ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
59.2K subscribers
68 photos
70 videos
19 files
1.73K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
ዐቅመ-ጋብቻ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

65፥4 *"እነዚያም ከሴቶቻቸው ከዐደፍ ያቋረጡት በዒዳቸው ሕግ ብትጠራጠሩ ዒዳቸው ሦስት ወር ነው፡፡ እነዚያም ገና ዐደፍ ያላዩት ዒዳቸው እንደዚሁ ነው፡፡ የእርግዝና ባለቤቶችም ጊዜያቸው እርጉዛቸውን መውለድ ነው"*፡፡ وَاللَّائِي يَئِسْنَ مِنَ الْمَحِيضِ مِن نِّسَائِكُمْ إِنِ ارْتَبْتُمْ فَعِدَّتُهُنَّ ثَلَاثَةُ أَشْهُرٍ وَاللَّائِي لَمْ يَحِضْنَ ۚ وَأُولَاتُ الْأَحْمَالِ أَجَلُهُنَّ أَن يَضَعْنَ حَمْلَهُنَّ

"ዐቅመ-ጋብቻ" ማለት አንድ ተባእት ለዐቅመ-አደም ሲደርስ እና አንዲት እንስት ለዐቅመ-ሐዋህ ስትደርስ ማለት ነው። ለምሳሌ “የቲም” يَتِيم ስንል አጠቃላይ “ወላጅ-አልባ” ማለትም “እናትና አባቱ” ወይም “አባቱን በልጅነቱ በሞት የተነጠቀ ሕፃን” ማለት ነው። የቲሞች እራሳቸው ይችሉ ወይም አይችሉ እንደሆነ ይፈተናሉ፥ ይህም ፈተና ለጋብቻ እስከሚደርሱበት ድረስ ነው፦
4፥6 *"የቲሞችንም ጋብቻን እስከደረሱ ጊዜ ድረስ ፈትኑዋቸው"*፡፡ وَابْتَلُوا الْيَتَامَىٰ حَتَّىٰ إِذَا بَلَغُوا النِّكَاحَ

"ኢዛ" إِذَا ማለት "ጊዜ" ማለት ሲሆን የጊዜ ተውሳከ-ግስ ነው። ጋብቻ የራሱ የሆነ ጊዜ እንዳለው አመላካች ነው፥ ይህም ጊዜ ለማመልከት "ጋብቻን እስከደረሱ" ድረስ በማለት ይናገራል። "በለጉ" بَلَغُوا ማለት "ለጋብቻ በሰሉ" ማለት ነው፥ "በለገ" بَلَغَ ማለት "ለጋብቻ በሰለ" ማለት ሲሆን "በለገት" بَلَغَت ማለት ደግሞ "ለጋብቻ በሰለች" ማለት ነው። "ባሊግ" بَٰلِغ ማለት እራሱ "ዐቅመ-ጋብቻ"Puberty" ማለት ነው፦
ተፍሢሩል ኢብኑ ከሲር 4፥6
*"ጋብቻን እስከደረሱ ጊዜ" የሚለውን ሙጃሂድ፦ "ለዐቅመ-ጋብቻ ነው" ብሏል፥ ዐበይት ምሁራን፦ "ለዐቅመ-ጋብቻ" ለጋዎች ኢሕቲላም ሲኖራቸው ነው" ብለዋል። አቢ ዳውድ በሡናው እንደዘገበው፥ ዐሊይ ኢብኑ አቢ ጧሊብ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአላህ መልዕክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ከዐቅመ-ጋብቻ በኃላ የቲምነት የለም"*።
( حتى إذا بلغوا النكاح ) قال مجاهد : يعني : الحلم . قال الجمهور من العلماء : البلوغ في الغلام تارة يكون بالحلم ، وهو أن يرى في منامه ما ينزل به الماء الدافق الذي يكون منه الولد . وقد روى أبو داود في سننه عن أمير المؤمنين علي بن أبي طالب ، رضي الله عنه ، قال : حفظت من رسول الله صلى الله عليه وسلم : " لا يتم بعد احتلام
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 18, ሐዲስ 12
ዐሊይ ኢብኑ አቢ ጧሊብ እንደተረከው፦ "የአላህ መልዕክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *"ከዐቅመ-ጋብቻ በኃላ የቲምነት የለም"*። قَالَ عَلِيُّ بْنُ أَبِي طَالِبٍ حَفِظْتُ عَنْ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ لاَ يُتْمَ بَعْدَ احْتِلاَمٍ

"ዐቅመ-ጋብቻ" አካል ተራክቦ ለማድረግ ሲበስል ነው፥ ከዐቅመ-ጋብቻ በኃላ የቲምነት ስለሌለ የቲሞች እራሳቸው እንዲችሉ ይፈተናሉ። "ኢሕቲላም" احْتِلاَم ማለት አንድ ልጅ ወይም አንዲት ልጂት ተራክቦ ለማድረግ የሚኖራቸው ፈሳሽ ነው። ይህ ፈሳሽ እስኪመጣ ድረስ ለዐቅመ-ጋብቻ ስላልደረሱ የሚሠሩት ሥራ አይመዘገብም፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 40, ሐዲስ 48
ዓኢሻህ "ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአላህ መልዕክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *"ብዕር ከሦስት ሰዎች ተነስቷል። እነርሱም፦ የተኛ ሰው እስኪነሳ ድረስ፣ ዕብደ ወደ ዐቅሉ እስኪመለስ ድረስ፣ ልጅ እስኪጎሎብት ድረስ"*። عَنْ عَائِشَةَ، رضى الله عنها أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ رُفِعَ الْقَلَمُ عَنْ ثَلاَثَةٍ عَنِ النَّائِمِ حَتَّى يَسْتَيْقِظَ وَعَنِ الْمُبْتَلَى حَتَّى يَبْرَأَ وَعَنِ الصَّبِيِّ حَتَّى يَكْبَرَ ‏
በእንቅልፍ ልብ፣ በዕብደት እና በእንጭጭነት የሚደረግ ሥራ መላእክት አይመዘግቡትም። አንድ ሕጻን ለዐቅመ-አደም ከደረሰ የሰው ቤት ዘው ብሎ አይገባም፥ ከዚያ ይልቅ አንኳክቶ ያስፈቅዳል፦
24፥59 *"ከእናንተም ሕፃናቶቹ አቅመ አዳምን በደረሱ ጊዜ እነዚያ ከእነርሱ በፊት የነበሩት እንዳስፈቀዱ ያስፈቅዱ"*፡፡ وَإِذَا بَلَغَ الْأَطْفَالُ مِنكُمُ الْحُلُمَ فَلْيَسْتَأْذِنُوا كَمَا اسْتَأْذَنَ الَّذِينَ مِن قَبْلِهِمْ

አሁን እዚህ አንቀጽ ላይ "ኢዛ" إِذَا የሚለው የጊዜ ተውሳከ-ግስ የዐቅመ-ጋብቻ ጊዜ አመላካች ነው፥ ይህንን ዐቅመ-ጋብቻ ለማመልከት "በለገ" بَلَغَ የሚል የግስ መደብ ይጠቀማል። አንዲት እንስት ለዐቅመ-ሐዋህ የመድረሷ የመጀመሪያው እና ዐቢይ ምልክት አድሬን-አርክ"adrenarche" አካሏ ለተራክቦ ዝግጁ ሲሆን እንዲሁ ጡቷ ሲያጎጠጉጥ ቴል-አርክ"thelarche" እና ብብቷና ብልቷ አካባቢ ጸጉር መብቀል ፑብ-አርክ"Pubarche" ሲጀምር የምታመነጨው ፈሳሽ"Vaginal lubrication" እንጂ የወር አበባ አይደለም፥ የወር አበባ ማየት አንዲት ሴት ለዐቅመ-ሐዋህ መድረሷን ከሚያሳዩ ሁለተኛ እና ንዑስ ምልክት ዕንቁላል ማምረት ጎናድ-አርክ"gonadarche" እንዲሁ የወር አበባ ደም ሜን-አርክ"menarche" ነው። አንዲት ሴት ስታርጥ የወር አበባ ይቋረጣል፥ ያኔ የምታመነጨው ፈሳሽ ያለ የወር አበባ ተራክቦ ማድረግ ትችላለች። ምክንያቱም ተራክቦ ለማድረግ የወር አበባ ብቻውን መስፈት አይደለም፥ የወር አበባ ለፅንስ እንጂ ለተራክቦ መስፈት አይደለም፦
65፥4 *"እነዚያም ከሴቶቻቸው ከዐደፍ ያቋረጡት በዒዳቸው ሕግ ብትጠራጠሩ ዒዳቸው ሦስት ወር ነው፡፡ እነዚያም ገና ዐደፍ ያላዩት ዒዳቸው እንደዚሁ ነው፡፡ የእርግዝና ባለቤቶችም ጊዜያቸው እርጉዛቸውን መውለድ ነው"*፡፡ وَاللَّائِي يَئِسْنَ مِنَ الْمَحِيضِ مِن نِّسَائِكُمْ إِنِ ارْتَبْتُمْ فَعِدَّتُهُنَّ ثَلَاثَةُ أَشْهُرٍ وَاللَّائِي لَمْ يَحِضْنَ ۚ وَأُولَاتُ الْأَحْمَالِ أَجَلُهُنَّ أَن يَضَعْنَ حَمْلَهُنَّ

“ዒዳህ” عِدَّة ማለት ሁለት ጥንዶች ከተጋቡ በኃላ ተራክቦ አድርገው ከዚያም አለመግባባት ቢፈጠር ፍቺ ለማድረግ ቢያስቡ ቅድሚያ ነፍሰ-ጡር መሆኗን ለማረጋገጥ የሚቆይበት የሦስት ወር ጊዜ ቆይታ ነው። "ዐደፍ" ለሚለው የገባው ቃል "መሒድ" مَحِيض ሲሆን "የወር አበባ" ማለት ነው። አንድ ወንድ ከዐደፍ ያቋረጠች ማለትም ያረጠች ሴት ለመፍታት ምናልባት አርጣለች ተብሎ እግዝና ስለሚከሰት የሦስት ወር ጊዜ ይኖራታል። አንዲት ሴት ልጅ ለዐቅመ-ሐዋህ ስደርስ ግንኙነትን ሲታሰብ ወይም ሲፈለግ የሚወጣ ያዝ የሚያደርግና የሚያጣብቅ ቀለም አልባ እና ሽታ አልባ ቀጭን ፈሳሽ"nocturnal emission" አላት፥ ነገር ግን ይህ ፈሳሽ ኖሮ የወር አበባዋ ሳይመጣ ብዙ ጊዜ ሊቆይ ይችላል። ይህንን የወር አበባ ያላዩ ሴቶች መሃል ላይ እንቁላል ማምረት ችለው እርግዝና ሊከሰት ስለሚችል ሦስት ወር ባል የማይፈታበት ጊዜ አለ፦
2፥235 *የተጻፈውም ዒዳህ ጊዜውን እስከሚደርስ ድረስ ጋብቻን ለመዋዋል ቁርጥ አሳብ አታድርጉ፡፡ አላህም በነፍሶቻችሁ ያለውን ነገር የሚያውቅ መኾኑን ዕወቁ፤ ተጠንቀቁትም፡፡ አላህም መሓሪ ታጋሽ መኾኑን ዕወቁ"*፡፡ وَلَا تَعْزِمُوا۟ عُقْدَةَ ٱلنِّكَاحِ حَتَّىٰ يَبْلُغَ ٱلْكِتَٰبُ أَجَلَهُۥ ۚ وَٱعْلَمُوٓا۟ أَنَّ ٱللَّهَ يَعْلَمُ مَا فِىٓ أَنفُسِكُمْ فَٱحْذَرُوهُ ۚ وَٱعْلَمُوٓا۟ أَنَّ ٱللَّهَ غَفُورٌ حَلِيمٌۭ

እንግዲህ ዐቅመ-ሐዋህ ጅማሬው አካላዊ ሽግግር"physical transition" የሆኑት ጡቷ ማጎጥጎጥ፣ ብብትና ብልት አካባቢ ጸጉር ማብቀል፣ የተራክቦ ፈሳሽ ማመንጨት ሲሆን ቀጣዩ የእንቁላል እድገት"ovarian development" ልጅ ለመፅነስ መደላድል ነው፥ እንቁላሉ የወንድ የዘር ሕዋስ ካላገኘ የወር አበባ ሆኖ ይወጣል። ይህንን በቅጡ ያልተረዱ ሚሽነሪዎች ዐይናቸውን በማንሸዋረር "የወር አበባ ያላየች ሴት" የሚለውን "ለዐቅመ-ሐዋህ ያልደረሰች" ብለው በማውረግረግ ኢሥላምን ሊዘልፉ ይፈልጋሉ፥ ይህ የደፈረሰ መረዳት ከላይ ያለውን ተስተምህሮት ጥልልና ጥንፍፍ አድርጎ ካለማየት የመጣ የተሳከረ መረዳት ነው። በኢሥላም ምንም ነገር መጉዳት አይፈቀድም፥ ጉዳትም ካለ በቂሷስ ይፈረዳል እንጂ ጉዳት አይመለስም፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 13, ሐዲስ 34
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ የአላህ መልዕክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ *"መጉዳት የለም፥ ጉዳትንም መመለስ የለም"*። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ لاَ ضَرَرَ وَلاَ ضِرَارَ ‏”‏ ‏.‏

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ብዙዎችን ለመቀየር ብዙዎች መሆን የለብህም፥ በዋጋ ከሁሉም የምታንሰው ትንሿ ጨው በዋጋ በሚበልጧት መኃል ገብታ ለሁሉም ለውጥ እና ጣዕምን እንደምትሰጥ ሁሉ በገባንበት ሁሉ የለውጥ እና የጣዕም ምክንያት ኢንሻሏህ እንሆናለህ፡፡ ከአንድ እስራ ሐሞት ይልቅ ጠብታ ማር ብዙ ንቦችን ትስባለች፥ ከጉልበት ብልሃት ከድፍረት ዕውቀት ይበልጣል።

ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
የቁርኣን ልኬት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

41፥42 *ከኋላውም ከፊቱም ውሸት አይመጣበትም፤ ጥበበኛ ምስጉን ከኾነው ጌታ የተወረደ ነው*፡፡ لَّا يَأْتِيهِ ٱلْبَٰطِلُ مِنۢ بَيْنِ يَدَيْهِ وَلَا مِنْ خَلْفِهِۦ ۖ تَنزِيلٌۭ مِّنْ حَكِيمٍ حَمِيدٍۢ

“አት-ተቅዪሥ” التقييس ማለት “ልኬት”Standardization” ማለት ነው፥ ቁርኣን በወረደበት ጊዜ ዐረቦች የተለያየ “ለህጃህ” لهجة ማለትም “ዘዬ”dialect” ነበራቸው፤ እነርሱም፦ “ቁሬይሽ” “ሁድኸይል” “ጠቂፍ” “ሃዋዚን” “ኪናነህ” “ተሚን” “የመኒ” የመሳሰሉት ነበሩ፣ እነዚህ ዘዬዎች የአነባነብ ሥርአታቸው ላይ “ተሽኪል” تَشْكِيل ማለትም “አናባቢ ድምጽ”Vowelling mark” ይለያያሉ፤ ይህም ልዩነት በማጥበቅና በማላላት፣ በመጎተትና በመጠቅለል የቃሉን መልእክት የተለያየ ትርጉም እንዲኖረው ሊያደርግ ይችላል። ለምሳሌ በአገራችን፦
“ገና” ብለን “ገ” ሆሄን ስናጥብቀው “ልደት” ማለት ሲሆን ስናላላው “መዘግየት” የሚል ትርጉም ይኖረዋል።
“የማይገባው” ብለን “ገ” ሆሄን ስናጥብቀው “ብቃት” ማለት ሲሆን ስናላላው ደግሞ “መረዳት” የሚል ትርጉም ይኖረዋል።
“የማይረዳኝ” ብለን “ዳ” ሆሄን ስናጥብቀው “ሃሳቤን የማይገባው” ማለት ሲሆን ስናላላው “የችግሬ መፍትሄ የማይሆን” የሚል ትርጉም ይኖረዋል።
“ዋና” ብለን “ዋ” ሆሄን ስናጥብቀው “ዐብይ” ማለት ሲሆን ስናላላው “መዋኘት” የሚል ትርጉም ይኖረዋል። እንዲሁ በዐረቢኛ ለምሳሌ፦
“አሊም” أَلِيم የሚለው በመነሻ ላይ በሃራካ “ሀምዛህ” ا ፈትሓህ “አ” أ አድርገን ስንቀራ “ህመም” ማለት ሲሆን “ዐሊም” عَلِيم የሚለውን በመነሻ ላይ በሃረካ “ዐይን” ع ፈትሓህ “ዐ” عَ አድርገን ስንቀራ ደግሞ “ዐዋቂ” ማለት ነው፡፡
“ከፈረ” كَفَرَ የሚለውን በግንድ ላይ በሃረካ “ፋ” ف ፈትሓህ “ፈ” فَ አድርገን ስንቀራ “ካደ” ማለት ሲሆን “ከፈረ” كَفَّرَ የሚለውን በግንድ ላይ በሸዳ “ፋ” ف ተሽዲድ ፈትሓህ “ፍፈ” فَّ አድርገን ስንቀራ “ሸፈነ” ማለት ነው።
“ነዘለ” نَزَلَ የሚለውን በግንድ ላይ በሃረካ “ዛል” ز ፈትሓህ “ዘ” زَ አድርገን ስንቀራ “ወረደ” ማለት ሲሆን “ነዘለ” نَزَّلَ የሚለውን በግንድ ላይ በሸዳ “ዛል” ز ፈትሓህ ተሽዲድ ፈትሓ “ዝዘ” زَّ አድርገን ስንቀራ “አወረደ” ማለት ነው። ብዙ ናሙና ማቅረብ ይቻል ነበር፤ ግን ይህ በቂ ነው፤ ይህ ሙግት የሥነ-አናባቢ ጥናት”orthography” ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው።

ሌላው “አብጀድ” أَبْجَد ማለትም “ተነባቢ ፊደላት”consonant” ላይም ልዩነት አላቸው፤ ድምጽ ያላቸው ሐርፎች 28 ሲሆን “አሊፍ” ا ደግሞ “አጫዋች ፊደል”stretch letter” ነው፤ በጥቅሉ 29 ሐርፎች ሲሆኑ በመካከላቸው ስናነባቸው የሚቀጥኑ ሐርፎች 19 ሲሆኑ “ተርቂይቅ” تَرْقِيْقٌ ይባላሉ፣ የሚወፍሩ ሐርፎች ደግሞ 7 ሲሆኑ “ተፍኺይም” تَفْخِيْمُ ይባላሉ፣ የሚወፍርና የሚቀጥኑ ሐርፎች ደግሞ ሁለት ሲሆኑ አንደኛው “ሯ” ر በፈትሓህ እና በደማ ሲቀራ ይወፍራል፤ በከስራ ሲቀራ ይቀጥናል። ሁለተኛ “ላም” ل በለፍዙል ጀላላ ማለትም በአላህ ስም ላይ ሲቀራ ይወፍራል፤ በሌሎች ላይ ሲቀራ ይቀጥናል።
በእነዚህ ተነባቢ ፊደላት ላይ “ኑቅጧህ” نُقْطَة‎ ማለትም “ነጥብ” ያላቸው 16 ሐርፎች “ሙአጀማ” ሲባሉ ነጥብ የሌላቸው 14 ሐርፎች ደግሞ “ሙሃመላ” ይባላል፣ አንዷ ሐርፍ “ያ” ي ደግሞ ሁለቱንም ናት።
ሐርፎች በመነሻ ቅጥያ”Prefix” ላይ፣ በግንድ”stem” ላይ እና በመዳረሻ ቅጥያ”Suffix” ላይ ቅርጻቸው ሲቀያየር “ረሥም” رَسْم ይባላል። ለናሙና ያክል አንዳንድ ሃርፎችን እንመልከት፦
1. ባ ب
መነሻ بـ መካከልـبـ መዳረሻ ـب
2. ታ ت
መነሻ تـ መካከልـتـ መዳረሻ ـت
3. ሳ ث
መነሻ ثـ መካከል ـثـ መዳረሻ ـث
4. ጂም ج
መነሻ جـ መካከል ـجـ መዳረሻ ـج
5. ሐ ح
መነሻح ـ መካከል ـحـ መዳረሻ ـح
6. ኸ خ
መነሻ خـ መካከል ـخـ መዳረሻ ـخ
ይህ ሙግት የሥነ-ተናባቢ ጥናት”Typography” ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው። ይህ እንዲህ በእንዲህ እያለ ቁርኣን በቁሬይሽ ዘዬ ወረደ፤ ሌሎች ሁድኸይል፣ ጠቂፍ፣ ሃዋዚን፣ ኪናነህ፣ ተሚን፣ የመኒ ወዘተ ከዚህ ዘዬ ወስደው ሲጠቀሙ በማጥበቅና በማላላት፤ በማቅጠንና በማወፈር በትርጉም ላይ ልዩነት አመጣ፤ ይህ ልዩነት ከዐረብ ውጪ ላሉት መከፋፈል አመጣ፤ ይህንን ልዩነት የታዘበው የነቢያችን”ﷺ” ሰሃቢይ ሑደይፋህ ኢብኑል-የማን በወቅቱ ኸሊፋህ ለነበረው ለዑስማን በመናገር በቁሬይሽ ዘዬ አንድ የጋራ ልኬት እንዲደረግ ተደርጓል፦
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 9
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ *”የሻም ሕዝብ እና የኢራቅ ሕዝብ አርመንያን እና አዛርባጃንን ለማሸነፍ ጦርነት ባደረጉ ጊዜ ሑደይፋህ ኢብኑል-የማን ወደ ዑስማን ሲመጣ የሻም እና የኢራቅ ሕዝቦች በቂርኣት ዘዬ ላይ ሲለያዩ ፈራ፤ ከዚያም ሑደይፋህም ለዑስማን፦ “የምእመናን አሚር ሆይ! ይህንን ዑማህ ታደግ፤ ስለ መጽሐፉ ከዑማህ በፊት ልክ የሁዲ እና ነሳራህ እንደተለያዩት እንዳይለያዩ። ከዚያም ዑስማንም ለሐፍሷህ፦ “የቁርኣን መሷሒፍ ላኪልኝ፤ በጥሩ ሙስሐፍ ካዘጋጀን በኃላ መሷሒፉን እመልስልሻለው” ብሎ ላከባት፤ ሐፍሷህም ለዑስማን ላከችለት፤ ከዚያም ዑስማን ለዘይድ ኢብኑ ሳቢት፣ ለዐብደሏህ ኢብኑ አዝ-ዙበይር፣ ለሠዒድ ኢብኑል ዓስ እና ለዐብዱ አር-ረሕማን ኢብኑል ሓሪስ ኢብኑ ሂሻም ከመሷሒፍ እንዲገለብጡ አዘዛቸው፤ ዑስማንም ለሦስቱ የቁሬይሽ ሰዎች፦ “ምናልባት በአገለባበጡ ከዘይድ ኢብኑ ሳቢት ጋር ያልተስማማችሁበት ነጥብ ካለ በቁሬሽ ዘዬ ጻፉት፤ ቁርኣን በእነርሱ ዘዬ ነው የወረደው፤ ከዚያም በእነርሱ ዘዬ አደረጉ። ብዙ ሱሑፎችን ገለበጡ፤ ዑስማንም የቁርኣንን መሷሒፍ ለሐፍሷህ መለሰላት። ከዚያም ዑስማንም ለሁሉም ሙስሊም አውራጃ እነርሱ ከገለበጡት ከላከ በኃላ ማንኛውም ሌሎች የቁርኣን እደ-ክታባት ሆኑ ግልባጮች ተቃጠሉ*። أَنَّ أَنَسَ بْنَ مَالِكٍ، حَدَّثَهُ أَنَّ حُذَيْفَةَ بْنَ الْيَمَانِ قَدِمَ عَلَى عُثْمَانَ وَكَانَ يُغَازِي أَهْلَ الشَّأْمِ فِي فَتْحِ إِرْمِينِيَةَ وَأَذْرَبِيجَانَ مَعَ أَهْلِ الْعِرَاقِ فَأَفْزَعَ حُذَيْفَةَ اخْتِلاَفُهُمْ فِي الْقِرَاءَةِ فَقَالَ حُذَيْفَةُ لِعُثْمَانَ يَا أَمِيرَ الْمُؤْمِنِينَ أَدْرِكْ هَذِهِ الأُمَّةَ قَبْلَ أَنْ يَخْتَلِفُوا فِي الْكِتَابِ اخْتِلاَفَ الْيَهُودِ وَالنَّصَارَى فَأَرْسَلَ عُثْمَانُ إِلَى حَفْصَةَ أَنْ أَرْسِلِي إِلَيْنَا بِالصُّحُفِ نَنْسَخُهَا فِي الْمَصَاحِفِ ثُمَّ نَرُدُّهَا إِلَيْكِ فَأَرْسَلَتْ بِهَا حَفْصَةُ إِلَى عُثْمَانَ فَأَمَرَ زَيْدَ بْنَ ثَابِتٍ وَعَبْدَ اللَّهِ بْنَ الزُّبَيْرِ وَسَعِيدَ بْنَ الْعَاصِ وَعَبْدَ الرَّحْمَنِ بْنَ الْحَارِثِ بْنِ هِشَامٍ فَنَسَخُوهَا فِي الْمَصَاحِفِ وَقَالَ عُثْمَانُ لِلرَّهْطِ الْقُرَشِيِّينَ الثَّلاَثَةِ إِذَا اخْتَلَفْتُمْ أَنْتُمْ وَزَيْدُ بْنُ ثَابِتٍ فِي شَىْءٍ مِنَ الْقُرْآنِ فَاكْتُبُوهُ بِلِسَانِ قُرَيْشٍ فَإِنَّمَا نَزَلَ بِلِسَانِهِمْ فَفَعَلُوا حَتَّى إِذَا نَسَخُوا الصُّحُفَ فِي الْمَصَاحِفِ رَدَّ عُثْمَانُ الصُّحُفَ إِلَى حَفْصَةَ وَأَرْسَلَ إِلَى كُلِّ أُفُقٍ بِمُصْحَفٍ مِمَّا نَسَخُوا وَأَمَرَ بِمَا سِوَاهُ مِنَ الْقُرْآنِ فِي كُلِّ صَحِيفَةٍ أَوْ مُصْحَفٍ أَنْ يُحْرَقَ‏.‏

ይህ ትልቅ መርሐ-ግብር ነው፤ የነቢያችን”ﷺ” ባልደረቦች ከቁርኣን ውጪ የነቢያችን”ﷺ” የሚሰሟቸው የቁርኣን ማብራሪያዎችን እና ዱዓዎችም በራሳቸው በሚጽፏቸው ቁርኣን ላይ ከግርጌ ፣ከራስጌ፣ ከፊት እና ከኃላ ይጽፉ ነበር፤ ይህ ጽሑፍ ለመጪው ትውልድ የቁርኣን ሱራ ተደርጎ እንዳይወሰድ ከላይ ከተጠቀሱ ችግሮች ጋር አብሮ ተቃጥሏል። ይህ የዑሥማን ልኬት ቱርክ ስታንቡል ቶካፒ በሚባል ሙዝየም ይገኛል። ይህንን ካርበን 14 በምርምር ከ 100-200 ዓመተ-ሒጅራህ ያሳያል። ይህንን የብራና ሙስሐፍ ከታች በፎቶ አስቀምጫለው። ይህ ከላይ ያለው መጣጥፍ የቁርኣን ዳራ ከሚል መጽሐፌ የተቀነጨበ ነው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሲፍር

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

39፥62 *አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው*፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡ اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ ۖ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ

አላህ “አል-ኻሊቅ” الخَٰلِق ማለትም “ፈጣሪ” ነው፥ ነገር ሁሉ ደግሞ “መኽሉቅ” مَخْلُق ማለትም “ፍጡር” ሲሆን አላህ የነገር ሁሉ ፈጣሪ ነው፦
39፥62 *አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው*፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡ اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ ۖ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ

“ሸይእ” شَىْء ማለት “ነገር’thing” ማለት ሲሆን “ነገር” በሚለው ቃል ውስጥ ዘመካን ይካተታል፥ “ዘመካን” زَمَكَان ማለት የዘማንና የመካን ቃላት ውቅር ነው። “ዘማን” زَمَان ማለት “ጊዜ”time” ማለት ነው፥ “መካን” مَكَان ደግሞ “ቦታ”space” ማለት ነው። ምንም ነገር ሳይኖር አላህ ብቻውን ነበረ፦
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 59, ሐዲስ 2
ዒምራም ኢብኑ ሑሰይን እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ *”ምንም ነገር ሳይኖር አላህ ነበረ። ከዚያ ዙፋኑን በውኃ ላይ ነበረ፥ ከዚያ ሁሉን ነገር ጻፈ። ከዚያ ሰማያትንና ምድርን ፈጠረ"*። عَنْ عِمْرَانَ بْنِ حُصَيْنٍ، قَالَ إِنِّي عِنْدَ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم كَانَ اللَّهُ وَلَمْ يَكُنْ شَىْءٌ غَيْرُهُ، وَكَانَ عَرْشُهُ عَلَى الْمَاءِ، وَكَتَبَ فِي الذِّكْرِ كُلَّ شَىْءٍ، وَخَلَقَ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضَ ‏

"ነገር" ከመፈጠሩ በፊት "ምንም" ነው። "ሲፍር" صِفْر የሚለው ቃል "ሶፊረ" صَفِرَ ማለትም "ምንም አደረገ" "ባዶ አደረገ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ምንም"empty" "no-thing" ማለት ነው፥ በግዕዝ "አልቦ" ሲባል በኢንግሊዝ "ዜሮ" 0 ይባላል። ሁሉም ነገር ዜሮ ምድገት"zero volume" ሆኖ ሳለ አምላካችን አላህ እምኀበ አልቦ ኀበቦ ማለትም ካለመኖር ወደ መኖር በይኹን ቃል ያስገኘው ነው፦
2፥117 *ሰማያትንና ምድርን ያለብጤ ፈጣሪ ነው፤ ነገርንም ማስገኘት በሻ ጊዜ ለእርሱ የሚለው፡- «ኹን» ነው፤ ወዲያውም ይኾናል*፡፡ بَدِيعُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۖ وَإِذَا قَضَىٰ أَمْرًا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُ كُن فَيَكُونُ
16፥40 *ለማንኛውም ነገር መኾኑን በሻነው ጊዜ ቃላችን ለእርሱ “ኹን” ማለት ብቻ ነው፥ ወዲውም ይኾናል*፡፡ إِنَّمَا قَوْلُنَا لِشَيْءٍ إِذَا أَرَدْنَاهُ أَن نَّقُولَ لَهُ كُن فَيَكُونُ

“ቃላችን” የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት። የሚፈጥበት የይኹን ቃል ግን ከነገር ውጪ የፈጣሪ ባሕርይ ነው። "ነገርን" ማስገኘት ሲፈልግ በቃሉ “ኩን” كُن ማለትም “ኹን” ይለዋል፥ ይኾናል። አምላካችን አሏህ ሁሉን ነገር በይሁን ንግግሩ ከማስገኘቱ በፊት ቀድሮታል፦
65፥3 *"አላህ ለነገሩ ሁሉ የተወሰነ ጊዜን በእርግጥ አድርጓል"*፡፡ إِنَّ اللَّهَ بَالِغُ أَمْرِهِ ۚ قَدْ جَعَلَ اللَّهُ لِكُلِّ شَيْءٍ قَدْرًا

አላህ መጀመሪያ የፈጠረው ቀለምን ነው፥ አሏህ ለቀለም፦ "ለዘላለም የሚሆነውን ጻፍ" አለው። አሏህ ከአምስት መቶ ሺህ ዓመት በፊት የፍጥረትን ግብዓት በጥብቁ ሰሌዳ ጻፈ፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3637
አቡ ሙሐመድ አለ፦ አባቴ ከአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ሰማው ብሎ እንደተከልኝ የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” አሉ፦ *"መጀመሪያ አላህ የፈጠረው ቀለምን ነው፥ አሏህ ለእርሱ ለዘላለም የሚሆነውን ጻፍ አለው"*። فَقَالَ عَطَاءٌ لَقِيتُ الْوَلِيدَ بْنَ عُبَادَةَ بْنِ الصَّامِتِ قَالَ حَدَّثَنِي أَبِي قَالَ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ ‏ “‏ إِنَّ أَوَّلَ مَا خَلَقَ اللَّهُ الْقَلَمَ فَقَالَ لَهُ اكْتُبْ فَجَرَى بِمَا هُوَ كَائِنٌ إِلَى الأَبَدِ ‏
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 46, ሐዲስ 27
ዐብደላህ ኢብኑ ዐምር ኢብሙል ዓስ ሰምቶ እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *"አላህ ሰማያትን እና ምድርን ከመፍጠሩ ከአምስት መቶ ሺህ ዓመት በፊት የፍጥረትን ግብዓት ጻፈ"*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرِو، بْنِ الْعَاصِ قَالَ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ ‏ "‏ كَتَبَ اللَّهُ مَقَادِيرَ الْخَلاَئِقِ قَبْلَ أَنْ يَخْلُقَ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضَ بِخَمْسِينَ أَلْفَ سَنَةٍ

አላህ ፍጥረትን ከምንም እንደ ፈጠረ እንዲሁ ፍጥረትን በፍርድ ቀን "ምንም" ያረገዋል፦
21፥104 *የመጀመሪያን ፍጥረት እንደ ጀመርን እንመልሰዋለን*፡፡ መፈጸሙ በእኛ ላይ የኾነን ቀጠሮ ቀጠርን፡፡ እኛ ሠሪዎች ነን፡፡ كَمَا بَدَأْنَا أَوَّلَ خَلْقٍ نُّعِيدُهُ ۚ وَعْدًا عَلَيْنَا ۚ إِنَّا كُنَّا فَاعِلِينَ

ከፍጥረት በፊት መጀመሪያ የሌለው ቀዳማይ እንደሆነ ሁሉ ከፍጥረት በኃላ መጨረሻ የሌለው ደኃራይ ይሆናል። የመጀመሪያን ፍጥረት ምንም በማድረግ ያጠፋውና ከፍጥረት በፊት ብቻውን እንደነበረ ይሆናል፦
28፥88 ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፡፡ ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፡፡ *ነገሩ ሁሉ ከአላህ በቀር ጠፊ ነው*፡፡ ፍርዱ የእርሱ ብቻ ነው፡፡ ወደ እርሱም ትመለሳላችሁ፡፡ وَلَا تَدْعُ مَعَ اللَّهِ إِلَـٰهًا آخَرَ ۘ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۚ كُلُّ شَيْءٍ هَالِكٌ إِلَّا وَجْهَهُ ۚ لَهُ الْحُكْمُ وَإِلَيْهِ تُرْجَعُونَ

"ነገሩ ሁሉ ከአላህ በቀር ጠፊ ነው" የሚለው ይሰመርበት። "ነገር" በሙሉ ጠፊ ነው፥ አላህ ብቻውን ይቀራል። ከዚያም በፍርዱ ቀን "ኹን" ሲል ፍጥረት ካለመኖር ወደ መኖር ተመልሶ ይመጣል፦
6፥73 እርሱም ያ ሰማያትንና ምድርን በእውነት የፈጠረ ነው፡፡ *«ኹን» የሚልበትንና ወዲያውም የሚኾንበትን ቀን አስታውስ፡፡ ቃሉ እውነት ነው*፡፡ በቀንዱም በሚነፋ ቀን ንግሥናው የእርሱ ብቻ ነው፡፡ ሩቁንና ቅርቡን ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ጥበበኛው ውስጥ ዐዋቂው ነው፡፡ وَهُوَ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ بِالْحَقِّ ۖ وَيَوْمَ يَقُولُ كُن فَيَكُونُ ۚ قَوْلُهُ الْحَقُّ ۚ وَلَهُ الْمُلْكُ يَوْمَ يُنفَخُ فِي الصُّورِ ۚ عَالِمُ الْغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ ۚ وَهُوَ الْحَكِيمُ الْخَبِيرُ

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ወሕይ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

42፥51 *ለሰው አላህ በራእይ፣ ወይም ከግርዶ ወዲያ፣ ወይም መልክተኛን መልአክን የሚልክ እና በፈቃዱ የሚሻውን “የሚያወርድለት” ቢሆን እንጅ በገሃድ “ሊያናግረው” ተገቢው አይደለም”*፥ እርሱ የበላይ ጥበበኛ ነውና። وَمَا كَانَ لِبَشَرٍ أَن يُكَلِّمَهُ ٱللَّهُ إِلَّا وَحْيًا أَوْ مِن وَرَآئِ حِجَابٍ أَوْ يُرْسِلَ رَسُولًۭا فَيُوحِىَ بِإِذْنِهِۦ مَا يَشَآءُ ۚ إِنَّهُۥ عَلِىٌّ حَكِيمٌۭ

“ወሕይ” وَحْى የሚለው ቃል “አውሓ” أَوْحَىٰ ማለትም “ገለጠ” ወይም “አወረደ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ግልጠተ-መለኮት” ወይም “ግህደተ-መለኮት”Revelation” ማለት ነው። “ወሕይ” የሚለው የስም መደብ በቁርኣን 6 ጊዜ ተጠቅሷል፥ “አውሓ” የሚለው የግስ መደብ እንደየ ዐውዱ የተለያየ ትርጉም ለመስጠት 72 ጊዜ ተጠቅሷል። ቁርኣን ላይ ተመሳሳይ ቃል ቢኖረው እንኳን ተመሳሳይ አሳብና ትርጉም አለው ማለት አይደለም፥ የአንድን ቃል አማራጭ ትርጉም የሚወስነው ቃሉ የሚገኝበት ዐረፍተ ነገር ወይም ዐውድ እንደ ሆነ ቅቡል ነው። ለምሳሌ ዘከርያ ወደ ሕዝቦቹ ጌታችሁን አወድሱ! በማለት ተናግሯል፦
19፥11 ከምኩራቡም በሕዝቦቹ ላይ ወጣ፥ *"ወደ እነርሱ፦ "በጧት እና በማታ ጌታችሁን አወድሱ! በማለት "ጠቀሰ"*፡፡ فَخَرَجَ عَلَىٰ قَوْمِهِ مِنَ الْمِحْرَابِ فَأَوْحَىٰ إِلَيْهِمْ أَن سَبِّحُوا بُكْرَةً وَعَشِيًّا

"ጠቀሰ" ለማለት የገባው ቃል "አውሓ" أَوْحَىٰ መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። እዚህ አንቀጽ ላይ መታየት ያለበት ቃሉ ሳይሆን ቃሉ የወከለው አሳብ ነው። ስለዚህ “አውሓ” أَوْحَىٰ ማለት "ገለጠ" ማለት ብቻ ሳይሆን "አሳወቀ" ወይም "ተናገረ" በሚል ይመጣል፦
16፥68 *"ጌታህም ወደ ንብ እንዲህ ሲል አስታወቀ፦ «ከተራራዎች፣ ከዛፍም፣ ሰዎች ከሚሠሩትም ቀፎ ቤቶችን ያዢ"*፡፡ وَأَوْحَىٰ رَبُّكَ إِلَى النَّحْلِ أَنِ اتَّخِذِي مِنَ الْجِبَالِ بُيُوتًا وَمِنَ الشَّجَرِ وَمِمَّا يَعْرِشُونَ
99፥5 *"ጌታህ ለእርሷ በማሳወቁ ምክንያት"*፡፡ بِأَنَّ رَبَّكَ أَوْحَىٰ لَهَا

ሁለቱም አናቅጽ ላይ "አሳወቀ" ለሚለው የገባው ቃል "አውሓ" أَوْحَىٰ ነው። አምላካችን አሏህ በሁሉም ሰማያት ውስጥ ትእዛዙ አውርዷል፦
41፥12 *"በሁለት ቀኖችም ውስጥ ሰባት ሰማያት አደረጋቸው፡፡ በሰማይቱም ሁሉ ነገሯን አዘጋጀ"*፡፡ فَقَضَاهُنَّ سَبْعَ سَمَاوَاتٍ فِي يَوْمَيْنِ وَأَوْحَىٰ فِي كُلِّ سَمَاءٍ أَمْرَهَا ۚ
65፥12 አላህ ያ ሰባትን ሰማያት የፈጠረ ነው፡፡ ከምድርም መሰላቸውን ፈጥሮአል፥ *"በመካከላቸው ትእዛዙ ይወርዳል"*፡፡ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَ سَبْعَ سَمَاوَاتٍ وَمِنَ الْأَرْضِ مِثْلَهُنَّ يَتَنَزَّلُ الْأَمْرُ بَيْنَهُنَّ لِتَعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ وَأَنَّ اللَّهَ قَدْ أَحَاطَ بِكُلِّ شَيْءٍ عِلْمًا

"ነገሯን" ለሚለው የገባው ቃል "አምረ-ሃ" أَمْرَهَا ሲሆን "ትእዛዝ" በሚል ለማመልከት "አምር" أَمْر ተብሏል። "አዘጋጀ" ለሚለው የገባው ቃል "አውሓ" أَوْحَىٰ ሲሆን "የተነዘሉ" يَتَنَزَّلُ ማለትም "ይወርዳል" በሚል መጥቷል። አምላካችን አሏህ በሰማያት ውስጥ ወዳሉት መላእክት ትእዛዙን መናገሩን ፍትውና ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፦
53፥26 *"በሰማያት ውስጥ ካሉ መላእክትም ብዙዎች ሊማለዱለት ለሚሻውና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጅ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም"*፡፡ وَكَم مِّن مَّلَكٍ فِي السَّمَاوَاتِ لَا تُغْنِي شَفَاعَتُهُمْ شَيْئًا إِلَّا مِن بَعْدِ أَن يَأْذَنَ اللَّهُ لِمَن يَشَاءُ وَيَرْضَىٰ
8፥12 *ጌታህ ወደ መላእክቱ፦ «እኔ ከእናንተ ጋር ነኝና እነዚያን ያመኑትን አጽናኑ! በእነዚያ በካዱት ልቦች ውስጥ ፍርሃትን በእርግጥ እጥላለሁ፡፡ ከአንገቶችም በላይ ራሶችን ምቱ! ከእነርሱም የቅርንጫፎችን መለያልይ ሁሉ ምቱ» ሲል ያወረደውን አስታውስ*፡፡ إِذْ يُوحِي رَبُّكَ إِلَى الْمَلَائِكَةِ أَنِّي مَعَكُمْ فَثَبِّتُوا الَّذِينَ آمَنُوا ۚ سَأُلْقِي فِي قُلُوبِ الَّذِينَ كَفَرُوا الرُّعْبَ فَاضْرِبُوا فَوْقَ الْأَعْنَاقِ وَاضْرِبُوا مِنْهُمْ كُلَّ بَنَانٍ

"ያወረደው" ለሚለው የገባው ቃል "ዩሒ" يُوحِي ሲሆን "ያሳወቀው" "የተናገረው" ለማለት ተፈልጎ ነው። አሏህ ለሙሳ እናት ያሳወቃትን ነገር ለማመልከት "አውሐይና" أَوْحَيْنَا ማለትም "አሳወቅን" ብሎ ተናግሯል፦
20፥38 *"ወደ እናትህ በልብ የሚፈስን ነገር ባሳወቅን ጊዜ"*፡፡ إِذْ أَوْحَيْنَا إِلَىٰ أُمِّكَ مَا يُوحَىٰ
ነገር ግን አምላካችን አሏህ ወደ አንድ ረሡል የሚያወርደው ወሕይ “ከላሙ አት-ተሽሪዒይ” كَلَٰم التَشْرِعِي ነው፥ “ተሽሪዒይ” تَشْرِعِي የሚለው ቃል “ሸረዐ” شَرَّعَ‎ ማለትም “ደነገገ” ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ድንጋጌ” ወይም “ሕግጋት” ማለት ነው። ይህ ሸሪዓህ ከአላህ ወደ ነቢያቱ የሚወርድ አድርግ እና አታድርግ መመሪያ፣ መርሕ፣ ሥርዓት ነው፥ “ሸሪዓህ” شَرِيعَة ማለት “ትክክለኛ ሕግ” ማለት ነው። ይህ ወሕይ ለአንድ ነቢይ ከሦስት መንገድ በአንዱ መንገድ ይወርድለታል፦
42፥51 *ለሰው አላህ በራእይ፣ ወይም ከግርዶ ወዲያ፣ ወይም መልክተኛን መልአክን የሚልክ እና በፈቃዱ የሚሻውን “የሚያወርድለት” ቢሆን እንጅ በገሃድ “ሊያናግረው” ተገቢው አይደለም”*፥ እርሱ የበላይ ጥበበኛ ነውና። وَمَا كَانَ لِبَشَرٍ أَن يُكَلِّمَهُ ٱللَّهُ إِلَّا وَحْيًا أَوْ مِن وَرَآئِ حِجَابٍ أَوْ يُرْسِلَ رَسُولًۭا فَيُوحِىَ بِإِذْنِهِۦ مَا يَشَآءُ ۚ إِنَّهُۥ عَلِىٌّ حَكِيمٌۭ

"የሚያወርድለት" ለሚለው የገባው ቃል "ዩሒየ" فَيُوحِىَ መሆኑን አንባቢ ልብ ይለዋል። ለአንድ ነቢይ ወሕይ የሚመጣለት መንገድ በራእይ ወይም ያለ ራእይ እና ያለ መልአክ ከግርዶ ወዲያ አሊያል በመልአክ ነው። “መለክ” مَلَك ወይም “መልአክ” مَلْأَك የሚለው ቃል “ለአከ” لَأَكَ ማለትም “ላከ” ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ተላላኪ” ማለት ነው።
ከዚህ በተቃራኒው ደግሞ የጂን ሸያጢን ወደ የሰው ሸያጢን ወደ መተተኛ፣ ወደ ድግምተኛ፣ ወደ ጠንቋይ ወዘተ ንግግራቸውን ያወርዳሉ፦
6፥112 *"እንደዚሁም ለነቢያት ሁሉ ከሰውና ከጋኔን የኾኑን ሰይጣናት ጠላት አደረግን፡፡ ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ለማታለል ልብስብስን ቃል ይጥላሉ"*፡፡ وَكَذَٰلِكَ جَعَلْنَا لِكُلِّ نَبِيٍّ عَدُوًّا شَيَاطِينَ الْإِنسِ وَالْجِنِّ يُوحِي بَعْضُهُمْ إِلَىٰ بَعْضٍ زُخْرُفَ الْقَوْلِ غُرُورًا
6፥121 በእርሱም ላይ የአላህ ስም ካልተጠራበት ነገር አትብሉ፡፡ እርሱም በእርግጥ አመጽ ነው፡፡ *"ሰይጣናትም ወደ ወዳጆቻቸው በክትን በመብላት ይከራከሯችሁ ዘንድ ያሾከሹካሉ"*፡፡ وَلَا تَأْكُلُوا مِمَّا لَمْ يُذْكَرِ اسْمُ اللَّهِ عَلَيْهِ وَإِنَّهُ لَفِسْقٌ ۗ وَإِنَّ الشَّيَاطِينَ لَيُوحُونَ إِلَىٰ أَوْلِيَائِهِمْ لِيُجَادِلُوكُمْ

"ይጥላሉ" ለሚለው የገባው የግስ መደብ "ዩሒ" يُوحِي ሲሆን "ያሾካሽካሉ" ለሚለው የገባው የግስ መደብ ደግሞ "ለዩሑነ" لَيُوحُونَ ሲሆን "ያወርዳሉ" ማለት ነው። ይህ የሚወሠውሱት ነገር ወሥዋሥ ነው፥ “ወሥዋሥ” وَسْوَاس ማለት “ጉትጎታ” ማለት ነው። ስለ ወሕይ እሳቤ በግርድፉ እና በሌጣው ይህንን ይመስላል።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሐዲሱ አን-ነበዊይ እና ሐዲሱል ቁድሢይ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

59፥7 *መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት! ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ*፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና፡፡ وَمَا آتَاكُمُ الرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَاكُمْ عَنْهُ فَانتَهُوا ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۖ إِنَّ اللَّهَ شَدِيدُ الْعِقَابِ

“ሐዲስ” حَدِيث የሚለው ቃል “ሐደሰ” حَدَّثَ‎ ማለትም “ተናገረ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ንግግር” ማለት ነው፥ ነቢያችን”ﷺ” በዐቂዳህ እና በፊቅህ ነጥብ ላይ የሚናገሩት ሐዲስ ሁሉ ወሕይ ነው፦
53፥3 *ከልብ ወለድም አይናገርም*፡፡ وَمَا يَنطِقُ عَنِ الْهَوَىٰ
53፥4 *እርሱ ንግግሩ የሚወረድ ወሕይ እንጅ ሌላ አይደለም*፡፡ إِنْ هُوَ إِلَّا وَحْيٌ يُوحَىٰ

“ወሕይ” وَحْي የሚለው ቃል “አውሓ” أَوْحَىٰٓ ማለትም “ገለጠ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ግልጠተ-መለኮት” ማለት ነው። “መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት! ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ” የሚለው ይህንኑ ሡናህ ዋቢና ታሳቢ ያደረገ ነው፦
59፥7 *መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት! ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ*፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና፡፡ وَمَا آتَاكُمُ الرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَاكُمْ عَنْهُ فَانتَهُوا ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۖ إِنَّ اللَّهَ شَدِيدُ الْعِقَابِ

ታዲያ ቁርኣን እና ሐዲስ ልዩነቱ ምንድን ነው? አዎ! ቁርኣን ለፍዙ ሆነ መዕናው የአላህ ነው፥ ሐዲስ ግን ለፍዙ የነቢያችን”ﷺ” ሲሆን ማዕናው የአላህ ነው። “ለፍዝ” لَفْظ ማለት “ቃል”Verbatim” ማለት ሲሆን “መዕና” مَعْنًى ማለት “መልእክት” “እሳቤ” “አሳብ”notion” ማለት ነው። የቁርኣን ተናጋሪ አላህ ብቻ ነው፥ ቃሉም የወከለው መልእክቱ፣ “እሳቤው፣ አሳቡ የራሱ ነው። ሐዲስ ደግሞ መልእክቱ፣ “እሳቤው፣ አሳቡ የአላህ ሲሆን ቃሉ ግን የራሳቸው የነቢያችን”ﷺ” ነው። አላህ የሐዲስን መልእክት ሲያወርድላቸው እሳቸው በራሳቸው ባህል፣ ወግ፣ ልምድ፣ ክህሎት፣ ትውፊት ያብራሩታል። ይህ ሐዲስ ደግሞ በሁለት ይከፈላል፥ እርሱም ሐዲሱ አን-ነበዊይ እና ሐዲሱል ቁድሢይ ነው።

ነጥብ አንድ
"ሐዲሱ አን-ነበዊይ"
“ነቢይ” نَبِيّ የሚለው ቃል “ነበአ” نَبَّأَ ማለትም “የሩቅ ወሬን አወራ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “የሩቅ ወሬ አውሪ” ማለት ነው፥ የነቢይ ገላጭ መደብ ደግሞ "ነበዊይ" نَبَوِيّ‎ ሲሆን "ነቢያዊ" ማለት ነው። በጥቅሉ "ሐዲሱ አን-ነበዊይ" حَدِيث الْنَبَوِيّ‎ ማለት "ነቢያዊ ሐዲስ" ማለት ነው፥ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ" ወይም "ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ" ተብሎ የሚናገሩት ንግግር ሁሉ ሐዲሱ አን-ነበዊይ ይባላል። ለምሳሌ፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 27, ሐዲስ 62
አቢ ዘር እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”የአንተ ፈገግታ በወንድምህ ፊት ለአንተ ሶደቃህ ነው”*። عَنْ أَبِي ذَرٍّ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ تَبَسُّمُكَ فِي وَجْهِ أَخِيكَ لَكَ صَدَقَةٌ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 80, ሐዲስ 102
አቢ ሙሣ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”ጌታውን የሚዘክር እና የማይዘክር ምሳሌ፥ ልክ እንደ ሕያው እና እንደ ሙታን ነው”*። عَنْ أَبِي مُوسَى ـ رضى الله عنه ـ قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ مَثَلُ الَّذِي يَذْكُرُ رَبَّهُ وَالَّذِي لاَ يَذْكُرُ مَثَلُ الْحَىِّ وَالْمَيِّتِ
ነጥብ ሁለይ
"ሐዲሱል ቁድሢይ"
"ቁድሥ" قُدْس የሚለው ቃል "ቀዱሠ" قَدُسَ ማለትም "ቀደሰ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ቅዱስ" ማለት ነው፥ የቁድሥ ገላጭ መደብ ደግሞ "ቁድሢይ" قُدْسِيّ ሲሆን "ቅዱሳዊ" ማለት ነው። በጥቅሉ "ሐዲሱል ቁድሢይ" حَدِيث الْقُدْسِيّ ማለት "ቅዱሳዊ ንግግር" ማለት ነው፥ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "አላህም እንዲህ አለ" ተብሎ የሚናገሩት ንግግር ሁሉ ሐዲሱል ቁድሢይ ይባላል። ለምሳሌ፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 13, ሐዲስ 212
አቢ ሁረይራ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "አላህም እንዲህ አለ፦ *“ከፆም በስተቀር የአደም ልጅ መልካም ሥራ ሁሉ ለራሱ ነው፥ ፆም ለእኔ ነው። እኔም ምንዳውን በእርሱ እከፍላለው"*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ يَقُولُ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ قَالَ اللَّهُ عَزَّ وَجَلَّ كُلُّ عَمَلِ ابْنِ آدَمَ لَهُ إِلاَّ الصِّيَامَ فَإِنَّهُ لِي وَأَنَا أَجْزِي بِهِ

ነቢያችን"ﷺ" ይህንን ወደ አሏህ አስጠግተው የሚነግሩን ቅዱሳዊ ንግግራቸው ከቁርኣን የሚለየው፦
1ኛ. ቁርኣን የአሏህ ንግግር ብቻ ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን በነቢያችን"ﷺ" ንግግር "አሏህ አለ" ተብሎ በኒስባህ መነገሩ ነው።
2ኛ. ቁርኣን አሏህ በጂብሪል በኩል የተናገረው የራሱ ንግግር ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን በነቢያችን"ﷺ" ሕልም "አሏህ አለ" ተብሎ በኒስባህ መነገሩ ነው።
3ኛ. ቁርኣን ሲቀራ ዒባዳህ የሚፈጸምበት ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን አይቀራም፥ በመነበቡ ዒባዳም አይፈጸምበትም።
4ኛ. ቁርኣን እያንዳንዱ ሐርፍ መቅራት አስር ሐሠናት ሲኖረው ሐዲሱል ቁድሢይ ግን በውስጡ ያሉትን በመታዘዝ እንጂ በመነበቡ ሐሠናት የለውም።
5ኛ. ቁርኣን በሡራህ፣ በአያት እና በጁዝ የተከፋፈለ ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን በምንም አልተከፋፈለም።
6ኛ. ቁርኣን በውዱእ መንካት ሙስተሐብ እና ያለ ውዱእ መንካት መክሩህ ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን ያለ ውዱእ መንካት ሙባሕ ነው።
7ኛ. ከተራክቦ በኃላ ቁርኣን ለመንካት የጀናባህ ትጥበት ፈርድ ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን ያለ ጀናባህ ትጥበት መንካት ሙባሕ ነው።
8ኛ. በሐይድ ይ ያለች እንስት ቁርኣንን መንካት ክልክል ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይን ግን መንካት ሙባሕ ነው።
9ኛ. ቁርኣን ለነቢያችን"ﷺ" ነቢይነት ታምር ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን ለነቢያችን"ﷺ" ነቢይነት ታምር አይደለም።
10ኛ. ቁርኣን ከፊቱ እና ከኃላው ውሸት እንይመጣበት አሏህ ሙሉ ለሙሉ እንደሚጠብቀው ቃል የገባለት የራሱ ንግግር እና በሙተዋቲር የመጣ ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን ሐዲስ ውስጥ ስለሚካተት መቅቡል እና መርዱድ አሉት። "መቅቡል" مَقْبُول ማለት "ቅቡል" ማለት ሲሆን ተቀባይነት ያላቸው የሚባሉት ሶሒሕ እና ሐሰን የሆኑ ናቸው። "መርዱድ" مَردُود "ውድቅ" ማለት ሲሆን ውድቅ ሐዲስ የሚባሉት ዶዒይፍ እና መውዱዕ የሆኑ ናቸው።

ዋቢ መጽሐፍ የሼይኽ ዶክተር ያሲር ቋዲ መጽሐፍ ይመልከቱ፦
Abu Ammaar Yasir Qadhi 1999. Introduction to the Sciences of the Qura̓an. Page 72-74

“አሏሁ አዕለም” اَللّٰهُ أَعْلَم‎

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
👇🙏💜

በሽታ ከሰው ወደ ሰው እንደሚጋባ ሁሉ ጤንነትም ከሰው ወደ ሰው ይጋባል። ጤናማ አስተሳሰብ ካላቸው ሰዎች ጋር መዋል ጤናማ አስተሳሰብ እንድንይዝ ያረገናል። ሰው የአስተሳሰብ እና የድርጊት ውጤት ነው።

የአስተሳሰብ ውጤት
ሰው ለራሱ እራሱ የሚሰጠው እና የሚነገረው ነገር ያ ማንነቱ ነው። ወሒድ ማለት ወሒድ ለወሒድ የነገረው ነገር ነው። ለራሴ እችላለው፣ እሞክራለው፣ እጎብዛለው ብዬ ካልኩት እችላለው፣ እሞክራለው፣ እጎብዛለው፥ በተቃራኒው ለራሴ አትችልም፣ አረባም፣ ደካማ ነኝ ካልኩት እራሴ የማይችል፣ የማይረባ እና ደካማ እሆናለው።

የድርጊት ውጤት
ሰው አስተዳደጉ እና አዋዋሉ በሕይወቱ ላይ አውንታዊ ሆነ አሉታዊ ተጽእኖ ማድረግ ይችላል። ልጆቻችንን በጥሩ አስተዳደግ ማሳደግ እና አዋዋላቸውን ማሳመር አለብን! ይህ ትውልድን የመቅረጽ መርሐ-ግብር ለትውልድ የሚሆን መደላድል ነው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
የቂራኣት ልዩነት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

25፥32 እነዚያ የካዱትም «ቁርኣን በእርሱ ላይ ለምን በጠቅላላ አንድ ጊዜ አልተወረደም» አሉ፡፡ *እንደዚሁ በእርሱ ልብህን ልናረጋ ከፋፍለን አወረድነው፤ ቀስ በቀስ መለያየትንም ለየነው*፡፡ وَقَالَ الَّذِينَ كَفَرُوا لَوْلَا نُزِّلَ عَلَيْهِ الْقُرْآنُ جُمْلَةً وَاحِدَةً ۚ كَذَٰلِكَ لِنُثَبِّتَ بِهِ فُؤَادَكَ ۖ وَرَتَّلْنَاهُ تَرْتِيلًا

“ቁርኣን” قُرْءَان የሚለው ቃል “ቀረአ” قَرَأَ ማለትም “አነበበ” ወይም “አነበነበ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን “መነባነብ”recitation” ማለት ነው፤ የቁርኣን “አነባነብ” ደግሞ “ቂራኣት” قـِراءات ይባላል፤ አምላካችን አላህ በጂብሪል ለነቢያችን”ﷺ” ቁርኣንን አስቀርቷቸዋል፦
87፥6 *ቁርኣንን በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም*፡፡ سَنُقْرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰ
75፥18 *ባነበብነውም ጊዜ ንባቡን ተከተል*፡፡ فَإِذَا قَرَأْنَاهُ فَاتَّبِعْ قُرْآنَهُ

“እናስነብብሃለን” ለሚለው የገባው “ሠኑቅኡሪኡከ” سَنُقْرِئُكَ ሲሆን “ባነበብነው” ለሚለው ደግሞ “ቀረእናሁ” قَرَأْنَاهُ ነው፤ ይህ የሚያሳየው የአላህ ንግግር መነባነብ መሆኑን ነው፤ አምላካችን አላህ ይህንን ቁርኣን ወደ ነቢያችን”ﷺ” ያስቀራው በተርቲል ነው፦
25፥32 እነዚያ የካዱትም «ቁርኣን በእርሱ ላይ ለምን በጠቅላላ አንድ ጊዜ አልተወረደም?» አሉ፤ *እንደዚሁ በእርሱ ልብህን ልናረጋ በተርቲል አነበብነው*፡፡ وَقَالَ الَّذِينَ كَفَرُوا لَوْلَا نُزِّلَ عَلَيْهِ الْقُرْآنُ جُمْلَةً وَاحِدَةً ۚ كَذَٰلِكَ لِنُثَبِّتَ بِهِ فُؤَادَكَ ۖ وَرَتَّلْنَاهُ تَرْتِيلًا

“ረተልናሁ” رَتَّلْنَاهُ ማለት “አነበብነው” ማለት ሲሆን “ተርቲል” تَرْتِيل ማለት “የአነባነብ ስልት”manner of recitation” ማለት ነው፦
73፥4 ወይም በእርሱ ላይ ጨምር፤ *ቁርኣንንም በተርቲል ማንበብን አንብብ*፡፡ أَوْ زِدْ عَلَيْهِ وَرَتِّلِ الْقُرْآنَ تَرْتِيلًا

እዚህ አንቀጽ ላይ “አንብብ” ለሚለው የገባው “ረተል” رَتَّلْ ሲሆን በተርቲል መቅራትን ያመልክታል፤ “ተርቲላ” تَرْتِيلًا የሚለው የተርቲል አንስታይ መደብ ነው። ይህ አንዱ ቁርኣን ወደ ነቢያችን”ﷺ” የወረደው በሰባት አይነት የአቀራር ስልት ነው፦
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 13
ኢብኑ ዐባሥ”ረ.ዐ.” እንደተረከው የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”ጂብሪል ለእኔ በአንድ ሐርፍ አቀራር ይቀራልኝ ነበር፤ ከዚያም እኔ በሌላ ሐርፍ እንዲያስቀራኝ ጠየኩት፤ በተደጋጋሚ ስጠይቀው በሰባት አሕሩፍ በመቅራት ጨመረልኝ*። أَنَّ ابْنَ عَبَّاسٍ ـ رضى الله عنهما ـ حَدَّثَهُ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ أَقْرَأَنِي جِبْرِيلُ عَلَى حَرْفٍ فَرَاجَعْتُهُ، فَلَمْ أَزَلْ أَسْتَزِيدُهُ وَيَزِيدُنِي حَتَّى انْتَهَى إِلَى سَبْعَةِ أَحْرُفٍ ‏”‌‏.‏
“ሐርፍ” حَرف ማለት ቋንቋዊ ትርጉሙ “ፊደል” ማለት ሲሆን እዚህ ዐውድ ላይ ግን “የአነባነብ ስልት”mode of recitation” ማለት ነው፤ ምክንያቱም “አቅረአኒ” أَقْرَأَنِي ማለትም “ይቀራልኝ” የሚል ሃይለ-ቃል ስላለ፤ የሐርፍ ብዙ ቁጥር “አሕሩፍ” أَحْرُف ነው፤ ይህ የቁርኣን አነባነብ ልዩነት ከአላህ በጂብሪል ለነቢያችን”ﷺ” የተወረደ ሲሆን ይህንን ልዩነት በነብያችን”ﷺ” ዘመን በአንድ የቁሬሽ ዘዬ በነበሩት በዑመር ኢብኑል ኸጧብ”ረ.ዐ.” እና በሂሻም ኢብኑ ሐኪም”ረ.ዐ.” መካከል በነበረው የቂራኣት ልዩነት ማየት ይቻላል፦
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 14
ዑመር ኢብኑል ኸጧብ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ *”የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” በሕይወት እያሉ ሂሻም ኢብኑ ሐኪም”ረ.ዐ.” ሱረቱል ፉርቃንን ሲቀራ ሰማሁት፤ የእርሱ አቀራር የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ለእኔ ባልቀሩልኝ በተለየ በሌላ ሐርፍ ሲቀራ ሰማሁት፤ በሶላቱ ላይ እያለ ወደ እርሱ ዘልዬ ነበር፤ ነገር ግን ንዴቴን መቆጣጠር ነበረብኝ፤ ሶላቱን በጨረሰ ጊዜ በአንገቱ ዙሪያ ከላይ ያለውን ልብስ አውልቄ በእርሱ ያዝኩትና፦ “እኔ የሰማሁትን ይህንን ማን ነው ያስተማረህ? ብዬ ስለው፦ “የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ብሎ መለሰልኝ፤ እኔም፦ “ከአንተ በተለየ ለእኔ የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ያስተማሩኝ? ትዋሻለህ አልኩት፤ ከዚያም ወደ የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” አመጣሁት፤ ከዚያም፦ “ለአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ይህንን ሰው ሱረቱል ፉርቃንን እርሶ ባላስተማሩኝ ሐርፍ ሲቀራ ሰማሁት፤ የአላህ መልእክተኛም”ﷺ”፦ “ልቀቀው፤ ሂሻም ሆይ! ቅራ አሉት፤ ከዚያም እኔ በሰማሁበት ሐርፍ ሲቀራ ሰማሁት፤ የአላህ መልእክተኛም”ﷺ”፦ “በዚህ ሐርፍ ለእኔ ተወርዶልኛል፤ ዑመር ሆይ! ቅራ አሉኝ፤ እኔ እሳቸው ባስተማሩኝ ቀራሁኝ፤ እርሳቸውም፦ “ለእኔ በዚህ ሐርፍ ተወርዶልኛል፤ ቁርኣንን በሰባት ሐርፎች እንድቀራ ተወርዶልኛል፤ ስለዚህ የትኛውንም የሚቀላችሁን ቅሩት*። سَمِعَا عُمَرَ بْنَ الْخَطَّابِ، يَقُولُ سَمِعْتُ هِشَامَ بْنَ حَكِيمٍ، يَقْرَأُ سُورَةَ الْفُرْقَانِ فِي حَيَاةِ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم فَاسْتَمَعْتُ لِقِرَاءَتِهِ فَإِذَا هُوَ يَقْرَأُ عَلَى حُرُوفٍ كَثِيرَةٍ لَمْ يُقْرِئْنِيهَا رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم فَكِدْتُ أُسَاوِرُهُ فِي الصَّلاَةِ فَتَصَبَّرْتُ حَتَّى سَلَّمَ فَلَبَّبْتُهُ بِرِدَائِهِ فَقُلْتُ مَنْ أَقْرَأَكَ هَذِهِ السُّورَةَ الَّتِي سَمِعْتُكَ تَقْرَأُ‏.‏ قَالَ أَقْرَأَنِيهَا رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم‏.‏ فَقُلْتُ كَذَبْتَ فَإِنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَدْ أَقْرَأَنِيهَا عَلَى غَيْرِ مَا قَرَأْتَ، فَانْطَلَقْتُ بِهِ أَقُودُهُ إِلَى رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم فَقُلْتُ إِنِّي سَمِعْتُ هَذَا يَقْرَأُ بِسُورَةِ الْفُرْقَانِ عَلَى حُرُوفٍ لَمْ تُقْرِئْنِيهَا‏.‏ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏”‏ أَرْسِلْهُ اقْرَأْ يَا هِشَامُ ‏”‌‏.‏ فَقَرَأَ عَلَيْهِ الْقِرَاءَةَ الَّتِي سَمِعْتُهُ يَقْرَأُ‏.‏ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏”‏ كَذَلِكَ أُنْزِلَتْ ‏”‌‏.‏ ثُمَّ قَالَ ‏”‏ اقْرَأْ يَا عُمَرُ ‏”‌‏.‏ فَقَرَأْتُ الْقِرَاءَةَ الَّتِي أَقْرَأَنِي، فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏”‏ كَذَلِكَ أُنْزِلَتْ، إِنَّ هَذَا الْقُرْآنَ أُنْزِلَ عَلَى سَبْعَةِ أَحْرُفٍ فَاقْرَءُوا مَا تَيَسَّرَ مِنْهُ ‏”‌‏.‏

እንግዲህ ይህንን ሰባት የአነባነብ ስልት ከነብያችን”ﷺ” በዋነኝነት ያስተላለፉ ሰሃባዎች ዑበይ ኢብኑ ከዐብ፣ ዘይድ ኢብኑ ሣቢት፣ ዐብደሏህ ኢብኑ መሥዑድ፣ አቡ አዝ-ዘርዳ፣ ዐሊ ኢብኑ አቡ ጧሊብ፣ አቡ ሙሳ አልሻሪ፣ ዑስማን ኢብኑ አፋን ናቸው።
በሰባቱ አነባነብ ስልት የተላለፈ ሪዋያህ ደግሞ፦
1ኛ. ቃሪ ከመዲና ናፊ ኢብኑ አብ ሲሆን ቂራአቱ የተላለፈው ደግሞ ከዑበይ ኢብኑ ከዐብ ነው።
2ኛ. ቃሪ ከመካ ኢብኑ ከሲር ሲሆን ቂራአቱ የተላለፈው ደግሞ ከዘይድ ኢብኑ ሣቢት ነው።
3ኛ. ቃሪ ከደማስቆ አቡ አምር ሲሆን ቂራአቱ የተላለፈው ደግሞ ከዐብደሏህ ኢብኑ መሥዑድ ነው።
4ኛ. ቃሪ ከባስራ ኢብኑ አምር ሲሆን ቂራአቱ የተላለፈው ደግሞ ከአቡ አዝ-ዘርዳ ነው።
5ኛ. ቃሪ ከኩፋ አሲም ኢብኑ አብ ሲሆን ቂራአቱ የተላለፈው ደግሞ ከዐሊ ኢብኑ አቡጣሊብ ነው።
6. ቃሪ ከኩፋ ሃምዛ ኢብኑ ሲሆን ቂራአቱ የተላለፈው ደግሞ ከአቡ ሙሳ አልሻሪ ነው።
7. ቃሪ ከኩፋ አል-ኪሳኢ ሲሆን ቂራአቱ የተላለፈው ሃቢብደግሞ ከዑስማን ኢብኑ አፋን ነው።

“ሪዋያህ” رِواية ማለት “መስተጋብ” “ስንክሳር” “transmission” ማለት ነው፤ ይህ በሙተዋቲር የተላለፈው ሰንሰለት የሃፍሥ ሪዋያ፣ የወርሽ ሪዋያ፣ የቃሉን ሪዋያ፣ የዱሪ ሪዋያ፣ የሂሻም ሪዋያ፣ የሩህ ሪዋያ እና የባዚ ሪዋያ ሲባል ሲሆን ከአላህ በጂብሪል የተወረደ ግህደተ-መለኮት እንጂ ሰዎች የፈጠሩት ልዩነት አይደለም።
የቁርኣን አነባነቡ ጤናማ የኢዕራብ ልዩነት አለው፤ “ኢዕራብ” إﻋﺮﺍﺏ ማለት “ሙያ”case” ማለት ሲሆን ይህ ሙያ “ፈትሐህ” فَتْحَة “ከሥራህ” كَسْرَة “ደማህ” ضَمَّة በሚባሉ አጭር አናባቢ ሐርፎች ላይ ያገለግላሉ።
በፈትሐህ የሚያገለግለው ሙያ “መንሱብ” منصوب ማለትም ተሳቢ ሙያ”accusative case” ይባላል።
በከሥራህ የሚያገለግለው ሙያ “መጅሩር” مجرور ማለትም አገናዛቢ ሙያ”genitive case” ይባላል።
በደማ የሚያገለግለው ሙያ ደግሞ “መርፉዕ” مرفوع ማለትም ባለቤት ሙያ”nominative case” ይባላል።
እዚህ ድረስ ከተግባባን ለናሙና ያክል ሁለት ሁለት ሪዋያዎችን ማየት እንችላለን፦
30፥54 *አላህ ያ “ከደካማ” ፍትወት ጠብታ የፈጠራችሁ ነው*፡፡ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَكُم مِّن ضَعْف
ሱነን አቢ ዳውድ: መጽሐፍ 32, ሐዲስ 10
ዐብደሏህ ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ ዐጢያህ ኢብኑ ሠዕድ አል-ዐውፍፊይ እንዳለው፦ *”እኔ ለዐብደሏህ ኢብኑ ዑመር “አላህ ያ “ከደካማ”ደዕፍ” ፍትወት ጠብታ የፈጠራችሁ ነው”* ብዬ ቀራሁለት፤ እርሱም፦ *”ከደካማ”ዱዕፍ”*
አለ፤ *አንተ ለእኔ እንደቀራኸው እኔም ለአላህ መልእክተኛ ቀርቻለው፤ እኔ አንተን እንዳስያዝኩህ እርሳቸው እኔን አስይዘውኛል”*። عَنْ عَطِيَّةَ بْنِ سَعْدٍ الْعَوْفِيِّ، قَالَ قَرَأْتُ عَلَى عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عُمَرَ ‏{‏ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَكُمْ مِنْ ضَعْفٍ ‏}‏ فَقَالَ ‏{‏ مِنْ ضُعْفٍ ‏}‏ قَرَأْتُهَا عَلَى رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم كَمَا قَرَأْتَهَا عَلَىَّ فَأَخَذَ عَلَىَّ كَمَا أَخَذْتُ عَلَيْكَ ‏.‏

የዱሪ ቂሪኣት “ዷድ” ض ፈትሐህ “ደ” ضَ በሚል ሪዋያህ “ደዕፍ” ضَعْف ብሎ ሲቀራው፤ የቃሉን ቂሪኣት ደግሞ “ዷድ” ض ደማህ “ዱ” ضُ በሚል ሪዋያህ “ዱዕፍ” ضُعْف ተብሎ ይቀራዋል።
እንቀጥል፦
11፥46 አላህም፦ «ኑሕ ሆይ! እርሱ ከቤተሰብህ አይደለም፤ *እርሱ መልካም ያልሆነ ሥራ ነው*። قَالَ يَا نُوحُ إِنَّهُ لَيْسَ مِنْ أَهْلِكَ ۖ إِنَّهُ عَمَلٌ غَيْرُ صَالِح
ሱነን አቢ ዳውድ: መጽሐፍ 32, ሐዲስ 15
ኡሙ ሰለማህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው፦
*”ሻህር ኢብኑ ሐውሸብም አለ፦ “እኔም ኡሙ ሰለማህን የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዴት አድርገው ነው “እርሱ መልካም ያልሆነ”ገይሩ” ሥራ ነው” የሚለውን ይህንን አንቀጽ የሚቀሩት? እርሷም፦ “እርሱ መልካም ያልሆነ”ገይረ” ሥራ ነው” ብለው ነው የሚቀሩት አለች*። عَنْ شَهْرِ بْنِ حَوْشَبٍ، قَالَ سَأَلْتُ أُمَّ سَلَمَةَ كَيْفَ كَانَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم يَقْرَأُ هَذِهِ الآيَةَ ‏{‏ إِنَّهُ عَمَلٌ غَيْرُ صَالِحٍ ‏}‏ فَقَالَتْ قَرَأَهَا ‏{‏ إِنَّهُ عَمِلَ غَيْرَ صَالِحٍ ‏}‏

የሂሻም ቂሪኣት “ሯ” ر ደማህ “ሩ” رُ በሚል ሪዋያህ “ገይሩ” غَيْرُ ብሎ ሲቀራው፤ የባዚ ቂሪኣት ደግሞ “ሯ” ر ፈትሐህ “ረ” رَ በሚል ሪዋያህ “ገይረ” غَيْرَ ተብሎ ይቀራዋል።
እንቀጥል፦
1፥4 *የፍርዱ ቀን ባለቤት ለኾነው*፡፡ مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ

የሃፍሥ ቂሪኣት “ሚም” م ፈትሐህ ያ ስኩን “ማ” مَا በሚል ሪዋያህ ሁለት ሃረካህ ስቦ “ማሊክ” مَالِك ብሎ ሲቀራው፤ የወርሽ ቂሪኣት ደግሞ “ሚም” م ፈትሐህ “መ” مَ በሚል ሪዋያህ አንድ ሃረካህ ስቦ “መሊክ” مَلِك ተብሎ ይቀራዋል።
እንቀጥል፦
1፥6 *ቀጥተኛውን “መንገድ” ምራን*፡፡ اهْدِنَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ

የሃፍሥ ቂሪኣት “ሷድ” ص ከሥራህ “ሲ” صِ በሚል ሪዋያህ “ሲሯጥ” صِرَٰط ብሎ ሲቀራው፤ የወርሽ ቂሪኣት ደግሞ “ሢን” س ከሥራህ “ሢ” سِ በሚል ሪዋያህ “ሢሯጥ” ِسِرَٰط ተብሎ ይቀራዋል።
እንቀጥል፦
5፥6 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ወደ ሶላት በቆማችሁ ጊዜ ፊቶቻችሁን፣ እጆቻችሁንም እስከ ክርኖች እጠቡ፡፡ ራሶቻችሁንም በውሃ አብሱ፤ *”እግሮቻችሁንም” እስከ ቁርጭምጭሚቶች እጠቡ*፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ إِذَا قُمْتُمْ إِلَى ٱلصَّلَوٰةِ فَٱغْسِلُوا۟ وُجُوهَكُمْ وَأَيْدِيَكُمْ إِلَى ٱلْمَرَافِقِ وَٱمْسَحُوا۟ بِرُءُوسِكُمْ وَأَرْجُلَكُمْ إِلَى ٱلْكَعْبَيْنِ

የዱሪ ቂሪኣት “ላም” ل ፈትሐህ “ለ” لَ በሚል ሪዋያህ “አርጁ’ለ’ኩም” أَرْجُلَكُمْ ብሎ ሲቀራው፤ የሩህ ቂሪኣት ደግሞ “ላም” ل ከሥራህ “ሊ” لِ በሚል ሪዋያህ “አርጁ’ሊ’ኩም” أَرْجُلِكُمْ ተብሎ ይቀራዋል።
እንቀጥል፦
33:40 ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድንም ሰው አባት አይደለም፤ ነገር ግን የአላህ መልክተኛ እና “”የነቢያት መደምደሚያ”” ነው፤ አላህም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው مَا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَا أَحَدٍ مِنْ رِجَالِكُمْ وَلَٰكِنْ رَسُولَ اللَّهِ وَخَاتَمَ النَّبِيِّينَ وَكَانَ اللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا

የአሲም ቂርአት ላይ “ኺታም” خِتَٰـم ሲሆን የኪሳእ ቂርአት ላይ ደግሞ “ኻተም” خَاتَم ሲሆን ትርጉሙ “መጨረሻ” “መቋጫ” “ማጠናቀቂያ” ማለት ነው። እንቀጥል፦
8፥128 *ከጎሳችሁ የሆነ ችግራችሁ በእርሱ ላይ ጽኑ የሆነ፣ በእናንተ እምነት ላይ የሚጓጓ፣ በምእምናን ላይ ርኅሩኅ አዛኝ የኾነ መልክተኛ በእርግጥ መጣላችሁ*፡፡ لَقَدْ جَاءَكُمْ رَسُولٌ مِّنْ أَنفُسِكُمْ عَزِيزٌ عَلَيْهِ مَا عَنِتُّمْ حَرِيصٌ عَلَيْكُم بِالْمُؤْمِنِينَ رَءُوفٌ رَّحِيمٌ

የሂሻም ቂሪኣት “ፋ” ف ደማህ “ፉ” فُ በሚል ሪዋያህ “አን’ፉ’ሢኩም” أَنْفُسِكُمْ ብሎ ሲቀራው፤ የባዚ ቂሪኣት ደግሞ “ፋ” ف ፈትሐህ “ፈ” فَ በሚል ሪዋያህ “አን’ፈ’ሲኩም” أَنْفَسِكُم ተብሎ ይቀራዋል።
እንዲህ አይነት ጤናማ የኢዕራብ ልዩነት ከዓለማቱ ጌታ ከአላህ የተወረደ እንጂ ነብያችን”ﷺ” ሆኑ ሶሐባህ ወይም ታቢኢይ አሊያም አትባኡ ታቢኢይ የፈለሰፉት አይደለም። አምላካችን አላህ እራሱ በተርቲል እንደለየው ይናገራል፦
25፥32 እነዚያ የካዱትም «ቁርኣን በእርሱ ላይ ለምን በጠቅላላ አንድ ጊዜ አልተወረደም» አሉ፡፡ *እንደዚሁ በእርሱ ልብህን ልናረጋ ከፋፍለን አወረድነው፤ ቀስ በቀስ መለያየትንም ለየነው*፡፡ وَقَالَ الَّذِينَ كَفَرُوا لَوْلَا نُزِّلَ عَلَيْهِ الْقُرْآنُ جُمْلَةً وَاحِدَةً ۚ كَذَٰلِكَ لِنُثَبِّتَ بِهِ فُؤَادَكَ ۖ وَرَتَّلْنَاهُ تَرْتِيلًا

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ፍች በኢሥላም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

65፥2 *"ጊዜያቸውንም ለመዳረስ በተቃረቡ ጊዜ በመልካም ያዙዋቸው፡፡ ወይም በመልካም ተለያዩዋቸው፡፡ ከእናንተም ውስጥ ሁለት የትክክለኛነት ባለቤቶችን አስመስክሩ፡፡ ምስክርነትንም ለአላህ አስተካክሉ"*፡፡ فَإِذَا بَلَغْنَ أَجَلَهُنَّ فَأَمْسِكُوهُنَّ بِمَعْرُوفٍ أَوْ فَارِقُوهُنَّ بِمَعْرُوفٍ وَأَشْهِدُوا ذَوَيْ عَدْلٍ مِّنكُمْ وَأَقِيمُوا الشَّهَادَةَ لِلَّهِ

“ሑክም” حُكْم የሚለው ቃል”ሐከመ” حَكَمَ ማለትም “ፈረደ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ፍርድ” ወይም “ሕግ” ማለት ነው፥ “አሕካም” أَحْكَام‎ ማለት ደግሞ የሑክም ብዙ ቁጥር ሲሆን “ሕግጋት” ማለት ነው። በኢሥላም አሕካም በአምስት ዋና ዋና ክፍል ይከፈላል፥ እነርሱም፦
1ኛ. “ፈርድ” فَرْد‎ ማለትም “የታዘዘ” ግዴታ ነው።
2ኛ. “ሙስተሐብ” مُسْتَحَبّ‎ ማለትም “የተወደደ” ሡናህ ነው።
3ኛ. “ሙባሕ” مُبَاح‌‌‎ ማለትም “የተፈቀደ” ሐላል ነው።
4ኛ. “መክሩህ” مَكْرُوه‎ ማለትም “የተጠላ” ነገር ነው።
5ኛ. “ሐራም” حَرَام ማለትም “የተከለከለ” ነገር ነው።

"ጦላቅ" طَّلَاق የሚለው ቃል "ጦሉቀ" طَلُقَ‎ ማለትም "ፈታ" ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ፍች"divorce" ማለት ነው፥ "አጥ-ጦላቅ" الطَّلَاق ደግሞ ከአምስቱ አሕካም መክሩህ ነው፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 10, ሐዲስ 2096
ዐብደሏህ ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"አሏህ ዘንድ የተጠላ ግን የተፈቀደው ፍች ነው"*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عُمَرَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ "‏ أَبْغَضُ الْحَلاَلِ إِلَى اللَّهِ الطَّلاَقُ

ጋብቻው ከጥቅሙ ጉዳቱ ካመዘነ ፍች የተጠላ ቢሆንም መፍትሔ ነው፥ ፍች ለማድረግ የተለያዩ ቅድመ-ሁኔታዎች አሉት። ለምሳሌ ፍች ለመፈጸም በተራክቦ ካልተነካኩ እና መህር ካልተወሰነ በማንኛውም ጊዜ መሆን ይችላል፦
2፥236 *"ሴቶችን ሳትነኳቸው ወይም ለእነርሱ መህርን ሳትወስኑላቸው ብትፈቷቸው በእናንተ ላይ ኃጢኣት የለባችሁም"*፡፡ لَّا جُنَاحَ عَلَيْكُمْ إِن طَلَّقْتُمُ النِّسَاءَ مَا لَمْ تَمَسُّوهُنَّ أَوْ تَفْرِضُوا لَهُنَّ فَرِيضَةً

ነገር ግን ተራክቦ ከተፈጸመ ፍች የሚፈጸመው የዒዳህ ጊዜ ሲገባደድ ነው፥ "ዒዳህ” عِدَّة ማለት ሁለት ጥንዶች ከተጋቡ በኃላ ተራክቦ አድርገው ከዚያም አለመግባባት ቢፈጠር ፍቺ ለማድረግ ቢያስቡ ቅድሚያ ነፍሰ-ጡር መሆኗን ለማረጋገጥ የሚቆይበት የሦስት ወር ጊዜ ቆይታ ነው፦
65፥1 *"አንተ ነቢዩ ሆይ! ሴቶችን መፍታት ባሰባችሁ ጊዜ ለዒዳቸው ፍቱዋቸው! ዒዳንም ቁጠሩ፡፡ አላህንም ጌታችሁን ፍሩ"*፡፡ يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ إِذَا طَلَّقْتُمُ النِّسَاءَ فَطَلِّقُوهُنَّ لِعِدَّتِهِنَّ وَأَحْصُوا الْعِدَّةَ ۖ وَاتَّقُوا اللَّهَ رَبَّكُمْ

"ፍቱዋቸው" ለሚለው የገባው ቃል "ጦለቁሁነ" طَلِّقُوهُنَّ መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። ጊዜያቸውንም ለመዳረስ በተቃረቡ ጊዜ ባል የማሰላሰያ ጊዜ አግኝቶ ከተጸጸተ በመልካም ሚስት አድርጎ መያዝ አለበት፥ አሊያም ጉዳይ ከበድ ያለ እና የማያዛልቅ ከሆነ በመልካም መለያየት ይቻላል፦
65፥2 *"ጊዜያቸውንም ለመዳረስ በተቃረቡ ጊዜ በመልካም ያዙዋቸው፡፡ ወይም በመልካም ተለያዩዋቸው፡፡ ከእናንተም ውስጥ ሁለት የትክክለኛነት ባለቤቶችን አስመስክሩ፡፡ ምስክርነትንም ለአላህ አስተካክሉ"*፡፡ فَإِذَا بَلَغْنَ أَجَلَهُنَّ فَأَمْسِكُوهُنَّ بِمَعْرُوفٍ أَوْ فَارِقُوهُنَّ بِمَعْرُوفٍ وَأَشْهِدُوا ذَوَيْ عَدْلٍ مِّنكُمْ وَأَقِيمُوا الشَّهَادَةَ لِلَّهِ

"በመልካም ተለያዩዋቸው" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! በጦላቅ "በኑናህ" ጥንቃቄ የተሞላበት እሳቤ ነው። "በኑናህ" بَيْنُونَة ማለት "መለየት" ማለት ሲሆን በኑናህ "በኑናቱ አስ-ሱጊራ" እና "በኑናቱል ኩብራ" ተብለው ለሁለት ይከፈላሉ።
"ሱግራ" صُغْرَى የሚለው ቃል "አስገር" أَصْغَر ለሚለው አንስታይ መደብ ሲሆን "ትንሽ" ማለት ነው፥ በጥቅሉ "በኑናቱ አስ-ሱግራ" بَيْنُونَة الصَغِيرَة ማለት "ትንሹ መለየት" ማለት ነው። ይህ ትንሹ ፍች የሚቻለው ሁለት ጊዜ ብቻ ነው፥ ከዚህ በኋላ በመልካም መያዝ ወይም በበጎ አኳኋን ማሰናበት ነው፦
2፥229 *"ፍች ሁለት ጊዜ ነው፥ ከዚህ በኋላ በመልካም መያዝ ወይም በበጎ አኳኋን ማሰናበት ነው"*፡፡ الطَّلَاقُ مَرَّتَانِ ۖ فَإِمْسَاكٌ بِمَعْرُوفٍ أَوْ تَسْرِيحٌ بِإِحْسَانٍ

ጥንዶቹ ሁለት ጊዜ ከተፋቱ በኃላ ከመማለስ በኃላ ለሦስተኛ ጊዜ ከተፋቱ ይህ ፍች በኑናቱል ኩብራ ነው። "ኩብራ" كُبْرَى የሚለው ቃል "አክበር" أَكْبَر ለሚለው አንስታይ መደብ ሲሆን "ትልቅ" ማለት ነው፥ በጥቅሉ "በኑናቱል ኩብራ" بَيْنُونَة الكُبْرَى ማለት "ትልቁ መለየት" ማለት ነው፦
2፥230 *"ሦስተኛ ቢፈታትም ከዚህ በኋላ ሌላን ባል እስከምታገባ ድረስ ለእርሱ አትፈቀድለትም፡፡ ሁለተኛው ባል ቢፈታትም የአላህን ሕግጋት መጠበቃቸውን ቢያውቁ በመማለሳቸው በሁለቱም ላይ ኃጢኣት የለባቸውም"*፡፡ ይህችም የአላህ ሕግጋት ናት ለሚያውቁ ሕዝቦች ያብራራታል፡፡ فَإِن طَلَّقَهَا فَلَا تَحِلُّ لَهُ مِن بَعْدُ حَتَّىٰ تَنكِحَ زَوْجًا غَيْرَهُ ۗ فَإِن طَلَّقَهَا فَلَا جُنَاحَ عَلَيْهِمَا أَن يَتَرَاجَعَا إِن ظَنَّا أَن يُقِيمَا حُدُودَ اللَّهِ ۗ وَتِلْكَ حُدُودُ اللَّهِ يُبَيِّنُهَا لِقَوْمٍ يَعْلَمُونَ

ጥንዶቹ ለሦስተኛ ጊዜ ከተፋቱ በኃላ ሌላ ማግባታቸው ሐላል ነው፥ በተቃራኒው ጥንዶቹ ለሦስተኛ ጊዜ ከተፋቱ በኃላ ከሁለት አንደኛው ሌላ አግብቶ እንካልፈታ ድረስ ተመልሶ መጋባት ሐራም ነው። ነገር ግን አንድ ወንድ ወይም አንዲት ሴት የበፊት የትዳር አጋር ተመልሶ ለማግባት ሲባል በውስጥ ፍችን ነይተው የኃለኛውን የትዳር አጋርን ማግባት እና መፍታት ከሐራምም አልፎ እርግማንም ነው፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 9, ሐዲስ 2011
ዑቅባህ ኢብኑ ዓሚር እንደተረከው፦ *"የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" ስለ ቅንዝንዝ ፍየል አልነገርኳችሁንም? አሉ፥ እነርሱም፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" ሆይ! አዎ አሉ። እርሳቸው፦ "ቅንዝንዝ ፍየል ሙሐሊል ነው፥ አሏህ ሙሐሊልን እና ሙሐለል ለሁ እረግሟል" አሉ"*። قَالَ عُقْبَةُ بْنُ عَامِرٍ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏"‏ أَلاَ أُخْبِرُكُمْ بِالتَّيْسِ الْمُسْتَعَارِ ‏"‏ ‏.‏ قَالُوا بَلَى يَا رَسُولَ اللَّهِ قَالَ ‏"‏ هُوَ الْمُحَلِّلُ لَعَنَ اللَّهُ الْمُحَلِّلَ وَالْمُحَلَّلَ لَهُ ‏"‏ ‏.‏
"ሙሐሊል" مُحَلِّل ማለት ሁለተኛ የትዳር አጋር ሆኖ ለመጀመሪያዋ የትዳር አጋር ሲል ለጊዜው አግብቶ ተራክቦ አድርጎ ለመጀመሪያዋ ሲል የሚፈታ ነው። በዚህም ቅንዝንዝ ፍየል ተብሏል፥ ቅንዝንዝ ፍየል ተራክቦ ያደረጋትን ሴት ፍየል ለሌላ ወንድ ፍየል ተራክቦ ማስደረግ ልማዱ ነው። "ሙሐለል ለሁ" مُحَلَّلَ لَهُ ማለት ደግሞ የመጀመሪያው የትዳር አጋር ሆኖ ሁለተኛ የትዳር አጋር ለጊዜው አግብቶ ተራክቦ አድርጎ እንዲሰጠው የሚጠባበቅ ነው፥ ከተጋቡ በኃላ ለፍች ምክንያት ከተፈጠረ መፋታቱ መክሩህ ቢሆንም ለጊዜው ተብሎ ተነይቶ ማግባት ግን ከድጡ ወደ ማጡ ስለሆነ ዝሙት ነው። ስለዚህ በትዳር፣ በፍቺ እና በመማለስ ቀልድ የለም፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 13, ሐዲስ 20
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" አሉ፦ *"ሦስቱ ነገራት የምር ይሁን የምር፥ የቀልድም ይሁን የምር ናቸው። እነርሱም ትዳር፣ ፍች እና መማለስ ናቸው"*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ ثَلاَثٌ جِدُّهُنَّ جِدٌّ وَهَزْلُهُنَّ جِدٌّ النِّكَاحُ وَالطَّلاَقُ وَالرَّجْعَةُ ‏"‏

"ረጅዓህ" رَّجْعَة ማለት "መማለስ" ማለት ሲሆን ከተፋቱ በኃላ እንደገና መጋባትን የሚያመላክት እሳቤ ነው፥ ትዳር ላይ በመልካም መኗኗር እንጂ ማጉላላት አያስልግም። ለአላስፈላጊ ነገር ፍች መጠየቅ መዘዙና ጠንቁ ብዙ ነው፦
4፥19 *"እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! ሴቶችን ያስገደዳችሁ ኾናችሁ ልትወርሱ እና ግልጽን መጥፎ ሥራ ካልሠሩ በስተቀር ከሰጣችኋቸው ከፊሉን ልትወስዱ ልታጉላሏቸውም ለእናንተ አይፈቀድም፡፡ በመልካምም ተኗኗሩዋቸው"*፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا لَا يَحِلُّ لَكُمْ أَن تَرِثُوا النِّسَاءَ كَرْهًا ۖ وَلَا تَعْضُلُوهُنَّ لِتَذْهَبُوا بِبَعْضِ مَا آتَيْتُمُوهُنَّ إِلَّا أَن يَأْتِينَ بِفَاحِشَةٍ مُّبَيِّنَةٍ ۚ وَعَاشِرُوهُنَّ بِالْمَعْرُوفِ
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 10, ሐዲስ 2134
ሰውባን እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ባሏን ለአላስፈላጊ ነገር ፍች የምትጠይቅ ማንኛውም ሴት የጀነት ሽታ በእርሷ ላይ እርም ነው"*። عَنْ ثَوْبَانَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ "‏ أَيُّمَا امْرَأَةٍ سَأَلَتْ زَوْجَهَا الطَّلاَقَ فِي غَيْرِ مَا بَأْسٍ فَحَرَامٌ عَلَيْهَا رَائِحَةُ الْجَنَّةِ ‏"‏

ፍች አሏህ ዘንድ የተጠላ ነው፥ "የተጠላ" ማለት "የማይመከር" ወይም "የማይበረታታ" ማለት ነው። ተስማምቶ መኖር ኃጢአት አይደለም፥ ከተጣሉም መታረቅም መልካም ነው፦
4፥128 *"ሴትም ከባልዋ ጥላቻን ወይም ፊቱን ማዞርን ብታውቅ በመካከላቸው መስማማትን ቢስማሙ በሁለቱ ላይ ኀጢአት የለም፡፡ መታረቅም መልካም ነው"*፡፡ وَإِنِ امْرَأَةٌ خَافَتْ مِن بَعْلِهَا نُشُوزًا أَوْ إِعْرَاضًا فَلَا جُنَاحَ عَلَيْهِمَا أَن يُصْلِحَا بَيْنَهُمَا صُلْحًا ۚ وَالصُّلْحُ خَيْرٌ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 67, ሐዲስ 140
ዓኢሻህ"ረ.ዐ." እንደተረከችው፦ *"ሴትም ከባልዋ ጥላቻን ወይም ፊቱን ማዞርን ብታውቅ" የሚለው ባሏ ከእርሷ ጋር መቆየት ስለማይፈልጋት ሴት እና ግን ፈቶ ሌላ ማግባት ስለሚፈልግ የሚናገር ነው። እርሷም ለእርሱ፦ "ያዘኝ፣ አትፍታኝ፣ ከዚያም ሌላ አግባ። እናም ከእኔ ጋር አታሳልፍ! አትተኛ" አለች። ""ሴትም ከባልዋ ጥላቻን ወይም ፊቱን ማዞርን ብታውቅ በመካከላቸው መስማማትን ቢስማሙ በሁለቱ ላይ ኀጢአት የለም፡፡ መታረቅም መልካም ነው" የሚለውን አሏህ የተናገረው ይህንን ለማመላከት ነው"*። عَنْ عَائِشَةَ ـ رضى الله عنها ـ ‏{‏وَإِنِ امْرَأَةٌ خَافَتْ مِنْ بَعْلِهَا نُشُوزًا أَوْ إِعْرَاضًا‏}‏ قَالَتْ هِيَ الْمَرْأَةُ تَكُونُ عِنْدَ الرَّجُلِ، لاَ يَسْتَكْثِرُ مِنْهَا فَيُرِيدُ طَلاَقَهَا، وَيَتَزَوَّجُ غَيْرَهَا، تَقُولُ لَهُ أَمْسِكْنِي وَلاَ تُطَلِّقْنِي، ثُمَّ تَزَوَّجْ غَيْرِي، فَأَنْتَ فِي حِلٍّ مِنَ النَّفَقَةِ عَلَىَّ وَالْقِسْمَةِ لِي، فَذَلِكَ قَوْلُهُ تَعَالَى ‏{‏فَلاَ جُنَاحَ عَلَيْهِمَا أَنْ يَصَّالَحَا بَيْنَهُمَا صُلْحًا وَالصُّلْحُ خَيْرٌ‏}‏

"ቋድይ" قَضْي የሚለው ቃል "ቋዶ" قَضَى ማለትም "አመዛዘነ" "በየነ" "ፈረደ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "አመዛዝኖ የሚበይን ፈራጅ ወይም ዋቢ" ማለት ነው፥ "ቋዲያህ" قَضِيَّة‎ ማለት ደግሞ "የፍርድ ጉዳይ" ማለት ነው። ቋዲዮች በባል እና በሚስት መካከል ጭቅጭቅ ሲያውቁ ከቤተሰቦቹ ሽማግሌን ከቤተሰቦችዋም ሽማግሌን ይልካሉ፥ ዋቢዎች ማስታረቅን ቢፈልጉ አሏህ ያስማማል። ቋድይ ኢ-ፍትሐዊ እስካልሆነ ድረስ አሏህ ከእርሱ ጋር ነው፦
4፥35 *"እናንተ ዋቢዎች የመካከላቸውንም ጭቅጭቅ ብታውቁ ከቤተሰቦቹ ሽማግሌን ከቤተሰቦችዋም ሽማግሌን ላኩ፡፡ ማስታረቅን ቢሹ አላህ በመካከላቸው ያስማማል"*፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነውና፡፡ وَإِنْ خِفْتُمْ شِقَاقَ بَيْنِهِمَا فَابْعَثُوا حَكَمًا مِّنْ أَهْلِهِ وَحَكَمًا مِّنْ أَهْلِهَا إِن يُرِيدَا إِصْلَاحًا يُوَفِّقِ اللَّهُ بَيْنَهُمَا ۗ إِنَّ اللَّهَ كَانَ عَلِيمًا خَبِيرًا
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 15, ሐዲስ 10
ዐብደሏህ ኢብኑ አቢ አል-አውፋ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ቋድይ ኢ-ፍትሐዊ እስካልሆነ ድረስ አሏህ ከእርሱ ጋር ነው። ኢ-ፍትሐዊ በሆነ ጊዜ ግን አሏህ ከእርሱ ጋር አይደለም፥ እርሱን ሸይጧን ይፈልገዋል"*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ أَبِي أَوْفَى، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ إِنَّ اللَّهَ مَعَ الْقَاضِي مَا لَمْ يَجُرْ فَإِذَا جَارَ تَخَلَّى عَنْهُ وَلَزِمَهُ الشَّيْطَانُ ‏"‏ ‏.‏

አሏህ መልካም እና ያማረ ትዳር ይስጠን! ከተጠላ ፍች ይጠብቀን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ፍች በባይብል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

4፥35 *"እናንተ ዋቢዎች የመካከላቸውንም ጭቅጭቅ ብታውቁ ከቤተሰቦቹ ሽማግሌን ከቤተሰቦችዋም ሽማግሌን ላኩ፡፡ ማስታረቅን ቢሹ አላህ በመካከላቸው ያስማማል"*፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነውና፡፡ وَإِنْ خِفْتُمْ شِقَاقَ بَيْنِهِمَا فَابْعَثُوا حَكَمًا مِّنْ أَهْلِهِ وَحَكَمًا مِّنْ أَهْلِهَا إِن يُرِيدَا إِصْلَاحًا يُوَفِّقِ اللَّهُ بَيْنَهُمَا ۗ إِنَّ اللَّهَ كَانَ عَلِيمًا خَبِيرًا

በሙሴ ሕግ አንድ ወንድ አንድ ሴት መፍታት የሚችለው የፍችዋን ወረቀት በመስጠት ነው፦
ዘዳግም 24፥1 *ሰው ሴትን ወስዶ ቢያገባ፥ የእፍረት ነገር ስላገኘባት በእርሱ ዘንድ ሞገስ ባታገኝ፥ ”የፍችዋን ጽሕፈት ጽፎ በእጅዋ ይስጣት፥ ከቤቱም ይስደዳት”*።
ዘዳግም 24፥3 *"ሁለተኛውም ባል ቢጠላት፥ “የፍችዋንም ጽሕፈት ጽፎ በእጅዋ ቢሰጣት”፥ ከቤቱም ቢሰድዳት፥ ወይም ሚስት አድርጎ ያገባት ሁለተኛው ባልዋ ቢሞት"*።

ነገር ግን በአዲስ ኪዳን አንድ ወንድ አንድ ሴት መፍታት የሚችለው ዝሙት ስትሠራ ብቻ ነው፦
ማቴዎስ 5፥31-32 *"ሚስቱን የሚፈታት ሁሉ የፍችዋን ጽሕፈት ይስጣት ተባለ። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ አመንዝራ ያደርጋታል፥ የተፈታችውንም የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል"*።
ማቴዎስ 19:9 እኔ ግን እላችኋለሁ *"ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን ፈትቶ ሌላዪቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል፥ የተፈታችውንም የሚያገባ ያመነዝራል አላቸው"*።

አንዲት ሴት በጠባይ አለመግባባት ቢኖር ወይም የፍቅር አለመጣጣም ቢኖር በዝሙት ካልሆነ መፈታት አትችልም። ከዚህ ሁሉ የሚገርመው ሚስቱን ፈትቶ ሌላ የሚያገባ አመንዝራ መባሉ ብቻ ሳይሆን የተፈታችው ሴት እርሱ በፈታት ሌላ ሰው እንዳያገባት እቀባ ተጥሎባታል፥ የተፈታች ሴት ሌላ ወንድ ካገባት አመንዝራ ይባላል። ሚስቱን ፈትቶ ሌላዪቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል፥ “የተፈታችውንም የሚያገባ ያመነዝራል አላቸው” የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት። እና ምን ትሆናለች? ሲባል ባልዋ እስኪሞት ድረስ ምንን ማግባት አትችልም፦
ሮሜ 7፥2-3 *"ያገባች ሴት ባልዋ በሕይወት ሲኖር ከእርሱ ጋር በሕግ ታስራለችና”፤ ባልዋ ቢሞት ግን ስለ ባል ከሆነው ሕግ ተፈትታለች። ”ስለዚህ ባልዋ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ ትባላለች”፤ ባልዋ ቢሞት ግን ከሕጉ አርነት ወጥታለችና ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ አይደለችም"*።

ልብ አድርጉ “ባልዋ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ ትባላለች” ባልዋ ቢሞት ግን ከሕጉ አርነት ወጥታለችና ሌላ ወንድ ማግባት ትችላለች። በተለይ የኢሥላምን ሕግ በምዕራባውያን ሚዛን ለሚመዝኑ ክርስቲያኖች ምን ይውጣቸው ይሆን? ዛሬስ በአገራችን ይህ የአዲስ ኪዳን ሕግ ይኖር ይሆን? ፍርድ ቤቱን ያጨናነቀው የክርስቲያኑን ፍቺ ያለ ዝሙት ነው። ከዚህ ሁሉ የሚገርመው ኢየሱስ ባል ሚስቱ ያለ ዝሙት ምክንያት ከፈታ አመንዝራ ነው ሲል ጳውሎስ ደግሞ በተቃራኒው ሚስት ከባልዋ መለያየት ትችላለች ግን ሌላ ወንድ ሳታገባ ትኑር በማለት ይቃረናል፦
1ኛ ቆሮንቶስ 7፥10-11 *"ሚስትም ከባልዋ አትለያይ፥ ”ብትለያይ ግን ሳታገባ ትኑር”*።

ሲጀመር ”ብትለያይ ግን ሳታገባ ትኑር” ማለት “ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን ፈትቶ ሌላዪቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል” ከሚለው ጋር አይጋጭም? ሲቀጥል “ሳታገባ ትኑር” ፍትሐዊ ብይን ነውን? ሢሰልስ ” ባልዋ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ ትባላለች” መባሉስ አግባብ ነውን? ጳውሎስን፦ "ይህንን ትምህርት በአንተ የሚናገረው ጌታ ነውን ወይስ እራስክ? ስንለው "እኔ እላለሁ፥ ጌታም አይደለም" ይለናል። ቀጥለን፦ "አንተስ ብትሆን የምትናገረው ጌታ ተናገር ብሎ አዞህ ነው ወይስ በሞኝነት? ስንለው አይ "የምናገረው በሞኝነት እንጂ ጌታ እንዳዘዘኝ አልናገርም" ይለናል፦
1 ቆሮንቶስ 7፥12 *"ሌሎችንም እኔ እላለሁ፥ ጌታም አይደለም"*።
2 ቆሮንቶስ 11፥17 እንደዚህ ታምኜ ስመካ የምናገረው በሞኝነት እንጂ ጌታ እንዳዘዘኝ አልናገርም።

ባሏ ከሞተስ? ትሉ ይሆናል፥ ባሏ ሲሞት ደግሞ መከራዋ አላለቀም። የባሏን ወንድም ታግባ የሚል ወፍራም ትእዛዝ ይጠብቃታል፦
ዘዳግም 25፥5-10 *"ወንድማማቾች በአንድነት ቢቀመጡ፥ አንዱም ልጅ ሳይኖረው ቢሞት፥ “”የሞተው ሰው ሚስት ሌላ ሰው ታገባ ዘንድ ወደ ውጭ አትሂድ፤ ነገር ግን የባልዋ ወንድም ወደ እርስዋ ገብቶ እርስዋን ያግባ””፥ ከእርስዋም ጋር ይኑር። የምዋቹ ስም ከእስራኤል ዘንድ እንዳይጠፋ ከእርስዋ የሚወለደው በኵር ልጅ በሞተው በወንድሙ ስም ይጠራ። ያም ሰው የወንድሙን ሚስት ማግባት ባይወድድ፥ ዋርሳይቱ በበሩ አደባባይ ወደሚቀመጡ ሽማግሌዎች ሄዳ፦ ዋርሳዬ በእስራኤል ዘንድ ለወንድሙ ስም ማቆም እንቢ አለ፤ ከእኔ ጋር ሊኖርም አልወደደም ትበላቸው። የከተማውም ሽማግሌዎች ጠርተው ይጠይቁት፤ እርሱም በዚያ ቆሞ፦ አገባት ዘንድ አልወድድም ቢል፥ ዋርሳይቱ በሽማግሌዎቹ ፊት ወደ እርሱ ቀርባ፦ የወንድሙን ቤት በማይሠራ ሰው ላይ እንዲህ ይደረግበታል ስትል ጫማውን ከእግሩ ታውጣ፥ በፊቱም እንትፍ ትበልበት። በእስራኤልም ዘንድ ስሙ የጫማ ፈቱ ቤት ተብሎ ይጠራ*።

“ያም ሰው የወንድሙን ሚስት ማግባት ባይወድድ” ስሙ የጫማ ፈቱ ቤት ተብሎ ይጠራ እንጂ በግድ አግባ አይባልም። እርሷን ግን እርሷ የሞተው ሰው ሚስት ሌላ ሰው ታገባ ዘንድ ወደ ውጭ አትሂድ ተብሎ ታዟል እንጂ እንደ ወንዱ የፈለገችውን ማግባት አትችልም። ይህ እኩልነት ነውን? ከዚያም አልፎ ሴቶች ምንም ባልሰሩት በባሎቻቸው ወንጀል ምክንያት ለሌላ ወንዶች ይሰጡ ነበር፦
ኤርሚያስ 8:10 ሰለዚህ *"ሚሰቶቻቸውንም ለሌሎች ወንዶች እሰጣለሁ"*።
2ኛ ሳሙኤል 12፥8 የጌታህንም ቤት ሰጠሁህ፥ *"የጌታህንም ሚስቶች” በብብትህ ጣልሁልህ"*።
2ኛ ሳሙኤል12፥11 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ ከቤትህ ክፉ ነገር አስነሣብሃለሁ፤ *”ሚስቶችህንም በዓይንህ ፊት እወስዳለሁ፥ ለዘመድህም እሰጣቸዋለሁ፥ በዚህችም ፀሐይ ዓይን ፊት ከሚስቶችህ ጋር ይተኛል"*።

እግር እራስን አያክም። በኢሥላም ያለውን የፍች እሳቤ ለመተቸት ቅድሚያ እነዚህ የባይብል አናቅጽ መልስ መስጠት ግድ ይላል እንጂ ሱሪ በአንገት ላድርግ አትበሉ። አሏህ ሂዳያ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ልጅት እናትን መደብደብ

በጥንት ጊዜ እመቤት ባሪያይቱን ትደበድባት ነበር። በመጨረሻው ዘመን ግን ልጅት እናትን መደብደብ ከሰዓቲቱ ምልክት አንዱ ነው፦
ዑመር ኢብኑ ኽጣብ እንዳስተላለፈው፦ “አንድ በጣም ነጭ ልብስ የለበሰና በጣም ጥቁር ጸጉር ያለው ሰው በመጣ ጊዜ ከአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ጋር ነበርን፤ ወደ እርሳቸው ሲጓዝ የመንገደኛነት ምልክት አይታይበትም ነበር፦ ወደ ነቢዩ”ﷺ” እስከሚደርስ ድረስ ከእኛ መካከል ማንም ዐላወቀውም፤ ጉልበቱን በእራሳቸው ጉልበት አስጠግቶ ከዚያም እንዲህ አለ፦ *”ስለ ሰዓቲቱ ንገረኝ" አላቸው፥ እርሳቸውም፦ "ስለ እርሷ ተጠያቂው እኮ ከጠያቂው የበለጠ ዐያውቅም" አሉ። እርሱም፦ "እሺ ስለ ምልክቶቿ ንገረኝ" አለ፥ እርሳቸውም፦ "ባሪያይቱ እመቤትዋን ስትወልድ እና ጫማ የሌላቸውን፣ የተራቆቱትን፣ ድሀና ችግረኛ እረኞችን በቤት ግንባታ ሲሽቀዳደሙህ ያየህ ጊዜ ነው"*። قَالَ عُمَرُ بْنُ الْخَطَّابِ كُنَّا عِنْدَ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم فَجَاءَ رَجُلٌ شَدِيدُ بَيَاضِ الثِّيَابِ شَدِيدُ سَوَادِ الشَّعَرِ لاَ يُرَى عَلَيْهِ أَثَرُ السَّفَرِ وَلاَ يَعْرِفُهُ مِنَّا أَحَدٌ حَتَّى أَتَى النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم فَأَلْزَقَ رُكْبَتَهُ بِرُكْبَتِهِ ثُمَّ قَالَ يَا مُحَمَّدُ أَخْبِرْنِي عَنْ السَّاعَةِ قَالَ مَا الْمَسْئُولُ عَنْهَا بِأَعْلَمَ بِهَا مِنْ السَّائِلِ قَالَ فَأَخْبِرْنِي عَنْ أَمَارَاتِهَا قَالَ أَنْ تَلِدَ الْأَمَةُ رَبَّتَهَا وَأَنْ تَرَى الْحُفَاةَ الْعُرَاةَ رِعَاءَ الشَّاءِ يَتَطَاوَلُونَ فِي الْبِنَاءِ

የነቢያችን"ﷺ" ትንቢት እየተፈጸመ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴት ልጅ እናቷ ቤት ልክ እንደ እመቤት መጦሯ እና እናት ልጇን ቤት ውስጥ እየሠራች መካደሟ እሙንና ቅቡል ቢሆን በህንድ አገር አንዲት ልጅት እናቷን ደብድባ ከአልጋ ላይ ወርራታለች። ይህ እኩይ ድርጊት ያማል! አሏህ ከእንዲህ እኩይ ተግባር ይጠብቀን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom