸው፣ እዚህ አንቀጽ ላይ ግን ዓውዱ የንግግር ቅድመ-ተከተል ታሳቢና ዋቢ ያደረገ ነው፤ አላህ ከዚያም ወደ ሰማይ እርሷ ጭስ ኾና ሳለች አሰበ፤ ጭስ የነበረችውን ሰማይ በሁለት ቀኖችም ውስጥ ሰባት ሰማያት አደረጋቸው፦
41፥12 በሁለት ቀኖችም ውስጥ ሰባት ሰማያት አደረጋቸው፡፡ فَقَضَىٰهُنَّ سَبْعَ سَمَٰوَاتٍۢ فِى يَوْمَيْنِ
2፥29 እርሱ ያ በምድር ያለውን ሁሉ ለእናንተ የፈጠረ ነው፡፡ *ከዚያም ወደ ሰማይ አሰበ፤ ሰባት ሰማያትም አደረጋቸው*፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ هُوَ ٱلَّذِى خَلَقَ لَكُم مَّا فِى ٱلْأَرْضِ جَمِيعًۭا ثُمَّ ٱسْتَوَىٰٓ إِلَى ٱلسَّمَآءِ فَسَوَّىٰهُنَّ سَبْعَ سَمَٰوَٰتٍۢ ۚ وَهُوَ بِكُلِّ شَىْءٍ عَلِيمٌۭ
ነጥብ ሁለት
“ማስተንተን”
በሰማያትና በምድር ያሉትን ከአጽናፍ እስከ አድማስ ያሉትን ትልቅ እና ደቂቅ ህልቆ-መሳፍርት ፍጥረታት እኛ ቀስ በቀስ በማስተንተን ማወቅ እንችላለን፤ በአላህ አፈጣጠር ውስጥ ምንም መዛነፍን አታይም፤ ዓይንህንም ወደ ፍጥረታት እይ ከስንጥቆች አንዳችን ታያለህን? በፍጹም አታይም፦
3፥191 እነርሱም እነዚያ ቆመው፣ ተቀምጠውም፣ በጎኖቻቸው ተጋድመውም አላህን የሚያወሱ *በሰማያትና በምድር አፈጣጠርም የሚያስተነትኑ*፡- «ጌታችን ሆይ! *ይህን በከንቱ አልፈጠርከውም*፤ ጥራት ይገባህ፤ ከእሳትም ቅጣት ጠብቀን» የሚሉ ናቸው፡፡ الَّذِينَ يَذْكُرُونَ اللَّهَ قِيَامًا وَقُعُودًا وَعَلَىٰ جُنُوبِهِمْ وَيَتَفَكَّرُونَ فِي خَلْقِ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ رَبَّنَا مَا خَلَقْتَ هَـٰذَا بَاطِلًا سُبْحَانَكَ فَقِنَا عَذَابَ النَّارِ
67፥3 ያ ሰባትን ሰማያት የተነባበሩ ኾነው የፈጠረ ነው፡፡ *በአልረሕማን አፈጣጠር ውስጥ ምንም መዛነፍን አታይም*፡፡ ዓይንህንም መልስ፡፡ «ከስንጥቆች አንዳችን ታያለህን?» الَّذِي خَلَقَ سَبْعَ سَمَاوَاتٍ طِبَاقًا ۖ مَّا تَرَىٰ فِي خَلْقِ الرَّحْمَـٰنِ مِن تَفَاوُتٍ ۖ فَارْجِعِ الْبَصَرَ هَلْ تَرَىٰ مِن فُطُورٍ

ለእኛም በሰማያት ያለውን እና በምድርም ያለውን ሁሉ በሙሉ ከአላህ ሲኾን የገራልን ነው፤ በዚህ አፈጣጥር ለሚያስተነትኑ ሕዝቦች ተዓምራት አልለበት፦
45፥13 ለእናንተም በሰማያት ያለውን እና በምድርም ያለውን ሁሉ በሙሉ ከእርሱ ሲኾን የገራላችሁ ነው፡፡ በዚህ *ለሚያስተነትኑ ሕዝቦች* ተዓምራት አልለበት፡፡ وَسَخَّرَ لَكُم مَّا فِي السَّمَاوَاتِ وَمَا فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا مِّنْهُ ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّقَوْمٍ يَتَفَكَّرُونَ
13፥3 እርሱም ያ ምድርን የዘረጋ በእሷም ተራራዎችንና ወንዞችን ያደረገ በውስጧም ከፍሬዎች ሁሉ ሁለት ሁለት ዓይነቶችን ያደረገ ነው፡፡ ሌሊትን በቀን ይሸፍናል፡፡ በዚህም ውስጥ *ለሚያስተነትኑ ሕዝቦች* ምልክቶች አሉ፡፡ وَهُوَ الَّذِي مَدَّ الْأَرْضَ وَجَعَلَ فِيهَا رَوَاسِيَ وَأَنْهَارًا ۖ وَمِن كُلِّ الثَّمَرَاتِ جَعَلَ فِيهَا زَوْجَيْنِ اثْنَيْنِ ۖ يُغْشِي اللَّيْلَ النَّهَارَ ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّقَوْمٍ يَتَفَكَّرُونَ

ሰማያትና ምድር ከጌታችንም ጸጋዎች ናቸው፦
55፥7 *ሰማይንም አጓናት*፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡ وَٱلسَّمَآءَ رَفَعَهَا وَوَضَعَ ٱلْمِيزَانَ
55፥10 *ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት*፡፡ وَٱلْأَرْضَ وَضَعَهَا لِلْأَنَامِ
55፥13 *ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?* فَبِأَىِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

በሰማያት ያለውንና በምድርም ያለውን ሁሉ ለእኛ ያገራልን ግልጽም ድብቅም ሲኾኑ የሞላላልን ጸጋዎቹንም ናቸው፦
31፥20 አላህ *በሰማያት ያለውንና በምድርም ያለውን ሁሉ ለእናንተ ያገራላችሁ ጸጋዎቹንም ግልጽም ድብቅም ሲኾኑ የሞላላችሁ መኾኑን አታዩምን?* أَلَمْ تَرَوْا أَنَّ اللَّهَ سَخَّرَ لَكُم مَّا فِي السَّمَاوَاتِ وَمَا فِي الْأَرْضِ وَأَسْبَغَ عَلَيْكُمْ نِعَمَهُ ظَاهِرَةً وَبَاطِنَةً ۗ

ሰማያትና ምድር፣ በሰማያት ያለውንና በምድርም ያለውን ሁሉ እኛ የደረስንበት ግልጽም ያልደረስንበት ድብቅም ለእኛ ያገራልን የአላህንም ጸጋ ናቸው፤ የአላህንም ጸጋ ብትቆጥረው አንዘልቀውም፦
16፥18 *የአላህንም ጸጋ ብትቆጥሩ አትዘልቋትም*፡፡ አላህ በእርግጥ መሓሪ አዛኝ ነውና፡፡ وَإِن تَعُدُّوا نِعْمَةَ اللَّهِ لَا تُحْصُوهَا ۗ إِنَّ اللَّهَ لَغَفُورٌ رَّحِيمٌ
መደምደሚያ
በተረፈ ዘፍጥረት 1፥1-31 የፈጣሪን ፍጥረት በከፊል እንጂ በሙሉ አይዘረዝርም። ለምሳሌ ሰባት ሰማያት፣ መላእክት፣ ውኃ፣ ፈንገስ፣ ባክቴሪያ፣ ጀርም ወዘተ መቼ እንደተፈጠሩ፣ ከምን እንደተፈጠሩ እና እንዴት እንደተፈጠሩ አይናገርም። ታላቁ ኢትዮጵያዊ ባለቅኔው ሎሬትዬ ጸጋዬ ገብረ መድኅን፦ የሰው ልጅ ከሁለት ነገር ይማራል፦ አንዱ “ሀ” ብሎ “በሳር” ሲሆን ሁለተኛው “ዋ” ብሎ “በአሳር” ይላልና፤ ክርስቲያን ሃያሲ ሂስ ለመስጠት “ሀ” ብሎ “በሳር” ከቁርአን መማር አሊያም “ዋ” ብሎ “በአሳር” ዘፍጥረት ላይ የሌሉትን ሃያ ሁለቱ ሥነ-ፍጥረት ብሎ አክሲማሮስ ውስጥ መደበቅ ነው፤ ይህ ደግሞ እንጥል ከመቧጠጥ ምንም አይተናነስም። ነገር ግን ፈጣሪ ከጥንት ጀምሮ እስከ ፍጻሜ ድረስ የሠራውን ሥራ ሰው መርምሮ አያገኝም፦
መክብብ 3፥11 ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው፤ *እግዚአብሔርም ከጥንት ጀምሮ እስከ ፍጻሜ ድረስ የሠራውን ሥራ ሰው መርምሮ እንዳያገኝ* ዘላለምነትን በልቡ ሰጠው።

አላህ የዓለማት ጌታ ነው፤ “ዓለሚን” عَٰلَمِين ማለት “ዓለማት” ማለት ሲሆን የዘመናችን የሥነ-ፈለክ አስተንታኞች “መልቲ-ቨርስ”multi-verse” ይሉታል፤ ይህም ህልቆ-መሳፍት የሆነውን አድማስና አፅናፍ ለማመልከት ይጠቀሙበታል፤ “አዕለም” أَعْلَم የዐለሚን ነጠላ ሲሆን ‘ዐልለመ” عَلَّمَ “አሳወቀ” ከሚለው ግስ የመጣ ሲሆን “ዓለም” ወይም “የታወቀ” ማለት ነው፤ አላህ በእኛ ዘመን ባሉት ያሳወቀው እኛ ያለንባት አንድ ዓለም “ዩኒ-ቨርስ”uni-verse” ነው፤ የእኛ ዓለም ከ 170 billion እስከ 200 billion “ረጨት”galaxy” ይዟል፤ “ረጨት” ማለት የከዋክብት ስብስብ ሲሆን የእኛ ረጨት “ፍኖተ-ሃሊብ”Milky Way” ረጨት ይባላል፤ ይህ ረጨት ውፍረቱ 1000 የብርሃን አመት ይገመታል፤ ከአንዱ ጫፍ እስከሌላኛው ጫፍ ያለው ርቀት በዲያሜትር ሲለካ ደግሞ 100,000 የብርሃን ዓመት ይሆናል፤ በውስጡ ከ100 እስከ 400 ቢልዮን ከዋክብቶች እንደያዘ ይገመታል።
ይህንን የከዋክብት ረጨት”constellation” አምላካችን አላህ የዛሬ 1407 ዓመት በቁርአን “ቡሩጅ” بُرُوج ይለዋል፦
85:1 #የቡርጆች الْبُرُوجِ ባለቤት በሆነችው ሰማይ እምላለሁ፤
25:61 ያ በሰማይ #ቡርጆችን بُرُوجًا ያደረገና በርሷም አንጸባራቂን ፀሐይ አብሪ ጨረቃንም ያደረገ ጌታ ክብሩ በጣም ላቀ።
15:16 በሰማይም ላይ #ቡርጆችን بُرُوجًا በእርግጥ አድርገናል፡፤ ለተመልካቾችም አጊጠናታል፡፡

አላህ የዛሬ 1400 ዓመት በተከበረው ቃሉ በቁርአን “በአጽናፎቹ ውስጥ ያሉትን ታምራቶቻችንን በእርግጥ እናሳያቸዋለን” ብሎ ቃል ገብቶ ነበር፦
41፥53 እርሱም ቁርአን እውነት መሆኑ ለነርሱ እስከሚገለጽላቸው ድረስ፣ #በአጽናፎቹ #ውስጥ እና በራሶቻቸውም ውስጥ #ያሉትን #ታምራቶቻችንን በእርግጥ #እናሳያቸዋለን፤ ጌታህም እርሱ በነገሩ ሁሉ ላይ አዋቂ መሆኑ አይበቃቸውምን?

ታዲያ በበረሃ ግመል ገፊ ነው ተብሎ በሚነገርላቸው ላይ ይህ ሁሉ እውቀት እንዴት ተዥጎደጎደ? ስንል፤ ይህንን እውቀት የዛሬ 1407 ዓመት ያ በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለውን ምስጢር የሚያውቀው አወረደው ይሆናል መልሱ፦
25:6 ያ በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለውን ምስጢር የሚያውቀው አወረደው፤ እርሱ መሐሪ አዛኝ ነውና፤ በላቸው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
ከሺርክ በስተጀርባ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

36፥60 *”የአደም ልጆች ሆይ! ሰይጣንን አታምልኩ! እርሱ ለእናንተ ግልጽ ጠላት ነውና በማለት ወደ እናንተ አላዘዝኩምን?* أَلَمْ أَعْهَدْ إِلَيْكُمْ يَا بَنِي آدَمَ أَن لَّا تَعْبُدُوا الشَّيْطَانَ ۖ إِنَّهُ لَكُمْ عَدُوٌّ مُّبِينٌ

“ዒባዳህ” عِبَادَة የሚለው ቃል “ዓበደ عَبَدَ ማለትም “አመለከ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “አምልኮ” ማለት ነው። ዒባዳህ በሦስት ይከፈላል፥ እርሱም፦
1ኛ. “ዒባደቱል ቀልቢያ” عِبَادَة قَلْبِيَّة ማለት “የኃልዮ አምልኮ” ማለት ነው፥ “ቀልብ” قَلْب ማለት “ኃልዮ” ወይም “ልብ” ማለት ነው።
2ኛ. “ዒባደቱል ቀውልያ” عِبَادَة قَوْلِيَّة ማለት “የነቢብ አምልኮ” ማለት ነው፥ “ቀውል” قَوْل ማለት “ነቢብ” ወይም “አንደበት” ማለት ነው።
3ኛ. “ዒባደቱል ዐመልያ” عِبَادَة عَمَلِيَّة ማለት “የገቢር አምልኮ” ማለት ነው፥ “ዐመል” عَمَل ማለት “ገቢር” ወይም “ድርጊት” ማለት ነው።

“ዱዓ” ደግሞ በቀውል ከሚከናወን ዒባዳህ አንዱ ነው፥ “ዱዓእ” دُعَآء የሚለው ቃል “ደዓ” دَعَا ማለትም “ለመነ” “ጠራ” “ጸለየ” “ተማጸነ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ልመና” “ጥሪ” “ጸሎት” “ተማጽንዖ” ማለት ነው። ዱዓእ የአንድ አምላክ የአላህ ሐቅና ገንዘብ ነው፦
2፥186 *”ባሮቼም ከእኔ በጠየቁህ “እኔ ቅርብ ነኝ፥ የለማኝን ጸሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ*”፡፡ ስለዚህ ለእኔ ይታዘዙ፤ በእኔም ይመኑ፤ እነርሱ ሊመሩ ይከጀላልና፡፡ وَإِذَا سَأَلَكَ عِبَادِي عَنِّي فَإِنِّي قَرِيبٌ ۖ أُجِيبُ دَعْوَةَ الدَّاعِ إِذَا دَعَانِ ۖ فَلْيَسْتَجِيبُوا لِي وَلْيُؤْمِنُوا بِي لَعَلَّهُمْ يَرْشُدُونَ
40፥60 ጌታችሁም አለ *«ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና፡፡ እነዚያ እኔን ከማምለክ የሚኮሩት ተዋራጆች ኾነው ገሀነምን በእርግጥ ይገባሉ”*፡፡ وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ ۚ إِنَّ الَّذِينَ يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِي سَيَدْخُلُونَ جَهَنَّمَ دَاخِرِينَ
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 34, ሐዲስ 2
አን-ኑዕማን ኢብኑ በሺር እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” አሉ፦ *”ዱዓእ ዒባዳህ ነው፥ ከዚያም፦ “ጌታችሁም አለ *«ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና” የሚለውን አንቀጽ ቀሩ”*። عَنِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏”‏ إِنَّ الدُّعَاءَ هُوَ الْعِبَادَةُ ‏”‏ ‏.‏ ثُمَّ قَرَأَ ‏{وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ}‏

ዱዓእ አምልኮ ከሆነ አምልኮ የአላህ ብቻ ሐቅ እና የባሕርይው ገንዘቡ ነው፥ አላህ ወደ እርሱ ዱዓእ ለሚያደርጉት ቅርብ ነው፥ አላህ መለኮት ነው። መለኮት በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው፣ ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው፣ ሁሉን ሰሚ ነው፣ ሁሉን ተመልካች ነው፣ በነገሩ ሁሉ ላይ ተቆጣጣሪ ነው፦
29፥20 አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው”*። إِنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ
65፥11 *”አላህም ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው”*፡፡ وَاللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمٌ
58፥1 *”አላህ ሰሚ ተመልካች ነው”*፡፡ إِنَّ اللَّهَ سَمِيعٌ بَصِير
2፥110 *”አላህ የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነው”*፡፡ إِنَّ اللَّهَ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ
4፥86 *አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ተቆጣጣሪ ነውና*፡፡ إِنَّ اللَّهَ كَانَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ حَسِيبًا

ነገር ግን ሰዎች ከዚህ በተቃራኒው ወደ ፍጡራን ዱዓእ ያረጋሉ። ፍጡራን ሁሉን የማወቅ፣ የመስማት፣ የማየት፣ የመቆጣጠር ችሎታ ውስንነት አለባቸው፥ ስለዚህ ወደ እነርሱ የሚደረግ ዱዓእ አይመልሱም፦
7፥194 *”እነዚያ ከአላህ ሌላ የምትጠሯቸው እንደ እናንተ አምላኪዎች ናቸው፥ እውነተኞችም እንደሆናችሁ ጥሩዋቸው እና ለእናንተ ይመልሱላችሁ አይችሉም”*። إِنَّ ٱلَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ عِبَادٌ أَمْثَالُكُمْ ۖ فَٱدْعُوهُمْ فَلْيَسْتَجِيبُوا۟ لَكُمْ إِن كُنتُمْ صَٰدِقِينَ ።

እነርሱ እንደ ማንኛውም ፈጣሪን አምላኪ አምላኪዎች ናቸው እንጂ ተመላኪዎች አይደሉም። በክርስትና ዱዓእ ከሚደረግላቸው ፍጡራን መካከል መላእክት ናቸው፥ አላህ የትንሳኤ ቀን መላእክትን፦ “እነዚህ እናንተን ያመልኩ ነበሩን? ብሎ ይጠይቃቸዋል፤ እነርሱም በፍጹም፦ “ይልቁንም ጂንን ያመልኩ ነበሩ” ብለው ይመልሳሉ፦
34፥40 *”ሁሉንም በሚሰበስባቸው እና ከዚያም ለመላእክቶቹ፦ «እነዚህ እናንተን ያመልኩ ነበሩን?» በሚላቸው ቀን የሚኾነውን አስታውስ*፡፡ وَيَوْمَ يَحْشُرُهُمْ جَمِيعًا ثُمَّ يَقُولُ لِلْمَلَائِكَةِ أَهَـٰؤُلَاءِ إِيَّاكُمْ كَانُوا يَعْبُدُونَ
34፥41 *መላእክቶቹም፦ «ጥራት ይገባህ “ከእነርሱ ይልቅ ረዳታችን አንተ ብቻ ነህ፥ እንደሚሉት አይደለም፥ ይልቁንም ጂንን ያመልኩ ነበሩ፡፡ አብዛኞቻቸው በእነርሱ አማኞች ናቸው» ይላሉ*፡፡ قَالُوا سُبْحَانَكَ أَنتَ وَلِيُّنَا مِن دُونِهِم ۖ بَلْ كَانُوا يَعْبُدُونَ الْجِنَّ ۖ أَكْثَرُهُم بِهِم مُّؤْمِنُونَ

ልብ አድርግ አድርግ ሰዎች ወደ መላእክት በዱዓእ ዒባዳህ ቢጠቀሙም ግን ያንን ዒባዳህ የሚቀበሉት ጂኒዎች ናቸው። እዚህ ዐውድ ላይ ጂን የተባሉት ሸያጢን ናቸው፥ አንድ ሰው ጣዖት ሲያመልክ ከጣዖቱ በስተኃላ አምልኮ የሚቀበለው ሸይጧን ነው፦
19፥42 *”ለአባቱ «አባቴ ሆይ! የማይሰማንና የማያይን ከአንተም ምንንም የማይጠቅምህን ጣዖት ለምን ታመልካለህን? ባለ ጊዜ አስታውስ”*። إِذْ قَالَ لِأَبِيهِ يَا أَبَتِ لِمَ تَعْبُدُ مَا لَا يَسْمَعُ وَلَا يُبْصِرُ وَلَا يُغْنِي عَنكَ شَيْئًا
19፥44 *«አባቴ ሆይ! ሰይጣንን አታምልክ፡፡ ሰይጣን ለአልረሕማን አመጸኛ ነውና”*፡፡ يَا أَبَتِ لَا تَعْبُدِ الشَّيْطَانَ ۖ إِنَّ الشَّيْطَانَ كَانَ لِلرَّحْمَـٰنِ عَصِيًّا
የኢብራሂም አባት የማይሰማና የማያይ ጣዖት ሲለማመን ከዚያ በስተኃላ የሚመለከው ሸይጧን ስለነበር፦ “አባቴ ሆይ! ሰይጣንን አታምልክ” አለው። እንግዲህ አንድ ሰው ፍጡራንን ሲጠራ ከአላህ ሌላ እረዳት አድርጎ በአላህ ላይ የሚያሻርከው ኩፋሩል ጂን የሆኑትን ሸያጢንን ነው፦
6፥100 *”ለአላህም ተጋሪዎች የፈጠራቸውን ጂንዎችን አደረጉ”*፡፡ ወንዶች ልጆችንና ሴቶች ልጆችንም ያለ ዕውቀት ለእርሱ ቀጠፉ፡፡ አላህ ጥራት የተገባው ከሚሉት ነገር የላቀ ነው፡፡ وَجَعَلُوا لِلَّهِ شُرَكَاءَ الْجِنَّ وَخَلَقَهُمْ ۖ وَخَرَقُوا لَهُ بَنِينَ وَبَنَاتٍ بِغَيْرِ عِلْمٍ ۚ سُبْحَانَهُ وَتَعَالَىٰ عَمَّا يَصِفُونَ
7፥30 ከፊሉን ወደ ቅን መንገድ መራ፡፡ ከፊሎቹም በእነሱ ላይ ጥመት ተረጋግጦባቸዋል፡፡ *እነርሱ ሰይጣናትን ከአላህ ሌላ ረዳቶች አድርገው ይዘዋልና”*፡፡ እነርሱም ቅኑን መንገድ የተመራን ነን ብለው ያስባሉ፡፡ فَرِيقًا هَدَىٰ وَفَرِيقًا حَقَّ عَلَيْهِمُ الضَّلَالَةُ ۗ إِنَّهُمُ اتَّخَذُوا الشَّيَاطِينَ أَوْلِيَاءَ مِن دُونِ اللَّهِ وَيَحْسَبُونَ أَنَّهُم مُّهْتَدُونَ

አላህ ሰዎችን በቀጥተኛው መንገድ በኢሥላም ላይ ፈጥሮ ሳለ ሸያጢን ግን ከዚህ ዲን በሺርክ ምክንያት ሰዎችን ያርቃሉ፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐግ 53, ሐዲስ 76
ዒያድ ኢብኑ ሒማር እንደተረከው፦ የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” ኹጥባህ በሚደረግበት ቀን እንዲህ አሉ፦ *”ለእናንተ ያስተማርኩት ጌታዬ ያዘዘኝ፥ እናንተ የማታውቁትን እርሱ ዛሬ ያሳወቀኝን። አላህም አለ፦ “እኔ የሰጠኃቸውንና ሕጋዊ የሆነላቸው ያ ሁሉ ንብረት ነው። እኔ ሁሉንም ባሮቼን በቀጥተኛው መንገድ ላይ ፈጠርኳቸው፥ ሸያጢን መጥተው ከዲናቸው አራቋቸው”*። عَنْ عِيَاضِ بْنِ حِمَارٍ الْمُجَاشِعِيِّ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ذَاتَ يَوْمٍ فِي خُطْبَتِهِ ‏”‏ أَلاَ إِنَّ رَبِّي أَمَرَنِي أَنْ أُعَلِّمَكُمْ مَا جَهِلْتُمْ مِمَّا عَلَّمَنِي يَوْمِي هَذَا كُلُّ مَالٍ نَحَلْتُهُ عَبْدًا حَلاَلٌ وَإِنِّي خَلَقْتُ عِبَادِي حُنَفَاءَ كُلَّهُمْ وَإِنَّهُمْ أَتَتْهُمُ الشَّيَاطِينُ فَاجْتَالَتْهُمْ عَنْ دِينِهِم

እዚህ ሐዲስ ላይ “ሁነፋእ” حُنَفَاءَ የሚለው ቃል “ሐኒፍ” حَنِيف ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ አላህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን ሃይማኖት “ሐኒፋ” حَنِيفًا ናት፦
30፥30 *”ፊትህንም ወደ ቀጥተኛ ሃይማኖት ቀጥ አድርግ፡፡ የአላህን ፍጥረት ያችን አላህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን ሃይማኖት ያዟት፡፡ የአላህን ፍጥረት መለወጥ የለም፡፡ ይህ ቀጥተኛ ሃይማኖት ነው”*፡፡ ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች አያውቁም፡፡ فَأَقِمْ وَجْهَكَ لِلدِّينِ حَنِيفًا ۚ فِطْرَتَ اللَّهِ الَّتِي فَطَرَ النَّاسَ عَلَيْهَا ۚ لَا تَبْدِيلَ لِخَلْقِ اللَّهِ ۚ ذَٰلِكَ الدِّينُ الْقَيِّمُ وَلَـٰكِنَّ أَكْثَرَ النَّاسِ لَا يَعْلَمُونَ

እዚህ አንቀጽ ላይ “ቀጥተኛ” ለሚለው ቃል የገባው “ሐኒፋ” حَنِيفًا ሲሆን አላህ ሰዎችን ሁሉ የፈጠረበት ሃይማኖት ኢሥላም “ሐኒፋ” መሆኑን ያሳያል። አንድ ሰው ፍጡርን በዱዓእ ከጠራ ከዱዓእ በስተኃላ ሸይጧን አምልኮ ስለሚቀበል አምላካችን አላህ በትንሳኤ ቀን፦ “ሸይጧንን አታምልኩ” “አምልኩኝ” ብሎ አዞ እንደነበር ይናገራል፦
36፥60 *የአደም ልጆች ሆይ! ሰይጣንን አታምልኩ! እርሱ ለእናንተ ግልጽ ጠላት ነውና በማለት ወደ እናንተ አላዘዝኩምን?* أَلَمْ أَعْهَدْ إِلَيْكُمْ يَا بَنِي آدَمَ أَن لَّا تَعْبُدُوا الشَّيْطَانَ ۖ إِنَّهُ لَكُمْ عَدُوٌّ مُّبِينٌ
36፥61 *”አምልኩኝ! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው፤ በማለትም አላዘዝኩምን?”*፡፡ وَأَنِ اعْبُدُونِي ۚ هَـٰذَا صِرَاطٌ مُّسْتَقِيمٌ

ሺርክ በአላህ ላይ ሌሎች ማንነትንና ምንነትን በአምልኮ ማሻረክ ነው፥ ከሺርክ በስተጀርባ ይህንን አምልኮ የሚቀበሉት ሸያጢን ናቸው። ክርስቲያኖች ሆይ! ሳታውቁ የመስማት፣ የማየት፣ የማወቅ፣ የመቆጣጠር ውስንነት ባሕርይ ያለባቸውን ፍጡራንን ስትለማመኑ፣ ስትማጸኑ፣ ስትጠሩ ከነበረ እንግዲያውስ ባለማወቅ ነውና የተውበት በር ሳይዘጋ ወደ ዲኑል ኢሥላም ኑ እና የመስማት፣ የማየት፣ የማወቅ፣ የመቆጣጠር ውስንነት ባሕርይ የሌለበትን ፈጣሪን አላህን በብቸኝነት አብረን እናምልክ። ወደ ፍጡራን ዱዓእ በማድረግ በአላህ ላይ በማሻረክ ለሸያጢን አምልኮ ከመስጠት አላህ ይጠብቀን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ከሁሉ በላይ የሆነ አምላክ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

87፥1 *ከሁሉ በላይ የሆነዉን ጌታህን* ስም አሞግሥ። سَبِّحِ ٱسْمَ رَبِّكَ ٱلْأَعْلَى

በክርስትና ስልታዊ ሥነ-መለኮት”systematic theology” የአምላክ ሰው መሆን አስተምህሮት “ተሰግዎት”Incarnation” ሲባል፥ በአገራችን “ሚስጥረ-ስጋዌ” ይሉታል። “ስጋዌ” የሚለው ቃል “ስግው” ማለትም “ስጋ” ከሚለው የመጣ ነው፥ መለኮት በትስብእት ተገለጠ ብለው ድምዳሜ ላይ ያደረሳቸው የጳውሎስ ንግግር ነው። ለእኛ ለሙሥሊሞች ጳውሎስ የኢየሱስ ሐዋርያ ሳይሆን የግሪክንና የሮምን ዶክትሪን ከኢየሱስ ደክትሪን ጋር ለማስማማት የታገለ ጥሩ ፈላስፋ ነው። ነገር ግን ለክርስቲያኖች እንደ ነብይ ስለሚታይ የእርሱ ትምህርት ለሙሥሊም ማስረጃ ባይሆንም ለእነርሱ ግን መረጃ አድርገን እናቀርባለን። ብዙ ጊዜ ጳውሎስ ኢየሱስን ቁጭ የሚያደርገው ከአንዱ አምላክ ከአብ ነጥሎ ነው፥ ነገር ግን ክርስቲያኖች በተቃራኒው "ጳውሎስ ስለ ኢየሱስ አምላክነት ተናግሯል" ይላሉ። እዚህ ድምዳሜ ላይ አደረሰን ከሚሏቸው አናቅጽ መካከል አንዱን ጥቅስ በአጽንዖትና በአንክሮት እንመልከት፦
ሮሜ 9፥5 አባቶችም ለእነርሱ ናቸውና፤ *"ከእነርሱም ክርስቶስ በሥጋ መጣ፥ ከሁሉ በላይ የሆነ አምላክ እርሱ ለዘላለም የተባረከ ይሁን! አሜን*"። καὶ ἐξ ὁ Χριστὸς τὸ κατὰ σάρκα ὁ ὢν ἐπὶ πάντων Θεὸς εὐλογητὸς εἰς τοὺς αἰῶνας ἀμήν.
Whose are the fathers, and of whom as concerning the flesh Christ came. God, who is over all be blessed for ever. Amen.” Reivised standard version 1971 ,

ግሪኩ ላይ "ኤስቲን" ἐστιν ማለትም "ነው" የሚል ቃል የለም። አዲሱ መደበኛ ትርጉም የግርጌ ማስታወሻ "ከሁሉ በላይ የሆነ አምላክ እርሱም ለዘላለም የተባረከ ይሁን" የሚል ፍቺ እንዳለው እሩቅ ሳንሄድ የዐማርኛ ምሁራን ይነግሩናል። በ 1971 ዕትም Reivised standard version "ይሁን"be" ብሎ አስቀምጦታል፥ "be blessed for ever"። "አሜን" የሚለው ቃል ለምስጋና የመጣ እስከሆነ ድረስ "ለዘላም የተባረከ ይሁን" ማለት ምስጋና ነው። ማነው ለዘላም የተባረከ ይሁን የተባለው? ስንል ለዘላም የተባረከ ይሁን የተባለው "ከሁሉ በላይ" የሆነ አምላክ ነው። እርሱም ከኢየሱስ እና ከመላው ፍጥረት ሁሉ በላይ የሆነው አብ ነው፦
ኤፌሶን 4፥6 *ከሁሉ በላይ የሚሆን πάντων በሁሉም የሚሠራ በሁሉም የሚኖር አንድ አምላክ የሁሉም አባት አለ*።
ዮሐንስ 10፥29 *"የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ πάντων ይበልጣል"*።
ዮሐንስ 14፥28 የምትወዱኝስ ብትሆኑ *ከእኔ አብ ይበልጣልና* ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር።

ኢየሱስን የሚበልጠው አብ "ፓንቶን" πάντων ማለትም "ከሁሉ በላይ" ተብሏል። ልብ አድርግ "ክርስቶስ በሥጋ መጣ" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት። በስጋ የመጣው አምላክ ሳይሆን ክርስቶስ ኢየሱስ ነው። ክርስቶስን ከዳዊት ዘር ያመጣው አምጪ አምላክ ነው፦
የሐዋርያት ሥራ 13፥23 *"ከዚህም ሰው ዘር "አምላክ" Θεὸς እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒትን እርሱም ኢየሱስን አመጣ"*።

"አመጣ" የሚለው ቃል ይሰመርበት። አምጪው አምላክ መጪው ኢየሱስ ከሆነ፥ ክርስቶስን በስጋ ያመጣው አምጪው "ከሁሉ በላይ የሆነ አምላክ ለዘላለም የተባረከ ይሁን" መልእክቱ ይህ ነው። "ለዘላለም የተባረከ" ደግሞ የኢየሱስ ክርስቶስ አባት እና አምላክ ነው፦
2ኛ ቆሮንቶስ 11፥31 *"ለዘላም የተባረከ εὐλογητὸς εἰς τοὺς αἰῶνας ἀμήν የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት"* እንዳልዋሽ ያውቃል።

ጳውሎስ አይሁዳዊ ነው፥ የሚሞግተውም የአይሁድ ዳራ ይዞ ነው። "ቶዩስ አዩናስ" τοὺς αἰῶνας ማለት "ከዘላለም እስከ ዘላለም" ማለት ነው፦
መዝሙር 41፥13 *"ከዘላለም እስከ ዘላለም የእስራኤል አምላክ ያህዌህ ይባረክ"። አሜን አሜን*።
መዝሙር 106፥48 *"ከዘላለም እስከ ዘላለም የእስራኤል አምላክ ያህዌህ ይባረክ፤ ሕዝብም ሁሉ አሜን ይበል"*። ሃሌ ሉያ።

ከዘላለም እስከ ዘላለም የተባረከ የእስራኤል አምላክ ያህዌህ ከሆነ፥ እስራኤላውያን አምላካችን የሚሉት ያህዌህን ነው፥ አምላካችን የሚሉት ኢየሱስን ሳይሆን አባቱን እንደሆነ እራሱ ኢየሱስ ተናግሯል፦
ዘዳግም 6፥4 *እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን ያህዌህ አንድ ያህዌህ ነው"*።
ዮሐንስ 8፥54 *"እናንተ አምላካችን የምትሉት አባቴ ነው"*።

የሮሜ መልእክት ጸሐፊ ክርስቶስን ለአምላክ ተቀበላችሁት፣ አምላክ የክርስቶስ አባት ነው፣ የክርስቶስ ራስ አምላክ ነው፣ ክርስቶስ የአምላክ ነው፣ ክርስቶስ በአምላክ ፊት ይታያል ወዘተ እያለ ለማምታታት ተመልሶ ክርስቶስ አምላክ ነው አይልም፦
ሮሜ 15፥7 ስለዚህ *"ክርስቶስ ለአምላክ Θεὸς ክብር እንደ ተቀበላችሁ"* እንዲሁ እርስ በርሳችሁ ተቀባበሉ።
ሮሜ 15፥6 በአንድ ልብ ሆናችሁ በአንድ አፍ *"አምላክን Θεὸς፥ እርሱም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባት"*፥ ታከብሩ ዘንድ፥
1ኛ ቆሮንቶስ 11፥3 ነገር ግን የወንድ ሁሉ ራስ ክርስቶስ፥ የሴትም ራስ ወንድ፥ የክርስቶስም ራስ አምላክ Θεὸς እንደ ሆነ ልታውቁ እወዳለሁ"*"*
1ኛ ቆሮንቶስ 3፥23 *"ሁሉ የእናንተ ነው፥ እናንተም የክርስቶስ ናችሁ ክርስቶስም የአምላክ Θεὸς ነው*።
ዕብራውያን 9፥24 *"ክርስቶስ በእጅ ወደ ተሰራች፥ የእውነተኛይቱ ምሳሌ ወደ ምትሆን ቅድስት አልገባምና፥ ነገር ግን በአምላክ Θεὸς *ፊት* ስለ እኛ አሁን ይታይ ዘንድ ወደ እርስዋ ወደ ሰማይ ገባ"*።

ክርስቶስ አምላክ ሳይሆን የአምላክ ነው። አምላክ ክርስቶስ ሳይሆን የክርስቶስ አባት እና ራስ ነው። አምላክ በአምላክ ፊት ከታየ ሁለት አምላክ ሊሆን ነው፥ ቅሉ ግን በአምላክ ፊት ስለ አማንያን የሚታየው ክርስቶስ ነው። "ክርስቶስ" ማለት እራሱ "የተቀባ" ማለት ነው፥ ቀቢ አምላክ ተቀቢ ሰው ነው፦
የሐዋርያት ሥራ 10፥38 *"አምላክ Θεὸς የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ አምላክ Θεὸς ከእርሱ ጋር ነበረና"*።

ክርስቶስ አምላክ ሳይሆን አምላክ የቀባው እና አምላክ ከእርሱ ጋር የነበረ ሰው ነው። አምላክ አምላክን ለመርዳት አብሮት ነበር ማለት መድበለ-አማልክት ይሆናል። አይ አምላክ በክርስቶስ ሆኖ የዕርቅ ሥራ ሠራ እንጂ አምላክ ክርስቶስ አይደለም፦
2ኛ ቆሮንቶስ 5፥19 *"አምላክ Θεὸς በክርስቶስ ሆኖ"* ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና።

"አምላክ በአምላክ ሆኖ" ትርጉም አይሰጥም፥ ሁለት አምላክ ይሆናል። "አንድ ሰው ከሌላ ሰው ጋር ነበረ" ብሎ ሁለቱም አንድ ሰው ሳይሆኑ ሁለት ሰዎች ናቸው።
ስለዚህ ጳውሎስ ለማለት የፈለገው "ክርስቶስን በስጋ ያመጣ ከሁሉ በላይ የሆነ አምላክ አብ ለዘላለም የተባረከ ይሁን! አሜን" የሚል ብቻ ነው። በኢሥላም ከሁሉ በላይ የሆነዉ ጌታ አምላክ አላህ ብቻ ነው፥ እነዚያ መሲሢሑን "አላህ ነው" ያሉ በእርግጥ ካዱ። ይህ በአላህ አምላክነትን ላይ ሰውን ማሻረክ ነው፥ እነሆ በአላህ ላይ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም ስላደረገበት እና መኖሪያውም እሳት ስለሆነች መሲሢሑን "አላህ ነው" የምትሉ የተውበት በሩ ሳይዘጋ በተውበት ወደ አላህ ተመለሱ፦
87፥1 *ከሁሉ በላይ የሆነዉን ጌታህን* ስም አሞግሥ። سَبِّحِ ٱسْمَ رَبِّكَ ٱلْأَعْلَى
5፥72 *" «አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ አልመሲህም አለ፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን ተገዙ፡፡» እነሆ! በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም"*፡፡ لَقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ ۖ وَقَالَ الْمَسِيحُ يَا بَنِي إِسْرَائِيلَ اعْبُدُوا اللَّهَ رَبِّي وَرَبَّكُمْ ۖ إِنَّهُ مَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ ۖ وَمَا لِلظَّالِمِينَ مِنْ أَنصَارٍ

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
አዶናይ እና አዶኒ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡

6፥164 በላቸው *«እርሱ አላህ “የሁሉ ጌታ” ሲሆን ከአላህ በቀር ”ሌላን ጌታ” እፈልጋለሁን?”* ነፍስም ሁሉ በራሷ ላይ እንጅ ክፉን አትሠራም፡፡ قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْءٍۢ ۚ وَلَا تَكْسِبُ كُلُّ نَفْسٍ إِلَّا عَلَيْهَا

በአዲስ ኪዳን ግሪክ ኮይኔ “ኩሪዮስ” κύριος የሚለው ቃል በግርድፉ “ጌታ” የሚል ፍቺ አሊያም “መምህር” ለሚል ተለዋዋጭ ቃል ቢኖረውም በዕብራይስጡ ብሉይ ኪዳን ግን “ጌታ” የሚለው የተለያየ ትርጉም አለው። “ያህዌህ አምላካችን አንድ ያህዌህ ነው” የሚለው “ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው” ብለው አስቀምጠውታል፦
ዘዳግም 6፥4 እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ *አምላካችን ያህዌህ አንድ ያህዌህ ነው*። שְׁמַע, יִשְׂרָאֵל: יְהוָה אֱלֹהֵינוּ, יְהוָה אֶחָד.
ማርቆስ 12፥29 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው። ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ። እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ *”ጌታ” κύριος አምላካችን አንድ “ጌታ” κύριος ነው”*።

መቼም ኢየሱስ ከዘዳግም 6፥4 ላይ ሲጠቅስ “ያህዌህ” የሚለውን ቴትራግራማተን እየመነቀረ መንግሎ “ኩሩዮስ” እያለ ተናገረ ማለት ዘበት ነው፥ የሚመነቅርበትና የሚመነግልበት አንዳች ቁብ የለውም፤ እርሱ የሙሴ ዚቅ የሚያቀነቅንና የሚወርብ ዚቀኛ እንጂ የሚቀናቀን ተቃራኒ በፍጹም አይደለም። ሲቀጥል ግሪከኛ ተናጋሪም አይደለም።
ደግሞም አንዱ ያህዌህ እና መሢሑ ሁለት ማንነት እና ምንነት ናቸው፦
መዝሙር 2፥2 የምድር ነገሥታት ተነሡ፥ አለቆችም *”በያህዌህ” יְהֹוָה እና በመሢሑ ላይ እንዲህ ሲሉ ተማከሩ”*።
የሐዋርያት ሥራ 4፥26 የምድር ነገሥታት ተነሡ አለቆችም *በጌታ” κύριος እና በተቀባው ላይ አብረው ተከማቹ”* ብለህ የተናገርህ አምላክ ነህ።

ያህዌህ እና መሢሑ “እና” በሚል መስተጻምር መለያየታቸው አንባቢ ልብ ይለዋል፤ ነገር ግን “ያህዌህ” የሚለው “ኩርዮስ” በሚል እንደተለወጠ ልብ በል።
አይሁዳውያን “ያህዌህ” יְהֹוָה በሚለው ፈንታ የሚጠቀሙበት “አዶናይ” אֲדֹנָ֥י የሚለውን ጌትነት ነው፥ “አዶናይ” ለአንድ አምላክ ብቻ የሚጠቀምበት ነው፤ ያህዌህ ብቻውን “አዶናይ” ተብሏል፤ አንድም ፍጡር “አዶናይ” ተብሎ የተጠራ የለም፤ እስቲ አንዱ አምላክ “አዶናይ” የተባለበትን አናቅፅ ለናሙና ያክል እንየው፦
መዝሙር 16፥2 ያህዌህን *”አንተ “ጌታዬ” אֲדֹנָ֥י ነህ አልሁ”*፤ ከአንተ በቀር በጎነት የለኝም።
መዝሙር 110፥5 “ጌታዬ” אֲדֹנָ֥י በቀኝህ ነገሥታትን በቍጣው ቀን ይቀጠቅጣቸዋል።

ልብ አድርግ ዳዊት አንድ ዐውድ ላይ ያህዌህን “አዶናይ” אֲדֹנָ֥י ሲል ኢየሱስ ግን “አዶኒ” אדֹנִ֗י ነው ያለው፦
መዝሙር 110፥1 *”ያህዌህ יְהֹוָה “ጌታዬን” אדֹנִ֗י ጠላቶችህን ለእግርህ መቀመጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው”*።
የሐዋርያት ሥራ 2፥34 ዳዊት ወደ ሰማያት አልወጣምና፥ ነገር ግን እርሱ። *”ጌታ κύριος “ጌታዬን” κύριος ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው”*።

ዘዳግም 6፥4 ላይ ያለው አንዱ ያህዌህ መሢሑን፦ “ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ” አለው። አንዱ ያህዌህ ባለቤት ሲሆን መሢሑ ተሳቢ ነው፥ በባለቤት እና በተሳቢ መካከል “አለው” የሚል ተሻጋሪ ግስ መኖሩ በራሱ አንዱ አምላክ ያህዌህ እና መሢሑ ሁለት የተለያዩ ማንነቶች እና ምንነቶች እንደሆኑ ቁልጭና ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ነገር ግን የአዲስ ኪዳን ተርጓሚዎች “ያህዌህ” የሚለውን “ኩርዮስ” በማለት “አዶኒ” የሚለውን “ኩርዮስ” በማለት የዳዊትን ንግግር አምታተውታል። አንደኛው ጌታ ሌላይኛውን ጌታ፦ “ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ” ያለው ይመስላል። ግን ዳዊት ያለው “አዶኒ” እንጂ “አዶናይ” አይደለም። ልክ እንደ ዳዊት የደማስቆ ሰው ኤሊዔዘር፦ “ያህዌህ ጌታዬን እጅግ ባረከው” አለ፦
ዘፍጥረት 24፥35 *”*”ያህዌህ יְהֹוָה “ጌታዬን” אדֹנִ֗י እጅግ ባረከው”*።

“ያህዌህ” የሚለውን “ጌታ” በሚል ከተካነው “ጌታ ጌታዬን እጅግ ባረከው” ይሆናል፤ ይህ ደግሞ እንጥል ከመቧጠጥ የዘለለ ትርጉም አይኖረውም። “አዶኒ” በተመሳሳይ ሳራ አብርሃምን ያለችበት ነው፦
ዘፍጥረት18፥12 ሣራም በልብዋ እንዲህ ስትል ሳቀች። ካረጀሁ በኋላ በውኑ ፍትወት ይሆንልኛልን? *”ጌታዬም אדֹנִ֗י ፈጽሞ ሸምግሎአል”*።
1 ጴጥሮስ 3፥6 እንዲሁም ሣራ ለአብርሃም፦ *”ጌታ” κύριος ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት”*።

የዘፍጥረት አንቀጽ ላይ ሳራ አብርሃምን “አዶኒ” אדֹנִ֗י ያለችው ወደ ግሪኩ ኮይኔ ሲመጣ “ኩርዮስ” κύριος ብለው አስቀምጠዋል። ነገር ግን “አዶኒ” אֲדֹנִֽי ለፍጡራን ማለትም ለመላእክት እና ለሰዎች አገልግሎት ላይ ውሏል።

ለመላእክት፦
ኢያሱ 5፥14 እርሱም፦ አይደለሁም እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቼአለሁ፡ አለ። ኢያሱም ወደ ምድር በግምባሩ ተደፍቶ ሰገደና፦ *”ጌታዬ”* אֲדֹנִֽי ለባሪያው የሚነግረው ምንድር ነው? አለው።
መሳፍንት 6፥13 ጌዴዎንም፦ *”ጌታዬ”* אֲדֹנִֽי ሆይ፥ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ይህ ነገር ሁሉ ለምን ደረሰብን?… አለው።
ዘካርያስ 6፥4 ከእኔ ጋር ይነጋገር ለነበረውም መልአክ መልሼ፦ *”ጌታዬ”* אֲדֹנִֽי ሆይ፥ እነዚህ ምንድር ናቸው? አልሁት።

ለሰዎች፦
ዘፍጥረት 32:4 እንዲህም ብሎ አዘዛቸው። *”ለጌታዬ”* אדֹנִ֗י ለዔሳው። ባሪያህ ያዕቆብ እንዲህ አለ፦ ብላችሁ ንገሩት።
ዘኊልቅ 11:28 ከልጅነቱ ጀምሮ የሙሴ አገልጋይ የነበረው የነዌ ልጅ ኢያሱ። *”ጌታዬ”* אדֹנִ֗י ሙሴ ሆይ፥ ከልክላቸው አለው።
1ሳሙኤል 24:8፤ ከእርሱም በኋላ ዳዊት ደግሞ ተነሣ፥ ከዋሻውም ወጣ፥ ከሳኦልም በኋላ። *”ጌታዬ”* אדֹנִ֗י ንጉሥ ሆይ፥ ብሎ ጮኸ፤
ዳንኤል 4:24፤ *”በጌታዬ”* אדֹנִ֗י በንጉሥ ላይ የወረደው የልዑሉ ትእዛዝ ነው፤

በዕብራይስጡ አዲስ ኪዳን ላይ ኢየሱስን ኤልሳቤጥ እና ዳዊት አዶኒ እንጂ አዶናይ በፍጹም አላሉትም፦
ሉቃስ 1፥43
וּמֵאַיִן בָּאַתְנִי כָזֹאת כִּי־אֵם אֲדֹנִי אֶלַי תָּבֹא׃
የሐዋርያት ሥራ 2፥34
כִּי דָוִד לֹא עָלָה הַשָּׁמָיְמָה וְהוּא בְּפִיו אָמַר נְאֻם יְהוָֹה לַאדֹנִי שֵׁב לִימִינִי

በዚሁ በሐዋርያት ሥራ ላይ “ጌታ” የተባለው የሚመለከውን አብን ለመግለጥ “የ-ሐ-ዋ-ሐ” የሚል ቴትራ ግራማተን ይጠቀማል፦
የሐዋርያት ሥራ 13፥2
בעבוֹדָתָם אֶת־יְהוָֹה וּבְצוֹמָם הָיָה דְבַר רוּחַ הַקֹּדֶשׁ הַבְדִּילוּ־נָא לִי אֶת־בַּר־נַבָּא וְאֶת־שָׁאוּל לַעֲשׂוֹת בַּמְּלָאכָה אֲשֶׁר קְרָאתִים לָהּ
በግሪኩ አዲስ ኪዳን ለኢየሱስ “ኩርዮስ” የተባለው “አዶኒ” የሚለውን ማዕረግ ለማሳየት እንጂ ያህዌህ ወይም አዶናይ የሚለውን ለማሳየት አይደለም፤ ስለዚህ የኢየሱስ ጌትነት የፍጡር ማእረግ ብቻ ነው። ምክንያቱም እዛው “ጌታ ጌታዬን” በተባለበት ዐውድ ላይ እግዚአብሔር ኢየሱስን ጌታ አደረገው ስለሚል፦
የሐዋርያት ሥራ 2፥36 አለ። እንግዲህ ይህን እናንተ የሰቀላችሁትን *ኢየሱስን እግዚአብሔር ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው* የእስራኤል ወገን ሁሉ በእርግጥ ይወቅ።

መቼም አንድ ጤነኛ የሆነ ሰው ፈጣሪን ፈጣሪ ጌታ አደረገው ብሎ እንደማይቀበል እሙን ነው፤ ይስሐቅ ያዕቆብን ጌታ አደረግሁት ይላል፦
ዘፍጥረት 27፥37 ይስሐቅም መለሰ ዔሳውንም አለው። እነሆ፥ *ጌታህ አደረግሁት*፥ ወንድሞቹንም ሁሉ ለእርሱ ተገዦች ይሆኑ ዘንድ ሰጠሁት፥

ይህም ስልጣንና ሹመትን አሊያም እልቅናና ክብርን ያመለክታል፤ ዮሴፍ፦ “እግዚአብሔር ጌታ አደረገኝ” ይላል፦
ዘፍጥረት 45፥9 *እግዚአብሔር በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ ጌታ አደረገኝ*፤ ወደ እኔ ና፥ አትዘግይ፤

ኢየሱስ ጌታ ተደረገ ሲባል ያዕቆብ ጌታ ተደረገ ዮሴፍ ጌታ ተደረገ በተባለበት ሒሳብ እንጂ የዓለማቱ ጌታ የሚለውን አያመለክትም፤ ይህም በራሡ የተብቃቃ አሊያም የባህርይ ገንዘቡ ሣይሆን በስጦታ ያገኘው ነው። አዶናይ የሁሉ ጌታ የሆነው አንድ አምላክ ነው። እርሱ አላህ “የሁሉ ጌታ” ሲሆን ከአላህ በቀር ”ሌላን ጌታ” እፈልጋለሁን? በፍጹም! ከዓለማቱ ጌታ ከአላህ በቀር ሌላ የዓለማት ጌታ የለም፦
6፥164 በላቸው *«እርሱ አላህ “የሁሉ ጌታ” ሲሆን ከአላህ በቀር ”ሌላን ጌታ” እፈልጋለሁን?”* ነፍስም ሁሉ በራሷ ላይ እንጅ ክፉን አትሠራም፡፡ قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْءٍۢ ۚ وَلَا تَكْسِبُ كُلُّ نَفْسٍ إِلَّا عَلَيْهَا

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሁለተኛው አጽናኝ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

61፥6 የመርየም ልጅ ዒሳም፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! እኔ ከተውራት በፊቴ ያለውን የማረጋግጥ እና *”ከእኔ በኋላ በሚመጣው መልክተኛ ስሙ አሕመድ በኾነው የማበስር”* ስኾን ወደ እናንተ የተላክሁ የአላህ መልክተኛ ነኝ» ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ በግልጽ ተዓምራቶች በመጣቸውም ጊዜ «ይህ ግልጽ ድግምት ነው» አሉ፡፡

መግቢያ
የመጽሐፉም ባለቤቶች ክርስቲያኖች እና አይሁዳውያን ከአላህ የወረደውን እውነት ከሰው ንግግር ቃል ቀላቅለዋል፤ በተጨማሪም ከአላህ የወረደውን እውነት ደብቀዋል፦
3፥71 የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! እውነቱን በውሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ *”እውነቱንም እናንተ የምታውቁ ስትኾኑ ለምን ትደብቃላችሁ”*?፤

በ 397 AD የተደረገው የካርቴጅ ጉባኤ ብዙ የወንጌል ቅሪት አፓክራፋ ብሎ ቀንሷል፤ “አፓክራፋ” ማለት “አፓክራፎስ” ἀπόκρυφος ከሚለው የግሪክ ቃል የተገኘ ሲሆን “ድብቅ” “ስውር” ማለት ነው፦
5፥15 የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! *”ከመጽሐፉ ትሸሽጉት ከነበራችሁት ነገር ብዙውን ለእናንተ የሚገልጽ ከብዙውም የሚተው”* ሲኾን መልክተኛችን በእርግጥ መጣላችሁ፡፡ ከአላህ ዘንድ ብርሃንና ገላጭ መጽሐፍ በእርግጥ መጣላችሁ፡፡
2፥146 እነዚያ መጽሐፍን የሰጠናቸው ወንዶች ልጆቻቸውን እንደሚያውቁ ያውቁታል፡፡ ከእነሱም የተለዩ ክፍሎች እነርሱ የሚያወቁ ሲኾኑ *”እውነቱን በእርግጥ ይደብቃሉ”* ፡፡

ከተደበቁት ዋናው አጀንዳ ወንዶች ልጆቻቸውን እንደሚያውቁ የምስራቹን የምስራች ያሰኘው ኢየሱስ ስለ ነብያችን”ﷺ” መምጣት ያበሰረውን የሚያወቁ ሲኾኑ ይህንን እውነቱን በእርግጥ ይደብቃሉ፤ አላህ ኢንጅል የሚለው ስለ ነብያችን”ﷺ” መምጣት የሚተነብየውን ወንጌል እንደሆነ ቅቡልና እሙን ነው፦
61፥6 የመርየም ልጅ ዒሳም፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! እኔ ከተውራት በፊቴ ያለውን የማረጋግጥ እና *”ከእኔ በኋላ በሚመጣው መልክተኛ ስሙ አሕመድ በኾነው የማበስር”* ስኾን ወደ እናንተ የተላክሁ የአላህ መልክተኛ ነኝ» ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ በግልጽ ተዓምራቶች በመጣቸውም ጊዜ «ይህ ግልጽ ድግምት ነው» አሉ፡፡

“ከእኔ በኋላ በሚመጣው መልክተኛ ስሙ አሕመድ በኾነው የማበስር ስኾን ወደ እናንተ የተላክሁ የአላህ መልክተኛ ነኝ”
ይህ ቃል በአራቱ ወንጌላት የለም ማለት ኢየሱስ አልተናገረውም ማለት አይደለም፤ ምክንያቱንም ኢየሱስ ተናግሮ በአራቱ ወንጌል ላይ ያልሰፈሩ ሃረጎች ስላሉ፤ ለምሳሌ፦
1ኛ ዮሐንስ 1፥5 ከእርሱ የሰማናት ለእናንተም የምናወራላችሁ መልእክት። *”እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም”* የምትል ይህች ናት።

ኢየሱስ፦ “”እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም”” ብሎ ተናግሮ ነበር፤ ዮሐንስም፦ “ከእርሱ(ከኢየሱስ) የሰማናት ለእናንተም የምናወራላችሁ መልእክት ይህች ናት” ብሎናል፤ ግን ይህ ከኢየሱስ የሰሙት መልእክት በአራቱ ወንጌላት የለም ማለት ኢየሱስ አልተናገረውም ማለት አይደለም፤ በተጨማሪ በተመሳሳይ መልኩ ኢየሱስ፦ “ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው” ብሎ ተናግሮ ነበር፤ ይህ ቃል አራቱ ወንጌል ላይ የለም፦
የሐዋርያት ሥራ 20:35 እንዲሁ እየደከማችሁ ድውዮችን ልትረዱና እርሱ ራሱ። *”ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው”* እንዳለ የጌታን የኢየሱስን ቃል ልታስቡ ይገባችሁ ዘንድ በሁሉ አሳየኋችሁ።

ይህንን በወፍ በረር ለመግቢያ ያክል ካየን በአራቱ ወንጌላት ቅሪት ላይም ስለ ነብያችን”ﷺ” መምጣት ኢየሱስ ትንቢት ተናግሮ እንደነበር በሰከነና በሰላ መረዳት እስቲ እናስተንትን፦
ዮሐንስ 14:15-16 ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ “አጽናኝ” Παράκλητον ይሰጣችኋል፤”

ነጥብ አንድ
“አጽናኝ”
“አጽናኝ” ተብሎ የተቀመጠው የግሪኩ ቃል “ፓራቅሊጦስ” Παράκλητον ሲሆን ኢየሱስ “ሌላ” ማለቱ “ተጨማሪ” ማለቱ ነው፤ ለምሳሌ “ሌላ አስተማሪ” ይመጣል ብል፤ ሌላው ሁለተኛ አስተማሪ ከመምጣቱ በፊት ፊተኛ አስተማሪ እንዳለ ያመለክታል፤ በተመሳሳይ “ሌላ አጽናኝ” የሚለው ቃል ፊተኛው አጽናኝ እንዳለ ያሳያል፤ ታዲያ የመጀመሪያው አጽናኝ ማን ነው? ስንል መልሱ ኢየሱስ ነው፦
1ኛ ዮሐንስ 2:1 ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ “አጽናኝ” παράκλητον አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

ኢየሱስ መንፈስ ቅዱስ በ 33 AD ከወረደ ከ 57 አመት በኋላ በ 90 AD አጽናኝ ተብሏል፣ አያችሁ እስከ 90 AD ድረስ ኢየሱስ አጽናኝ እንደነበረ ካየን እስከ 90 AD ጊዜ ድረስ ሌላው አጽናኝ አልመጣም ማለት ነው፤ ግን እውን ኢየሱስ ግሪክ ተናጋሪ ነበርን? አይ አረማይክ ተናጋሪ ነበር ይሉናል፤ ታዲያ “ሌላ አጽናኝ” ይሰጣችኋል” ነው ያለው ወይስ “ሌላ ነብይ” ይሰጣችኋል” ነው ያለው? ይህ የደበቁት እውነት እንገልጠዋለን፦
የሐዋርያት ሥራ 4:36 ትውልዱም የቆጵሮስ ሰው የነበረ አንድ ሌዋዊ ዮሴፍ የሚሉት ነበረ፥ እርሱም በሐዋርያት “በርናባስ” ተባለ ትርጓሜውም *የመጽናናት ልጅ* ነው፤

ልብ አድርጉ “በርናባስ” בר נביא የአረማይክ ቃል ነው፤ የሁለት ቃላት ውቅር ነው፤ “ባር-ነቢያ” בר נביא ሲሆን “የነብይ ልጅ” ማለት ነው፤ “ባር” בר ማለት “ልጅ” ማለት ሲሆን “ነብያ” נביא ማለት ደግሞ “ነብይ” ማለት ነው፤ ግን ግሪኩ ላይ ሲተረጎም “ሃይኦ ፓራክሌቶስ” υἱός παρακλήσεως ማለትም “የመጽናናት ወይም የአጽናኝ ልጅ” አሉት፤ ይህንን ያነሳሁበት ቃሉ እየለወጡ እንዴት እውነቱን እንደሚደብቁ ለማሳየት ነው፤ ስለዚህ “ፓራቅሊጦስ” Παράκλητον ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ነብያ” נביא ማለት ከሆነ ኢየሱስ በአረማይክ “ሌላ ነብይ ይሰጣችኋል” ብሎ ነው የተናገረው ማለት ነው፤ ይህ ነብይ ማን ነው? ምሁራን፦ “አንድ አፅናኝ የሚያፅናናው በትንቢት ነው” ይሉናል፦
1ኛ ቆሮንቶስ 14:3 *”ትንቢት”* የሚናገር ግን ለማነጽና ለመምከር *”ለማጽናናትም”* ለሰው “ይናገራል።”

አዎ የሚመጣው ነብይ ግን ልክ እንደ ኢየሱስ ከላከው እየሰማ መጪውን ክስተት የሚናገር እንጂ ከራሱ ምንም አይናገርም፦
ዮሐንስ 16:13 እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ *”የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል”* እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ *የሚመጣውንም ይነግራችኋል*።”

መቼም ሁለተኛ ነብይ መንፈስ ቅዱስ ነው ካላችሁን እስቲ መንፈስ ቅዱስ ከኢየሱስ በተለየ መልኩ አዲስ ያስተማረው ትምህርቱ የት ይገኛል?
ነጥብ ሁለት
“ሌላ”
“ሌላ” የሚለው ገላጭ ደግሞ “አሎን” ἄλλον ነው፣ “አሎን” ተመሳሳይ ባህርይ ያለውን ምንነት ለማመልከት የሚውል ገላጭ ነው፣ ለምሳሌ፦
ማቴዎስ 5:39 ቀኝ ጉንጭህን በጥፊ ለሚመታህ ሁሉ *ሌላውን* ἄλλην ደግሞ አዙርለት፤

ቀኝ ጉንጭ ከግራ ጉንጭ እንደሚመሳሰል ሁሉ ሁለተኛ አጽናኝም ከመጀመሪያ አጽናኝ ጋር ይመሳሰላል፣ ሁለተኛ አጽናኝ ምን እንደሆነና ማን እንደሆነ ለመረዳት የመጀመሪያውን አጽናኝ በቅጡ መረዳት ግድ ይላል፦
@የመጀመሪያው አጽናኝ ከላከው ሰምቶ የሚናገር ሰው ነው፦
ዮሐንስ 8:40 ነገር ግን አሁን ከእግዚእብሔር የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን *”ሰው”* ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ፤

@የመጀመሪያው አጽናኝ ፈጣሪ ያናገረው ነብይ ነው፦
ማርቆስ 6:4 ኢየሱስም። *”ነቢይ”* ከገዛ አገሩና ከገዛ ዘመዶቹ ከገዛ ቤቱም በቀር ሳይከበር አይቀርም አላቸው።

@የመጀመሪያው አጽናኝ ከላከው መልእክት የተቀበለ መልዕተኛ ነው፦
ዮሐንስ 8:26 ዳሩ ግን *”የላከኝ እውነተኛ ነው እኔም ከእርሱ የሰማሁትን ይህን ለዓለም እናገራለሁ”* አላቸው።
ዮሐንስ 12:49 እኔ *”ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ”*።

ሹፍ እንግዲህ የመጀመሪያው አጽናኝ ከፈጣሪ ሰምቶ የሚናገር ሰው፣ ነብይ፣ መልዕተኛና ትእዛዝን የተቀበለ ነው እንጂ ከራሱ የሚናገር አይደለም፣ ሁለተኛውም አጽናኝ ከፈጣሪ ሰምቶ የሚናገር እንጂ ከራሱ የሚናገር አይደለም፦
ዮሐንስ 16፥12-15 የምነግራችሁ ገና ብዙ አለኝ፥ ነገር ግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም። ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል። እርሱ ያከብረኛል፥ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋልና። ለአብ ያለው ሁሉ የእኔ ነው፤ ስለዚህ፦ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋል አልሁ።

ሁለተኛው አጽናኝ ኢየሱስ ያልተናገራቸውንና ኢየሱስ ተናግሮ ያስተማራቸውን የአምላክ አንድነት ትምህርት ከፈጣሪ ሰምቶ የሚያስተላልፍ እራሱን የቻለ ቅዋሜ-ማንነት ያለው ነው፣ ይህንን ለማሳየት *ከራሱ* himself” የሚለው ድርብ ተውላጠ-ስም”Reflexive pronoun” ይጠቀማል፤ ኢየሱስም ለራሱ ሲጠቀም *ከራሴ* my self” የሚለውን አጠቃቀም ያመሳስለዋል፣ ይህም የመጀመሪያው አጽናኝ ሰው፣ ነብይ፣ መልዕተኛ ሆኖ ከፈጣሪ ሰምቶ የሚያስተላልፍ ከሆነ ሁለተኛውም አጽናኝ በተመሳሳይ መልኩ ከፈጣሪ ሰምቶ የሚያስተላልፍ ሰው፣ ነብይ እና መልዕተኛ ነው። ከዚህ ነብይ በኃላ ሌላ ነብይ ስለማይመጣ ለዘላለም ከእኛ ጋር በነብይነቱ ይኖራል፤ ክርስቲያኖች ይህንን ሁለተኛ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ ነው ሲሉ ከአውዱ ጋር ይጣላሉ፦
ዮሐንስ 16፤7 እኔ ግን እውነት እነግራችኋለሁ፤ እኔ እንድሄድ ይሻላችኋል። *”እኔ ባልሄድ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣምና”*፤

ሁለተኛው አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ እንዳልሆነ ጥልልና ጥንፍፍ ባለ መልኩ መረዳ ግድ ይላል፣ ኢየሱስ ስለ ሁለተኛው አጽናኝ የተናገረው ከማረጉ ማለትም ወደ ፈጣሪ ሳይሄድ ነው፣ ታዲያ ኢየሱስ ሳያርግ ሁለተኛው አጽናኝ እንደማይመጣ ተናግሮ እያለ ከማረጉ በፊትና ስለ ሁለተኛው አጽናኝ ከተናገረ በኋላ መንፈስ ቅዱስ መጥቷል፦
ዮሐንስ 20:22 ይህንም ብሎ እፍ አለባቸውና። መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።

ሁለተኛው አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ ነው የሚለውን ብዥታ በህዝብ ላይ የጣሉት ሰዎች ናቸው፦
ዮሐንስ 14:26 አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።

መንፈስ ቅዱስ የሆነው የሚለው ቃል በፓፒረስ 75 ላይ፣ በፓፒረስ 22 ላይ፣ በፓፒረስ 52 ላይ፣ በፓፒረስ 90 ላይና ቤአፍሬማይ እደ-ክታብ”manuscript” ላይ የሉም፣ በተለይ በ 107-130 AD በተዘጋጁ ፓፒረሶች ላይ *መንፈስ ቅዱስ የሆነው* የሚለው ቃል አለመኖሩና ከዛ በኋላ ባሉት ላይ የመጨመሩ ጉዳይ የብርዘት ውጤቶች ናቸው፤ የመጀመሪያ መቶ ክፍለ-ዘመን የኢየሱስ ተከታዮች የሚባሉት የዮሐንስ ማህበረሰብ ሁለተኛው አጽናኝ ነብይ ነው ብለው ይጠብቁ ነበር፤ ነገር ግን ይህን እሳቤ ወደ መንፈስ ቅዱስ ያሸጋገሩት ሰዎች ናቸው፣ በዚህ ጥናት ዙርያ ዋቢ መጽሐፍትን ይመልከቱ፦
1. Cambridge History of Christianity, 6: Johannine Christianity, 2006
2. The Early Christian Community: From Diversity to Unity to Orthodoxy, lecture delivered February 25, 2000
3. Bart D Ehrman, 2002. Lost Christianities: Christian Scriptures and the Battles over Authentication.

መደምደሚያ
የመጽሐፉም ባለቤቶች ክርስቲያኖች እና አይሁዳውያን በነብያችን”ﷺ” በአመኑ እና ከክህደትም በተጠነቀቁ ኖሮ ከእነርሱ ኃጢኣቶቻቸውን በእርግጥ በታበሰ እና የመጠቀሚያ ገነቶችንም በእርግጥ በገቡ ነበር፤ ተውራትን እና ኢንጂልን ከጌታቸውም ወደ እነርሱ የተወረደውን የደበቁትን ባቋቋሙ ኖሮ ከበላያቸውና ከእግሮቻቸው ሥር በተመገቡ ነበር፦
5፥65 የመጽሐፉም ባለቤቶች *”በአመኑ እና ከክህደትም በተጠነቀቁ ኖሮ ከእነርሱ ኃጢኣቶቻቸውን በእርግጥ ባበስንና የመጠቀሚያ ገነቶችንም በእርግጥ ባገባናቸው ነበር”*፡፡
5፥66 እነርሱም *”ተውራትን እና ኢንጂልን ከጌታቸውም ወደ እነርሱ የተወረደውን ባቋቋሙ”* ኖሮ ከበላያቸውና ከእግሮቻቸው ሥር በተመገቡ ነበር፡፡ *”ከእነርሱ ውስጥ ትክክለኞች ሕዝቦች አልሉ፡፡ ከእነርሱም ብዙዎቹ የሚሠሩት ነገር ከፋ”*!

ከእነርሱ ውስጥ ይህን እውነትን ተቀብለው የሚሰልሙ ትክክለኞች ሕዝቦች አሉ፤ ነገር ግን ከእነርሱም ብዙዎቹ እውነትን በመደበቅ የሚሠሩት ነገር ከፋ፤ ስለ ነብያችን”ﷺ” መምጣት የሚተነብይ ከጌታቸውም ወደ እነርሱ የተወረደውን ተውራትን እና ኢንጂልን ውስጥ የነበረውን እውነት እያወቁ ደብቀውታል፦
7፥157 ለእነዚያ ያንን እነርሱ ዘንድ *”በተውራትና በኢንጂል ተጽፎ የሚያገኙትን የማይጽፍና የማያነብ ነቢይ”* የኾነውን መልክተኛ የሚከተሉ ለኾኑት በእርግጥ እጽፍለታለሁ፡፡

ፊዳከ አቢ ወኡሚ ያ ረሱሉሏህ!

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
አሥ-ሠላሙ ዐለይኩም ያ ጀመዓህ!

"ቁርኣን አይጋጭም" የሚለው የወንድም ወሒድ ዑመር መጽሐፍ በገበያ ላይ ውሏል።
በአት-ተውባህ የመጽሐፍት መደብር፣
በአን-ነጃሺይ የመጽሐፍት መደብር፤
በአቅሷ የመጽሐፍት መደብር ያገኙታል።
የበለጠ መረጃ ለማግኘት ዐብዱ አር-ራሕማን 0920781016 ብለው ይደውሉ!
ከቁርኣን አይጋጭ መቅድም የተወሰደ!

ኢሥላምን የሕይወቴ መርሕ አርጌ ከመያዜ በፊት በክርስትና ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ጥናት በጀመርኩበት ጊዜ ወደ ሃይማኖት ንጽጽር ውስጥ ገባሁኝ። ሙሥሊሞች ባይብል ላይ ከሚያነሱት ጥያቄ የተነሳ እከክልኝ ልከክልህ በሚል መርሕ ቁርኣንን ማጥናት ጀመርኩኝ፥ ያ አልበቃ ብሎኝ ሐዲስን፣ ሲራን፣ ተፍሢሪን ማንበብ ጀመርኩኝ። አላማዬና ኢላማዬ ግን ለመሥለም ሳይሆን ቁርኣንን ለማብጠልጠል፣ ለማነወር፣ ለመተቸት ነበር። ነገር ግን ቁርኣንን በማጠናበት ጊዜ የቁርኣን ተናጋሪ እንደ ባይብሉ ሰዎች ሳይሆን የዓለማቱ ጌታ አላህ መሆኑ አስደነገጠኝ፥ ቁርኣንን የማስበው የአንድ ግመል ገፊ ሰው ድርሰት እንጂ የዓለማቱ ጌታ በመልአኩ ለነቢዩ ያወረደው ወሕይ ነው" ብዬ በእውኔ ሆነ በሕልሜ አስቤው ዐላውቅም።

በመቀጠል ክርስትና ከእሥልምና ጋር ያለውን ሥነ-መለኮታዊ ልዩነት ማጥናት ጀመርኩኝ፥ አምላካችን አላህ በአንድ ምንነቱ ላይ ሁሉት ወይም ሦስት ማንነት የሌለበት፣ በአምላክነቱ ላይ ሰውነት የሌለበት፣ በጌትነቱ ላይ ባርነት የሌለበት፣ በሕያውነቱ ላይ ሞት የሌለበት፣ በጥበቃው ላይ እንቅልፍ የሌለበት፣ በኀያልነቱ ላይ ድካም የሌለበት፣ በፈጣሪነቱ ፍጡርነት የሌለበት መሆኑን እና መከፋፈል፣ ሰው መሆን፣ ባሪያ መሆን፣ መሞት፣ ማንቀላፋት፣ መድከም፣ መፈጠር የፍጡር ባሕርይ መሆኑን ደረስኩበት።
ክርስትና የሚጣራው ሦስት ማንነቶችን ማለትም ሥላሴን እንድናመልክ ነው። ግን መመለክ ያለበት አንድ ማንነት ብቻ ነው።
ክርስትና የሚጣራው ሰው እንድናመልክ፣ ኢየሱስ ሰውነቱ ይመለካል፣ በሰውነቱ ፍጡር ነው ይላሉና።ግን መመለክ ያለበት አንድ ፈጣሪ ብቻ ነው።
ክርስትና የሚጣራው ፍጡራንን በሌሉበት ወደ እነርሱ መጎባደድ፣ መተናነስ፣ ማሸርገድ፣ መለማመን፣ መጸለይ፣ ስለት መሳል፣ መስዋዕት ማቅረብ፣ ስማቸውን መጥራት ነው። ሁሉን የሚሰማ፣ የሚያይ፣ የሚያውቅ አንድ መለኮት ብቻ ሆኖ ሳለ ወደ መላእክትና ቅዱሳን ይህንን ማድረግ ሺርክ ነው።
ክርስትና የሚጣራው ለተቀረጸ ምስል እንድንሰግድ ነው። ለተቀረጸ ምስል አትስገድ ተብሎ ነገር ግን በተቃራኒው ከእንጨት፣ ከብር፣ ከወርቅ፣ ከብረት፣ ከድንጋይ ለተቀረጹ መስቀል፣ ስዕል እና ሃውልት ይሰግዳሉ። ይህም ሺክር ነው።
ይህንን የኢሥላም ሥነ-መለኮት ልዋጋ መጥቼ በቁርኣን ተማርኬ ከቀረሁኝ አሁን ሰባት ዓመት ሞላኝ። ወደ ዲኑል ኢሥላም ከመጣሁኝ በኃላ በኢሥላም ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች መልስ በመስጠት ላይ እገኛለሁኝ። ከዚህ ጎን ለጎን ኢሥልምና ዱር ሙሥሊሙ ሐሩር እንዲሆን ቀን ከሌሊት ደፋ ቀና፥ ጠብ እርግፍ የሚሉት አግድም አደግ ዕውቀት ያላቸው ሚሽነሪዎች ደግሞ፦ "ቁርኣን እርስ በእርሱ ይጋጫል" በማለት ስሑት ሙግት አላቸው። እኔ ደግሞ ቁርኣን ምንም አይጋጭም ብዬ ስሙር ሙግት አቅሬቤአለሁኝ፥ መልካም ንባብ ይሁንልዎ!

ወሒድ ዑመር
አሥ-ሠላሙ ዐለይኩም ያ ጀመዓህ!

በአገር ውስጥ ያለው የዘር ፓለቲካ ይዞ የመጣ ፈሣድ እየተቀጣጠለ ስለሆነ ከስሜታዊነት ወጥተን ለሊሏሂ ብለን ፍትኃዊ እንሁን! በዘር ፓለቲካ እርስ በእርስ መሰዳድብ፣ መነቋቆር እና መዘራረጥ ዲናዊ አይደለም። ጥቂት የዘር ፓለቲካ አንቀንቃኞች ብዙኃኑ ላይ ፕሮፓጋንዳ በመቅረፅ እና በማስረፅ እያፋጁት ይገኛሉ። አሏህ በዟሊሚን ላይ ቁጣውን ያውርድባቸው! አሚን።