ነጥብ አሥራ ሦስት
የውመል ሐሥራህ"
"የውመል ሐሥራህ" يَوْمَ الْحَسْرَة ማለት "የቁልጭቱን ቀን" ማለት ነው፦
19፥39 *እነርሱም አሁን በዝንጋቴ ላይ ኾነው ሳሉ እነርሱም የማያምኑ ሲኾኑ ነገሩ በሚፈረድበት ጊዜ "የቁልጭቱን ቀን አስጠንቅቃቸው*፡፡ وَأَنذِرْهُمْ يَوْمَ الْحَسْرَةِ إِذْ قُضِيَ الْأَمْرُ وَهُمْ فِي غَفْلَةٍ وَهُمْ لَا يُؤْمِنُونَ
በዚህ ቀን ኩፋሮች በቁጭት ከሚሉት መካከል፦ “ከመልክተኛው ጋር ቀጥተኛን መንገድ ይዤ በኾነ ዋ ምኞቴ” “አላህን በተገዛን መልክተኛውንም በታዘዝን ኖሮ” በማለት ይቆጫሉ፦
25፥27 *በዳይም «ከመልክተኛው ጋር ቀጥተኛን መንገድ ይዤ በኾነ ዋ ምኞቴ!» እያለ በጸጸት ሁለት እጆቹን የሚነክስበትን ቀን አስታውስ*፡፡ وَيَوْمَ يَعَضُّ الظَّالِمُ عَلَىٰ يَدَيْهِ يَقُولُ يَا لَيْتَنِي اتَّخَذْتُ مَعَ الرَّسُولِ سَبِيلًا
33፥66 ፊቶቻቸው በእሳት ውሰጥ በሚገለባበጡ ቀን *«ዋ ምኞታችን! አላህን በተገዛን መልክተኛውንም በታዘዝን ኖሮ» እያሉ ይጸጸታሉ*፡፡ يَوْمَ تُقَلَّبُ وُجُوهُهُمْ فِي النَّارِ يَقُولُونَ يَا لَيْتَنَا أَطَعْنَا اللَّهَ وَأَطَعْنَا الرَّسُولَا
ኩፋሮች ከቁጭትዋ የተነሳ ሲቆጩ የእሳት ዘበኞች፦ “አስጠንቃቂ አልመጣችሁምን?” በማለት ይጠይቋቸዋል፦
67፥8 *ከቁጭትዋ የተነሳ ልትቆራረጥ ትቀርባለች፡፡ በውስጧ ጭፍሮች በተጣሉ ቁጥር ዘበኞችዋ *«አስጠንቃቂ አልመጣችሁምን?*» በማለት ይጠይቋቸዋል፡፡ تَكَادُ تَمَيَّزُ مِنَ الْغَيْظِ ۖ كُلَّمَا أُلْقِيَ فِيهَا فَوْجٌ سَأَلَهُمْ خَزَنَتُهَا أَلَمْ يَأْتِكُمْ نَذِيرٌ
ኩፋሮች ይህንን መልእክት ተቀብለው ከሙሥሊሞች ጋር በመሆን አንዱን አምላክ ማምለክ ሲገባቸው የተውበት በሩ ከተዘጋ በኃላ በቁጭቱ ቀን፦ “ታላቅ ዕድልን አገኝ ዘንድ ከእነርሱ ጋር በኾንኩ ወይ ምኞቴ” “ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ መልካምን ሥራ ባስቀደምኩ ኖሮ” “ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ” “ዋ ጥፋቴ! እገሌን ወዳጅ ባልያዝኩ ኖሮ እመኛለሁ” ይላሉ፦
4፥73 ከአላህም የኾነ ችሮታ ቢያገኛችሁ በእናንተና በእርሱ መካከል ፍቅር እንዳልነበረች ሁሉ *«ታላቅ ዕድልን አገኝ ዘንድ ከእነርሱ ጋር በኾንኩ ወይ ምኞቴ!»* ይላል፡፡ وَلَئِنْ أَصَابَكُمْ فَضْلٌ مِّنَ اللَّهِ لَيَقُولَنَّ كَأَن لَّمْ تَكُن بَيْنَكُمْ وَبَيْنَهُ مَوَدَّةٌ يَا لَيْتَنِي كُنتُ مَعَهُمْ فَأَفُوزَ فَوْزًا عَظِيمًا
89፥24 *«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ መልካምን ሥራ ባስቀደምኩ ኖሮ»* ይላል፡፡ يَقُولُ يَا لَيْتَنِي قَدَّمْتُ لِحَيَاتِي
78፥40 እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም፦ *ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ* በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡ إِنَّا أَنذَرْنَاكُمْ عَذَابًا قَرِيبًا يَوْمَ يَنظُرُ الْمَرْءُ مَا قَدَّمَتْ يَدَاهُ وَيَقُولُ الْكَافِرُ يَا لَيْتَنِي كُنتُ تُرَابًا
25፥28 *«ዋ ጥፋቴ! እገሌን ወዳጅ ባልያዝኩ ኖሮ እመኛለሁ*፡፡ يَا وَيْلَتَىٰ لَيْتَنِي لَمْ أَتَّخِذْ فُلَانًا خَلِيلًا
ነጥብ አሥራ አራት
"የውሙም መሽሁድ"
"የውሙም መሽሁድ" يَوْمٌ مَّشْهُود ማለት "የሚመሰከሩበት ቀን" ማለት ነው፦
11፥103 *በዚህ ውስጥ የመጨረሻውን ቀን ቅጣት ለሚፈሩ ሁሉ መገሰጫ አለ፡፡ ይህ የትንሣኤ ቀን ሰዎች በእርሱ የሚሰበሰቡበት ቀን ነው፡፡ ይህም የሚመሰከሩበት ቀን ነው"*፡፡ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً لِّمَنْ خَافَ عَذَابَ الْآخِرَةِ ۚ ذَٰلِكَ يَوْمٌ مَّجْمُوعٌ لَّهُ النَّاسُ وَذَٰلِكَ يَوْمٌ مَّشْهُودٌ
በቁርኣን አናቅጽ ላይ “ሻሂድ” شَاهِد ማለት የሚመሰክር “መስካሪ” ማለት ሲሆን “መሽሁድ” مَشْهُود ማለት ደግሞ የሚመሰከርበት “ተመስካሪ” ማለት ነው። በተቀጠረው ቀን መስካሪ በተመስካሪ ላይ ይመሰክራሉ፦
85፥2 *”በተቀጠረው ቀንም እምላለው”*። وَالْيَوْمِ الْمَوْعُودِ
85፥3 *”በመስካሪ እና በተመስካሪ እምላለሁ”*፡፡ وَشَاهِدٍ وَمَشْهُودٍ
“መስካሪ” የተባሉት “ነቢያት” ሲሆኑ “የሚመሰከርባቸው” ደግሞ “ኡማቸው” ናቸው፦
16፥84 *”ከየሕዝቡም ሁሉ መስካሪን የምንቀሰቅስበትን ቀን አስታውስ”*፡፡ وَيَوْمَ نَبْعَثُ مِن كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا
4፥41 *”ከሕዝቦችም ሁሉ መስካሪን ባመጣን ጊዜ አንተንም በእነዚህ ሕዝብ ላይ መስካሪ አድርገን በምናመጣህ ጊዜ የከሓዲዎች ኹኔታ እንዴት ይኾን?”* فَكَيْفَ إِذَا جِئْنَا مِن كُلِّ أُمَّةٍ بِشَهِيدٍ وَجِئْنَا بِكَ عَلَىٰ هَـٰؤُلَاءِ شَهِيدًا
16፥89 *”በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ ከራሳቸው በእነርሱ ላይ መስካሪን የምንቀሰቅስበትን አንተንም በእነዚህ ሕዝብ ላይ መስካሪ አድርገን የምናመጣህን ቀን አስታውስ”*፡፡ وَيَوْمَ نَبْعَثُ فِي كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا عَلَيْهِم مِّنْ أَنفُسِهِمْ ۖ وَجِئْنَا بِكَ شَهِيدًا عَلَىٰ هَـٰؤُلَاء
28፥75 *”ከሕዝቦችም ሁሉ መስካሪን እናወጣለን፡፡ ያን ጊዜ እውነተኛውም አምላክነት ለአላህ ብቻ መኾኑን ያውቃሉ፡፡ ይቀጣጥፉት የነበሩትም ከእነርሱ ይጠፋቸዋል”*፡፡ وَنَزَعْنَا مِن كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا فَقُلْنَا هَاتُوا بُرْهَانَكُمْ فَعَلِمُوا أَنَّ الْحَقَّ لِلَّهِ وَضَلَّ عَنْهُم مَّا كَانُوا يَفْتَرُونَ
“ኡማህ” أُمَّة ማለት “ሕዝብ” ማለት ሲሆን በአንድ ነቢይ ዘመነ-መግቦት”dispensation” የሚቆዩትን “ሰዎች” ያመለክታል። እያንዳንዱ ነቢይ በራሱ ኡማህ ላይ በትንሳኤ ቀን ይመሰክራሉ።
የውመል ሐሥራህ"
"የውመል ሐሥራህ" يَوْمَ الْحَسْرَة ማለት "የቁልጭቱን ቀን" ማለት ነው፦
19፥39 *እነርሱም አሁን በዝንጋቴ ላይ ኾነው ሳሉ እነርሱም የማያምኑ ሲኾኑ ነገሩ በሚፈረድበት ጊዜ "የቁልጭቱን ቀን አስጠንቅቃቸው*፡፡ وَأَنذِرْهُمْ يَوْمَ الْحَسْرَةِ إِذْ قُضِيَ الْأَمْرُ وَهُمْ فِي غَفْلَةٍ وَهُمْ لَا يُؤْمِنُونَ
በዚህ ቀን ኩፋሮች በቁጭት ከሚሉት መካከል፦ “ከመልክተኛው ጋር ቀጥተኛን መንገድ ይዤ በኾነ ዋ ምኞቴ” “አላህን በተገዛን መልክተኛውንም በታዘዝን ኖሮ” በማለት ይቆጫሉ፦
25፥27 *በዳይም «ከመልክተኛው ጋር ቀጥተኛን መንገድ ይዤ በኾነ ዋ ምኞቴ!» እያለ በጸጸት ሁለት እጆቹን የሚነክስበትን ቀን አስታውስ*፡፡ وَيَوْمَ يَعَضُّ الظَّالِمُ عَلَىٰ يَدَيْهِ يَقُولُ يَا لَيْتَنِي اتَّخَذْتُ مَعَ الرَّسُولِ سَبِيلًا
33፥66 ፊቶቻቸው በእሳት ውሰጥ በሚገለባበጡ ቀን *«ዋ ምኞታችን! አላህን በተገዛን መልክተኛውንም በታዘዝን ኖሮ» እያሉ ይጸጸታሉ*፡፡ يَوْمَ تُقَلَّبُ وُجُوهُهُمْ فِي النَّارِ يَقُولُونَ يَا لَيْتَنَا أَطَعْنَا اللَّهَ وَأَطَعْنَا الرَّسُولَا
ኩፋሮች ከቁጭትዋ የተነሳ ሲቆጩ የእሳት ዘበኞች፦ “አስጠንቃቂ አልመጣችሁምን?” በማለት ይጠይቋቸዋል፦
67፥8 *ከቁጭትዋ የተነሳ ልትቆራረጥ ትቀርባለች፡፡ በውስጧ ጭፍሮች በተጣሉ ቁጥር ዘበኞችዋ *«አስጠንቃቂ አልመጣችሁምን?*» በማለት ይጠይቋቸዋል፡፡ تَكَادُ تَمَيَّزُ مِنَ الْغَيْظِ ۖ كُلَّمَا أُلْقِيَ فِيهَا فَوْجٌ سَأَلَهُمْ خَزَنَتُهَا أَلَمْ يَأْتِكُمْ نَذِيرٌ
ኩፋሮች ይህንን መልእክት ተቀብለው ከሙሥሊሞች ጋር በመሆን አንዱን አምላክ ማምለክ ሲገባቸው የተውበት በሩ ከተዘጋ በኃላ በቁጭቱ ቀን፦ “ታላቅ ዕድልን አገኝ ዘንድ ከእነርሱ ጋር በኾንኩ ወይ ምኞቴ” “ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ መልካምን ሥራ ባስቀደምኩ ኖሮ” “ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ” “ዋ ጥፋቴ! እገሌን ወዳጅ ባልያዝኩ ኖሮ እመኛለሁ” ይላሉ፦
4፥73 ከአላህም የኾነ ችሮታ ቢያገኛችሁ በእናንተና በእርሱ መካከል ፍቅር እንዳልነበረች ሁሉ *«ታላቅ ዕድልን አገኝ ዘንድ ከእነርሱ ጋር በኾንኩ ወይ ምኞቴ!»* ይላል፡፡ وَلَئِنْ أَصَابَكُمْ فَضْلٌ مِّنَ اللَّهِ لَيَقُولَنَّ كَأَن لَّمْ تَكُن بَيْنَكُمْ وَبَيْنَهُ مَوَدَّةٌ يَا لَيْتَنِي كُنتُ مَعَهُمْ فَأَفُوزَ فَوْزًا عَظِيمًا
89፥24 *«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ መልካምን ሥራ ባስቀደምኩ ኖሮ»* ይላል፡፡ يَقُولُ يَا لَيْتَنِي قَدَّمْتُ لِحَيَاتِي
78፥40 እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም፦ *ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ* በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡ إِنَّا أَنذَرْنَاكُمْ عَذَابًا قَرِيبًا يَوْمَ يَنظُرُ الْمَرْءُ مَا قَدَّمَتْ يَدَاهُ وَيَقُولُ الْكَافِرُ يَا لَيْتَنِي كُنتُ تُرَابًا
25፥28 *«ዋ ጥፋቴ! እገሌን ወዳጅ ባልያዝኩ ኖሮ እመኛለሁ*፡፡ يَا وَيْلَتَىٰ لَيْتَنِي لَمْ أَتَّخِذْ فُلَانًا خَلِيلًا
ነጥብ አሥራ አራት
"የውሙም መሽሁድ"
"የውሙም መሽሁድ" يَوْمٌ مَّشْهُود ማለት "የሚመሰከሩበት ቀን" ማለት ነው፦
11፥103 *በዚህ ውስጥ የመጨረሻውን ቀን ቅጣት ለሚፈሩ ሁሉ መገሰጫ አለ፡፡ ይህ የትንሣኤ ቀን ሰዎች በእርሱ የሚሰበሰቡበት ቀን ነው፡፡ ይህም የሚመሰከሩበት ቀን ነው"*፡፡ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً لِّمَنْ خَافَ عَذَابَ الْآخِرَةِ ۚ ذَٰلِكَ يَوْمٌ مَّجْمُوعٌ لَّهُ النَّاسُ وَذَٰلِكَ يَوْمٌ مَّشْهُودٌ
በቁርኣን አናቅጽ ላይ “ሻሂድ” شَاهِد ማለት የሚመሰክር “መስካሪ” ማለት ሲሆን “መሽሁድ” مَشْهُود ማለት ደግሞ የሚመሰከርበት “ተመስካሪ” ማለት ነው። በተቀጠረው ቀን መስካሪ በተመስካሪ ላይ ይመሰክራሉ፦
85፥2 *”በተቀጠረው ቀንም እምላለው”*። وَالْيَوْمِ الْمَوْعُودِ
85፥3 *”በመስካሪ እና በተመስካሪ እምላለሁ”*፡፡ وَشَاهِدٍ وَمَشْهُودٍ
“መስካሪ” የተባሉት “ነቢያት” ሲሆኑ “የሚመሰከርባቸው” ደግሞ “ኡማቸው” ናቸው፦
16፥84 *”ከየሕዝቡም ሁሉ መስካሪን የምንቀሰቅስበትን ቀን አስታውስ”*፡፡ وَيَوْمَ نَبْعَثُ مِن كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا
4፥41 *”ከሕዝቦችም ሁሉ መስካሪን ባመጣን ጊዜ አንተንም በእነዚህ ሕዝብ ላይ መስካሪ አድርገን በምናመጣህ ጊዜ የከሓዲዎች ኹኔታ እንዴት ይኾን?”* فَكَيْفَ إِذَا جِئْنَا مِن كُلِّ أُمَّةٍ بِشَهِيدٍ وَجِئْنَا بِكَ عَلَىٰ هَـٰؤُلَاءِ شَهِيدًا
16፥89 *”በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ ከራሳቸው በእነርሱ ላይ መስካሪን የምንቀሰቅስበትን አንተንም በእነዚህ ሕዝብ ላይ መስካሪ አድርገን የምናመጣህን ቀን አስታውስ”*፡፡ وَيَوْمَ نَبْعَثُ فِي كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا عَلَيْهِم مِّنْ أَنفُسِهِمْ ۖ وَجِئْنَا بِكَ شَهِيدًا عَلَىٰ هَـٰؤُلَاء
28፥75 *”ከሕዝቦችም ሁሉ መስካሪን እናወጣለን፡፡ ያን ጊዜ እውነተኛውም አምላክነት ለአላህ ብቻ መኾኑን ያውቃሉ፡፡ ይቀጣጥፉት የነበሩትም ከእነርሱ ይጠፋቸዋል”*፡፡ وَنَزَعْنَا مِن كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا فَقُلْنَا هَاتُوا بُرْهَانَكُمْ فَعَلِمُوا أَنَّ الْحَقَّ لِلَّهِ وَضَلَّ عَنْهُم مَّا كَانُوا يَفْتَرُونَ
“ኡማህ” أُمَّة ማለት “ሕዝብ” ማለት ሲሆን በአንድ ነቢይ ዘመነ-መግቦት”dispensation” የሚቆዩትን “ሰዎች” ያመለክታል። እያንዳንዱ ነቢይ በራሱ ኡማህ ላይ በትንሳኤ ቀን ይመሰክራሉ።
አሥራ አምስት
"የውሙል ኹሉድ"
ኹሉድ" خُلُود የሚለው ቃል "ኸለደ" خَلَدَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ዘላለማዊነት" ማለት ነው፥ "የውሙል ኹሉድ" يَوْمُ الْخُلُود ማለት "የዘላለማዊነት ወይም የመዘውተሪያ ቀን" ማለት ነው፦
50፥34 *"«በሰላም ግቧት ይህ "የመዘውተሪያ ቀን" ነው»* ይባላሉ፡፡ ادْخُلُوهَا بِسَلَامٍ ۖ ذَٰلِكَ يَوْمُ الْخُلُودِ
የትንሳኤ ቀን የጀነት ባለቤቶች በጀነት ውስጥ ለዘላለም ይኖራሉ፥ የእሳት ባለቤቶች በእሳት ውስጥ ለዘላለም ይኖራሉ። ሞት ይጠፋል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 81, ሐዲስ 134
አቡ ሁራይራህ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ለጀነት ባለቤቶች፦ "ለእናንተ ዘላለማዊነት እንጂ ሞት የለም" ይባላሉ፥ ለእሳት ባለቤቶች፦ "ለእናንተ ዘላለማዊነት እንጂ ሞት የለም" ይባላሉ"*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم " يُقَالُ لأَهْلِ الْجَنَّةِ خُلُودٌ لاَ مَوْتَ. وَلأَهْلِ النَّارِ يَا أَهْلَ النَّارِ خُلُودٌ لاَ مَوْتَ "
"ኻሊድ" خَالِد ማለት "ዘላለማዊ" "ዘውታሪ" ማለት ነው፥ የኻሊድ ብዙ ቁጥር ደግሞ "ኻሊዲን" خَالِدِين ወይም "ኻሊዱን" خَالِدُون ሲሆን "ዘላለማውያን" ወይም "ዘውታሪያን" ማለት ነው። በጀነት የሚኖሩ አማንያን "አስሓቡል ጀናህ" أَصْحَابُ الْجَنَّة ማለትም "የገነት ጓዶች" ሆነው ለዘላለም ይኖራሉ፦
2፥82 *እነዚያም ያመኑት በጎ ሥራዎችንም የሠሩት እነዚያ የገነት ጓዶች ናቸው፡፡ እነርሱ በውስጧ ዘላለም ዘውታሪዎች ናቸው*፡፡ وَالَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ أُولَـٰئِكَ أَصْحَابُ الْجَنَّةِ ۖ هُمْ فِيهَا خَالِدُونَ
በተቃራኒው ጀሀነም የሚኖሩ ከሃድያን "አስሓቡን ናር" أَصْحَابُ النَّار ማለትም "የእሳት ጓዶች" ሆነው ለዘላለም ይኖራሉ፦
2፥39 *እነዚያም በመልክተኞቻችን የካዱ በአንቀጾቻችንም ያስተባበሉ እነዚያ የእሳት ጓዶች ናቸው፡፡ እነርሱ በውስጧ ዘውታሪዎች ናቸው*፡፡ وَالَّذِينَ كَفَرُوا وَكَذَّبُوا بِآيَاتِنَا أُولَـٰئِكَ أَصْحَابُ النَّارِ ۖ هُمْ فِيهَا خَالِدُونَ
የአላህ ዘላለማዊነት መነሻ የሌለው ቀዳማይ፥ መዳረሻ የሌለው ደኃራይ ነው። በጀነት እና በጀሀነም ያሉትን መነሻ ያላቸው ስለሆኑ ዘላለማዊነታቸው ቂደም አይደለም፥ "ቂደም" قِدَم የሚለው ቃል "ቀዱመ" قَدُمَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ጅማሬ ወይም መነሻ የሌለው ቀዳማዊ ዘላለም"pre eternity" ማለት ነው፥ ይህ ዘላለማዊነት የአላህ ብቻ ነው።
ነገር ግን በጀነት እና በጀሀነም ያሉትን ዘላለማዊነታቸው በቃእ ነው፥ "በቃእ" بَقَاء የሚለው ቃል "በቂየ" بَقِيَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ፍጻሜ ወይም መዳረሻ የሌለው ደኃራዊ ዘላለም"post eternity" ማለት ነው። ስለ የመጨረሻው ቀን እሳቤ ከብዙ በጥቂቱ ይንን ይመስላል። አምላካችን አላህ ዒባዳችንን በኢኽላስ ተቀብሎ አስሓቡል ጀናህ ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
"የውሙል ኹሉድ"
ኹሉድ" خُلُود የሚለው ቃል "ኸለደ" خَلَدَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ዘላለማዊነት" ማለት ነው፥ "የውሙል ኹሉድ" يَوْمُ الْخُلُود ማለት "የዘላለማዊነት ወይም የመዘውተሪያ ቀን" ማለት ነው፦
50፥34 *"«በሰላም ግቧት ይህ "የመዘውተሪያ ቀን" ነው»* ይባላሉ፡፡ ادْخُلُوهَا بِسَلَامٍ ۖ ذَٰلِكَ يَوْمُ الْخُلُودِ
የትንሳኤ ቀን የጀነት ባለቤቶች በጀነት ውስጥ ለዘላለም ይኖራሉ፥ የእሳት ባለቤቶች በእሳት ውስጥ ለዘላለም ይኖራሉ። ሞት ይጠፋል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 81, ሐዲስ 134
አቡ ሁራይራህ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ለጀነት ባለቤቶች፦ "ለእናንተ ዘላለማዊነት እንጂ ሞት የለም" ይባላሉ፥ ለእሳት ባለቤቶች፦ "ለእናንተ ዘላለማዊነት እንጂ ሞት የለም" ይባላሉ"*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم " يُقَالُ لأَهْلِ الْجَنَّةِ خُلُودٌ لاَ مَوْتَ. وَلأَهْلِ النَّارِ يَا أَهْلَ النَّارِ خُلُودٌ لاَ مَوْتَ "
"ኻሊድ" خَالِد ማለት "ዘላለማዊ" "ዘውታሪ" ማለት ነው፥ የኻሊድ ብዙ ቁጥር ደግሞ "ኻሊዲን" خَالِدِين ወይም "ኻሊዱን" خَالِدُون ሲሆን "ዘላለማውያን" ወይም "ዘውታሪያን" ማለት ነው። በጀነት የሚኖሩ አማንያን "አስሓቡል ጀናህ" أَصْحَابُ الْجَنَّة ማለትም "የገነት ጓዶች" ሆነው ለዘላለም ይኖራሉ፦
2፥82 *እነዚያም ያመኑት በጎ ሥራዎችንም የሠሩት እነዚያ የገነት ጓዶች ናቸው፡፡ እነርሱ በውስጧ ዘላለም ዘውታሪዎች ናቸው*፡፡ وَالَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ أُولَـٰئِكَ أَصْحَابُ الْجَنَّةِ ۖ هُمْ فِيهَا خَالِدُونَ
በተቃራኒው ጀሀነም የሚኖሩ ከሃድያን "አስሓቡን ናር" أَصْحَابُ النَّار ማለትም "የእሳት ጓዶች" ሆነው ለዘላለም ይኖራሉ፦
2፥39 *እነዚያም በመልክተኞቻችን የካዱ በአንቀጾቻችንም ያስተባበሉ እነዚያ የእሳት ጓዶች ናቸው፡፡ እነርሱ በውስጧ ዘውታሪዎች ናቸው*፡፡ وَالَّذِينَ كَفَرُوا وَكَذَّبُوا بِآيَاتِنَا أُولَـٰئِكَ أَصْحَابُ النَّارِ ۖ هُمْ فِيهَا خَالِدُونَ
የአላህ ዘላለማዊነት መነሻ የሌለው ቀዳማይ፥ መዳረሻ የሌለው ደኃራይ ነው። በጀነት እና በጀሀነም ያሉትን መነሻ ያላቸው ስለሆኑ ዘላለማዊነታቸው ቂደም አይደለም፥ "ቂደም" قِدَم የሚለው ቃል "ቀዱመ" قَدُمَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ጅማሬ ወይም መነሻ የሌለው ቀዳማዊ ዘላለም"pre eternity" ማለት ነው፥ ይህ ዘላለማዊነት የአላህ ብቻ ነው።
ነገር ግን በጀነት እና በጀሀነም ያሉትን ዘላለማዊነታቸው በቃእ ነው፥ "በቃእ" بَقَاء የሚለው ቃል "በቂየ" بَقِيَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ፍጻሜ ወይም መዳረሻ የሌለው ደኃራዊ ዘላለም"post eternity" ማለት ነው። ስለ የመጨረሻው ቀን እሳቤ ከብዙ በጥቂቱ ይንን ይመስላል። አምላካችን አላህ ዒባዳችንን በኢኽላስ ተቀብሎ አስሓቡል ጀናህ ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የሥላሴአውያን ቅዠት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
15፥74 ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው፡፡ فَجَعَلْنَا عَالِيَهَا سَافِلَهَا وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِمْ حِجَارَةً مِّن سِجِّيلٍ
አምላካችን አላህ ወንድ እና ወንድ በተዳሩት ሰዶማውያን ላይ የሸክላ ደንጊያዎች የሆነ ዝናብ ከላይ አዝንቦባቸዋል፦
15፥74 ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነርሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው፡፡ فَجَعَلْنَا عَالِيَهَا سَافِلَهَا وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِمْ حِجَارَةً مِّن سِجِّيلٍ
7፥84 *በእነርሱም ላይ ዝናብን አዘነብንባቸው*፡፡ የኃጢአተኞችም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡ وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِم مَّطَرًا ۖ فَانظُرْ كَيْفَ كَانَ عَاقِبَةُ الْمُجْرِمِينَ
27፥58 በእነርሱም ላይ ዝናብን አዘነብንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናብ ከፋ፡፡ وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِم مَّطَرًا ۖ فَسَاءَ مَطَرُ الْمُنذَرِينَ
ይህ ዘገባ በተመሳሳይ ባይብል ላይ አለ፦
ዘፍጥረት 19፥24 *እግዚአብሔርም በሰዶምና በገሞራ ላይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ከሰማይ እሳትና ዲን አዘነበ*።
ነገር ግን የሥላሴ አማንያን እዚህ አንቀጽ ላይ “ወልድ” እና “አብ” የሚል ሃይለ-ቃል ሳይኖር፦”እግዚአብሔር ወልድ በሰዶምና በገሞራ ላይ ከእግዚአብሔር አብ ዘንድ እሳትና ዲን አዘነበ” ብለው ይተረጉማሉ፤ አንቀጹ ላይ፦ “አንደኛው ማንንነት ከሌላው ማንነት ዘንድ እሳትና ዲን አዘነበ” አይልም። ነገር ግን የሚለው፦ “እግዚአብሔርም በሰዶምና በገሞራ ላይ ከእግዚአብሔር ዘንድ እሳትና ዲን አዘነበ” ነው፤
ለመሆኑ ስንት እግዚአብሔር አለ? እስቲ እናስተንትን፦
ዘዳግም 6፥4 እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር *አንድ እግዚአብሔር ነው*።
እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ከሆነ በሰዶምና በገሞራ ላይ እሳትና ዲን ያዘነበው እራሱ እግዚአብሔር ከራሱ ዘንድ ነው፤ ይህንን ነጥብ በነጥብ እንመልከት፦
ነጥብ አንድ
“ሥስተኛ መደብ”
እግዚአብሔር እራሱን በሦስተኛ መደብ አድርጎ፦ “ሰዶምንና ገሞራን እግዚአብሔር ገለበጣቸው” ይለናል፦
አሞጽ 4፥11 *ሰዶምንና ገሞራን እግዚአብሔር እንደ ገለበጣቸው፥ እንዲሁ ገለበጥኋችሁ… ይላል እግዚአብሔር።
ኤርምያስ 50፥40 *ሰዶምንና ገሞራን በአጠገባቸውም የነበሩትን ከተምች እግዚአብሔር እንደ ገለበጣቸው፥ ይላል
እግዚአብሔር*፥ እንዲሁ ሰው በዚያ አይቀመጥም የሰውም ልጅ አይኖርባትም።
እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ ሰይጣን ሆይ፥ እግዚአብሔር ይገሥጽህ ብሎታል፦
ዘካርያስ 3፥2 *እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ ሰይጣን ሆይ፥ እግዚአብሔር ይገሥጽህ*፤ ኢየሩሳሌምን የመረጠ እግዚአብሔር ይገሥጽህ፤ በውኑ ይህ ከእሳት የተነጠቀ ትንታግ አይደለምን? *አለው*።
ያ ማለት አንደኛው እግዚአብሔር በሌላው እግዚአብሔር እየገሰጸ ነው ማለት አይደለም፤ እራሱ በራሱ እየገሰጸው ነው፦
ኢዮብ 2÷3 *እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ በውኑ ባሪያዬን ኢዮብን ተመለከትኸውን? በምድር ላይ እንደ እርሱ ፍጹምና ቅን፥ እግዚአብሔርንም የሚፈራ*፥ ከክፋትም የራቀ ሰው የለም፤
እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ “እኔንም የሚፈራ” በማለት ፋንታ በሦስተኛ መደብ “እግዚአብሔርንም የሚፈራ” ብሏል፦
ዘጸአት 20፥7 *የእግዚአብሔርን የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ፤ እግዚአብሔር ስሙን በከንቱ የሚጠራውን ከበደል አያነጻውምና*።
እግዚአብሔርም፦ “የእኔን ስም በከንቱ አትጥራ፤ ስሜን በከንቱ የሚጠራውን ከበደል አላነጻውምና” በማለት ፋንታ በሦስተኛ መደብ “የእግዚአብሔርን የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ፤ እግዚአብሔር ስሙን በከንቱ የሚጠራውን ከበደል አያነጻውምና” ብሏል፦
ዘካርያስ 10፥12 *በአምላካቸው በእግዚአብሔር አበረታቸዋለሁ፥ በስሙም ይመካሉ፥ ይላል እግዚአብሔር*።
እራሱ እግዚአብሔር በአምላካቸው በእግዚአብሔር አበረታቸዋለሁ ማለቱ አንባቢ ልብ ይለዋል። ይህንን ናሙና በሌሎች ጥቅሶች አንብቡት፦
1ኛ ሳሙኤል 20፥12-13 *ዮናታንም ዳዊትን አለው፦….እግዚአብሔር በዮናታን ይህን ያድርግ ይህንም ይጨምር*፤
1ኛ ነገሥት 1፥33 ንጉሡም አላቸው፦ የጌታችሁን ባሪያዎች ይዛችሁ ሂዱ፥ ልጄንም ሰሎሞንን በበቅሎዬ ላይ አስቀምጡት፥ ወደ ግዮንም አውርዱት፤
አስቴር 8፥7-8 *ንጉሡም አርጤክስስ ንግሥቲቱን አስቴርንና አይሁዳዊውን መርዶክዮስን፦ እነሆ የሐማን ቤት ለአስቴር ሰጥቻለሁ፥ እርሱም እጆቹን በአይሁድ ላይ ስለ ዘረጋ በግንድ ላይ ተሰቀለ።
በንጉሡ ስም የተጻፈና በንጉሡ ቀለበት የታተመ አይገለበጥምና እናንተ ደግሞ ደስ የሚያሰኛችሁን በንጉሡ ስም ስለ አይሁድ ጻፉ፥ በንጉሡም ቀለበት አትሙ፡ አላቸው*።
ሉቃስ 9፥26 *በእኔና በቃሌ የሚያፍር ሁሉ፥ የሰው ልጅ በክብሩ በአባቱና በቅዱሳን መላእክቱ ክብርም ሲመጣ* በእርሱ ያፍርበታል።
አንድ ማንነት በሦስተኛ መደብ መገለጹ ያንን ማንነት ብዙ እንደማያደርገው ካየን ዘንዳ አሁን ደግሞ “ዘንድ” የሚለው መስተዋድድ በአንድ ማንነት እንዴት እንዳገለገለ በሚቀጥለው ነጥብ እንመልከት፦
ነጥብ ሁለት
“ዘንድ”
ዳዊት የምስጋና ስእለት ከእርሱ ዘንድ ሰጥቷል፦
መዝሙር 56፥12 አቤቱ፥ *የምስጋና ስእለት የምሰጥህ ከእኔ ዘንድ ነው*።
ዳዊት አንድ ሰውና ማንነት ሆኖ ሳለ ሰጪ እርሱ የሚሰጠው ከእርሱ ዘንድ እንደሆነ ተናግሯል፤ ያ ማለት ዳዊት ሁለት ሰው ወይም ሁለት ማንነት መሆኑን ያሳያልን? አንድ ሆኖ ሳለ “አለይ” עָלַ֣י ማለትም “ዘንድ” የሚል መስተዋድድ ይጠቀማል፤ ይህ የተለመደ ሰዋስው ነው፦
ዘዳግም 15፥12 “አንተም” ወንድምህን ዕብራዊውን ወይም ዕብራዊቱን ብትገዛ ስድስት ዓመት ያገልግሉህ በሰባተኛውም ዓመት *ከአንተ ዘንድ አርነት አውጣው*።
“ከአንተ ዘንድ” የሚለው ቃል “መሚከ” מֵעִמָּֽךְ ተብሎ የተቀመጠ ሲሆን “አንተ” በሚል ተውላጠ-ስም ላይ “ዘንድ” የሚል መስተዋድድ መነሻ ቅጥያ ሆኖ መጥቷል፤ “አንተ ከአንተ ዘንድ አርነት አውጣው” ማለት ያ ሰው ሁለት ሰው ወይም ሁለት ማንነት ሆነ ማለት ነው? የእግዚአብሔርም ክብር የእግዚአብሔርን ቤት ሞልቶት ነበር፦
2ኛ ዜና 7፥2 *የእግዚአብሔርም ክብር የእግዚአብሔርን ቤት ሞልቶት ነበርና* ካህናቱ ወደ እግዚአብሔር ቤት መግባት አልቻሉም።
ዘኍልቍ 14፥20 እግዚአብሔርም አለ፦ *”እንደ ቃልህ ይቅር አልሁ፤ ነገር ግን እኔ ሕያው ነኛ በእውነት የእግዚአብሔር ክብር ምድርን ሁሉ ይሞላል”*።
“የ” የሚል አገናዛቢ ቃል “እግዚአብሔር” በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ መግባቱ እና “እግዚአብሔር” የሚለው ቃል ሁለቴ መግባቱ ሁለት እግዚአብሔር ወይም ሁለት ማንነቶች አያሳም።
በተጨማሪም “የእኔ ክብር ምድርን ሁሉ ይሞላል” በማለት ፈንታ “በእውነት የእግዚአብሔር ክብር ምድርን ሁሉ ይሞላል” ማለቱ እግዚአብሔር ወይም ሁለት ማንነቶች እንደማያሳይ ሁሉ ከላይ ያለውን የዘፍጥረትን 19፥24 ያለውን ጥቅስ በዚህ ስሌትና ቀመር መረዳት ይቻላል። የሥላሴ አማንያን ሁለት ቃላት ከተገኘ አብ እና ወልድ ሦስት ቃላት ከተገኘ ሥላሴ የሚል ቅዠት አላቸው፤ የሥላሴ አማንያን ቅዠት አያልቅም።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
15፥74 ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው፡፡ فَجَعَلْنَا عَالِيَهَا سَافِلَهَا وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِمْ حِجَارَةً مِّن سِجِّيلٍ
አምላካችን አላህ ወንድ እና ወንድ በተዳሩት ሰዶማውያን ላይ የሸክላ ደንጊያዎች የሆነ ዝናብ ከላይ አዝንቦባቸዋል፦
15፥74 ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነርሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው፡፡ فَجَعَلْنَا عَالِيَهَا سَافِلَهَا وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِمْ حِجَارَةً مِّن سِجِّيلٍ
7፥84 *በእነርሱም ላይ ዝናብን አዘነብንባቸው*፡፡ የኃጢአተኞችም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡ وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِم مَّطَرًا ۖ فَانظُرْ كَيْفَ كَانَ عَاقِبَةُ الْمُجْرِمِينَ
27፥58 በእነርሱም ላይ ዝናብን አዘነብንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናብ ከፋ፡፡ وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِم مَّطَرًا ۖ فَسَاءَ مَطَرُ الْمُنذَرِينَ
ይህ ዘገባ በተመሳሳይ ባይብል ላይ አለ፦
ዘፍጥረት 19፥24 *እግዚአብሔርም በሰዶምና በገሞራ ላይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ከሰማይ እሳትና ዲን አዘነበ*።
ነገር ግን የሥላሴ አማንያን እዚህ አንቀጽ ላይ “ወልድ” እና “አብ” የሚል ሃይለ-ቃል ሳይኖር፦”እግዚአብሔር ወልድ በሰዶምና በገሞራ ላይ ከእግዚአብሔር አብ ዘንድ እሳትና ዲን አዘነበ” ብለው ይተረጉማሉ፤ አንቀጹ ላይ፦ “አንደኛው ማንንነት ከሌላው ማንነት ዘንድ እሳትና ዲን አዘነበ” አይልም። ነገር ግን የሚለው፦ “እግዚአብሔርም በሰዶምና በገሞራ ላይ ከእግዚአብሔር ዘንድ እሳትና ዲን አዘነበ” ነው፤
ለመሆኑ ስንት እግዚአብሔር አለ? እስቲ እናስተንትን፦
ዘዳግም 6፥4 እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር *አንድ እግዚአብሔር ነው*።
እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ከሆነ በሰዶምና በገሞራ ላይ እሳትና ዲን ያዘነበው እራሱ እግዚአብሔር ከራሱ ዘንድ ነው፤ ይህንን ነጥብ በነጥብ እንመልከት፦
ነጥብ አንድ
“ሥስተኛ መደብ”
እግዚአብሔር እራሱን በሦስተኛ መደብ አድርጎ፦ “ሰዶምንና ገሞራን እግዚአብሔር ገለበጣቸው” ይለናል፦
አሞጽ 4፥11 *ሰዶምንና ገሞራን እግዚአብሔር እንደ ገለበጣቸው፥ እንዲሁ ገለበጥኋችሁ… ይላል እግዚአብሔር።
ኤርምያስ 50፥40 *ሰዶምንና ገሞራን በአጠገባቸውም የነበሩትን ከተምች እግዚአብሔር እንደ ገለበጣቸው፥ ይላል
እግዚአብሔር*፥ እንዲሁ ሰው በዚያ አይቀመጥም የሰውም ልጅ አይኖርባትም።
እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ ሰይጣን ሆይ፥ እግዚአብሔር ይገሥጽህ ብሎታል፦
ዘካርያስ 3፥2 *እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ ሰይጣን ሆይ፥ እግዚአብሔር ይገሥጽህ*፤ ኢየሩሳሌምን የመረጠ እግዚአብሔር ይገሥጽህ፤ በውኑ ይህ ከእሳት የተነጠቀ ትንታግ አይደለምን? *አለው*።
ያ ማለት አንደኛው እግዚአብሔር በሌላው እግዚአብሔር እየገሰጸ ነው ማለት አይደለም፤ እራሱ በራሱ እየገሰጸው ነው፦
ኢዮብ 2÷3 *እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ በውኑ ባሪያዬን ኢዮብን ተመለከትኸውን? በምድር ላይ እንደ እርሱ ፍጹምና ቅን፥ እግዚአብሔርንም የሚፈራ*፥ ከክፋትም የራቀ ሰው የለም፤
እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ “እኔንም የሚፈራ” በማለት ፋንታ በሦስተኛ መደብ “እግዚአብሔርንም የሚፈራ” ብሏል፦
ዘጸአት 20፥7 *የእግዚአብሔርን የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ፤ እግዚአብሔር ስሙን በከንቱ የሚጠራውን ከበደል አያነጻውምና*።
እግዚአብሔርም፦ “የእኔን ስም በከንቱ አትጥራ፤ ስሜን በከንቱ የሚጠራውን ከበደል አላነጻውምና” በማለት ፋንታ በሦስተኛ መደብ “የእግዚአብሔርን የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ፤ እግዚአብሔር ስሙን በከንቱ የሚጠራውን ከበደል አያነጻውምና” ብሏል፦
ዘካርያስ 10፥12 *በአምላካቸው በእግዚአብሔር አበረታቸዋለሁ፥ በስሙም ይመካሉ፥ ይላል እግዚአብሔር*።
እራሱ እግዚአብሔር በአምላካቸው በእግዚአብሔር አበረታቸዋለሁ ማለቱ አንባቢ ልብ ይለዋል። ይህንን ናሙና በሌሎች ጥቅሶች አንብቡት፦
1ኛ ሳሙኤል 20፥12-13 *ዮናታንም ዳዊትን አለው፦….እግዚአብሔር በዮናታን ይህን ያድርግ ይህንም ይጨምር*፤
1ኛ ነገሥት 1፥33 ንጉሡም አላቸው፦ የጌታችሁን ባሪያዎች ይዛችሁ ሂዱ፥ ልጄንም ሰሎሞንን በበቅሎዬ ላይ አስቀምጡት፥ ወደ ግዮንም አውርዱት፤
አስቴር 8፥7-8 *ንጉሡም አርጤክስስ ንግሥቲቱን አስቴርንና አይሁዳዊውን መርዶክዮስን፦ እነሆ የሐማን ቤት ለአስቴር ሰጥቻለሁ፥ እርሱም እጆቹን በአይሁድ ላይ ስለ ዘረጋ በግንድ ላይ ተሰቀለ።
በንጉሡ ስም የተጻፈና በንጉሡ ቀለበት የታተመ አይገለበጥምና እናንተ ደግሞ ደስ የሚያሰኛችሁን በንጉሡ ስም ስለ አይሁድ ጻፉ፥ በንጉሡም ቀለበት አትሙ፡ አላቸው*።
ሉቃስ 9፥26 *በእኔና በቃሌ የሚያፍር ሁሉ፥ የሰው ልጅ በክብሩ በአባቱና በቅዱሳን መላእክቱ ክብርም ሲመጣ* በእርሱ ያፍርበታል።
አንድ ማንነት በሦስተኛ መደብ መገለጹ ያንን ማንነት ብዙ እንደማያደርገው ካየን ዘንዳ አሁን ደግሞ “ዘንድ” የሚለው መስተዋድድ በአንድ ማንነት እንዴት እንዳገለገለ በሚቀጥለው ነጥብ እንመልከት፦
ነጥብ ሁለት
“ዘንድ”
ዳዊት የምስጋና ስእለት ከእርሱ ዘንድ ሰጥቷል፦
መዝሙር 56፥12 አቤቱ፥ *የምስጋና ስእለት የምሰጥህ ከእኔ ዘንድ ነው*።
ዳዊት አንድ ሰውና ማንነት ሆኖ ሳለ ሰጪ እርሱ የሚሰጠው ከእርሱ ዘንድ እንደሆነ ተናግሯል፤ ያ ማለት ዳዊት ሁለት ሰው ወይም ሁለት ማንነት መሆኑን ያሳያልን? አንድ ሆኖ ሳለ “አለይ” עָלַ֣י ማለትም “ዘንድ” የሚል መስተዋድድ ይጠቀማል፤ ይህ የተለመደ ሰዋስው ነው፦
ዘዳግም 15፥12 “አንተም” ወንድምህን ዕብራዊውን ወይም ዕብራዊቱን ብትገዛ ስድስት ዓመት ያገልግሉህ በሰባተኛውም ዓመት *ከአንተ ዘንድ አርነት አውጣው*።
“ከአንተ ዘንድ” የሚለው ቃል “መሚከ” מֵעִמָּֽךְ ተብሎ የተቀመጠ ሲሆን “አንተ” በሚል ተውላጠ-ስም ላይ “ዘንድ” የሚል መስተዋድድ መነሻ ቅጥያ ሆኖ መጥቷል፤ “አንተ ከአንተ ዘንድ አርነት አውጣው” ማለት ያ ሰው ሁለት ሰው ወይም ሁለት ማንነት ሆነ ማለት ነው? የእግዚአብሔርም ክብር የእግዚአብሔርን ቤት ሞልቶት ነበር፦
2ኛ ዜና 7፥2 *የእግዚአብሔርም ክብር የእግዚአብሔርን ቤት ሞልቶት ነበርና* ካህናቱ ወደ እግዚአብሔር ቤት መግባት አልቻሉም።
ዘኍልቍ 14፥20 እግዚአብሔርም አለ፦ *”እንደ ቃልህ ይቅር አልሁ፤ ነገር ግን እኔ ሕያው ነኛ በእውነት የእግዚአብሔር ክብር ምድርን ሁሉ ይሞላል”*።
“የ” የሚል አገናዛቢ ቃል “እግዚአብሔር” በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ መግባቱ እና “እግዚአብሔር” የሚለው ቃል ሁለቴ መግባቱ ሁለት እግዚአብሔር ወይም ሁለት ማንነቶች አያሳም።
በተጨማሪም “የእኔ ክብር ምድርን ሁሉ ይሞላል” በማለት ፈንታ “በእውነት የእግዚአብሔር ክብር ምድርን ሁሉ ይሞላል” ማለቱ እግዚአብሔር ወይም ሁለት ማንነቶች እንደማያሳይ ሁሉ ከላይ ያለውን የዘፍጥረትን 19፥24 ያለውን ጥቅስ በዚህ ስሌትና ቀመር መረዳት ይቻላል። የሥላሴ አማንያን ሁለት ቃላት ከተገኘ አብ እና ወልድ ሦስት ቃላት ከተገኘ ሥላሴ የሚል ቅዠት አላቸው፤ የሥላሴ አማንያን ቅዠት አያልቅም።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
ሦስት አምላክ
እዚህ ቻናል ስንት ሰው አለ? ብል ሺህ ትሉኛላችሁ፥ ከሰማያት በላይ ስንት አምላክ አለ? ብል 1 አምላክ ትሉኛላችሁ። እዚህ ቻናል ያለው ሰው 17100 ሺህ የሆነው በአካል የተለያየን ስለሆንን ነው፥ አምላክ በአካል ሦስት ከሆነ አንድ ሳይሆን ሦስት አምላክ ነው። የሥላሴ አማንያን "ኤሎሂም” אלהים ማለት "አማልክት" ማለት ሲሆን ሥላሴን ያሳያል ይላሉ፥ በጣም ጥሩ ሦስቱ አካላት አማልክት ናቸው ማለት ነው። ለዛውም ሦስት አምላክ ሳይሆን ሦስት አምላክት ነው፥ እነዚህ ሥስት አካሎች “ጌቶች” ይባላሉ። “አጋዕዝተ-ዓለም ሥላሴ” ማለት “የዓለም ጌቶች ሥላሴ” ማለት ነው፥ “እግዚእ” በነጠላ “ጌታ” ማለት ሲሆን “አጋዕዝት” ማለት ደግሞ በብዜት “ጌቶች” ማለት ነው፥ ስለዚህ ሥላሴ ሦስት ጌቶች ናቸው። ተመልሰው አንድ አምላክ አንድ ጌታ ትላላችሁ። ዘመወዛገብ ይሉሃል እንዲህ ነው፥ እራሳችሁ ሳይገባችሁ እንዴት ማስረዳት ትችላላችሁ?
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
እዚህ ቻናል ስንት ሰው አለ? ብል ሺህ ትሉኛላችሁ፥ ከሰማያት በላይ ስንት አምላክ አለ? ብል 1 አምላክ ትሉኛላችሁ። እዚህ ቻናል ያለው ሰው 17100 ሺህ የሆነው በአካል የተለያየን ስለሆንን ነው፥ አምላክ በአካል ሦስት ከሆነ አንድ ሳይሆን ሦስት አምላክ ነው። የሥላሴ አማንያን "ኤሎሂም” אלהים ማለት "አማልክት" ማለት ሲሆን ሥላሴን ያሳያል ይላሉ፥ በጣም ጥሩ ሦስቱ አካላት አማልክት ናቸው ማለት ነው። ለዛውም ሦስት አምላክ ሳይሆን ሦስት አምላክት ነው፥ እነዚህ ሥስት አካሎች “ጌቶች” ይባላሉ። “አጋዕዝተ-ዓለም ሥላሴ” ማለት “የዓለም ጌቶች ሥላሴ” ማለት ነው፥ “እግዚእ” በነጠላ “ጌታ” ማለት ሲሆን “አጋዕዝት” ማለት ደግሞ በብዜት “ጌቶች” ማለት ነው፥ ስለዚህ ሥላሴ ሦስት ጌቶች ናቸው። ተመልሰው አንድ አምላክ አንድ ጌታ ትላላችሁ። ዘመወዛገብ ይሉሃል እንዲህ ነው፥ እራሳችሁ ሳይገባችሁ እንዴት ማስረዳት ትችላላችሁ?
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
መንገድ ጠራጊ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
5፥17 *እነዚያ አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ*፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ
የሥላሴ አማንያን ከባይብል ኢየሱስን አምላክ ለማድረግ የማይቆፍሩት ጉድጓድ፣ የማይፈነቅሉት ድንጋይ፣ የማይደረምሱት መሬት የለም። ኢሳይያስ ላይ ያህዌህ መንገድ እንደሚጠረግለት ተነግሮ አዲስ ኪዳን ላይ ግን መጥምቁ ዮሐንስ መንገድ የጠረገው ለኢየሱስ ስለሆነ "ኢየሱስ ያህዌህ ነው" ብለው ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል፦
ኢሳይያስ 40፥3 የአዋጅ ነጋሪ ቃል፦ *"የያህዌን መንገድ በምድረ በዳ ጥረጉ፥ ለአምላካችንም ጐዳና በበረሀ አስተካከሉ"*።
ማርቆስ 1፥2 *"እነሆ መንገድህን የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ፥ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ ተብሎ በነቢዩ በኢሳይያስ እንደ ተጻፈ"*።
እዚህ ጥቅስ ላይ ብዙ ችግር አለ። አንደኛ "በምድረ በዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ" የሚለው ኢሳይያስ ላይ የለም። ሁለተኛ "እነሆ መንገድህን የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ" የሚለው "በነቢዩ በኢሳይያስ እንደ ተጻፈ" ይላል እንጂ ኢሳይያስ አልተጻፈም። የተጻፈው ሚልክያስ ላይ ነው፦
ሚልክያስ 3፥1 *"እነሆ መልእክተኛዬን እልካለሁ፥ መንገድንም በፊቴ ያስተካክላል"*።
ሦስተኛ በትንቢቱ ላይ "በፊቴ" እንጂ "በፊትህ" የሚል የለም። አራተኛ ሙግቱን ጠበብ አርገነው አብ ለወልድ በሁለተኛ መደብ "በፊትህ" ካለ መልእክተኛውን መንገድ የሚጠርገው በሚልክያስ ላይ "በፊቴ" ላለው አብ እና በማርቆስ ላይ "በፊትህ" ለተባለው ለወልድ ነው። ምክንያቱም አብ ለወልድ "መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ" ብሎ መንገድ ጠራጊውን ዮሐንስን ልኳል፦
ዮሐንስ 1፥6 *"ከእግዚአብሔር የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ"*።
ሉቃስ 1፥76 *"ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና"*።
ዮሐንስ የልዑል ነቢይ ከሆነ ልዑል የተባለው አብ እንጂ ኢየሱስ አይደለም፥ ኢየሱስ የልዑል ልጅ እንጂ ልዑል አልተባለም። ሲቀጥል ሉቃስ 1፥76 ላይ "ጌታ" የተባለው "አብ" ነው፥ ዐውደ-ንባቡ ላይ "በጌታ ፊት ሊያቆሙት ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት" ይላል፦
ሉቃስ 1፥32 *እርሱ ታላቅ ይሆናል "የልዑል ልጅም" ይባላል*።
ሉቃስ 2፥22 በጌታ ፊት ሊያቆሙት...ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት"*።
ስለዚህ "መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና" ሲል "ጌታ" የተባለው አብ ነው፥ ምክንያቱም ወልድን "በጌታ ፊት ሊያቆሙት ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት" ስለሚል። ዮሐንስ የአብ ማለትም ያያህዌን መንገድ እና የወልድ ማለትም የመሢሑን መንገድ ጠራጊ ነው። አራት ቆጠራችሁ? አምስተኛ ደግሞ ብሉይ ላይ የተጠቀሰ ጥቅስ አዲስ ላይ ፍጻሜ ካገኘ ብሉይ ላይ ያለ ጥቅስ የአዲስ ኪዳኑ ማንነት ነው ተብሎ በአራት ነጥብ አይደመደምም። አንዳንድ ናሙና እስቲ እንይ፦
2 ሳሙኤል 7፥14 *"እኔም አባት እሆነዋለሁ፥ እርሱም ልጅ ይሆነኛል፤ ክፉ ነገርም ቢያደርግ፥ ሰው በሚቀጣበት በትርና በሰው ልጆች መቀጫ እገሥጸዋለሁ"*።
ዕብራውያን 1፥5 *"ደግሞም፦ እኔ አባት እሆነዋለሁ እርሱም ልጅ ይሆነኛል" ያለው ከቶ ለማን ነው?*።
"እኔ አባት እሆነዋለሁ እርሱም ልጅ ይሆነኛል" የሳሙኤል ዐውደ-ንባብ የሚናገረው ለንጉሥ ሰለሞን ነው፥ የዕብራውያን ጸሐፊ ለኢየሱስ ነው ይለናል። እና ኢየሱስ ብሉይ ላይ የነበረው ሰለሞን ነውን? እንደ እናንተ እምነት ኢየሱስ ያህዌህ ከሆነ ያህዌህ አምላክ እንዴት ፍጡሩን ሰለሞን ይሆናል? መልሱ፦ "ድርብ አጠቃቀም ነው" የሚል ነው፥ እንግዲያውስ ብሉይ ላይ የያህዌህ መንገድ ተብሎ አዲስ ላይ የጌታ መንገድ መባሉ "ድርብ አጠቃቀም ነው" በሚል ስሌትና ቀመር መረዳት ይቻላል። ናሙናውን እንቀጥል፦
ሆሴዕ 11፥1-2 *"እስራኤል ሕፃን በነበረ ጊዜ ወደድሁት፥ ልጄንም ከግብፅ ጠራሁት። አብዝቼ ብጠራቸው አጥብቀው ከፊቴ ራቁ፤ ለበኣሊምም ይሠዉ ነበር፥ ለተቀረጹ ምስሎችም ያጥኑ ነበር"*።
ማቴዎስ 2፥14-15 *"እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን በሌሊት ያዘና ከጌታ ዘንድ በነቢይ፦ "ልጄን ከግብፅ ጠራሁት" የተባለው እንዲፈጸም ወደ ግብፅ ሄደ፥ ሄሮድስም እስኪሞት ድረስ በዚያ ኖረ"*።
"ልጄንም ከግብፅ ጠራሁት" የሆሴዕ ዐውደ-ንባብ የሚናገረው ለእስራኤል ሕዝብ ነው፥ የማቴዎስ ጸሐፊ ለኢየሱስ ነው ይለናል። ታዲያ ኢየሱስ ሲጠራ አጥብቆ ከአምላክ ፊት የራቀ ነውን? ለበኣሊምም ይሠዋ ነበርን? ለተቀረጹ ምስሎችም ያጥን ነበርን? ቅሉ ግን "ድርብ አጠቃቀም ነው" የሚል ነው፥ እንግዲያውስ ብሉይ ላይ የያህዌህ መንገድ ተብሎ አዲስ ላይ የጌታ መንገድ መባሉ "ድርብ አጠቃቀም ነው" በሚል ልክና መልክ መረዳት ይቻላል። ስድስተኛ "የያህዌህን መንገድ ማለት የያህዌህ ሕግ፣ ሥርዓት፣ ትእዛዝ፣ መርሕ እና ቃል ነው፦
መዝሙር 18፥21 *"የያህዌህን መንገድ ጠብቄአለሁ፥ በአምላኬም አላመፅሁም"*።
መዝሙር 18፥30 *"የአምላኬ መንገድ ፍጹም ነው፥ የያህዌህን ቃል የነጠረ ነው፥ በእርሱ ለሚታመኑት ሁሉ ጋሻ ነው"*።
ምሳሌ 10፥29 *የያህዌህ መንገድ ያለ ነውር ለሚሄድ አምባ ነው፥ ጥፋት ግን ክፋትን ለሚያደርጉ*።
ኤርምያስ 5፥4 እኔም፦ የያህዌህን መንገድና የአምላካቸውን ሕግ አላወቁምና እነዚህ በእውነት ድሆችና ሰነፎች ናቸው"*።
የኢየሱስ ትምህርት እና ሕግ የያህዌህ ሕግ ነው፥ የራሱ ሳይሆን የላከኝ አብ የሰጠው ትእዛዝ ነው፦
ዮሐንስ 12፥49 *እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፥ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ"*።
ዮሐንስ 14፥24 የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም፤ *"የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም"*።
ዮሐንስ 17፥8 *"የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና እነርሱም ተቀበሉት"*።
የአብን ቃል ወደ እራሱ በማስጠጋት "ቃሌ" ማለቱ በራሱ የአብ እና የወልድ መንገድ አንድ መሆኑን ያሳያል። ዮሐንስ አዋጅ ነጋሪ የሆነ እና የጠረገው የያህዌህን እና የመሢሑን መንገድ ነው። ስለዚህ ኢሳይያስ 40፥3 ኢየሱስ ያህዌህ መሆኑን በፍጹም አያሳይም። እነዚያ ፈጣሪን ከሴት የተወለደው መሢሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ፦
5፥17 *እነዚያ አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ*፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
5፥17 *እነዚያ አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ*፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ
የሥላሴ አማንያን ከባይብል ኢየሱስን አምላክ ለማድረግ የማይቆፍሩት ጉድጓድ፣ የማይፈነቅሉት ድንጋይ፣ የማይደረምሱት መሬት የለም። ኢሳይያስ ላይ ያህዌህ መንገድ እንደሚጠረግለት ተነግሮ አዲስ ኪዳን ላይ ግን መጥምቁ ዮሐንስ መንገድ የጠረገው ለኢየሱስ ስለሆነ "ኢየሱስ ያህዌህ ነው" ብለው ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል፦
ኢሳይያስ 40፥3 የአዋጅ ነጋሪ ቃል፦ *"የያህዌን መንገድ በምድረ በዳ ጥረጉ፥ ለአምላካችንም ጐዳና በበረሀ አስተካከሉ"*።
ማርቆስ 1፥2 *"እነሆ መንገድህን የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ፥ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ ተብሎ በነቢዩ በኢሳይያስ እንደ ተጻፈ"*።
እዚህ ጥቅስ ላይ ብዙ ችግር አለ። አንደኛ "በምድረ በዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ" የሚለው ኢሳይያስ ላይ የለም። ሁለተኛ "እነሆ መንገድህን የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ" የሚለው "በነቢዩ በኢሳይያስ እንደ ተጻፈ" ይላል እንጂ ኢሳይያስ አልተጻፈም። የተጻፈው ሚልክያስ ላይ ነው፦
ሚልክያስ 3፥1 *"እነሆ መልእክተኛዬን እልካለሁ፥ መንገድንም በፊቴ ያስተካክላል"*።
ሦስተኛ በትንቢቱ ላይ "በፊቴ" እንጂ "በፊትህ" የሚል የለም። አራተኛ ሙግቱን ጠበብ አርገነው አብ ለወልድ በሁለተኛ መደብ "በፊትህ" ካለ መልእክተኛውን መንገድ የሚጠርገው በሚልክያስ ላይ "በፊቴ" ላለው አብ እና በማርቆስ ላይ "በፊትህ" ለተባለው ለወልድ ነው። ምክንያቱም አብ ለወልድ "መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ" ብሎ መንገድ ጠራጊውን ዮሐንስን ልኳል፦
ዮሐንስ 1፥6 *"ከእግዚአብሔር የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ"*።
ሉቃስ 1፥76 *"ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና"*።
ዮሐንስ የልዑል ነቢይ ከሆነ ልዑል የተባለው አብ እንጂ ኢየሱስ አይደለም፥ ኢየሱስ የልዑል ልጅ እንጂ ልዑል አልተባለም። ሲቀጥል ሉቃስ 1፥76 ላይ "ጌታ" የተባለው "አብ" ነው፥ ዐውደ-ንባቡ ላይ "በጌታ ፊት ሊያቆሙት ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት" ይላል፦
ሉቃስ 1፥32 *እርሱ ታላቅ ይሆናል "የልዑል ልጅም" ይባላል*።
ሉቃስ 2፥22 በጌታ ፊት ሊያቆሙት...ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት"*።
ስለዚህ "መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና" ሲል "ጌታ" የተባለው አብ ነው፥ ምክንያቱም ወልድን "በጌታ ፊት ሊያቆሙት ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት" ስለሚል። ዮሐንስ የአብ ማለትም ያያህዌን መንገድ እና የወልድ ማለትም የመሢሑን መንገድ ጠራጊ ነው። አራት ቆጠራችሁ? አምስተኛ ደግሞ ብሉይ ላይ የተጠቀሰ ጥቅስ አዲስ ላይ ፍጻሜ ካገኘ ብሉይ ላይ ያለ ጥቅስ የአዲስ ኪዳኑ ማንነት ነው ተብሎ በአራት ነጥብ አይደመደምም። አንዳንድ ናሙና እስቲ እንይ፦
2 ሳሙኤል 7፥14 *"እኔም አባት እሆነዋለሁ፥ እርሱም ልጅ ይሆነኛል፤ ክፉ ነገርም ቢያደርግ፥ ሰው በሚቀጣበት በትርና በሰው ልጆች መቀጫ እገሥጸዋለሁ"*።
ዕብራውያን 1፥5 *"ደግሞም፦ እኔ አባት እሆነዋለሁ እርሱም ልጅ ይሆነኛል" ያለው ከቶ ለማን ነው?*።
"እኔ አባት እሆነዋለሁ እርሱም ልጅ ይሆነኛል" የሳሙኤል ዐውደ-ንባብ የሚናገረው ለንጉሥ ሰለሞን ነው፥ የዕብራውያን ጸሐፊ ለኢየሱስ ነው ይለናል። እና ኢየሱስ ብሉይ ላይ የነበረው ሰለሞን ነውን? እንደ እናንተ እምነት ኢየሱስ ያህዌህ ከሆነ ያህዌህ አምላክ እንዴት ፍጡሩን ሰለሞን ይሆናል? መልሱ፦ "ድርብ አጠቃቀም ነው" የሚል ነው፥ እንግዲያውስ ብሉይ ላይ የያህዌህ መንገድ ተብሎ አዲስ ላይ የጌታ መንገድ መባሉ "ድርብ አጠቃቀም ነው" በሚል ስሌትና ቀመር መረዳት ይቻላል። ናሙናውን እንቀጥል፦
ሆሴዕ 11፥1-2 *"እስራኤል ሕፃን በነበረ ጊዜ ወደድሁት፥ ልጄንም ከግብፅ ጠራሁት። አብዝቼ ብጠራቸው አጥብቀው ከፊቴ ራቁ፤ ለበኣሊምም ይሠዉ ነበር፥ ለተቀረጹ ምስሎችም ያጥኑ ነበር"*።
ማቴዎስ 2፥14-15 *"እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን በሌሊት ያዘና ከጌታ ዘንድ በነቢይ፦ "ልጄን ከግብፅ ጠራሁት" የተባለው እንዲፈጸም ወደ ግብፅ ሄደ፥ ሄሮድስም እስኪሞት ድረስ በዚያ ኖረ"*።
"ልጄንም ከግብፅ ጠራሁት" የሆሴዕ ዐውደ-ንባብ የሚናገረው ለእስራኤል ሕዝብ ነው፥ የማቴዎስ ጸሐፊ ለኢየሱስ ነው ይለናል። ታዲያ ኢየሱስ ሲጠራ አጥብቆ ከአምላክ ፊት የራቀ ነውን? ለበኣሊምም ይሠዋ ነበርን? ለተቀረጹ ምስሎችም ያጥን ነበርን? ቅሉ ግን "ድርብ አጠቃቀም ነው" የሚል ነው፥ እንግዲያውስ ብሉይ ላይ የያህዌህ መንገድ ተብሎ አዲስ ላይ የጌታ መንገድ መባሉ "ድርብ አጠቃቀም ነው" በሚል ልክና መልክ መረዳት ይቻላል። ስድስተኛ "የያህዌህን መንገድ ማለት የያህዌህ ሕግ፣ ሥርዓት፣ ትእዛዝ፣ መርሕ እና ቃል ነው፦
መዝሙር 18፥21 *"የያህዌህን መንገድ ጠብቄአለሁ፥ በአምላኬም አላመፅሁም"*።
መዝሙር 18፥30 *"የአምላኬ መንገድ ፍጹም ነው፥ የያህዌህን ቃል የነጠረ ነው፥ በእርሱ ለሚታመኑት ሁሉ ጋሻ ነው"*።
ምሳሌ 10፥29 *የያህዌህ መንገድ ያለ ነውር ለሚሄድ አምባ ነው፥ ጥፋት ግን ክፋትን ለሚያደርጉ*።
ኤርምያስ 5፥4 እኔም፦ የያህዌህን መንገድና የአምላካቸውን ሕግ አላወቁምና እነዚህ በእውነት ድሆችና ሰነፎች ናቸው"*።
የኢየሱስ ትምህርት እና ሕግ የያህዌህ ሕግ ነው፥ የራሱ ሳይሆን የላከኝ አብ የሰጠው ትእዛዝ ነው፦
ዮሐንስ 12፥49 *እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፥ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ"*።
ዮሐንስ 14፥24 የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም፤ *"የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም"*።
ዮሐንስ 17፥8 *"የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና እነርሱም ተቀበሉት"*።
የአብን ቃል ወደ እራሱ በማስጠጋት "ቃሌ" ማለቱ በራሱ የአብ እና የወልድ መንገድ አንድ መሆኑን ያሳያል። ዮሐንስ አዋጅ ነጋሪ የሆነ እና የጠረገው የያህዌህን እና የመሢሑን መንገድ ነው። ስለዚህ ኢሳይያስ 40፥3 ኢየሱስ ያህዌህ መሆኑን በፍጹም አያሳይም። እነዚያ ፈጣሪን ከሴት የተወለደው መሢሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ፦
5፥17 *እነዚያ አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ*፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ግመልህን እሰርና በአላህ ላይ ተመካ!
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።
6፥159 *”ቁርጥ ሐሳብም ባደረግህ ጊዜ በአላህ ላይ ተመካ፡፡ አላህ በእርሱ ላይ ተመኪዎችን ይወዳልና”*፡፡ فَإِذَا عَزَمْتَ فَتَوَكَّلْ عَلَى اللَّهِ ۚ إِنَّ اللَّهَ يُحِبُّ الْمُتَوَكِّلِينَ
አምላካችን አላህ ለእስራኤልም ልጆች፦ “ከእኔ ሌላ መመኪያን አትያዙ” በማለት ተናግሯል፦
17፥2 ሙሳንም መጽሐፉን ሰጠነው፡፡ ለእስራኤልም ልጆች መሪ አደረግነው፡፡ *”ከእኔ ሌላ መመኪያን አትያዙ! አልናቸውም”*፡፡ وَآتَيْنَا مُوسَى الْكِتَابَ وَجَعَلْنَاهُ هُدًى لِّبَنِي إِسْرَائِيلَ أَلَّا تَتَّخِذُوا مِن دُونِي وَكِيلًا
“አል-ወኪል” الْوَكِيل ማለት “መመኪያ” “መጠጊያ” “መሸሸጊያ” ማለት ሲሆን በቁርኣን ከተገለጹ 99 ስሞች አንዱ ነው፦
39፥9 እርሱም የምሥራቅና የምዕራብ ጌታ ነው፡፡ *”ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ መጠጊያ አድርገህም ያዘው”*፡፡ رَّبُّ الْمَشْرِقِ وَالْمَغْرِبِ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ فَاتَّخِذْهُ وَكِيلًا
አላህን መጠጊያ መመኪያ፣ መጠጊያ፣ መሸሸጊያ አድርጎ መያዝ “ተወኩል” تَوَكُّل ይባላል። ሰይጧን በእነዚያ ባመኑት እና በአላህ ላይ በሚመኩት ላይ ስልጣን የለውም፦
16፥99 *”እርሱ በእነዚያ ባመኑት እና በጌታቸው ላይ በሚጠጉት ላይ ለእርሱ ስልጣን የለውምና”*፡፡ إِنَّهُ لَيْسَ لَهُ سُلْطَانٌ عَلَى الَّذِينَ آمَنُوا وَعَلَىٰ رَبِّهِمْ يَتَوَكَّلُونَ
“በሚጠጉት” ለሚለው ቃል የገባው “የተወከሉን” يَتَوَكَّلُون ሲሆን ቁርጥ ሐሳብም ባደረጉ ጊዜ አላህ በቂዬ ነው ብለው በአላህ ላይ ሙሉ ለሙሉ የተወከሉ ባሮቹ ደግሞ “ሙተወከሉን” مُتَوَكِّلُون ይባላል፦
39፥38 *«አላህ በቂዬ ነው፡፡ በእርሱ ላይ ተመኪዎች ይመካሉ»* በል፡፡ قُلْ حَسْبِيَ اللَّهُ ۖ عَلَيْهِ يَتَوَكَّلُ الْمُتَوَكِّلُونَ
6፥159 *”ቁርጥ ሐሳብም ባደረግህ ጊዜ በአላህ ላይ ተመካ፡፡ አላህ በእርሱ ላይ ተመኪዎችን ይወዳልና”*፡፡ فَإِذَا عَزَمْتَ فَتَوَكَّلْ عَلَى اللَّهِ ۚ إِنَّ اللَّهَ يُحِبُّ الْمُتَوَكِّلِينَ
"ቁርጥ ሐሳብም ባደረግህ" ማለት አንድ ሙሥሊም ሙሲባህ ሲመጣበት ጥንቃቄ በማድረግ ሰበቡ ያደርሳል፥ ከዚያ በላይ ከአቅሙ በላይ ያለውን ለአላህ ሰጥቶ በአላህ ላይ ይመካል። ለዛ ነው ነቢያችን"ﷺ" "ግመልህን እሰርና በአላህ ላይ ተመካ" ያሉት፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 2707
አነሥ ኢብኑ ማሊ እንዳስተላለፈው፦ “አንድ ሰው፦ *"የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" ሆይ! ግመሌን ልሰራትና በአላህ ላይ ልመካ ወይስ ልተዋትና በአላህ ላይ ልመካ? ብሎ ጠየቀ። እርሳቸውም፦ "እሰራትና በአላህ ላይ ተመካ" አሉት"*። قَالَ سَمِعْتُ أَنَسَ بْنَ مَالِكٍ، يَقُولُ قَالَ رَجُلٌ يَا رَسُولَ اللَّهِ أَعْقِلُهَا وَأَتَوَكَّلُ أَوْ أُطْلِقُهَا وَأَتَوَكَّلُ قَالَ " اعْقِلْهَا وَتَوَكَّلْ "
አምላካችን አላህ ሰበቡን አንድርሰን በእርሱ ላይ የምመካ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።
6፥159 *”ቁርጥ ሐሳብም ባደረግህ ጊዜ በአላህ ላይ ተመካ፡፡ አላህ በእርሱ ላይ ተመኪዎችን ይወዳልና”*፡፡ فَإِذَا عَزَمْتَ فَتَوَكَّلْ عَلَى اللَّهِ ۚ إِنَّ اللَّهَ يُحِبُّ الْمُتَوَكِّلِينَ
አምላካችን አላህ ለእስራኤልም ልጆች፦ “ከእኔ ሌላ መመኪያን አትያዙ” በማለት ተናግሯል፦
17፥2 ሙሳንም መጽሐፉን ሰጠነው፡፡ ለእስራኤልም ልጆች መሪ አደረግነው፡፡ *”ከእኔ ሌላ መመኪያን አትያዙ! አልናቸውም”*፡፡ وَآتَيْنَا مُوسَى الْكِتَابَ وَجَعَلْنَاهُ هُدًى لِّبَنِي إِسْرَائِيلَ أَلَّا تَتَّخِذُوا مِن دُونِي وَكِيلًا
“አል-ወኪል” الْوَكِيل ማለት “መመኪያ” “መጠጊያ” “መሸሸጊያ” ማለት ሲሆን በቁርኣን ከተገለጹ 99 ስሞች አንዱ ነው፦
39፥9 እርሱም የምሥራቅና የምዕራብ ጌታ ነው፡፡ *”ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ መጠጊያ አድርገህም ያዘው”*፡፡ رَّبُّ الْمَشْرِقِ وَالْمَغْرِبِ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ فَاتَّخِذْهُ وَكِيلًا
አላህን መጠጊያ መመኪያ፣ መጠጊያ፣ መሸሸጊያ አድርጎ መያዝ “ተወኩል” تَوَكُّل ይባላል። ሰይጧን በእነዚያ ባመኑት እና በአላህ ላይ በሚመኩት ላይ ስልጣን የለውም፦
16፥99 *”እርሱ በእነዚያ ባመኑት እና በጌታቸው ላይ በሚጠጉት ላይ ለእርሱ ስልጣን የለውምና”*፡፡ إِنَّهُ لَيْسَ لَهُ سُلْطَانٌ عَلَى الَّذِينَ آمَنُوا وَعَلَىٰ رَبِّهِمْ يَتَوَكَّلُونَ
“በሚጠጉት” ለሚለው ቃል የገባው “የተወከሉን” يَتَوَكَّلُون ሲሆን ቁርጥ ሐሳብም ባደረጉ ጊዜ አላህ በቂዬ ነው ብለው በአላህ ላይ ሙሉ ለሙሉ የተወከሉ ባሮቹ ደግሞ “ሙተወከሉን” مُتَوَكِّلُون ይባላል፦
39፥38 *«አላህ በቂዬ ነው፡፡ በእርሱ ላይ ተመኪዎች ይመካሉ»* በል፡፡ قُلْ حَسْبِيَ اللَّهُ ۖ عَلَيْهِ يَتَوَكَّلُ الْمُتَوَكِّلُونَ
6፥159 *”ቁርጥ ሐሳብም ባደረግህ ጊዜ በአላህ ላይ ተመካ፡፡ አላህ በእርሱ ላይ ተመኪዎችን ይወዳልና”*፡፡ فَإِذَا عَزَمْتَ فَتَوَكَّلْ عَلَى اللَّهِ ۚ إِنَّ اللَّهَ يُحِبُّ الْمُتَوَكِّلِينَ
"ቁርጥ ሐሳብም ባደረግህ" ማለት አንድ ሙሥሊም ሙሲባህ ሲመጣበት ጥንቃቄ በማድረግ ሰበቡ ያደርሳል፥ ከዚያ በላይ ከአቅሙ በላይ ያለውን ለአላህ ሰጥቶ በአላህ ላይ ይመካል። ለዛ ነው ነቢያችን"ﷺ" "ግመልህን እሰርና በአላህ ላይ ተመካ" ያሉት፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 2707
አነሥ ኢብኑ ማሊ እንዳስተላለፈው፦ “አንድ ሰው፦ *"የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" ሆይ! ግመሌን ልሰራትና በአላህ ላይ ልመካ ወይስ ልተዋትና በአላህ ላይ ልመካ? ብሎ ጠየቀ። እርሳቸውም፦ "እሰራትና በአላህ ላይ ተመካ" አሉት"*። قَالَ سَمِعْتُ أَنَسَ بْنَ مَالِكٍ، يَقُولُ قَالَ رَجُلٌ يَا رَسُولَ اللَّهِ أَعْقِلُهَا وَأَتَوَكَّلُ أَوْ أُطْلِقُهَا وَأَتَوَكَّلُ قَالَ " اعْقِلْهَا وَتَوَكَّلْ "
አምላካችን አላህ ሰበቡን አንድርሰን በእርሱ ላይ የምመካ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ተስሊብ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
12፥41 *"የወህኒ ቤት ጓደኞቼ ሆይ! አንደኛችሁማ ጌታውን (ንጉሡን) ጠጅ ያጠጣል፡፡ ሌላውማ "ይሰቀላል"፡፡ ከራሱም በራሪ (አሞራ) ትበላለች፡፡ ያ ፍቹን የምትጠይቁት ነገር ተፈጸመ"* አላቸው፡፡ يَا صَاحِبَيِ السِّجْنِ أَمَّا أَحَدُكُمَا فَيَسْقِي رَبَّهُ خَمْرًا ۖ وَأَمَّا الْآخَرُ فَيُصْلَبُ فَتَأْكُلُ الطَّيْرُ مِن رَّأْسِهِ ۚ قُضِيَ الْأَمْرُ الَّذِي فِيهِ تَسْتَفْتِيَانِ
አምላካችን አላህ በዩሱፍ ዘመን የነበረው ክስተት "ነቅሱ ዐለይከ" نَقُصُّ عَلَيْكَ ማለትም "እንተርክልሃለን" በማለት ክስተቱን ይተርካል፦
12፥3 እኛ ይህንን ቁርኣን ወደ አንተ በማውረዳችን በጣም መልካም ዜናዎችን በአንተ ላይ እንተርክልሃለን፡፡ እነሆ ከእርሱ በፊት በእርግጥ ከዘንጊዎቹ ነበርክ"*፡፡ نَحْنُ نَقُصُّ عَلَيْكَ أَحْسَنَ الْقَصَصِ بِمَا أَوْحَيْنَا إِلَيْكَ هَـٰذَا الْقُرْآنَ وَإِن كُنتَ مِن قَبْلِهِ لَمِنَ الْغَافِلِينَ
አላህ በሡረቱ ዩሱፍ ከተረካቸው አንዱ ስለ ተስሊብ ነው፥ "ተስሊብ" تَصْلِيب የሚለው ቃል "ሶልለበ" صَلَّبَ ማለትም "ሰቀለ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ስቅላት" ማለት ነው። "ሶልብ" صَلْب የሚለው ቃል "ሶለበ" صَلَبَ ማለትም "ተሰቀለ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ስቅለት" ማለት ነው። የግብጽ ነገሥታት ወንጀለኛ በስቅላት ይቀጡ እንደነበር እንዲህ ይተርክልናል፦
12፥41 *"የወህኒ ቤት ጓደኞቼ ሆይ! አንደኛችሁማ ጌታውን (ንጉሡን) ጠጅ ያጠጣል፡፡ ሌላውማ "ይሰቀላል"፡፡ ከራሱም በራሪ (አሞራ) ትበላለች፡፡ ያ ፍቹን የምትጠይቁት ነገር ተፈጸመ"* አላቸው፡፡ يَا صَاحِبَيِ السِّجْنِ أَمَّا أَحَدُكُمَا فَيَسْقِي رَبَّهُ خَمْرًا ۖ وَأَمَّا الْآخَرُ فَيُصْلَبُ فَتَأْكُلُ الطَّيْرُ مِن رَّأْسِهِ ۚ قُضِيَ الْأَمْرُ الَّذِي فِيهِ تَسْتَفْتِيَانِ
እዚህ አንቀጽ "ይሰቀላል" ለሚለው የግስ መደብ የገባው ቃል "ዩስለቡ" يُصْلَبُ ነው። "ጌታው" የተባለው በዩሱፍ ዘመን የነበረው ፈርዖን ነው፥ የግብጽ ነገሥታት ወንጀለኛ በስቅላት እንደሚቀጡ የሚያሳይ ታሪካዊ ሆነ ሥነ-ቁፋሮአዊ መረጃ አልተገኘም። ታሪክ ሆነ ሥነ-ቁፋሮ ወንጀለኛ በስቅላት ያለው መረጃ በ 559 ቅድመ-ልደት በፋርሳዊያን ጊዜ ነው፥ ያ ማለት ከዚያ በፊት ወንጀለኛ በስቅላት አይቀጡም ነበር ማለት አይደለም። ምክንያቱም ታሪክ ያለፈውን ክስተት የሚተርክ የምርምር ጥናት እና አሰሳ ሲሆን በታሪክ ጥናት ውስጥ ለታሪክ ምንጭ የሚሆኑ ሁለት መረጃዎች አሉ፥ አንደኛው ትውፊት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የሥነ-ቁፋሮ ጥናት ነው። “ትውፊት” ከትውልድ ወደ ትውልድ በቃል የሚተላለፍ ቅብብል ሲሆን "ሥነ-ቁፋሮ ጥናት" ደግሞ በተለያየ ቁስ ላይ የተጻፉትን ጽሑፎች አስሶና ቆፍሮ የሚያቀርብ የታሪክ ምንጭ ነው። ትውፊት ሆነ ሥነ-ቁፋሮ ጥናት ባህል ላይ እና ስልጣኔ ላይ መሠረት ያደረጉ ግምት”speculation” ናቸው።
ይህን ግምት የታሪክ ምሁራን በስድስት ከፍለው ያስቀምጡታል፥ እነዚህም፦ መቼ ተገኘ ጊዜን፣ የት ተገኘ ቦታን፣ ማን ደረስው ምንጭን፣ ቅድመ-ሁኔታ፣ ስምምነት እና ዋጋነት ናቸው። አራቱ ግምቶች መቼ ተገኘ፣ የት ተገኘ፣ ማን ደረስው እና ቅድመ-ትንታኔ ላዕላይ ኂስ ሲባሉ አምስተኛው ግምት ስምምነት ደግሞ ታኅታይ እና ውጫዊ ኂስ ነው፥ በመቀጠል ስድስተኛው ግምት ዋጋነት ውስጣዊ ኂስ ነው። የታሪክ ምሁራን እንደሚያስተነትኑት ታሪክ መረጃ እንጂ ማስረጃ አይደለም። አምላካችን አላህ በዩሱፍ ዘመን የነበረው ክስተት የተረከው ትረካ ግን ማስረጃ መሆን ይችላል፥ ምክንያቱም እርሱ “አል-ገይቡል ማዲ” ٱلْغَيْب الْمَاضِي ማለትም “ኀላፊያት የሩቅ ነገር” በትክክል የሚያውቅ ሁሉን ዐዋቂ ነውና።
እዚህ ድረስ ከተግባባ የግብጽ ነገሥታት ወንጀለኛ በስቅላት እንደሚቀጡ የሚያሳይ ታሪካዊ ሆነ ሥነ-ቁፋሮአዊ መረጃ አለመገኘቱ ክስተቱን ውሸት ካደረገው እንግዲያውስ ከፋርሳዊያን በፊት አንድ ሺህ ዓመት ቀደም ብሎ የግብጽ ነገሥታት ወንጀለኛ በስቅላት እንደሚቀጡ የሚያሳይ ተመሳሳይ ታሪክ እና ትርክት በባይብል ቁልጭና ፍንትው ብሎ ተቀምጧል፦
ዘፍጥረት 40፥19 *"እስከ ሦስት ቀን ድረስ ፈርዖን ራስህን ከፍ ያደርጋል፥ "በእንጨትም ላይ ይሰቅልሃል"፣ ወፎችም ሥጋህን ይበሉታል"*። שלשת ימים ישא פרעה את־ראשך מעליך ותלה אותך על־עץ ואכל העוף את־בשרך מעליך׃
እዚህ አንቀጽ ላይ "ይሰቅላል" ለሚለው "ታላህ" תָלָ֥ה ሲሆን የሚገርመው በፋርሱ ንጉሥ በአርጤክስስ እጃቸውን ያነሱት ሁለቱ የአርጤክስስ ጃንደረቦች በስቅላት "ተሰቀሉ" ለሚለው የግስ መደብ የገባው ተመሳሳይ ርቢ ያለው "ዪታሉ" יִּתָּל֥וּ ነው፦
አስቴር 2፥23 *"ነገሩም ተመረመረ፥ እንዲህም ሆኖ ተገኘ፥ "ሁለቱም በዛፍ ላይ ተሰቀሉ" ያም በንጉሡ ፊት በታሪክ መጽሐፍ ተጻፈ"*። ויבקש הדבר וימצא ויתלו שניהם על עץ ויכתב בספר דברי הימים לפני המלך׃
በእንጨት ላይ በማንጠልጠል የሚቀጣው ቅጣት ስቅላት ይባላል። ቅሉና ጥቅሉ የስቅለት ቅጣት ከፋርሳውያን 1000 ዓመት በፊት በፈርዖኑ ጊዜ ነበረ፦
ዘፍጥረት 40፥22 *"የእንጀራ አበዛዎቹንም አለቃ "ሰቀለው"፥ ዮሴፍ እንደተረጎመላቸው"*።
ዘፍጥረት 41፥13 እንዲህም ሆነ እንደ ተረጐመልን እንደዚያው ሆነ፤ እኔ ወደ ሹመቴ ተመለስሁ፥ *"እርሱም ተሰቀለ"*።
ከፋርሳውያን 800 ዓመት በፊት በሙሴ ጊዜ ነበረ፦
ዘዳግም 21፥22-23 *"ማንም ሰው ለሞት የሚያበቃውን ኃጢአት ቢሠራ፥ እንዲሞትም ቢፈረድበት፥ *"በእንጨትም ላይ ብትሰቅለው፥ በእንጨት ላይ የተሰቀለ"* በእግዚአብሔር ዘንድ የተረገመ ነውና ሬሳው በእንጨት ላይ አይደር።
ከፋርሳውያን 400 ዓመት በፊት በዳዊት ጊዜ ነበረ፦
2 ሳሙኤል 21፥12 ዳዊትም ሄደ፥ ሳኦልንም በጊልቦዓ በገደሉ ጊዜ ፍልስጥኤማውያን *"ከሰቀሉአቸው"* ስፍራ ከቤትሳን አደባባይ ከሰረቁት ከኢያቢስ ገለዓድ ሰዎች የሳኦልንና የልጁን የዮናታንን አጥንት ወሰደ፤
የብሪታኒካ የዓለም ሃይማኖቶች መድብለ ዕውቀት ገጽ 270 ላይ፦ "ወንጀለኛ በስቅላት መስቀል የተጀመረው በ 559 ቅድመ-ልደት በፋርሳዊያን ጊዜ ነው" ካለ ከላይ ያሉት የባይብል ትርክቶች ገደል ገቡ ማለት ነው። አይ "ታሪክ እና ሥነ-ቁፋሮ ያልደረሱበት ጉዳይ ነው" ካላችሁ እንግዲያውስ ከላይ ያለውንም የአምላካችን የአላህ ትርክት ታሪክ እና ሥነ-ቁፋሮ ያልደረሱበት ጉዳይ ነው በሚል ቀመርና ስሌት ተረዱት።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
12፥41 *"የወህኒ ቤት ጓደኞቼ ሆይ! አንደኛችሁማ ጌታውን (ንጉሡን) ጠጅ ያጠጣል፡፡ ሌላውማ "ይሰቀላል"፡፡ ከራሱም በራሪ (አሞራ) ትበላለች፡፡ ያ ፍቹን የምትጠይቁት ነገር ተፈጸመ"* አላቸው፡፡ يَا صَاحِبَيِ السِّجْنِ أَمَّا أَحَدُكُمَا فَيَسْقِي رَبَّهُ خَمْرًا ۖ وَأَمَّا الْآخَرُ فَيُصْلَبُ فَتَأْكُلُ الطَّيْرُ مِن رَّأْسِهِ ۚ قُضِيَ الْأَمْرُ الَّذِي فِيهِ تَسْتَفْتِيَانِ
አምላካችን አላህ በዩሱፍ ዘመን የነበረው ክስተት "ነቅሱ ዐለይከ" نَقُصُّ عَلَيْكَ ማለትም "እንተርክልሃለን" በማለት ክስተቱን ይተርካል፦
12፥3 እኛ ይህንን ቁርኣን ወደ አንተ በማውረዳችን በጣም መልካም ዜናዎችን በአንተ ላይ እንተርክልሃለን፡፡ እነሆ ከእርሱ በፊት በእርግጥ ከዘንጊዎቹ ነበርክ"*፡፡ نَحْنُ نَقُصُّ عَلَيْكَ أَحْسَنَ الْقَصَصِ بِمَا أَوْحَيْنَا إِلَيْكَ هَـٰذَا الْقُرْآنَ وَإِن كُنتَ مِن قَبْلِهِ لَمِنَ الْغَافِلِينَ
አላህ በሡረቱ ዩሱፍ ከተረካቸው አንዱ ስለ ተስሊብ ነው፥ "ተስሊብ" تَصْلِيب የሚለው ቃል "ሶልለበ" صَلَّبَ ማለትም "ሰቀለ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ስቅላት" ማለት ነው። "ሶልብ" صَلْب የሚለው ቃል "ሶለበ" صَلَبَ ማለትም "ተሰቀለ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ስቅለት" ማለት ነው። የግብጽ ነገሥታት ወንጀለኛ በስቅላት ይቀጡ እንደነበር እንዲህ ይተርክልናል፦
12፥41 *"የወህኒ ቤት ጓደኞቼ ሆይ! አንደኛችሁማ ጌታውን (ንጉሡን) ጠጅ ያጠጣል፡፡ ሌላውማ "ይሰቀላል"፡፡ ከራሱም በራሪ (አሞራ) ትበላለች፡፡ ያ ፍቹን የምትጠይቁት ነገር ተፈጸመ"* አላቸው፡፡ يَا صَاحِبَيِ السِّجْنِ أَمَّا أَحَدُكُمَا فَيَسْقِي رَبَّهُ خَمْرًا ۖ وَأَمَّا الْآخَرُ فَيُصْلَبُ فَتَأْكُلُ الطَّيْرُ مِن رَّأْسِهِ ۚ قُضِيَ الْأَمْرُ الَّذِي فِيهِ تَسْتَفْتِيَانِ
እዚህ አንቀጽ "ይሰቀላል" ለሚለው የግስ መደብ የገባው ቃል "ዩስለቡ" يُصْلَبُ ነው። "ጌታው" የተባለው በዩሱፍ ዘመን የነበረው ፈርዖን ነው፥ የግብጽ ነገሥታት ወንጀለኛ በስቅላት እንደሚቀጡ የሚያሳይ ታሪካዊ ሆነ ሥነ-ቁፋሮአዊ መረጃ አልተገኘም። ታሪክ ሆነ ሥነ-ቁፋሮ ወንጀለኛ በስቅላት ያለው መረጃ በ 559 ቅድመ-ልደት በፋርሳዊያን ጊዜ ነው፥ ያ ማለት ከዚያ በፊት ወንጀለኛ በስቅላት አይቀጡም ነበር ማለት አይደለም። ምክንያቱም ታሪክ ያለፈውን ክስተት የሚተርክ የምርምር ጥናት እና አሰሳ ሲሆን በታሪክ ጥናት ውስጥ ለታሪክ ምንጭ የሚሆኑ ሁለት መረጃዎች አሉ፥ አንደኛው ትውፊት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የሥነ-ቁፋሮ ጥናት ነው። “ትውፊት” ከትውልድ ወደ ትውልድ በቃል የሚተላለፍ ቅብብል ሲሆን "ሥነ-ቁፋሮ ጥናት" ደግሞ በተለያየ ቁስ ላይ የተጻፉትን ጽሑፎች አስሶና ቆፍሮ የሚያቀርብ የታሪክ ምንጭ ነው። ትውፊት ሆነ ሥነ-ቁፋሮ ጥናት ባህል ላይ እና ስልጣኔ ላይ መሠረት ያደረጉ ግምት”speculation” ናቸው።
ይህን ግምት የታሪክ ምሁራን በስድስት ከፍለው ያስቀምጡታል፥ እነዚህም፦ መቼ ተገኘ ጊዜን፣ የት ተገኘ ቦታን፣ ማን ደረስው ምንጭን፣ ቅድመ-ሁኔታ፣ ስምምነት እና ዋጋነት ናቸው። አራቱ ግምቶች መቼ ተገኘ፣ የት ተገኘ፣ ማን ደረስው እና ቅድመ-ትንታኔ ላዕላይ ኂስ ሲባሉ አምስተኛው ግምት ስምምነት ደግሞ ታኅታይ እና ውጫዊ ኂስ ነው፥ በመቀጠል ስድስተኛው ግምት ዋጋነት ውስጣዊ ኂስ ነው። የታሪክ ምሁራን እንደሚያስተነትኑት ታሪክ መረጃ እንጂ ማስረጃ አይደለም። አምላካችን አላህ በዩሱፍ ዘመን የነበረው ክስተት የተረከው ትረካ ግን ማስረጃ መሆን ይችላል፥ ምክንያቱም እርሱ “አል-ገይቡል ማዲ” ٱلْغَيْب الْمَاضِي ማለትም “ኀላፊያት የሩቅ ነገር” በትክክል የሚያውቅ ሁሉን ዐዋቂ ነውና።
እዚህ ድረስ ከተግባባ የግብጽ ነገሥታት ወንጀለኛ በስቅላት እንደሚቀጡ የሚያሳይ ታሪካዊ ሆነ ሥነ-ቁፋሮአዊ መረጃ አለመገኘቱ ክስተቱን ውሸት ካደረገው እንግዲያውስ ከፋርሳዊያን በፊት አንድ ሺህ ዓመት ቀደም ብሎ የግብጽ ነገሥታት ወንጀለኛ በስቅላት እንደሚቀጡ የሚያሳይ ተመሳሳይ ታሪክ እና ትርክት በባይብል ቁልጭና ፍንትው ብሎ ተቀምጧል፦
ዘፍጥረት 40፥19 *"እስከ ሦስት ቀን ድረስ ፈርዖን ራስህን ከፍ ያደርጋል፥ "በእንጨትም ላይ ይሰቅልሃል"፣ ወፎችም ሥጋህን ይበሉታል"*። שלשת ימים ישא פרעה את־ראשך מעליך ותלה אותך על־עץ ואכל העוף את־בשרך מעליך׃
እዚህ አንቀጽ ላይ "ይሰቅላል" ለሚለው "ታላህ" תָלָ֥ה ሲሆን የሚገርመው በፋርሱ ንጉሥ በአርጤክስስ እጃቸውን ያነሱት ሁለቱ የአርጤክስስ ጃንደረቦች በስቅላት "ተሰቀሉ" ለሚለው የግስ መደብ የገባው ተመሳሳይ ርቢ ያለው "ዪታሉ" יִּתָּל֥וּ ነው፦
አስቴር 2፥23 *"ነገሩም ተመረመረ፥ እንዲህም ሆኖ ተገኘ፥ "ሁለቱም በዛፍ ላይ ተሰቀሉ" ያም በንጉሡ ፊት በታሪክ መጽሐፍ ተጻፈ"*። ויבקש הדבר וימצא ויתלו שניהם על עץ ויכתב בספר דברי הימים לפני המלך׃
በእንጨት ላይ በማንጠልጠል የሚቀጣው ቅጣት ስቅላት ይባላል። ቅሉና ጥቅሉ የስቅለት ቅጣት ከፋርሳውያን 1000 ዓመት በፊት በፈርዖኑ ጊዜ ነበረ፦
ዘፍጥረት 40፥22 *"የእንጀራ አበዛዎቹንም አለቃ "ሰቀለው"፥ ዮሴፍ እንደተረጎመላቸው"*።
ዘፍጥረት 41፥13 እንዲህም ሆነ እንደ ተረጐመልን እንደዚያው ሆነ፤ እኔ ወደ ሹመቴ ተመለስሁ፥ *"እርሱም ተሰቀለ"*።
ከፋርሳውያን 800 ዓመት በፊት በሙሴ ጊዜ ነበረ፦
ዘዳግም 21፥22-23 *"ማንም ሰው ለሞት የሚያበቃውን ኃጢአት ቢሠራ፥ እንዲሞትም ቢፈረድበት፥ *"በእንጨትም ላይ ብትሰቅለው፥ በእንጨት ላይ የተሰቀለ"* በእግዚአብሔር ዘንድ የተረገመ ነውና ሬሳው በእንጨት ላይ አይደር።
ከፋርሳውያን 400 ዓመት በፊት በዳዊት ጊዜ ነበረ፦
2 ሳሙኤል 21፥12 ዳዊትም ሄደ፥ ሳኦልንም በጊልቦዓ በገደሉ ጊዜ ፍልስጥኤማውያን *"ከሰቀሉአቸው"* ስፍራ ከቤትሳን አደባባይ ከሰረቁት ከኢያቢስ ገለዓድ ሰዎች የሳኦልንና የልጁን የዮናታንን አጥንት ወሰደ፤
የብሪታኒካ የዓለም ሃይማኖቶች መድብለ ዕውቀት ገጽ 270 ላይ፦ "ወንጀለኛ በስቅላት መስቀል የተጀመረው በ 559 ቅድመ-ልደት በፋርሳዊያን ጊዜ ነው" ካለ ከላይ ያሉት የባይብል ትርክቶች ገደል ገቡ ማለት ነው። አይ "ታሪክ እና ሥነ-ቁፋሮ ያልደረሱበት ጉዳይ ነው" ካላችሁ እንግዲያውስ ከላይ ያለውንም የአምላካችን የአላህ ትርክት ታሪክ እና ሥነ-ቁፋሮ ያልደረሱበት ጉዳይ ነው በሚል ቀመርና ስሌት ተረዱት።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ይሄድልናል ወይስ ይሄድላቸዋል?
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
6፥19 *«እርሱ አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ እኔም ከምታጋሩት ነገር ንጹሕ ነኝ»* በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا هُوَ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ وَإِنَّنِى بَرِىٓءٌۭ مِّمَّا تُشْرِكُونَ
"ሰፕቱጀንት" ወይም "ሰፕቱአጀንት"Ἑβδομήκοντα" ማለት "ሰባ" ማለት ሲሆን በ 280 ቅድመ-ልደት በአሌክሳንድያ ይኖሩ የነበሩ የግሪክ አይሁዳውያን 70 ምሁራን ስም ነው፥ በሮማውያን ቁጥር ምልክት"LXX" ይባላል። እነዚህ ምሁራን 72 ነበሩ፥ ሁለቱ ሲሞቱ ሰባው ሊቃናት የዕብራይስጡን ቅዱሳን ጽሑፎች ወደ ሄለናዊ ግሪክ ኮይኔ ተርጉመውታል። እዚህ ትርጉም ላይ ለዚህ ሕዝብ ማንስ ይሄድላቸዋል? የሚል ኃይለ-ቃል አለ፦
ኢሳይያስ 6፥8 *የጌታንም ድምፅ፦ ማንን እልካለሁ? ለዚህ ሕዝብ ማንስ ይሄድላቸዋል? ሲል ሰማሁ። እኔም፦ እነሆኝ፥ እኔን ላከኝ" አልሁ"*። καὶ ἤκουσα τῆς φωνῆς Κυρίου λέγοντος· τίνα ἀποστείλω, καὶ τίς πορεύσεται πρὸς τὸν λαὸν τοῦτον; καὶ εἶπα· ἰδοὺ ἐγώ εἰμι· ἀπόστειλόν με.
ልብ አድርግ የሚለው "ይሄድላቸዋል" ነው። ለማን ሲባል "ለዚህ ሕዝብ" ኢሳይያስም በብዜት "እኔን ላኩኝ" ሳይሆን በነጠላ "እኔን ላከኝ" ብሏል፥ ጌታም፦ "ሂድ፥ ይህን ሕዝብ፦ መስማትን ትሰማላችሁ አታስተውሉምም፤ ማየትንም ታያላችሁ አትመለከቱምም" በላቸው" አለ፦
ኢሳይያስ 6፥9 *"እርሱም፦ ሂድ፥ ይህን ሕዝብ፦ መስማትን ትሰማላችሁ አታስተውሉምም፤ ማየትንም ታያላችሁ አትመለከቱምም" በላቸው"*።
ነገር ግን ከግሪክ ሰፕቱጀት 100 ዓመት በኃላ 875 ድኅረ-ልደት የተዘጋጀው ማሶሬቲክ እደ-ክታብ ላይ በተቃራኒው ማንስ ይሄድልናል? የሚል ኃይለ-ቃል አለ፦
ኢሳይያስ 6፥8 *የጌታንም ድምፅ፦ ማንን እልካለሁ? ይሄድልናል? ሲል ሰማሁ። እኔም፦ እነሆኝ፥ እኔን ላከኝ" አልሁ"*። וָאֶשְׁמַ֞ע אֶת־קֹ֤ול אֲדֹנָי֙ אֹמֵ֔ר אֶת־מִ֥י אֶשְׁלַ֖ח וּמִ֣י יֵֽלֶךְ־לָ֑נוּ וָאֹמַ֖ר הִנְנִ֥י שְׁלָחֵֽנִ
ትክክሉ የቱ ነው? ይሄድላቸዋል የሚለው የግሪክ ሰፕቱጀንት ወይስ ይሄድልናል የማሶሬቲክ እደ-ክታብ? ሁለቱን ለመዳኘት ከግሪክ ሰፕቱጀንት በፊት የነበረውን የነቢያት ፓሌዎ ዕብራይስጥ ጽሑሮች ጠፍተዋል፥ ግን ከደኃራይ ማሶሬቲክ ይልቅ ቀዳማይ ሰፕቱጀንት ሚዛን ይደፋል። ሙግቱን እናጥብብ እና "ይሄድልናል" ቢባልስ ሥላሴን ያሳያልን? በፍጹም። ምክንያቱን አንድ ማንነት ብዜት ተሳቢ ተውላጠ-ስም ተጠቀመ ማለት ያ ማንነት ሥላሴ ነበር ማለት አይደለም፥ "ኒ" נִי የነበረው ነጠላ ተሳቢ ተውላጠ-ስም በብዜት "ኑ" נוּ በሚል መጥቷል፦
ዕዝራ 4፥7 *"በአርጤክስስ ዘመን ቢሽላም፥ ሚትሪዳጡ፥ ጣብኤል ተባባሪዎቹም ለፋርስ ንጉሥ ለአርጤክስስ ጻፉ"*።
ዕዝራ 4፥18 ሰላም! *"አሁንም "ወደ እኛ" עֲלֶ֑ינָא የላካችሁት ደብዳቤ በፊቴ ተተርጕሞ ተነበበ"*።
ልብ አድርግ "አርጤክስስ" የሚለው ቃላ ላይ መነሻ ቅጥያ ያለው "ለ" የሚለው መስተዋድድ ለንጉሡ ብቻ የተላከ ደብዳቤ ነው። ንጉሡ ግን በዐረማይክ "ና" נָא ብሎ በብዜት ተጠቅሟል፥ ግን ንጉሡ አንድም ሦስትም ሆኖ አይደለም፦
ዳንኤል 2፥25 *የዚያን ጊዜም አርዮክ ዳንኤልን ፈጥኖ ወደ ንጉሡ አስገባውና፦ "ከይሁዳ ምርኮኞች ያለውን ለንጉሡ ፍቺውን የሚያስታውቀውን ሰው አግኝቼአለሁ" አለው*።
ዳንኤል 2፥36 ሕልሙ ይህ ነው፥ *"አሁንም ፍቺውን በንጉሡ ፊት እንናገራለን" נֵאמַ֥ר *።
"አማር" אֲמַר በሚል ግስ ላይ "ኔ" נֵ የሚል "ባለቤት ተውላጠ-ስም አለ። አርዮክ ወደ ንጉሡ ያስገባው ዳንኤልን ብቻ ሆኖ ሳለ ዳንኤን በብዜት "እንናገራለን" ብሏል፥ ግን ዳንኤል አንድም ሦስትም ሆኖ አይደለም። ሙግቱን አሁንም እናጥብበውና "ይሄድልናል" የሚለው ከአንድ በላይ ላሉ ማንነቶች ነው ነው ብንል እንኳን አሁንም ሥላሴን በፍጹም አያሳይም። ዐውዱ ላይ መላእክት አሉ፥ ኢሳይያስ ሲናገር ከሱራፌልም አንዱ እየበረረ ወደ እርሱ መጥቶ፦ "እነሆ፥ ይህ ከንፈሮችህን ነክቶአል፤ በደልህም ከአንተ ተወገደ፥ ኃጢአትህም ተሰረየልህ" አለው፦
ኢሳይያስ 6፥2 *"ሱራፌልም ከእርሱ በላይ ቆመው ነበር"*።
ኢሳይያስ 6፥5-7 *"እኔም፦ ከንፈሮቼ የረከሱብኝ ሰው በመሆኔ፥ ከንፈሮቻቸውም በረከሱባቸው ሕዝብ መካከል በመቀመጤ ዓይኖቼ የሠራዊትን ጌታ ንጉሡን እግዚአብሔርን ስለ አዩ ጠፍቻለሁና ወዮልኝ! አልሁ*። ከሱራፌልም አንዱ እየበረረ ወደ እኔ መጣ፥ በእጁም ከመሠዊያው በጕጠት የወሰደው ፍም ነበረ። አፌንም ዳሰሰበትና፦ እነሆ፥ ይህ ከንፈሮችህን ነክቶአል፤ በደልህም ከአንተ ተወገደ፥ ኃጢአትህም ተሰረየልህ፡ አለኝ*።
እንደ ባይብሉ እግዚአብሔር የሰማይም ሠራዊት ሁሉ በቀኙና በግራው አሉ፥ ያዕቆብ ከእግዚአብሔር እና ከመልአኩ ጋር ስለተነጋገረ " ከእኛ ጋር ተነጋገረ" ብሏል፦
1ኛ ነገሥት 22፥19 *"እግዚአብሔር በዙፋኑ ተቀምጦ፥ የሰማይም ሠራዊት ሁሉ በቀኙና በግራው ቆመው አየሁ*።
ሆሴዕ 12፥4 ከመልአኩም ጋር ታግሎ አሸነፈ፤ አልቅሶም ለመነው። በቤቴልም አገኘው፥ *"በዚያም "ከ-እኛ" ጋር עִמָּֽנוּ ተነጋገረ"*።
አየክ "ኑ" נוּ የሚለው ተሳቢ ተውላጠ-ስም ከመላእክት ጋር እንዳገለገለ? በምንም ሒሳብ ሥላሴን አያመለከትም። በተረፈ አንዱ አምላክ አንድ ማንነት ኖሮት ለግነት እኛነት ሲጠቀም በውስጡ ሦስት አባላት አሉት ብሎ ሌሎችን ማንነቶችን በማንነቱ ላይ ማጋራት ሺርክ ነው። እርሱ አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ እኔም ከምታጋሩት ነገር ንጹሕ ነኝ፦
6፥19 *«እርሱ አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ እኔም ከምታጋሩት ነገር ንጹሕ ነኝ»* በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا هُوَ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ وَإِنَّنِى بَرِىٓءٌۭ مِّمَّا تُشْرِكُونَ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
6፥19 *«እርሱ አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ እኔም ከምታጋሩት ነገር ንጹሕ ነኝ»* በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا هُوَ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ وَإِنَّنِى بَرِىٓءٌۭ مِّمَّا تُشْرِكُونَ
"ሰፕቱጀንት" ወይም "ሰፕቱአጀንት"Ἑβδομήκοντα" ማለት "ሰባ" ማለት ሲሆን በ 280 ቅድመ-ልደት በአሌክሳንድያ ይኖሩ የነበሩ የግሪክ አይሁዳውያን 70 ምሁራን ስም ነው፥ በሮማውያን ቁጥር ምልክት"LXX" ይባላል። እነዚህ ምሁራን 72 ነበሩ፥ ሁለቱ ሲሞቱ ሰባው ሊቃናት የዕብራይስጡን ቅዱሳን ጽሑፎች ወደ ሄለናዊ ግሪክ ኮይኔ ተርጉመውታል። እዚህ ትርጉም ላይ ለዚህ ሕዝብ ማንስ ይሄድላቸዋል? የሚል ኃይለ-ቃል አለ፦
ኢሳይያስ 6፥8 *የጌታንም ድምፅ፦ ማንን እልካለሁ? ለዚህ ሕዝብ ማንስ ይሄድላቸዋል? ሲል ሰማሁ። እኔም፦ እነሆኝ፥ እኔን ላከኝ" አልሁ"*። καὶ ἤκουσα τῆς φωνῆς Κυρίου λέγοντος· τίνα ἀποστείλω, καὶ τίς πορεύσεται πρὸς τὸν λαὸν τοῦτον; καὶ εἶπα· ἰδοὺ ἐγώ εἰμι· ἀπόστειλόν με.
ልብ አድርግ የሚለው "ይሄድላቸዋል" ነው። ለማን ሲባል "ለዚህ ሕዝብ" ኢሳይያስም በብዜት "እኔን ላኩኝ" ሳይሆን በነጠላ "እኔን ላከኝ" ብሏል፥ ጌታም፦ "ሂድ፥ ይህን ሕዝብ፦ መስማትን ትሰማላችሁ አታስተውሉምም፤ ማየትንም ታያላችሁ አትመለከቱምም" በላቸው" አለ፦
ኢሳይያስ 6፥9 *"እርሱም፦ ሂድ፥ ይህን ሕዝብ፦ መስማትን ትሰማላችሁ አታስተውሉምም፤ ማየትንም ታያላችሁ አትመለከቱምም" በላቸው"*።
ነገር ግን ከግሪክ ሰፕቱጀት 100 ዓመት በኃላ 875 ድኅረ-ልደት የተዘጋጀው ማሶሬቲክ እደ-ክታብ ላይ በተቃራኒው ማንስ ይሄድልናል? የሚል ኃይለ-ቃል አለ፦
ኢሳይያስ 6፥8 *የጌታንም ድምፅ፦ ማንን እልካለሁ? ይሄድልናል? ሲል ሰማሁ። እኔም፦ እነሆኝ፥ እኔን ላከኝ" አልሁ"*። וָאֶשְׁמַ֞ע אֶת־קֹ֤ול אֲדֹנָי֙ אֹמֵ֔ר אֶת־מִ֥י אֶשְׁלַ֖ח וּמִ֣י יֵֽלֶךְ־לָ֑נוּ וָאֹמַ֖ר הִנְנִ֥י שְׁלָחֵֽנִ
ትክክሉ የቱ ነው? ይሄድላቸዋል የሚለው የግሪክ ሰፕቱጀንት ወይስ ይሄድልናል የማሶሬቲክ እደ-ክታብ? ሁለቱን ለመዳኘት ከግሪክ ሰፕቱጀንት በፊት የነበረውን የነቢያት ፓሌዎ ዕብራይስጥ ጽሑሮች ጠፍተዋል፥ ግን ከደኃራይ ማሶሬቲክ ይልቅ ቀዳማይ ሰፕቱጀንት ሚዛን ይደፋል። ሙግቱን እናጥብብ እና "ይሄድልናል" ቢባልስ ሥላሴን ያሳያልን? በፍጹም። ምክንያቱን አንድ ማንነት ብዜት ተሳቢ ተውላጠ-ስም ተጠቀመ ማለት ያ ማንነት ሥላሴ ነበር ማለት አይደለም፥ "ኒ" נִי የነበረው ነጠላ ተሳቢ ተውላጠ-ስም በብዜት "ኑ" נוּ በሚል መጥቷል፦
ዕዝራ 4፥7 *"በአርጤክስስ ዘመን ቢሽላም፥ ሚትሪዳጡ፥ ጣብኤል ተባባሪዎቹም ለፋርስ ንጉሥ ለአርጤክስስ ጻፉ"*።
ዕዝራ 4፥18 ሰላም! *"አሁንም "ወደ እኛ" עֲלֶ֑ינָא የላካችሁት ደብዳቤ በፊቴ ተተርጕሞ ተነበበ"*።
ልብ አድርግ "አርጤክስስ" የሚለው ቃላ ላይ መነሻ ቅጥያ ያለው "ለ" የሚለው መስተዋድድ ለንጉሡ ብቻ የተላከ ደብዳቤ ነው። ንጉሡ ግን በዐረማይክ "ና" נָא ብሎ በብዜት ተጠቅሟል፥ ግን ንጉሡ አንድም ሦስትም ሆኖ አይደለም፦
ዳንኤል 2፥25 *የዚያን ጊዜም አርዮክ ዳንኤልን ፈጥኖ ወደ ንጉሡ አስገባውና፦ "ከይሁዳ ምርኮኞች ያለውን ለንጉሡ ፍቺውን የሚያስታውቀውን ሰው አግኝቼአለሁ" አለው*።
ዳንኤል 2፥36 ሕልሙ ይህ ነው፥ *"አሁንም ፍቺውን በንጉሡ ፊት እንናገራለን" נֵאמַ֥ר *።
"አማር" אֲמַר በሚል ግስ ላይ "ኔ" נֵ የሚል "ባለቤት ተውላጠ-ስም አለ። አርዮክ ወደ ንጉሡ ያስገባው ዳንኤልን ብቻ ሆኖ ሳለ ዳንኤን በብዜት "እንናገራለን" ብሏል፥ ግን ዳንኤል አንድም ሦስትም ሆኖ አይደለም። ሙግቱን አሁንም እናጥብበውና "ይሄድልናል" የሚለው ከአንድ በላይ ላሉ ማንነቶች ነው ነው ብንል እንኳን አሁንም ሥላሴን በፍጹም አያሳይም። ዐውዱ ላይ መላእክት አሉ፥ ኢሳይያስ ሲናገር ከሱራፌልም አንዱ እየበረረ ወደ እርሱ መጥቶ፦ "እነሆ፥ ይህ ከንፈሮችህን ነክቶአል፤ በደልህም ከአንተ ተወገደ፥ ኃጢአትህም ተሰረየልህ" አለው፦
ኢሳይያስ 6፥2 *"ሱራፌልም ከእርሱ በላይ ቆመው ነበር"*።
ኢሳይያስ 6፥5-7 *"እኔም፦ ከንፈሮቼ የረከሱብኝ ሰው በመሆኔ፥ ከንፈሮቻቸውም በረከሱባቸው ሕዝብ መካከል በመቀመጤ ዓይኖቼ የሠራዊትን ጌታ ንጉሡን እግዚአብሔርን ስለ አዩ ጠፍቻለሁና ወዮልኝ! አልሁ*። ከሱራፌልም አንዱ እየበረረ ወደ እኔ መጣ፥ በእጁም ከመሠዊያው በጕጠት የወሰደው ፍም ነበረ። አፌንም ዳሰሰበትና፦ እነሆ፥ ይህ ከንፈሮችህን ነክቶአል፤ በደልህም ከአንተ ተወገደ፥ ኃጢአትህም ተሰረየልህ፡ አለኝ*።
እንደ ባይብሉ እግዚአብሔር የሰማይም ሠራዊት ሁሉ በቀኙና በግራው አሉ፥ ያዕቆብ ከእግዚአብሔር እና ከመልአኩ ጋር ስለተነጋገረ " ከእኛ ጋር ተነጋገረ" ብሏል፦
1ኛ ነገሥት 22፥19 *"እግዚአብሔር በዙፋኑ ተቀምጦ፥ የሰማይም ሠራዊት ሁሉ በቀኙና በግራው ቆመው አየሁ*።
ሆሴዕ 12፥4 ከመልአኩም ጋር ታግሎ አሸነፈ፤ አልቅሶም ለመነው። በቤቴልም አገኘው፥ *"በዚያም "ከ-እኛ" ጋር עִמָּֽנוּ ተነጋገረ"*።
አየክ "ኑ" נוּ የሚለው ተሳቢ ተውላጠ-ስም ከመላእክት ጋር እንዳገለገለ? በምንም ሒሳብ ሥላሴን አያመለከትም። በተረፈ አንዱ አምላክ አንድ ማንነት ኖሮት ለግነት እኛነት ሲጠቀም በውስጡ ሦስት አባላት አሉት ብሎ ሌሎችን ማንነቶችን በማንነቱ ላይ ማጋራት ሺርክ ነው። እርሱ አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ እኔም ከምታጋሩት ነገር ንጹሕ ነኝ፦
6፥19 *«እርሱ አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ እኔም ከምታጋሩት ነገር ንጹሕ ነኝ»* በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا هُوَ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ وَإِنَّنِى بَرِىٓءٌۭ مِّمَّا تُشْرِكُونَ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ከእኛ እንደ አንዱ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
14፥52 *ይህ ቁርኣን ለሰዎች ገላጭ ነው፡፡ ሊመከሩበት፣ በእርሱም ሊያስጠነቅቁበት፣ እርሱም አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት እና የአእምሮ ባለቤቶችም ሊገሰፁበት የተወረደ ነው*፡፡ هَـٰذَا بَلَاغٌ لِّلنَّاسِ وَلِيُنذَرُوا بِهِ وَلِيَعْلَمُوا أَنَّمَا هُوَ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ وَلِيَذَّكَّرَ أُولُو الْأَلْبَابِ
ቁርኣን ከወረደበት አንዱ ፈጣሪ አላህ አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት ነው፦
14፥52 *ይህ ቁርኣን ለሰዎች ገላጭ ነው፡፡ ሊመከሩበት፣ በእርሱም ሊያስጠነቅቁበት፣ እርሱም አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት እና የአእምሮ ባለቤቶችም ሊገሰፁበት የተወረደ ነው*፡፡ هَـٰذَا بَلَاغٌ لِّلنَّاسِ وَلِيُنذَرُوا بِهِ وَلِيَعْلَمُوا أَنَّمَا هُوَ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ وَلِيَذَّكَّرَ أُولُو الْأَلْبَابِ
ይህ የአንድ አምላክ እሳቤ በመለኮታዊ ቅሪት እንዲህ ተቀምጧል፦
ዘዳግም 6፥4 እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ *አምላካችን ያህዌህ አንድ ያህዌህ ነው*። שְׁמַע, יִשְׂרָאֵל: יְהוָה אֱלֹהֵינוּ, יְהוָה אֶחָד.
ያህዌህ አንድ ያህዌህ ሲሆን እርሱ ሌሎችን ማንነቶችን ጨምሮ፦ “ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ” ብሏል፦
ዘፍጥረት 3፥22 *ያህዌህ አምላክም አለ፦ *እነሆ አዳም መልካምንና ክፉን ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ*፤ וַיֹּאמֶר יְהוָה אֱלֹהִים, הֵן הָאָדָם הָיָה כְּאַחַד מִמֶּנּוּ, לָדַעַת, טוֹב וָרָע; וְעַתָּה פֶּן-
“እንደ አንዱ” እና “እኛ” ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን ነጥብ በነጥብ ጥርስና ምላሱን እየነቀስን እናየዋለን፦
ነጥብ አንድ
“እንደ አንዱ”
“ከ-አሐድ” כְּאַחַ֣ד ማለት “እንደ አንዱ”as one of” ማለት ነው፤ ያ ማለት በከፊል መመሳሰልን ያሳያል፦
1ኛ ሳሙኤል 17፥36 *እኔ ባሪያህ “አንበሳ እና ድብ” መታሁ፤ ይህም ያልተገረዘው ፍልስጥኤማዊ የሕያውን አምላክ ጭፍሮች ተገዳድሮአልና “ከእነርሱ እንደ አንዱ” ይሆናል*። גַּם אֶת-הָאֲרִי גַּם-הַדֹּב, הִכָּה עַבְדֶּךָ; וְהָיָה הַפְּלִשְׁתִּי הֶעָרֵל הַזֶּה, כְּאַחַד מֵהֶם, כִּי חֵרֵף, מַעַרְכֹת אֱלֹהִים חַיִּים.
“ከ-አሐድ ሜሄም” כְּאַחַד מֵהֶם ማለት “ከእነርሱ እንደ አንዱ”as one of them” ማለት ሲሆን ፍልስጥኤማዊ ጎልያድ በዳዊት በመገደል ደረጃ “እንደ አንበሳ እና ድብ” ይሆናል ማለት ነው እንጂ ጎልያድ አውሬ ይሆናል ማለት አይደለም፣ “እንደ” የሚለው ተውሳከ-ግስ የተወሰነን መመሳሰል ለማመልከት የሚገባ ነው፣ ልክ እንደዚሁ አደም መልካምና ክፉ በማወቅ እንደ እንደ እነርሱ ሆኗል፤ ለዛ ነው “ከ-አሐድ ሜንሁ” כְּאַחַ֣ד מִמֶּ֔נּוּ ማለትም “ከእኛ እንደ አንዱ”as one of us” የሚለው፤ ያህዌህ ታዲያ ማንን ጨምሮ ነው “እኛ” የሚለው?
ነጥብ ሁለት
“እኛ”
ያህዌህ “እኛ” የሚለው ማንን ጨምሮ ነው የሚለው ለመረዳት እዚሁ ዐውድ ላይ አዳም ከእኛዎቹ እንደ አንዱ የሚሆነው “መልካምንና ክፉን ለማወቅ” እንደሆነ ይሰመርበት፤ እዛው ዐውድ ላይ አዳም ቢበላ “እንደ አማልክትም መልካምንና ክፉን የሚያውቁ” እንደሆነ ተነግሯል፦
ዘፍጥረት 3፥5 ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ *“እንደ አማልክትም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ”* ያህዌህ ስለሚያውቅ ነው እንጂ። כִּי, יֹדֵעַ אֱלֹהִים, כִּי בְּיוֹם אֲכָלְכֶם מִמֶּנּוּ, וְנִפְקְחוּ עֵינֵיכֶם; וִהְיִיתֶם, כֵּאלֹהִים, יֹדְעֵי, טוֹב וָרָע.
የግዕዙ ዕትም፦
ዘፍጥረት 3፥5 *“ዘይቤ ከመ ኢትኩኑ አማልክተ ወኢታምሩ ሠናየ ወእኩየ”*
የኢንግሊሹ ዕትም፦
For God doth know that in the day ye eat thereof, then your eyes shall be opened, and *ye shall be as gods, knowing good and evil*.(KJV)
የግሪክ ሰፕቱአጀንት”LXX”፦
ዘፍጥረት 3፥5 ᾔδει γὰρ ὁ Θεός, ὅτι ᾗ ἂν ἡμέρᾳ φάγητε ἀπ᾿ αὐτοῦ, διανοιχθήσονται ὑμῶν οἱ ὀφθαλμοὶ καὶ ἔσεσθε ὡς *θεοί*, γινώσκοντες καλὸν καὶ πονηρόν.
የግዕዙ ዕትም ላይ “አማልክት” ብሎ እንዳስቀመጠው አስተውል፤ “ኤሎሂም” כֵּֽאלֹהִ֔ים ማለት “አማልክት” ማለት ነው፤ ይህ ቃል ለነጠላ ማንነት ወይንም ለብዙ ማንነት ይውላል፤ እዚህ አንቀጽ ላይ ግን ለብዙ መባሉን በግሪክ ሰፕቱጀንት ላይ “ቶኢ” θεοί ማለትም “አማልክት” ብሎ በብዙ ቁጥር አስቀምጦታል፤ ልብ አድርግ የቴኦ ነጠላ “ቴኦስ” Θεὸς ነው፤ “ቴኦስ” ብሎ በነጠላ አለማስቀመጡ ለብዙ ማንነቶች መሆኑን ያሳያል፤ በኢንግሊሹም ደግሞ በብዙ ቁጥር “gods” መባሉን አስተውል። በብሉይ ደግሞ ብዙ ቦታ አማልክት የተባሉት መላእክት ናቸው፦
መዝሙር 97፥7 *”አማልክትም” כֵּֽאלֹהִ֔ים ሁሉ ስገዱለት*።
መዝሙር 104፥4 *“አማልክትን” כֵּֽאלֹהִ֔ים መንፈስ የሚያደርግ፥*
መዝሙር 8፥5 *“ከአማልክትን” כֵּֽאלֹהִ֔ים እጅግ ጥቂት አሳነስኸው*፤
መዝሙር 103፥20 የቃሉንም ድምፅ የምትሰሙ *“አማልክቱ” כֵּֽאלֹהִ֔ים ሁሉ ያህዌህን ባርኩ*።
መዝሙር 138፥1 *”በአማልክት כֵּֽאלֹהִ֔ים ፊት እዘምርልሃለሁ*።
ስለዚህ አዳም ዛፉን ሲበላ መልካም እና ክፉውን በማወቅ እንደ መላእክት ከሆነ ያህዌህ ደግሞ መልካምና ክፉ ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ የሚለው እነዚህን አማልክት ታሳቢና ዋቢ ያደረገ ነው፦
ሆሴዕ 12፥4 *በጕልማስነቱም ጊዜ “ከአምላክ” ጋር ታገለ፤ “ከመልአኩም” ጋር ታግሎ አሸነፈ፤ አልቅሶም ለመነው። በቤቴልም አገኘው፥ በዚያም “ከእኛ” ጋር ተነጋገረ*።
ያዕቆብ የተነጋገረው ከመልአኩ ጋር እና ከያህዌህ ጋር ነው፤ ያህዌህ መልአኩን ጨምሮ “ከእኛ” እንዳለ አንባቢ ልብ ይለዋል። አይ ያህዌህ እኛ የሚለው ሥላሴን ያሳየል ከተባለ ዕውዱ ላይ ስለ ሥላሴ የሚያሳይ ሃይለ-ቃል ፈልቅቆ ማሳየት ይጠበቅባችኃል፤ ወይም ይህ አንቀጽ ስለ ሥላሴ ያወራል ብሎ የተናገረ ነብይ ወይም ሐዋርያ ጠቅሳችሁና አጣቅሳችሁ መሞገትና መሟገት ይጠበቅባችኃል።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
14፥52 *ይህ ቁርኣን ለሰዎች ገላጭ ነው፡፡ ሊመከሩበት፣ በእርሱም ሊያስጠነቅቁበት፣ እርሱም አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት እና የአእምሮ ባለቤቶችም ሊገሰፁበት የተወረደ ነው*፡፡ هَـٰذَا بَلَاغٌ لِّلنَّاسِ وَلِيُنذَرُوا بِهِ وَلِيَعْلَمُوا أَنَّمَا هُوَ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ وَلِيَذَّكَّرَ أُولُو الْأَلْبَابِ
ቁርኣን ከወረደበት አንዱ ፈጣሪ አላህ አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት ነው፦
14፥52 *ይህ ቁርኣን ለሰዎች ገላጭ ነው፡፡ ሊመከሩበት፣ በእርሱም ሊያስጠነቅቁበት፣ እርሱም አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት እና የአእምሮ ባለቤቶችም ሊገሰፁበት የተወረደ ነው*፡፡ هَـٰذَا بَلَاغٌ لِّلنَّاسِ وَلِيُنذَرُوا بِهِ وَلِيَعْلَمُوا أَنَّمَا هُوَ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ وَلِيَذَّكَّرَ أُولُو الْأَلْبَابِ
ይህ የአንድ አምላክ እሳቤ በመለኮታዊ ቅሪት እንዲህ ተቀምጧል፦
ዘዳግም 6፥4 እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ *አምላካችን ያህዌህ አንድ ያህዌህ ነው*። שְׁמַע, יִשְׂרָאֵל: יְהוָה אֱלֹהֵינוּ, יְהוָה אֶחָד.
ያህዌህ አንድ ያህዌህ ሲሆን እርሱ ሌሎችን ማንነቶችን ጨምሮ፦ “ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ” ብሏል፦
ዘፍጥረት 3፥22 *ያህዌህ አምላክም አለ፦ *እነሆ አዳም መልካምንና ክፉን ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ*፤ וַיֹּאמֶר יְהוָה אֱלֹהִים, הֵן הָאָדָם הָיָה כְּאַחַד מִמֶּנּוּ, לָדַעַת, טוֹב וָרָע; וְעַתָּה פֶּן-
“እንደ አንዱ” እና “እኛ” ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን ነጥብ በነጥብ ጥርስና ምላሱን እየነቀስን እናየዋለን፦
ነጥብ አንድ
“እንደ አንዱ”
“ከ-አሐድ” כְּאַחַ֣ד ማለት “እንደ አንዱ”as one of” ማለት ነው፤ ያ ማለት በከፊል መመሳሰልን ያሳያል፦
1ኛ ሳሙኤል 17፥36 *እኔ ባሪያህ “አንበሳ እና ድብ” መታሁ፤ ይህም ያልተገረዘው ፍልስጥኤማዊ የሕያውን አምላክ ጭፍሮች ተገዳድሮአልና “ከእነርሱ እንደ አንዱ” ይሆናል*። גַּם אֶת-הָאֲרִי גַּם-הַדֹּב, הִכָּה עַבְדֶּךָ; וְהָיָה הַפְּלִשְׁתִּי הֶעָרֵל הַזֶּה, כְּאַחַד מֵהֶם, כִּי חֵרֵף, מַעַרְכֹת אֱלֹהִים חַיִּים.
“ከ-አሐድ ሜሄም” כְּאַחַד מֵהֶם ማለት “ከእነርሱ እንደ አንዱ”as one of them” ማለት ሲሆን ፍልስጥኤማዊ ጎልያድ በዳዊት በመገደል ደረጃ “እንደ አንበሳ እና ድብ” ይሆናል ማለት ነው እንጂ ጎልያድ አውሬ ይሆናል ማለት አይደለም፣ “እንደ” የሚለው ተውሳከ-ግስ የተወሰነን መመሳሰል ለማመልከት የሚገባ ነው፣ ልክ እንደዚሁ አደም መልካምና ክፉ በማወቅ እንደ እንደ እነርሱ ሆኗል፤ ለዛ ነው “ከ-አሐድ ሜንሁ” כְּאַחַ֣ד מִמֶּ֔נּוּ ማለትም “ከእኛ እንደ አንዱ”as one of us” የሚለው፤ ያህዌህ ታዲያ ማንን ጨምሮ ነው “እኛ” የሚለው?
ነጥብ ሁለት
“እኛ”
ያህዌህ “እኛ” የሚለው ማንን ጨምሮ ነው የሚለው ለመረዳት እዚሁ ዐውድ ላይ አዳም ከእኛዎቹ እንደ አንዱ የሚሆነው “መልካምንና ክፉን ለማወቅ” እንደሆነ ይሰመርበት፤ እዛው ዐውድ ላይ አዳም ቢበላ “እንደ አማልክትም መልካምንና ክፉን የሚያውቁ” እንደሆነ ተነግሯል፦
ዘፍጥረት 3፥5 ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ *“እንደ አማልክትም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ”* ያህዌህ ስለሚያውቅ ነው እንጂ። כִּי, יֹדֵעַ אֱלֹהִים, כִּי בְּיוֹם אֲכָלְכֶם מִמֶּנּוּ, וְנִפְקְחוּ עֵינֵיכֶם; וִהְיִיתֶם, כֵּאלֹהִים, יֹדְעֵי, טוֹב וָרָע.
የግዕዙ ዕትም፦
ዘፍጥረት 3፥5 *“ዘይቤ ከመ ኢትኩኑ አማልክተ ወኢታምሩ ሠናየ ወእኩየ”*
የኢንግሊሹ ዕትም፦
For God doth know that in the day ye eat thereof, then your eyes shall be opened, and *ye shall be as gods, knowing good and evil*.(KJV)
የግሪክ ሰፕቱአጀንት”LXX”፦
ዘፍጥረት 3፥5 ᾔδει γὰρ ὁ Θεός, ὅτι ᾗ ἂν ἡμέρᾳ φάγητε ἀπ᾿ αὐτοῦ, διανοιχθήσονται ὑμῶν οἱ ὀφθαλμοὶ καὶ ἔσεσθε ὡς *θεοί*, γινώσκοντες καλὸν καὶ πονηρόν.
የግዕዙ ዕትም ላይ “አማልክት” ብሎ እንዳስቀመጠው አስተውል፤ “ኤሎሂም” כֵּֽאלֹהִ֔ים ማለት “አማልክት” ማለት ነው፤ ይህ ቃል ለነጠላ ማንነት ወይንም ለብዙ ማንነት ይውላል፤ እዚህ አንቀጽ ላይ ግን ለብዙ መባሉን በግሪክ ሰፕቱጀንት ላይ “ቶኢ” θεοί ማለትም “አማልክት” ብሎ በብዙ ቁጥር አስቀምጦታል፤ ልብ አድርግ የቴኦ ነጠላ “ቴኦስ” Θεὸς ነው፤ “ቴኦስ” ብሎ በነጠላ አለማስቀመጡ ለብዙ ማንነቶች መሆኑን ያሳያል፤ በኢንግሊሹም ደግሞ በብዙ ቁጥር “gods” መባሉን አስተውል። በብሉይ ደግሞ ብዙ ቦታ አማልክት የተባሉት መላእክት ናቸው፦
መዝሙር 97፥7 *”አማልክትም” כֵּֽאלֹהִ֔ים ሁሉ ስገዱለት*።
መዝሙር 104፥4 *“አማልክትን” כֵּֽאלֹהִ֔ים መንፈስ የሚያደርግ፥*
መዝሙር 8፥5 *“ከአማልክትን” כֵּֽאלֹהִ֔ים እጅግ ጥቂት አሳነስኸው*፤
መዝሙር 103፥20 የቃሉንም ድምፅ የምትሰሙ *“አማልክቱ” כֵּֽאלֹהִ֔ים ሁሉ ያህዌህን ባርኩ*።
መዝሙር 138፥1 *”በአማልክት כֵּֽאלֹהִ֔ים ፊት እዘምርልሃለሁ*።
ስለዚህ አዳም ዛፉን ሲበላ መልካም እና ክፉውን በማወቅ እንደ መላእክት ከሆነ ያህዌህ ደግሞ መልካምና ክፉ ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ የሚለው እነዚህን አማልክት ታሳቢና ዋቢ ያደረገ ነው፦
ሆሴዕ 12፥4 *በጕልማስነቱም ጊዜ “ከአምላክ” ጋር ታገለ፤ “ከመልአኩም” ጋር ታግሎ አሸነፈ፤ አልቅሶም ለመነው። በቤቴልም አገኘው፥ በዚያም “ከእኛ” ጋር ተነጋገረ*።
ያዕቆብ የተነጋገረው ከመልአኩ ጋር እና ከያህዌህ ጋር ነው፤ ያህዌህ መልአኩን ጨምሮ “ከእኛ” እንዳለ አንባቢ ልብ ይለዋል። አይ ያህዌህ እኛ የሚለው ሥላሴን ያሳየል ከተባለ ዕውዱ ላይ ስለ ሥላሴ የሚያሳይ ሃይለ-ቃል ፈልቅቆ ማሳየት ይጠበቅባችኃል፤ ወይም ይህ አንቀጽ ስለ ሥላሴ ያወራል ብሎ የተናገረ ነብይ ወይም ሐዋርያ ጠቅሳችሁና አጣቅሳችሁ መሞገትና መሟገት ይጠበቅባችኃል።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ይህ ያውቁ ኖሯል?
በዓለም ላይ 23 ሺ የክርስትና ዓይነት አለ። ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ፦
1.ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
2. ኦርቶዶክስ ቅባት
3. ኦርቶዶክስ ጸጋ
4. ኦርቶዶክስ ተሃድሶ
5. ካቶሊክ
6. ፕሮቴስታንት
7. የይሆዋ ምስክር
8. ኦንልይ ጂሰስ
9. አድቬንቲስት
10. ዴቪድያን
11. የእግዚአብሔር መንግሥት(የካሳ ኬርጋ)
12. ሞርሞን
13. ኒው ኤጅ ሙቭመንት
14. ቢብሊካል ዩኒታሪያን
15. ናዝራዊያን አሉ።
ለዛሬ ይህ በቂ ነው። ለበለጠ ትምህርት በዚህ ተከታተሉ፦ https://tttttt.me/Wahidcom
በዓለም ላይ 23 ሺ የክርስትና ዓይነት አለ። ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ፦
1.ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
2. ኦርቶዶክስ ቅባት
3. ኦርቶዶክስ ጸጋ
4. ኦርቶዶክስ ተሃድሶ
5. ካቶሊክ
6. ፕሮቴስታንት
7. የይሆዋ ምስክር
8. ኦንልይ ጂሰስ
9. አድቬንቲስት
10. ዴቪድያን
11. የእግዚአብሔር መንግሥት(የካሳ ኬርጋ)
12. ሞርሞን
13. ኒው ኤጅ ሙቭመንት
14. ቢብሊካል ዩኒታሪያን
15. ናዝራዊያን አሉ።
ለዛሬ ይህ በቂ ነው። ለበለጠ ትምህርት በዚህ ተከታተሉ፦ https://tttttt.me/Wahidcom
1_4929402749520445745.pdf
657.2 KB
የመጨረሻው ቀን
በወንድም ወሒድ ዑመር
በወንድም ወሒድ ዑመር
እንፍጠር ወይስ ልፍጠር?
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
38፥71 ጌታህ ለመላእክት *«እኔ ሰውን ከጭቃ እፈጥራለሁ»* ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ إِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي خَالِقٌ بَشَرًا مِّن طِينٍ
አምላካችን አላህ ለመላእክት የተናገረው፦ “እኔ በምድር ላይ ምትክን አድራጊ ነኝ፤ ሰውን ከጭቃ እፈጥራለሁ” የሚል ነው እንጂ “እንፍጠር” አላላቸውም፦
2፥30 ጌታህ ለመላእክት፡- *«እኔ በምድር ላይ ምትክን አድራጊ ነኝ»* ባለ ጊዜ አስታውስ፤ وَإِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي جَاعِلٌ فِي الْأَرْضِ خَلِيفَةً
38፥71 ጌታህ ለመላእክት *«እኔ ሰውን ከጭቃ እፈጥራለሁ»* ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ إِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي خَالِقٌ بَشَرًا مِّن طِينٍ
“እንፍጠር” የሚባለው መፍጠር ለሚችል ማንነትና ምንነት ብቻ ነው፤ በባይብልም ከሄድን ያህዌህ ለመላእክት ያለው፦ “ሰው ብቻውን መሆኑ መልካም አይደለምና የሚስማማውን ረዳት አበጅለታለው” የሚል ነው፦
1ኛ. ዕብራይስጡ፦
ዘፍጥረት 2፥18 וַיֹּאמֶר יְהוָה אֱלֹהִים, לֹא-טוֹב הֱיוֹת הָאָדָם לְבַדּוֹ; אֶעֱשֶׂה-לּוֹ עֵזֶר, כְּנֶגְדּוֹ.
2ኛ. ኢንግሊሹ፦
Genesis 2፥18 The LORD God said, “It is not good for the man to be alone. I will make a helper suitable for him.” NIV
3ኛ. አዲሱ መደበኛ ትርጉም፦
ዘፍጥረት 2፥18 ያህዌህ ኤሎሂም፦ “ሰው ብቻውን መሆኑ መልካም አይደለምና የሚስማማውን ረዳት *አበጅለታለው”* አለ።
4ኛ. 1879 አማርኛ እትም፦
ዘፍጥረት 2፥18 እግዚአብሔር አምላክም አለ፦ “ሰው ብቻውን መሆኑ መልካም አይደለም፤ የምትረዳውን፣ በአገቡ የምትሆን፣ የምትስማማውን *ልፍጠርለት*።
የዕብራይስጡ ላይ “ኤሴህ” אֶֽעֱשֶׂהּ ማለትም “ልፍጠር” አለ እንጂ “እንፍጠር” አላለም፤ እንግሊዘኞቹም፦ “I will make” ብለው አስቀምጠውታል። ታዲያ “እንፍጠር” ከየት መጣ? አዎ ግሪክ ሰፕቱአጀን”LXX” እና ግዕዙ ላይ “እንፍጠር” የሚል አለ፦
1ኛ. ግሪክ ሰፕቱአጀን፦
Καὶ εἶπε Κύριος ὁ Θεός· οὐ καλὸν εἶναι τὸν ἄνθρωπον μόνον· ποιήσωμεν αὐτῷ βοηθὸν κατ᾿ αὐτόν.
2ኛ. ግዕዙ፦
ወይቤ እግዚአብሔር ኢኮነ ሠናይ ለእጓለ እመሕያው ይንበር ባሕቲቱ *ንግበር* ሎቱ ቢጸ ዘይረድኦ።
3ኛ. አማርኛ 1954 እትም፦
ዘፍጥረት 2፥18 እግዚአብሔር አምላክም አለ፦ ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት *እንፍጠርለት*።
የግሪክ ሰፕቱአጀን ላይ “ፓኢሴሜን” ποιήσωμεν ማለት “እንፍጠር” ብሎ አስቀምጦታል፤ ግዕዙም፦ “ንግበር” ማለትም “እንፍጠር” ብሎ አስቀምጠውታል። ታዲያ “እንፍጠር” ያለውም ለማን ነው? ስንል ኩፋሌ ላይ ደግሞ ለፍጡራን እንዳለ ይናገራል፦
1ኛ. ግዕዙ፦
ኩፋሌ 4፥4 *ወይቤለነ እግዚአብሔር ለነ*፤ አኮ ሰናይ የሀሉ ብእሲ ባሕቲቱ፤ አላ *ንግበር* ሎቱ መርድአ ዘከማሁ፤ መወየደ *እግዚአብሔር አምላክነ* ሕድመተ ላዕሌሁ ወኖመ”
2ኛ. አማርኛው፦
ኩፋሌ 4፥4 *ፈጣሪያችን* እግዚአብሔር ለእኛ *እንዲህ አለን*፦ “ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት *”እንፍጠርለት”*።
“ፈጣሪያችን” የሚል ሃይለ-ቃል ይሰመርበት፤ እግዚአብሔር እንፍጠር ያለው ለፈጠራቸው መሆኑን ለማሳየት እዛው አንቀጽ ላይ፦ “እንዲህ አለን” ይላሉ፤ ያላቸውም፦ “እንፍጠርለት” ነው፤ እነዚህ ማንነቶች እነማን ናቸው? ብለን ስንሞግት “መላእክት ናቸው” ይሉናል፤ አንቀጹ ላይ መላእክት ስለመሆናቸው ምንም ሽታው እንኳን የለም። ነገር ግን ኩፋሌ 1፥25 ኩፋሌ 2፥1 ኩፋሌ 2፥4 ኩፋሌ 4፥1 ለሙሴ የፊቱ መልአክ እየተናገረ ነው በሚል መላእክት ናቸው እንበልና ሙግቱን እናጥበው፤ መላእክት ይፈጥራሉ እንዴ? እኔ “እንብላ” ብዬ ብል የሚበላ ማንነትን እያናገርኩኝ ነው፤ የማይበላ ከሆነ “ልብላ” ብዬ ነው የምለው እንጂ “እንብላ” አልለውም፤ የማይፈጥር ማንነት እንፍጠር ወይስ ልፍጠር? የቱ ነው ስሜት የሚሰጠው?
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
38፥71 ጌታህ ለመላእክት *«እኔ ሰውን ከጭቃ እፈጥራለሁ»* ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ إِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي خَالِقٌ بَشَرًا مِّن طِينٍ
አምላካችን አላህ ለመላእክት የተናገረው፦ “እኔ በምድር ላይ ምትክን አድራጊ ነኝ፤ ሰውን ከጭቃ እፈጥራለሁ” የሚል ነው እንጂ “እንፍጠር” አላላቸውም፦
2፥30 ጌታህ ለመላእክት፡- *«እኔ በምድር ላይ ምትክን አድራጊ ነኝ»* ባለ ጊዜ አስታውስ፤ وَإِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي جَاعِلٌ فِي الْأَرْضِ خَلِيفَةً
38፥71 ጌታህ ለመላእክት *«እኔ ሰውን ከጭቃ እፈጥራለሁ»* ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ إِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي خَالِقٌ بَشَرًا مِّن طِينٍ
“እንፍጠር” የሚባለው መፍጠር ለሚችል ማንነትና ምንነት ብቻ ነው፤ በባይብልም ከሄድን ያህዌህ ለመላእክት ያለው፦ “ሰው ብቻውን መሆኑ መልካም አይደለምና የሚስማማውን ረዳት አበጅለታለው” የሚል ነው፦
1ኛ. ዕብራይስጡ፦
ዘፍጥረት 2፥18 וַיֹּאמֶר יְהוָה אֱלֹהִים, לֹא-טוֹב הֱיוֹת הָאָדָם לְבַדּוֹ; אֶעֱשֶׂה-לּוֹ עֵזֶר, כְּנֶגְדּוֹ.
2ኛ. ኢንግሊሹ፦
Genesis 2፥18 The LORD God said, “It is not good for the man to be alone. I will make a helper suitable for him.” NIV
3ኛ. አዲሱ መደበኛ ትርጉም፦
ዘፍጥረት 2፥18 ያህዌህ ኤሎሂም፦ “ሰው ብቻውን መሆኑ መልካም አይደለምና የሚስማማውን ረዳት *አበጅለታለው”* አለ።
4ኛ. 1879 አማርኛ እትም፦
ዘፍጥረት 2፥18 እግዚአብሔር አምላክም አለ፦ “ሰው ብቻውን መሆኑ መልካም አይደለም፤ የምትረዳውን፣ በአገቡ የምትሆን፣ የምትስማማውን *ልፍጠርለት*።
የዕብራይስጡ ላይ “ኤሴህ” אֶֽעֱשֶׂהּ ማለትም “ልፍጠር” አለ እንጂ “እንፍጠር” አላለም፤ እንግሊዘኞቹም፦ “I will make” ብለው አስቀምጠውታል። ታዲያ “እንፍጠር” ከየት መጣ? አዎ ግሪክ ሰፕቱአጀን”LXX” እና ግዕዙ ላይ “እንፍጠር” የሚል አለ፦
1ኛ. ግሪክ ሰፕቱአጀን፦
Καὶ εἶπε Κύριος ὁ Θεός· οὐ καλὸν εἶναι τὸν ἄνθρωπον μόνον· ποιήσωμεν αὐτῷ βοηθὸν κατ᾿ αὐτόν.
2ኛ. ግዕዙ፦
ወይቤ እግዚአብሔር ኢኮነ ሠናይ ለእጓለ እመሕያው ይንበር ባሕቲቱ *ንግበር* ሎቱ ቢጸ ዘይረድኦ።
3ኛ. አማርኛ 1954 እትም፦
ዘፍጥረት 2፥18 እግዚአብሔር አምላክም አለ፦ ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት *እንፍጠርለት*።
የግሪክ ሰፕቱአጀን ላይ “ፓኢሴሜን” ποιήσωμεν ማለት “እንፍጠር” ብሎ አስቀምጦታል፤ ግዕዙም፦ “ንግበር” ማለትም “እንፍጠር” ብሎ አስቀምጠውታል። ታዲያ “እንፍጠር” ያለውም ለማን ነው? ስንል ኩፋሌ ላይ ደግሞ ለፍጡራን እንዳለ ይናገራል፦
1ኛ. ግዕዙ፦
ኩፋሌ 4፥4 *ወይቤለነ እግዚአብሔር ለነ*፤ አኮ ሰናይ የሀሉ ብእሲ ባሕቲቱ፤ አላ *ንግበር* ሎቱ መርድአ ዘከማሁ፤ መወየደ *እግዚአብሔር አምላክነ* ሕድመተ ላዕሌሁ ወኖመ”
2ኛ. አማርኛው፦
ኩፋሌ 4፥4 *ፈጣሪያችን* እግዚአብሔር ለእኛ *እንዲህ አለን*፦ “ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት *”እንፍጠርለት”*።
“ፈጣሪያችን” የሚል ሃይለ-ቃል ይሰመርበት፤ እግዚአብሔር እንፍጠር ያለው ለፈጠራቸው መሆኑን ለማሳየት እዛው አንቀጽ ላይ፦ “እንዲህ አለን” ይላሉ፤ ያላቸውም፦ “እንፍጠርለት” ነው፤ እነዚህ ማንነቶች እነማን ናቸው? ብለን ስንሞግት “መላእክት ናቸው” ይሉናል፤ አንቀጹ ላይ መላእክት ስለመሆናቸው ምንም ሽታው እንኳን የለም። ነገር ግን ኩፋሌ 1፥25 ኩፋሌ 2፥1 ኩፋሌ 2፥4 ኩፋሌ 4፥1 ለሙሴ የፊቱ መልአክ እየተናገረ ነው በሚል መላእክት ናቸው እንበልና ሙግቱን እናጥበው፤ መላእክት ይፈጥራሉ እንዴ? እኔ “እንብላ” ብዬ ብል የሚበላ ማንነትን እያናገርኩኝ ነው፤ የማይበላ ከሆነ “ልብላ” ብዬ ነው የምለው እንጂ “እንብላ” አልለውም፤ የማይፈጥር ማንነት እንፍጠር ወይስ ልፍጠር? የቱ ነው ስሜት የሚሰጠው?
የባሰው ደግሞ በክሌመንት ላይ፦ “እግዚአብሔር አብ ለወልድ እና ለመንፈስ ቅዱስ እንፍጠር” አላቸው ይለናል፦
1ኛ. ግዕዙ፦
ቀለሚንጦስ 1፥33 *ወይቤሎሙ እግዚአብሔር አብ ለወልድ ወለመንፈስ ቅዱስ ንዑ ንግበር ሰብእ በአርአያነ ወበአምሳሊነ*።
2ኛ. አማርኛው፦
ቀለሚንጦስ 1፥33 *እግዚአብሔር አብ ለወልድ እና ለመንፈስ ቅዱስ በአርአያችንና በአምሳላችን ሰውን እንፍጠር አላቸው*።
ታዲያ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ፍጡር ናቸውን? ምክንያቱም ኩፋሌ ላይ “ፈጣሪያችን” ብለዋልና። እሺ አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ “ፈጣሪ” ወይስ “ፈጣሪዎች” ? መልክአ ሥላሴ ላይ ሥላሴ “ፈጣሪዎች” ተብለዋል፦
መልክአ ሥላሴ ቁጥር 39
*”ሥሉስ ቅዱስ ሆይ! የአደምና የሔዋን “ፈጣሪዎቻቸው” እንደመሆናችሁ”*።
ሥላሴን “ፈጣሪዎች” ከተባሉ ሦስት ፈጣሪ መሆናቸው ነው። ይህንን የሥላሴ ውዝግብና ትርምስ የሚፈታው የዐለማቱ ጌታ አላህ ለመላእክት ምን ብሎ እንደነበር በሚናገርበት አንቀጽ ነው፦
38፥71 ጌታህ ለመላእክት *«እኔ ሰውን ከጭቃ እፈጥራለሁ»* ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ إِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي خَالِقٌ بَشَرًا مِّن طِينٍ
ቁርኣን ከወረደበት ግብና አላማ፣ ፋይዳና ሚና አንዱ ከእነርሱ ጋር ያለውን መለኮታዊ እውነት ለማረጋገጥ እና ቀጥፈው የጨመሩትን ሐሰት ሊያርም ነው፤ ከእነርሱ ጋር ያለውን እውነትን ስለሚያረጋግጥ “ሙሰዲቃን” مُصَدِّقًا ማለትም “አረጋጋጭ” ሲባል፤ የሰዎች ንግግር የገቡበትን በማረሙ ደግሞ “ሙሃይሚን” مُهَيْمِنًا ማለትም “አራሚ” correcter” ወይም “ተቆጣጣሪ”supervisor” የሚል ስም አለው፦
5፥48 *ወደ አንተም መጽሐፉን ከበፊቱ ያለውን መጽሐፍ አረጋጋጭ እና በእርሱ ላይ ተጠባባቂ ሲኾን በእውነት አወረድን*። وَأَنزَلْنَآ إِلَيْكَ ٱلْكِتَٰبَ بِٱلْحَقِّ مُصَدِّقًۭا لِّمَا بَيْنَ يَدَيْهِ مِنَ ٱلْكِتَٰبِ وَمُهَيْمِنًا عَلَيْهِ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
1ኛ. ግዕዙ፦
ቀለሚንጦስ 1፥33 *ወይቤሎሙ እግዚአብሔር አብ ለወልድ ወለመንፈስ ቅዱስ ንዑ ንግበር ሰብእ በአርአያነ ወበአምሳሊነ*።
2ኛ. አማርኛው፦
ቀለሚንጦስ 1፥33 *እግዚአብሔር አብ ለወልድ እና ለመንፈስ ቅዱስ በአርአያችንና በአምሳላችን ሰውን እንፍጠር አላቸው*።
ታዲያ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ፍጡር ናቸውን? ምክንያቱም ኩፋሌ ላይ “ፈጣሪያችን” ብለዋልና። እሺ አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ “ፈጣሪ” ወይስ “ፈጣሪዎች” ? መልክአ ሥላሴ ላይ ሥላሴ “ፈጣሪዎች” ተብለዋል፦
መልክአ ሥላሴ ቁጥር 39
*”ሥሉስ ቅዱስ ሆይ! የአደምና የሔዋን “ፈጣሪዎቻቸው” እንደመሆናችሁ”*።
ሥላሴን “ፈጣሪዎች” ከተባሉ ሦስት ፈጣሪ መሆናቸው ነው። ይህንን የሥላሴ ውዝግብና ትርምስ የሚፈታው የዐለማቱ ጌታ አላህ ለመላእክት ምን ብሎ እንደነበር በሚናገርበት አንቀጽ ነው፦
38፥71 ጌታህ ለመላእክት *«እኔ ሰውን ከጭቃ እፈጥራለሁ»* ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ إِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي خَالِقٌ بَشَرًا مِّن طِينٍ
ቁርኣን ከወረደበት ግብና አላማ፣ ፋይዳና ሚና አንዱ ከእነርሱ ጋር ያለውን መለኮታዊ እውነት ለማረጋገጥ እና ቀጥፈው የጨመሩትን ሐሰት ሊያርም ነው፤ ከእነርሱ ጋር ያለውን እውነትን ስለሚያረጋግጥ “ሙሰዲቃን” مُصَدِّقًا ማለትም “አረጋጋጭ” ሲባል፤ የሰዎች ንግግር የገቡበትን በማረሙ ደግሞ “ሙሃይሚን” مُهَيْمِنًا ማለትም “አራሚ” correcter” ወይም “ተቆጣጣሪ”supervisor” የሚል ስም አለው፦
5፥48 *ወደ አንተም መጽሐፉን ከበፊቱ ያለውን መጽሐፍ አረጋጋጭ እና በእርሱ ላይ ተጠባባቂ ሲኾን በእውነት አወረድን*። وَأَنزَلْنَآ إِلَيْكَ ٱلْكِتَٰبَ بِٱلْحَقِّ مُصَدِّقًۭا لِّمَا بَيْنَ يَدَيْهِ مِنَ ٱلْكِتَٰبِ وَمُهَيْمِنًا عَلَيْهِ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
የብረት ጥሩር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
34፥11 *"ሰፋፊዎችን "ጥሩሮች" ሥራ! በአሠራርዋም መጥን! መልካምንም ሥራ ሥሩ*፡፡ እኔ የምትሠሩትን ነገር ሁሉ ተመልካች ነኝና" አልነው፡፡ أَنِ اعْمَلْ سَابِغَاتٍ وَقَدِّرْ فِي السَّرْدِ ۖ وَاعْمَلُوا صَالِحًا ۖ إِنِّي بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ
የታሪክ ተመራማሪዎች ለታሪክ ምንጭ ሁለት መረጃዎች አሏቸው፥ አንደኛው ትውፊት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የሥነ-ቁፋሮ ጥናት ነው። የታሪክ ተመራማሪዎች ያለፈውን ክስተት ሲፈጸም በቦታው ስላልነበሩ ከትውፊት እና ከሥነ-ቁፋሮ ግኝት በስተቀር ሙሉ ዕውቀት የላቸውም፥ አንድ ያለፈ ክስተት እነርሱ አላገኙትም ማለት ክስተቱ አልተከሰተም ማለት አይደለም። የክርስትናው ዐቃቤ እምነት አንቶንይ ሮጀርስ፦ "በዳዊት ዘመን የብረት ጥሩር ስለሌለ በቁርኣን በዳዊት ጊዜ ስለ ብረት ጥሩር የተገለጸው ገለጻ ስህተት ነው" ይለናል፦
34፥11 *"ሰፋፊዎችን "ጥሩሮች" ሥራ! በአሠራርዋም መጥን! መልካምንም ሥራ ሥሩ*፡፡ እኔ የምትሠሩትን ነገር ሁሉ ተመልካች ነኝና" አልነው፡፡ أَنِ اعْمَلْ سَابِغَاتٍ وَقَدِّرْ فِي السَّرْدِ ۖ وَاعْمَلُوا صَالِحًا ۖ إِنِّي بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ
"ሣቢጋት" سَٰبِغَٰت የሚለው ቃል "አሥበገ" أَسْبَغَ ማለትም "አገራ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "የተገራ" ማለት ነው። አላህ ለዳውድ ሐዲድን ማግራቱን የሚያሳይ ነው፦
34፥10 ለዳውድም ከእኛ የኾነን ችሮታ በእርግጥ ሰጠነው፡፡ «ተራራዎች ሆይ! ከእርሱ ጋር ውዳሴን መላልሱ» አልን። በራሪዎችንም ገራንለት፡፡ *ብረትንም ለእርሱ አለዘብንለት"*፡፡ وَلَقَدْ آتَيْنَا دَاوُودَ مِنَّا فَضْلًا ۖ يَا جِبَالُ أَوِّبِي مَعَهُ وَالطَّيْرَ ۖ وَأَلَنَّا لَهُ الْحَدِيدَ
የታሪክ ተመራማሪዎች የብረት ጥሩር በሦስተኛ ክፍለ ዘመን አገኙ ማለት ከዚያ በፊት ላለመኖሩ ማስረጃ መሆን አይችልም፥ ይህ ሙግት ሥነ-አመክንዮን ታሳቢና ዋቢ ያላደረገ ስሑት ሙግት ነው። ለምሳሌ በዳዊት ዘመን የነበሩ ሰዎች ለእግዚአብሔርም ቤት አገልግሎት አሥር ሺህ “ዳሪክ” እንደሰጡ የዜና መዋዕል ጸሐፊ ይነግረናል፦
1ኛ ዜና 29፥7 ለ*"እግዚአብሔርም ቤት አገልግሎት *አምስት ሺህ መክሊት ወርቅና አሥር ሺህ “ዳሪክ”፥ አሥር ሺህም መክሊት ብር፥ አሥራ ስምንት ሺህም መክሊት ናስ፥ መቶ ሺህም መክሊት ብረት ሰጡ*።
ዳሪክ ደግሞ መገበያያነቱ የተጀመረው በ 521-486 ቅድመ-ልደት በፐርሺያን ንጉሥ በዳሪዮስ ዘመነ-መንግሥት እንደሆነ የታሪክ ተመራማሪዎች ያትታሉ። ታዲያ በዳዊትና በዳሪዮስ መካከል የ 400 ዓመት ልዩነት ካለ፥ ታሪክ ስላላገኘው ትርክቱ ትክክል አይደለም ብሎ በአራት ነጥብ መደምደም ይቻላልን?
"ጥሩር" በዕብራይስጥ "ተህራ" תַחְרָ֛א ወይም "ሲሪዩን" שִׁרְיוֹן ነው፥ "ጥሩር" ከዳዊት በፊት በሙሴ ዘመን እና በዳዊትም ጊዜ ነበር፦
ዘጸአት 28፥32 *ከላይም በመካከል አንገትጌ ይሁንበት እንዳይቀደድም እንደ "ጥሩር" תַחְרָ֛א የተሠራ ጥልፍ በአንገትጌው ዙሪያ ይሁንበት።
ዘጸአት 39፥23 በቀሚሱም መካከል አንገትጌ ነበረ፤ እንዳይቀደድም እንደ "ጥሩር" שִׁרְיוֹן תַחְרָ֛א የተሠራ ጥልፍ በአንገትጌው ዙሪያ ነበረ*።
1ኛ ሳሙኤል 17፥5 *በራሱም የናስ ቍር ደፍቶ ነበር፥ "ጥሩርም" שִׁרְיוֹן ለብሶ ነበር፤ የጥሩሩም ሚዛን አምስት ሺህ ሰቅል ናስ ነበረ"*።
1ኛ ሳሙኤል 17፥38 *"ሳኦልም ዳዊትን የገዛ ራሱን ልብስ አለበሰው፥ በራሱም ላይ የናስ ቍር ደፋለት፥ ጥሩርም አለበሰው"*።
የታሪክ ተመራማሪዎች የብረት ጥሩር በሦስተኛ ክፍለ ዘመን ስላገኙ ባይብል "ጥሩር ከዳዊት በፊት በሙሴ ዘመን እና በዳዊትም ጊዜ ነበር" የሚለው ገለጻ ስህተት ነው ብሎ ተብሎ መደምደም ይቻላል። ግን ቅሉና ጥቅሉ "አንድ ያለፈ ክስተት የታሪክ ተመራማሪዎች አላገኙትም ማለት ክስተቱ አልተከሰተም ማለት አይደለም" የሚል ነው፥ የቁርኣኑንን ትርክትም በዚህ ልክና መልክ ተረዱት።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
34፥11 *"ሰፋፊዎችን "ጥሩሮች" ሥራ! በአሠራርዋም መጥን! መልካምንም ሥራ ሥሩ*፡፡ እኔ የምትሠሩትን ነገር ሁሉ ተመልካች ነኝና" አልነው፡፡ أَنِ اعْمَلْ سَابِغَاتٍ وَقَدِّرْ فِي السَّرْدِ ۖ وَاعْمَلُوا صَالِحًا ۖ إِنِّي بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ
የታሪክ ተመራማሪዎች ለታሪክ ምንጭ ሁለት መረጃዎች አሏቸው፥ አንደኛው ትውፊት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የሥነ-ቁፋሮ ጥናት ነው። የታሪክ ተመራማሪዎች ያለፈውን ክስተት ሲፈጸም በቦታው ስላልነበሩ ከትውፊት እና ከሥነ-ቁፋሮ ግኝት በስተቀር ሙሉ ዕውቀት የላቸውም፥ አንድ ያለፈ ክስተት እነርሱ አላገኙትም ማለት ክስተቱ አልተከሰተም ማለት አይደለም። የክርስትናው ዐቃቤ እምነት አንቶንይ ሮጀርስ፦ "በዳዊት ዘመን የብረት ጥሩር ስለሌለ በቁርኣን በዳዊት ጊዜ ስለ ብረት ጥሩር የተገለጸው ገለጻ ስህተት ነው" ይለናል፦
34፥11 *"ሰፋፊዎችን "ጥሩሮች" ሥራ! በአሠራርዋም መጥን! መልካምንም ሥራ ሥሩ*፡፡ እኔ የምትሠሩትን ነገር ሁሉ ተመልካች ነኝና" አልነው፡፡ أَنِ اعْمَلْ سَابِغَاتٍ وَقَدِّرْ فِي السَّرْدِ ۖ وَاعْمَلُوا صَالِحًا ۖ إِنِّي بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ
"ሣቢጋት" سَٰبِغَٰت የሚለው ቃል "አሥበገ" أَسْبَغَ ማለትም "አገራ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "የተገራ" ማለት ነው። አላህ ለዳውድ ሐዲድን ማግራቱን የሚያሳይ ነው፦
34፥10 ለዳውድም ከእኛ የኾነን ችሮታ በእርግጥ ሰጠነው፡፡ «ተራራዎች ሆይ! ከእርሱ ጋር ውዳሴን መላልሱ» አልን። በራሪዎችንም ገራንለት፡፡ *ብረትንም ለእርሱ አለዘብንለት"*፡፡ وَلَقَدْ آتَيْنَا دَاوُودَ مِنَّا فَضْلًا ۖ يَا جِبَالُ أَوِّبِي مَعَهُ وَالطَّيْرَ ۖ وَأَلَنَّا لَهُ الْحَدِيدَ
የታሪክ ተመራማሪዎች የብረት ጥሩር በሦስተኛ ክፍለ ዘመን አገኙ ማለት ከዚያ በፊት ላለመኖሩ ማስረጃ መሆን አይችልም፥ ይህ ሙግት ሥነ-አመክንዮን ታሳቢና ዋቢ ያላደረገ ስሑት ሙግት ነው። ለምሳሌ በዳዊት ዘመን የነበሩ ሰዎች ለእግዚአብሔርም ቤት አገልግሎት አሥር ሺህ “ዳሪክ” እንደሰጡ የዜና መዋዕል ጸሐፊ ይነግረናል፦
1ኛ ዜና 29፥7 ለ*"እግዚአብሔርም ቤት አገልግሎት *አምስት ሺህ መክሊት ወርቅና አሥር ሺህ “ዳሪክ”፥ አሥር ሺህም መክሊት ብር፥ አሥራ ስምንት ሺህም መክሊት ናስ፥ መቶ ሺህም መክሊት ብረት ሰጡ*።
ዳሪክ ደግሞ መገበያያነቱ የተጀመረው በ 521-486 ቅድመ-ልደት በፐርሺያን ንጉሥ በዳሪዮስ ዘመነ-መንግሥት እንደሆነ የታሪክ ተመራማሪዎች ያትታሉ። ታዲያ በዳዊትና በዳሪዮስ መካከል የ 400 ዓመት ልዩነት ካለ፥ ታሪክ ስላላገኘው ትርክቱ ትክክል አይደለም ብሎ በአራት ነጥብ መደምደም ይቻላልን?
"ጥሩር" በዕብራይስጥ "ተህራ" תַחְרָ֛א ወይም "ሲሪዩን" שִׁרְיוֹן ነው፥ "ጥሩር" ከዳዊት በፊት በሙሴ ዘመን እና በዳዊትም ጊዜ ነበር፦
ዘጸአት 28፥32 *ከላይም በመካከል አንገትጌ ይሁንበት እንዳይቀደድም እንደ "ጥሩር" תַחְרָ֛א የተሠራ ጥልፍ በአንገትጌው ዙሪያ ይሁንበት።
ዘጸአት 39፥23 በቀሚሱም መካከል አንገትጌ ነበረ፤ እንዳይቀደድም እንደ "ጥሩር" שִׁרְיוֹן תַחְרָ֛א የተሠራ ጥልፍ በአንገትጌው ዙሪያ ነበረ*።
1ኛ ሳሙኤል 17፥5 *በራሱም የናስ ቍር ደፍቶ ነበር፥ "ጥሩርም" שִׁרְיוֹן ለብሶ ነበር፤ የጥሩሩም ሚዛን አምስት ሺህ ሰቅል ናስ ነበረ"*።
1ኛ ሳሙኤል 17፥38 *"ሳኦልም ዳዊትን የገዛ ራሱን ልብስ አለበሰው፥ በራሱም ላይ የናስ ቍር ደፋለት፥ ጥሩርም አለበሰው"*።
የታሪክ ተመራማሪዎች የብረት ጥሩር በሦስተኛ ክፍለ ዘመን ስላገኙ ባይብል "ጥሩር ከዳዊት በፊት በሙሴ ዘመን እና በዳዊትም ጊዜ ነበር" የሚለው ገለጻ ስህተት ነው ብሎ ተብሎ መደምደም ይቻላል። ግን ቅሉና ጥቅሉ "አንድ ያለፈ ክስተት የታሪክ ተመራማሪዎች አላገኙትም ማለት ክስተቱ አልተከሰተም ማለት አይደለም" የሚል ነው፥ የቁርኣኑንን ትርክትም በዚህ ልክና መልክ ተረዱት።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ርኅሩኅ እና አዛኝ ነቢይ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
9፥128 *"ከራሳችሁ የሆነ ችግራችሁ በእርሱ ላይ ጽኑ የሆነ፣ በእናንተ ላይ የሚጓጓ፣ በምእምናን ላይ ርኅሩኅ አዛኝ የኾነ መልክተኛ በእርግጥ መጣላችሁ"*፡፡ لَقَدْ جَاءَكُمْ رَسُولٌ مِّنْ أَنفُسِكُمْ عَزِيزٌ عَلَيْهِ مَا عَنِتُّمْ حَرِيصٌ عَلَيْكُم بِالْمُؤْمِنِينَ رَءُوفٌ رَّحِيمٌ
አምላካችን አላህ በእርግጥ ርኅሩኅ አዛኝ ነው፥ እርሱ ከአዛኞች ሁሉ ይበልጥ አዛኝ ነው፦
16፥47 ወይም ቀስ በቀስ በማጉደል ላይ የሚይዛቸው መኾኑን አይፈሩምን? *"ጌታችሁም በእርግጥ ርኅሩኅ አዛኝ ነው"*፡፡ أَوْ يَأْخُذَهُمْ عَلَىٰ تَخَوُّفٍ فَإِنَّ رَبَّكُمْ لَرَءُوفٌ رَّحِيمٌ
21፥83 አዩብንም ጌታውን «እኔ መከራ አገኘኝ፥ *"አንተም ከአዛኞች ሁሉ ይበልጥ አዛኝ ነህ»* ሲል በተጣራ ጊዜ አስታውስ፡፡ وَأَيُّوبَ إِذْ نَادَىٰ رَبَّهُ أَنِّي مَسَّنِيَ الضُّرُّ وَأَنتَ أَرْحَمُ الرَّاحِمِينَ
"ረሒም" رَّحِيم በነጠላ "አዛኝ" ማለት ሲሆን "ራሒሚን" رَّاحِمِين ደግሞ በብዜት "አዛኞች" ማለት ነው። ከአዛኞች መካከል አንዱ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ናቸው፥ እርሳቸው በምእምናን ላይ ርኅሩኅ አዛኝ የኾነ መልክተኛ ናቸው፦
9፥128 *"ከራሳችሁ የሆነ ችግራችሁ በእርሱ ላይ ጽኑ የሆነ፣ በእናንተ ላይ የሚጓጓ፣ በምእምናን ላይ ርኅሩኅ አዛኝ የኾነ መልክተኛ በእርግጥ መጣላችሁ"*፡፡ لَقَدْ جَاءَكُمْ رَسُولٌ مِّنْ أَنفُسِكُمْ عَزِيزٌ عَلَيْهِ مَا عَنِتُّمْ حَرِيصٌ عَلَيْكُم بِالْمُؤْمِنِينَ رَءُوفٌ رَّحِيمٌ
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 43, ሐዲስ 164
ሙሐመድ ኢብኑ ጁበይር ኢብኑ ሙጥዒም ከአባቱ ሰምቶ እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *“እኔ ሙሐመድ ነኝ፣ እኔ አሕመድ ነኝ፣ እኔ አላህ በእኔ ሰበብ ክህደትን የሚደመስስብኝ አል-ማሒ ነኝ፣ እኔ ያ ሰዎች ከእርሱ ኋላ ተከትለውት የሚቀሰቀሱበት አል-ሓሺር ነኝ፣ ከዚህ በኃላ ነብይ የለምና እኔ ዓቂብ(መጨረሻ) ነኝ። በእርግጥም አላህ ርኅሩኅ አዛኝ ብሎ የጠራው ነኝ"*። عَنْ مُحَمَّدِ بْنِ جُبَيْرِ بْنِ مُطْعِمٍ، عَنْ أَبِيهِ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " إِنَّ لِي أَسْمَاءً أَنَا مُحَمَّدٌ وَأَنَا أَحْمَدُ وَأَنَا الْمَاحِي الَّذِي يَمْحُو اللَّهُ بِيَ الْكُفْرَ وَأَنَا الْحَاشِرُ الَّذِي يُحْشَرُ النَّاسُ عَلَى قَدَمَىَّ وَأَنَا الْعَاقِبُ الَّذِي لَيْسَ بَعْدَهُ أَحَدٌ " . وَقَدْ سَمَّاهُ اللَّهُ رَءُوفًا رَحِيمًا
እኛ ክርስቲያኖችን፦ "ኢየሱስ ፍጡር ሆኖ ሳለ ለምን ታመልኩታላችሁ" ብለን ስንጠይቅ፥ እከክልኝ ልከክልህ በሚል ስሜት፦ "ጌታችሁም በእርግጥ ርኅሩኅ አዛኝ ነው፥ ያም ርኅሩኅ አዛኝ በምእምናን ላይ ርኅሩኅ አዛኝ የኾነ መልክተኛ ነው። ስለዚህ ነቢያችሁ ጌታችሁ ነው" ብለው አረፉት። ይህ ቁርኣንን አገላብጦ ካለማንበብና ካለመረዳት የሚመጣ የተውረገረገ፣ የተንሸዋረረ፣ የተሳከረ፣ የደፈረሰ መረዳት ነው። አምላካችን አላህ የሚመስለው ምንም ነገር የለም፥ እርሱ ሰሚ ተመልካች ነው፦
42፥11 የሚመስለው ምንም ነገር የለም፡፡ *"እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው"*፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِۦ شَىْءٌۭ ۖ وَهُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلْبَصِيرُ
ሰውም አላህ በምንም አይመስልም፥ ግን ሰውም ሰሚ ተመልካች ነው፦
76፥2 እኛ ሰውን በሕግ ግዳጅ የምንፈትነው ስንኾን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነው፡፡ *ሰሚ ተመልካችም አደረግነው*፡፡ إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن نُّطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَّبْتَلِيهِ فَجَعَلْنَاهُ سَمِيعًا بَصِيرًا
አላህ የሚመስለው ምንም ነገር ስለሌለ አላህ ሰሚ እና ተመልካች የተባለው ሰው ሰሚ እና ተመልካች በተባለበት ስሌትና ቀመር እንዳልሆነ እሙንና ቅቡል ነው። አምላካችን አላህ የሚመስለው ምንም ነገር የለም፥ እርሱ አመስጋኝ ታጋሽ ነው፦
64፥17 ለአላህ መልካም ብድርን ብታበድሩ ምንዳውን ለእናንተ ይደራርበዋል፥ ለእናንተም ይምራል። *"አላህም አመስጋኝ ታጋሽ ነው"*፡፡ إِن تُقْرِضُوا اللَّهَ قَرْضًا حَسَنًا يُضَاعِفْهُ لَكُمْ وَيَغْفِرْ لَكُمْ ۚ وَاللَّهُ شَكُورٌ حَلِيمٌ
ሰውም አላህ በምንም አይመስልም፥ ግን ሰውም ታጋሽና አመስጋኝ ተብሏል፦
42፥33 ቢሻ ነፋሱን የረጋ ያደርገዋል፡፡ በባሕሩም ጀርባ ላይ ረጊዎች ይኾናሉ፡፡ *"በዚህ ውሰጥ በጣም ታጋሽና አመስጋኝ ለኾነ ሁሉ በእርግጥ ምልክቶች አሉ"*፡፡ إِن يَشَأْ يُسْكِنِ الرِّيحَ فَيَظْلَلْنَ رَوَاكِدَ عَلَىٰ ظَهْرِهِ ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّكُلِّ صَبَّارٍ شَكُورٍ
አላህ የሚመስለው ምንም ነገር ስለሌለ አላህ አመስጋኝ እና ታጋሽ የተባለው ሰው አመስጋኝ እና ታጋሽ በተባለበት ስሌትና ቀመር እንዳልሆነ እሙንና ቅቡል ነው። አምላካችን አላህ የሚመስለው ምንም ነገር የለም፥ እርሱ ርኅሩኅ ታጋሽ ነው፦
2፥225 *"አላህም በጣም ርኅሩኅ ታጋሽ ነው"*፡፡ وَاللَّهُ غَفُورٌ حَلِيمٌ
ሰውም አላህ በምንም አይመስልም፥ ለምሳሌ ኢብራሂም ርኅሩኅ ታጋሽ ተብሏል፦
9፥114 *"ኢብራሂም በእርግጥ በጣም ርኅሩኅ ታጋሽ ነውና"*፡፡ إِنَّ إِبْرَاهِيمَ لَأَوَّاهٌ حَلِيمٌ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
9፥128 *"ከራሳችሁ የሆነ ችግራችሁ በእርሱ ላይ ጽኑ የሆነ፣ በእናንተ ላይ የሚጓጓ፣ በምእምናን ላይ ርኅሩኅ አዛኝ የኾነ መልክተኛ በእርግጥ መጣላችሁ"*፡፡ لَقَدْ جَاءَكُمْ رَسُولٌ مِّنْ أَنفُسِكُمْ عَزِيزٌ عَلَيْهِ مَا عَنِتُّمْ حَرِيصٌ عَلَيْكُم بِالْمُؤْمِنِينَ رَءُوفٌ رَّحِيمٌ
አምላካችን አላህ በእርግጥ ርኅሩኅ አዛኝ ነው፥ እርሱ ከአዛኞች ሁሉ ይበልጥ አዛኝ ነው፦
16፥47 ወይም ቀስ በቀስ በማጉደል ላይ የሚይዛቸው መኾኑን አይፈሩምን? *"ጌታችሁም በእርግጥ ርኅሩኅ አዛኝ ነው"*፡፡ أَوْ يَأْخُذَهُمْ عَلَىٰ تَخَوُّفٍ فَإِنَّ رَبَّكُمْ لَرَءُوفٌ رَّحِيمٌ
21፥83 አዩብንም ጌታውን «እኔ መከራ አገኘኝ፥ *"አንተም ከአዛኞች ሁሉ ይበልጥ አዛኝ ነህ»* ሲል በተጣራ ጊዜ አስታውስ፡፡ وَأَيُّوبَ إِذْ نَادَىٰ رَبَّهُ أَنِّي مَسَّنِيَ الضُّرُّ وَأَنتَ أَرْحَمُ الرَّاحِمِينَ
"ረሒም" رَّحِيم በነጠላ "አዛኝ" ማለት ሲሆን "ራሒሚን" رَّاحِمِين ደግሞ በብዜት "አዛኞች" ማለት ነው። ከአዛኞች መካከል አንዱ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ናቸው፥ እርሳቸው በምእምናን ላይ ርኅሩኅ አዛኝ የኾነ መልክተኛ ናቸው፦
9፥128 *"ከራሳችሁ የሆነ ችግራችሁ በእርሱ ላይ ጽኑ የሆነ፣ በእናንተ ላይ የሚጓጓ፣ በምእምናን ላይ ርኅሩኅ አዛኝ የኾነ መልክተኛ በእርግጥ መጣላችሁ"*፡፡ لَقَدْ جَاءَكُمْ رَسُولٌ مِّنْ أَنفُسِكُمْ عَزِيزٌ عَلَيْهِ مَا عَنِتُّمْ حَرِيصٌ عَلَيْكُم بِالْمُؤْمِنِينَ رَءُوفٌ رَّحِيمٌ
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 43, ሐዲስ 164
ሙሐመድ ኢብኑ ጁበይር ኢብኑ ሙጥዒም ከአባቱ ሰምቶ እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *“እኔ ሙሐመድ ነኝ፣ እኔ አሕመድ ነኝ፣ እኔ አላህ በእኔ ሰበብ ክህደትን የሚደመስስብኝ አል-ማሒ ነኝ፣ እኔ ያ ሰዎች ከእርሱ ኋላ ተከትለውት የሚቀሰቀሱበት አል-ሓሺር ነኝ፣ ከዚህ በኃላ ነብይ የለምና እኔ ዓቂብ(መጨረሻ) ነኝ። በእርግጥም አላህ ርኅሩኅ አዛኝ ብሎ የጠራው ነኝ"*። عَنْ مُحَمَّدِ بْنِ جُبَيْرِ بْنِ مُطْعِمٍ، عَنْ أَبِيهِ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " إِنَّ لِي أَسْمَاءً أَنَا مُحَمَّدٌ وَأَنَا أَحْمَدُ وَأَنَا الْمَاحِي الَّذِي يَمْحُو اللَّهُ بِيَ الْكُفْرَ وَأَنَا الْحَاشِرُ الَّذِي يُحْشَرُ النَّاسُ عَلَى قَدَمَىَّ وَأَنَا الْعَاقِبُ الَّذِي لَيْسَ بَعْدَهُ أَحَدٌ " . وَقَدْ سَمَّاهُ اللَّهُ رَءُوفًا رَحِيمًا
እኛ ክርስቲያኖችን፦ "ኢየሱስ ፍጡር ሆኖ ሳለ ለምን ታመልኩታላችሁ" ብለን ስንጠይቅ፥ እከክልኝ ልከክልህ በሚል ስሜት፦ "ጌታችሁም በእርግጥ ርኅሩኅ አዛኝ ነው፥ ያም ርኅሩኅ አዛኝ በምእምናን ላይ ርኅሩኅ አዛኝ የኾነ መልክተኛ ነው። ስለዚህ ነቢያችሁ ጌታችሁ ነው" ብለው አረፉት። ይህ ቁርኣንን አገላብጦ ካለማንበብና ካለመረዳት የሚመጣ የተውረገረገ፣ የተንሸዋረረ፣ የተሳከረ፣ የደፈረሰ መረዳት ነው። አምላካችን አላህ የሚመስለው ምንም ነገር የለም፥ እርሱ ሰሚ ተመልካች ነው፦
42፥11 የሚመስለው ምንም ነገር የለም፡፡ *"እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው"*፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِۦ شَىْءٌۭ ۖ وَهُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلْبَصِيرُ
ሰውም አላህ በምንም አይመስልም፥ ግን ሰውም ሰሚ ተመልካች ነው፦
76፥2 እኛ ሰውን በሕግ ግዳጅ የምንፈትነው ስንኾን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነው፡፡ *ሰሚ ተመልካችም አደረግነው*፡፡ إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن نُّطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَّبْتَلِيهِ فَجَعَلْنَاهُ سَمِيعًا بَصِيرًا
አላህ የሚመስለው ምንም ነገር ስለሌለ አላህ ሰሚ እና ተመልካች የተባለው ሰው ሰሚ እና ተመልካች በተባለበት ስሌትና ቀመር እንዳልሆነ እሙንና ቅቡል ነው። አምላካችን አላህ የሚመስለው ምንም ነገር የለም፥ እርሱ አመስጋኝ ታጋሽ ነው፦
64፥17 ለአላህ መልካም ብድርን ብታበድሩ ምንዳውን ለእናንተ ይደራርበዋል፥ ለእናንተም ይምራል። *"አላህም አመስጋኝ ታጋሽ ነው"*፡፡ إِن تُقْرِضُوا اللَّهَ قَرْضًا حَسَنًا يُضَاعِفْهُ لَكُمْ وَيَغْفِرْ لَكُمْ ۚ وَاللَّهُ شَكُورٌ حَلِيمٌ
ሰውም አላህ በምንም አይመስልም፥ ግን ሰውም ታጋሽና አመስጋኝ ተብሏል፦
42፥33 ቢሻ ነፋሱን የረጋ ያደርገዋል፡፡ በባሕሩም ጀርባ ላይ ረጊዎች ይኾናሉ፡፡ *"በዚህ ውሰጥ በጣም ታጋሽና አመስጋኝ ለኾነ ሁሉ በእርግጥ ምልክቶች አሉ"*፡፡ إِن يَشَأْ يُسْكِنِ الرِّيحَ فَيَظْلَلْنَ رَوَاكِدَ عَلَىٰ ظَهْرِهِ ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّكُلِّ صَبَّارٍ شَكُورٍ
አላህ የሚመስለው ምንም ነገር ስለሌለ አላህ አመስጋኝ እና ታጋሽ የተባለው ሰው አመስጋኝ እና ታጋሽ በተባለበት ስሌትና ቀመር እንዳልሆነ እሙንና ቅቡል ነው። አምላካችን አላህ የሚመስለው ምንም ነገር የለም፥ እርሱ ርኅሩኅ ታጋሽ ነው፦
2፥225 *"አላህም በጣም ርኅሩኅ ታጋሽ ነው"*፡፡ وَاللَّهُ غَفُورٌ حَلِيمٌ
ሰውም አላህ በምንም አይመስልም፥ ለምሳሌ ኢብራሂም ርኅሩኅ ታጋሽ ተብሏል፦
9፥114 *"ኢብራሂም በእርግጥ በጣም ርኅሩኅ ታጋሽ ነውና"*፡፡ إِنَّ إِبْرَاهِيمَ لَأَوَّاهٌ حَلِيمٌ
አላህ የሚመስለው ምንም ነገር ስለሌለ አላህ ርኅሩኅ እና ታጋሽ የተባለው ኢብራሂም ርኅሩኅ እና ታጋሽ በተባለበት ስሌትና ቀመር እንዳልሆነ እሙንና ቅቡል ነው። እስቲ ለናሙና ያክል ከባይብል በንጽጽር እንይ! እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው። ሰይጣን ፈታኝ ነው፦
ዘፍጥረት 22፥1 ከእነዚህም ነገሮች በኋላ *”እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው”*፥
ማቴዎስ 4፥3 *”ፈታኝም”* ቀርቦ፦ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው።
እግዚአብሔር ፈታኝ ሰይጣን ነውን? ማነው ፈታኝ? እግዚአብሔር ወይስ ሰይጣን? እግዚአብሔር አጥፊ ተብሏል። ሰይጣንም አጥፊ ተብሏል፦
ዘጸአት 12፥12 እኔም በዚያች ሌሊት በግብፅ አገር አልፋለሁ፥ *”በግብፅም አገር ከሰው እስከ እንስሳ ድረስ በኵርን ሁሉ እገድላለሁ፤ በግብፅም አማልክት ሁሉ ላይ እፈርድባቸዋለሁ፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ”*።
ዕብራውያን 11፥28 *”አጥፊው”* የበኵሮችን ልጆች እንዳይነካ ፋሲካንና ደምን መርጨትን በእምነት አደረገ።
ራእይ 9፥11 *”በእነርሱም ላይ ንጉሥ አላቸው እርሱም የጥልቅ መልአክ ነው፥ ስሙም በዕብራይስጥ አብዶን በግሪክም አጶልዮን ይባላል”*።
በዕብራይስጥ “አብዶን” ማለት እና በግሪክ “አጶልዮን” ማለት ትርጉሙ “አጥፊ” ማለት ነው። እግዚአብሔር የጥልቁ መልአክ ሰይጣን ነውን? ማነው አጥፊ? እግዚአብሔር ወይስ ሰይጣን? እንዲህ ማነጻጸር ይቻላል። "እረ ወሒድ ምን ነካህ? እግዚአብሔር ፈታኝና አጥፊ የተባለው ሰይጧን ፈታኝና አጥፊ በተባለበት ሒሳብ አይደለም" ካላችሁ እንግዲያውስ በሰፈሩት ቁና መሰፈር ይሉካል እንደዚህ ነው።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ዘፍጥረት 22፥1 ከእነዚህም ነገሮች በኋላ *”እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው”*፥
ማቴዎስ 4፥3 *”ፈታኝም”* ቀርቦ፦ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው።
እግዚአብሔር ፈታኝ ሰይጣን ነውን? ማነው ፈታኝ? እግዚአብሔር ወይስ ሰይጣን? እግዚአብሔር አጥፊ ተብሏል። ሰይጣንም አጥፊ ተብሏል፦
ዘጸአት 12፥12 እኔም በዚያች ሌሊት በግብፅ አገር አልፋለሁ፥ *”በግብፅም አገር ከሰው እስከ እንስሳ ድረስ በኵርን ሁሉ እገድላለሁ፤ በግብፅም አማልክት ሁሉ ላይ እፈርድባቸዋለሁ፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ”*።
ዕብራውያን 11፥28 *”አጥፊው”* የበኵሮችን ልጆች እንዳይነካ ፋሲካንና ደምን መርጨትን በእምነት አደረገ።
ራእይ 9፥11 *”በእነርሱም ላይ ንጉሥ አላቸው እርሱም የጥልቅ መልአክ ነው፥ ስሙም በዕብራይስጥ አብዶን በግሪክም አጶልዮን ይባላል”*።
በዕብራይስጥ “አብዶን” ማለት እና በግሪክ “አጶልዮን” ማለት ትርጉሙ “አጥፊ” ማለት ነው። እግዚአብሔር የጥልቁ መልአክ ሰይጣን ነውን? ማነው አጥፊ? እግዚአብሔር ወይስ ሰይጣን? እንዲህ ማነጻጸር ይቻላል። "እረ ወሒድ ምን ነካህ? እግዚአብሔር ፈታኝና አጥፊ የተባለው ሰይጧን ፈታኝና አጥፊ በተባለበት ሒሳብ አይደለም" ካላችሁ እንግዲያውስ በሰፈሩት ቁና መሰፈር ይሉካል እንደዚህ ነው።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ሦስቱ መላእክት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
29፥31 *መልእክተኞቻችንም ኢብራሂምን በብስራት በመጡት ጊዜ «እኛ የዚህችን ከተማ ሰዎች አጥፊዎች ነን፡፡ ሰዎቿ በዳዮች ነበሩና» አሉት*፡፡ وَلَمَّا جَاءَتْ رُسُلُنَا إِبْرَاهِيمَ بِالْبُشْرَىٰ قَالُوا إِنَّا مُهْلِكُو أَهْلِ هَـٰذِهِ الْقَرْيَةِ ۖ إِنَّ أَهْلَهَا كَانُوا ظَالِمِينَ
ኦሪት ዘፍጥረት ላይ አብርሃም ቤት ሦስት ሰዎች በእንግድነት እንደተስተናገዱ ይናገራል፤ ዐበይት ክርስቲያኖች፦ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ እና አንግሊካን እነዚህ ሦስት ሰዎች ሥላሴ ናቸው ይላሉ፤ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በ 220 ድህረ-ልደት”AD” ቱርቱሊያም ይህንን አንቀጽ ይዞ የሥላሴን ቶኦሎጅይ ቴኦሌጃይዝ ያደረገው፤ በአገራችንም በየወሩ በሰባተኛው ቀን የአብርሃሙ ሦላሴ እየተባለ ይዘከራል፤ እውን ይህ አንቀጽ ለሥላሴ ተስተምህሮት መደላለል ይሆናልን? እስቲ ጥንልልና ጥንፍፍ አርገን እናስተንትነው፦
ዘፍጥረት 18፥1-2 በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ *እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት*። ዓይኑንም አነሣና እነሆ፥ *ሦስት ሰዎች በፊቱ ቆመው አየ*፤
እዚህ ጥቅስ ላይ ስለ ሥላሴ ምንም ሽታው እንኳን የለም። እነዚህ ሦስት ሰዎች አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ ናቸው የሚል ዐውዱ ላይ ምንም አናገኝም። ይህንን አንቀጽ ለሥላሴ የተጠቀመ ነብይም ሆነ ሃዋርያ የለም፤ እነዚህ ሰዎች እነማን ናቸው ታዲያ? ለሚለው ጥያቄ መልስ ለዐውደ ንባቡ ቦታውን እንልቀቅ፦
ዘፍጥረት 18፥16 *ሰዎቹም ከዚያ ተነሥተው ወደ ሰዶም አቀኑ* አብርሃምም ሊሸኛቸው አብሮአቸው ሄደ።
ዘፍጥረት 18፥22 *ሰዎቹም ከዚያ ፊታቸውን አቀኑ፥ ወደ ሰዶምም ሄዱ* አብርሃም ግን በእግዚአብሔር ፊት ገና ቆሞ ነበር።
እነዚህ ሰዎች ከአብርሃም ቤት ወደ ሰዶም አቀኑ፣ ወደ ሰዶምም ሄዱ፤ ከዚያስ? በመሸ ጊዜ ወደ ሰዶም ገቡ፦
ዘፍጥረት 19፥1 *ሁለቱም መላእክት በመሸ ጊዜ ወደ ሰዶም ገቡ*፤
እግዚአብሔር ከአብርሃም ጋር ሲነጋገር የነበረው በሦስት ሰዎች ነው፤ ሁለቱ ሰዎች ሲሄዱ ግን “አብርሃም በእግዚአብሔር ፊት ገና ቆሞ ነበር” ይላል፤ እግዚአብሔር በአንዱ ሰው ሲነጋገር ሁለቱ ሰዎች ሎጥ ቤት ገብተዋል፦
ዘፍጥረት 19፥10 *ሁለቱም ሰዎች እጃቸውን ዘርግተው ሎጥን ወደ እነርሱ ዘንድ ወደ ቤት አገቡት መዝጊያውንም ዘጉት*።
ዘፍጥረት 19፥12 *ሁለቱም ሰዎች ሎጥን አሉት*።
ዘፍጥረት 19፥13 *እኛ ይህን ስፍራ እናጠፋለንና፥ ጩኸታቸው በእግዚአብሔር ፊት ትልቅ ሆኖአልና እናጠፋውም ዘንድ እግዚአብሔር ሰድዶናል*።
“ሁለቱ ሰዎች” የሚለው ሃይለ-ቃል ይሰመርበት፤ ምን ትፈልጋለህ? ከአብርሃም ቤት ወጥተው ወደ ሎጥ ቤት የገቡት ሰዎች በቁጥር ሁለት መሆናቸውን እና ሁለት መላእክት መሆናቸውን ተገልጻል፤ እግዚአብሔር ብዙ ጊዜ በአንድ ሰው ይናገራል፤ ይህም ሰው መልአክ ተብሏል፤ ለምሳሌ ያዕቆብ ሲታገለው የነበረው መልአክ ሰው ተብሏል፦
ዘፍጥረት 32፥28 አለውም፦ ከእንግዲህ ወዲህ ስምህ እስራኤል ይባል እንጂ ያዕቆብ አይባል፤ *ከእግዚአብሔር እና ከሰውም ጋር ታግለህ አሸንፈሃልና*።
ሆሴዕ 12፥3-4 በማኅፀን ውስጥ ወንድሙን በተረከዙ ያዘው፥ በጕልማስነቱም ጊዜ *ከአምላክ ጋር ታገለ፤ ከመልአኩም ጋር ታግሎ አሸነፈ*፤ አልቅሶም ለመነው። በቤቴልም አገኘው፥ በዚያም *ከእኛ ጋር ተነጋገረ*።
“ከእኛ ጋር ተነጋገረ” የሚለው ሃይለ-ቃል ይሰመርበት፤ እግዚአብሔር እዚህ አንቀጽ ላይ፦ “እኛ” የሚለው መልአኩን ጨምሮ እንደሆነ አንባቢ ልብ ይለዋል፤ ምነው ገብርኤል ሰው ተብሎ የለ እንዴ? መላእክት በሰው ቅርጽ ስለሚመጡ ሰው ይባላሉ፦
ዳንኤል 9፥21 ገናም በጸሎት ስናገር አስቀድሜ በራእይ አይቼው *የነበረው ሰው ገብርኤል* እነሆ እየበረረ መጣ፤ በማታም መሥዋዕት ጊዜ ዳሰሰኝ።
እግዚአብሔር ግን ሰው አይደለም፤ አይበላም አይጠጣምም፦
ሆሴዕ 11፥9 *እኔ አምላክ ነኝ እንጂ ሰው አይደለሁምና*፥
መዝሙር 50፥12 *ብራብም ለአንተ አልነግርህም፥ ዓለምና ሞላው የእኔ ነውና። የፍሪዳውን ሥጋ እበላለሁን? የፍየሉንስ ደም እጠጣለሁን?*
ፈጣሪ፦ እበላለሁን? እጠጣለሁን? ሲል በምጸታዊ አነጋገር አልበላም አልጠጣም እያለ ነው፤ አንዳንድ ቂሎች፦ “አብርሃም ቤት የገቡት ሰዎች ምግብ በልተዋል፤ መላእክት እንዴት ይበላሉ? ብለው ይጠይቃሉ፤ የቱ ይቀላል መጋቢ ፈጣሪ መብላቱ ወይስ ፍጡር የሆኑት መላእክት መብላታቸው? አዎ መላእክቱ በልተዋል ይለናል፦
ዘፍጥረት 18፥8 እርጎና ወተትም ያዘጋጀውንም ጥጃ አመጣ፥ በፊታቸውም አቀረበው እርሱም ከዛፉ በታች በፊታቸው ቆሞ ነበር፥ *እነርሱም በሉ*።
ዘፍጥረት 19፥3 እጅግም ዘበዘባቸው ወደ እርሱም አቀኑ፥ ወደ ቤቱም ገቡ ማዕድ አቀረበላቸው፥ ቂጣንም ጋገረ *እነርሱም በሉ*።
ሎጥ ቤት የበሉት መላእክት ሥላሴ ናቸው ብላችሁ እንዳታርፉት፤ የዕብራውያን ጸሐፊ፦ “አንዳንዶች በእንግድነት መላእክትን ተቀብለዋል” በማለት አብርሃምን እና ሎጥን ያስታውሰናል፦
ዕብራውያን 13፥2 *እንግዶችን መቀበል አትርሱ*፤ በዚህ አንዳንዶች *ሳያውቁ መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና*።
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
29፥31 *መልእክተኞቻችንም ኢብራሂምን በብስራት በመጡት ጊዜ «እኛ የዚህችን ከተማ ሰዎች አጥፊዎች ነን፡፡ ሰዎቿ በዳዮች ነበሩና» አሉት*፡፡ وَلَمَّا جَاءَتْ رُسُلُنَا إِبْرَاهِيمَ بِالْبُشْرَىٰ قَالُوا إِنَّا مُهْلِكُو أَهْلِ هَـٰذِهِ الْقَرْيَةِ ۖ إِنَّ أَهْلَهَا كَانُوا ظَالِمِينَ
ኦሪት ዘፍጥረት ላይ አብርሃም ቤት ሦስት ሰዎች በእንግድነት እንደተስተናገዱ ይናገራል፤ ዐበይት ክርስቲያኖች፦ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ እና አንግሊካን እነዚህ ሦስት ሰዎች ሥላሴ ናቸው ይላሉ፤ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በ 220 ድህረ-ልደት”AD” ቱርቱሊያም ይህንን አንቀጽ ይዞ የሥላሴን ቶኦሎጅይ ቴኦሌጃይዝ ያደረገው፤ በአገራችንም በየወሩ በሰባተኛው ቀን የአብርሃሙ ሦላሴ እየተባለ ይዘከራል፤ እውን ይህ አንቀጽ ለሥላሴ ተስተምህሮት መደላለል ይሆናልን? እስቲ ጥንልልና ጥንፍፍ አርገን እናስተንትነው፦
ዘፍጥረት 18፥1-2 በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ *እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት*። ዓይኑንም አነሣና እነሆ፥ *ሦስት ሰዎች በፊቱ ቆመው አየ*፤
እዚህ ጥቅስ ላይ ስለ ሥላሴ ምንም ሽታው እንኳን የለም። እነዚህ ሦስት ሰዎች አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ ናቸው የሚል ዐውዱ ላይ ምንም አናገኝም። ይህንን አንቀጽ ለሥላሴ የተጠቀመ ነብይም ሆነ ሃዋርያ የለም፤ እነዚህ ሰዎች እነማን ናቸው ታዲያ? ለሚለው ጥያቄ መልስ ለዐውደ ንባቡ ቦታውን እንልቀቅ፦
ዘፍጥረት 18፥16 *ሰዎቹም ከዚያ ተነሥተው ወደ ሰዶም አቀኑ* አብርሃምም ሊሸኛቸው አብሮአቸው ሄደ።
ዘፍጥረት 18፥22 *ሰዎቹም ከዚያ ፊታቸውን አቀኑ፥ ወደ ሰዶምም ሄዱ* አብርሃም ግን በእግዚአብሔር ፊት ገና ቆሞ ነበር።
እነዚህ ሰዎች ከአብርሃም ቤት ወደ ሰዶም አቀኑ፣ ወደ ሰዶምም ሄዱ፤ ከዚያስ? በመሸ ጊዜ ወደ ሰዶም ገቡ፦
ዘፍጥረት 19፥1 *ሁለቱም መላእክት በመሸ ጊዜ ወደ ሰዶም ገቡ*፤
እግዚአብሔር ከአብርሃም ጋር ሲነጋገር የነበረው በሦስት ሰዎች ነው፤ ሁለቱ ሰዎች ሲሄዱ ግን “አብርሃም በእግዚአብሔር ፊት ገና ቆሞ ነበር” ይላል፤ እግዚአብሔር በአንዱ ሰው ሲነጋገር ሁለቱ ሰዎች ሎጥ ቤት ገብተዋል፦
ዘፍጥረት 19፥10 *ሁለቱም ሰዎች እጃቸውን ዘርግተው ሎጥን ወደ እነርሱ ዘንድ ወደ ቤት አገቡት መዝጊያውንም ዘጉት*።
ዘፍጥረት 19፥12 *ሁለቱም ሰዎች ሎጥን አሉት*።
ዘፍጥረት 19፥13 *እኛ ይህን ስፍራ እናጠፋለንና፥ ጩኸታቸው በእግዚአብሔር ፊት ትልቅ ሆኖአልና እናጠፋውም ዘንድ እግዚአብሔር ሰድዶናል*።
“ሁለቱ ሰዎች” የሚለው ሃይለ-ቃል ይሰመርበት፤ ምን ትፈልጋለህ? ከአብርሃም ቤት ወጥተው ወደ ሎጥ ቤት የገቡት ሰዎች በቁጥር ሁለት መሆናቸውን እና ሁለት መላእክት መሆናቸውን ተገልጻል፤ እግዚአብሔር ብዙ ጊዜ በአንድ ሰው ይናገራል፤ ይህም ሰው መልአክ ተብሏል፤ ለምሳሌ ያዕቆብ ሲታገለው የነበረው መልአክ ሰው ተብሏል፦
ዘፍጥረት 32፥28 አለውም፦ ከእንግዲህ ወዲህ ስምህ እስራኤል ይባል እንጂ ያዕቆብ አይባል፤ *ከእግዚአብሔር እና ከሰውም ጋር ታግለህ አሸንፈሃልና*።
ሆሴዕ 12፥3-4 በማኅፀን ውስጥ ወንድሙን በተረከዙ ያዘው፥ በጕልማስነቱም ጊዜ *ከአምላክ ጋር ታገለ፤ ከመልአኩም ጋር ታግሎ አሸነፈ*፤ አልቅሶም ለመነው። በቤቴልም አገኘው፥ በዚያም *ከእኛ ጋር ተነጋገረ*።
“ከእኛ ጋር ተነጋገረ” የሚለው ሃይለ-ቃል ይሰመርበት፤ እግዚአብሔር እዚህ አንቀጽ ላይ፦ “እኛ” የሚለው መልአኩን ጨምሮ እንደሆነ አንባቢ ልብ ይለዋል፤ ምነው ገብርኤል ሰው ተብሎ የለ እንዴ? መላእክት በሰው ቅርጽ ስለሚመጡ ሰው ይባላሉ፦
ዳንኤል 9፥21 ገናም በጸሎት ስናገር አስቀድሜ በራእይ አይቼው *የነበረው ሰው ገብርኤል* እነሆ እየበረረ መጣ፤ በማታም መሥዋዕት ጊዜ ዳሰሰኝ።
እግዚአብሔር ግን ሰው አይደለም፤ አይበላም አይጠጣምም፦
ሆሴዕ 11፥9 *እኔ አምላክ ነኝ እንጂ ሰው አይደለሁምና*፥
መዝሙር 50፥12 *ብራብም ለአንተ አልነግርህም፥ ዓለምና ሞላው የእኔ ነውና። የፍሪዳውን ሥጋ እበላለሁን? የፍየሉንስ ደም እጠጣለሁን?*
ፈጣሪ፦ እበላለሁን? እጠጣለሁን? ሲል በምጸታዊ አነጋገር አልበላም አልጠጣም እያለ ነው፤ አንዳንድ ቂሎች፦ “አብርሃም ቤት የገቡት ሰዎች ምግብ በልተዋል፤ መላእክት እንዴት ይበላሉ? ብለው ይጠይቃሉ፤ የቱ ይቀላል መጋቢ ፈጣሪ መብላቱ ወይስ ፍጡር የሆኑት መላእክት መብላታቸው? አዎ መላእክቱ በልተዋል ይለናል፦
ዘፍጥረት 18፥8 እርጎና ወተትም ያዘጋጀውንም ጥጃ አመጣ፥ በፊታቸውም አቀረበው እርሱም ከዛፉ በታች በፊታቸው ቆሞ ነበር፥ *እነርሱም በሉ*።
ዘፍጥረት 19፥3 እጅግም ዘበዘባቸው ወደ እርሱም አቀኑ፥ ወደ ቤቱም ገቡ ማዕድ አቀረበላቸው፥ ቂጣንም ጋገረ *እነርሱም በሉ*።
ሎጥ ቤት የበሉት መላእክት ሥላሴ ናቸው ብላችሁ እንዳታርፉት፤ የዕብራውያን ጸሐፊ፦ “አንዳንዶች በእንግድነት መላእክትን ተቀብለዋል” በማለት አብርሃምን እና ሎጥን ያስታውሰናል፦
ዕብራውያን 13፥2 *እንግዶችን መቀበል አትርሱ*፤ በዚህ አንዳንዶች *ሳያውቁ መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና*።
ሎጥ ቤት የበሉት መላእክት ሥላሴ ናቸው ብላችሁ እንዳታርፉት፤ የዕብራውያን ጸሐፊ፦ “አንዳንዶች በእንግድነት መላእክትን ተቀብለዋል” በማለት አብርሃምን እና ሎጥን ያስታውሰናል፦
ዕብራውያን 13፥2 *እንግዶችን መቀበል አትርሱ*፤ በዚህ አንዳንዶች *ሳያውቁ መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና*።
ከሎጥ ሌላ በእንግድነት እግር አጥቦና ጋብዞ እንግዳ የተቀበለ አብርሃም ነው። ደግሞም ድርሳነ ሚካኤል አብርሃም ቤት ገብተው አብርሃምን ያበሰሩት መላእክት እንደሆኑ ይናገራል፦
ድርሳነ ሚካኤል ዘሚያዝያ ቁጥር 11
ግዕዙ፦
*ወካዕበ መጽኡ መላእክት ወበጽሑ ኀበ አብርሃም ወነገርዎ ከመ ይትወለድ ይስሐቅ*።
አማርኛው፦
*ዳግመኛ መላእክት ወደ አብርሃም ዘንድ መጥተው ይስሐቅን እንደሚወልድ ነገሩት*።
አምላካችን አላህ ወደ ኢብራሂም ቤት በብስራት የመጡት መልእክተኞቹ እንደሆኑና እነዚህም መላእክትም ወደ ሉጥ ቤት እንደገቡ ይናገራል፦
29፥31 *መልክተኞቻችንም ኢብራሂምን በብስራት በመጡት ጊዜ «እኛ የዚህችን ከተማ ሰዎች አጥፊዎች ነን፡፡ ሰዎቿ በዳዮች ነበሩና» አሉት*፡፡ وَلَمَّا جَاءَتْ رُسُلُنَا إِبْرَاهِيمَ بِالْبُشْرَىٰ قَالُوا إِنَّا مُهْلِكُو أَهْلِ هَـٰذِهِ الْقَرْيَةِ ۖ إِنَّ أَهْلَهَا كَانُوا ظَالِمِينَ
11፥77 *መልእክተኞቻችንም ሉጥን በመጡት ጊዜ በእነርሱ ምክንያት አዘነ፡፡ ልቡም በነሱ ተጨነቀ፡፡ «ይህ ብርቱ ቀን ነውም» አለ*፡፡ وَلَمَّا جَاءَتْ رُسُلُنَا لُوطًا سِيءَ بِهِمْ وَضَاقَ بِهِمْ ذَرْعًا وَقَالَ هَـٰذَا يَوْمٌ عَصِيبٌ
እነዚህ መላእክት የቁጥራቸው መጠን ቁርኣን ላይ በእርግጥ አልተገለጸም፤ እንዲሁ ቁርኣን እነዚህ መላእክት በሉ አይልም፤ ኢብራሂም የተጠበሰን የወይፈን ስጋ ሲያመጣላቸው እጆቻቸውም ወደ ምግቡ የማይደርሱ መኾነቸውን ባየ ጊዜ ሸሻቸው፤ ምግብ የማይበሉ መሆናቸውን ሲረዳ ከእነርሱም ፍርሃት ተሰማው፦
11፥69 *መልእክተኞቻችንም ኢብራሂምን በልጅ ብስራት በእርግጥ መጡት፡፡ ሰላም አሉት፡፡ ሰላም አላቸው፡፡ ጥቂትም ሳይቆይ ወዲያውኑ የተጠበሰን የወይፈን ስጋ አመጣ*፡፡ وَلَقَدْ جَاءَتْ رُسُلُنَا إِبْرَاهِيمَ بِالْبُشْرَىٰ قَالُوا سَلَامًا ۖ قَالَ سَلَامٌ ۖ فَمَا لَبِثَ أَن جَاءَ بِعِجْلٍ حَنِيذٍ
11፥70 *እጆቻቸውም ወደ እርሱ የማይደርሱ መኾነቸውን ባየ ጊዜ ሸሻቸው፡፡ ከእነርሱም ፍርሃት ተሰማው፡፡ «አትፍራ እኛ ወደ ሉጥ ሕዝቦች ተልከናልና» አሉት*፡፡ فَلَمَّا رَأَىٰ أَيْدِيَهُمْ لَا تَصِلُ إِلَيْهِ نَكِرَهُمْ وَأَوْجَسَ مِنْهُمْ خِيفَةً ۚ قَالُوا لَا تَخَفْ إِنَّا أُرْسِلْنَا إِلَىٰ قَوْمِ لُوطٍ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ዕብራውያን 13፥2 *እንግዶችን መቀበል አትርሱ*፤ በዚህ አንዳንዶች *ሳያውቁ መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና*።
ከሎጥ ሌላ በእንግድነት እግር አጥቦና ጋብዞ እንግዳ የተቀበለ አብርሃም ነው። ደግሞም ድርሳነ ሚካኤል አብርሃም ቤት ገብተው አብርሃምን ያበሰሩት መላእክት እንደሆኑ ይናገራል፦
ድርሳነ ሚካኤል ዘሚያዝያ ቁጥር 11
ግዕዙ፦
*ወካዕበ መጽኡ መላእክት ወበጽሑ ኀበ አብርሃም ወነገርዎ ከመ ይትወለድ ይስሐቅ*።
አማርኛው፦
*ዳግመኛ መላእክት ወደ አብርሃም ዘንድ መጥተው ይስሐቅን እንደሚወልድ ነገሩት*።
አምላካችን አላህ ወደ ኢብራሂም ቤት በብስራት የመጡት መልእክተኞቹ እንደሆኑና እነዚህም መላእክትም ወደ ሉጥ ቤት እንደገቡ ይናገራል፦
29፥31 *መልክተኞቻችንም ኢብራሂምን በብስራት በመጡት ጊዜ «እኛ የዚህችን ከተማ ሰዎች አጥፊዎች ነን፡፡ ሰዎቿ በዳዮች ነበሩና» አሉት*፡፡ وَلَمَّا جَاءَتْ رُسُلُنَا إِبْرَاهِيمَ بِالْبُشْرَىٰ قَالُوا إِنَّا مُهْلِكُو أَهْلِ هَـٰذِهِ الْقَرْيَةِ ۖ إِنَّ أَهْلَهَا كَانُوا ظَالِمِينَ
11፥77 *መልእክተኞቻችንም ሉጥን በመጡት ጊዜ በእነርሱ ምክንያት አዘነ፡፡ ልቡም በነሱ ተጨነቀ፡፡ «ይህ ብርቱ ቀን ነውም» አለ*፡፡ وَلَمَّا جَاءَتْ رُسُلُنَا لُوطًا سِيءَ بِهِمْ وَضَاقَ بِهِمْ ذَرْعًا وَقَالَ هَـٰذَا يَوْمٌ عَصِيبٌ
እነዚህ መላእክት የቁጥራቸው መጠን ቁርኣን ላይ በእርግጥ አልተገለጸም፤ እንዲሁ ቁርኣን እነዚህ መላእክት በሉ አይልም፤ ኢብራሂም የተጠበሰን የወይፈን ስጋ ሲያመጣላቸው እጆቻቸውም ወደ ምግቡ የማይደርሱ መኾነቸውን ባየ ጊዜ ሸሻቸው፤ ምግብ የማይበሉ መሆናቸውን ሲረዳ ከእነርሱም ፍርሃት ተሰማው፦
11፥69 *መልእክተኞቻችንም ኢብራሂምን በልጅ ብስራት በእርግጥ መጡት፡፡ ሰላም አሉት፡፡ ሰላም አላቸው፡፡ ጥቂትም ሳይቆይ ወዲያውኑ የተጠበሰን የወይፈን ስጋ አመጣ*፡፡ وَلَقَدْ جَاءَتْ رُسُلُنَا إِبْرَاهِيمَ بِالْبُشْرَىٰ قَالُوا سَلَامًا ۖ قَالَ سَلَامٌ ۖ فَمَا لَبِثَ أَن جَاءَ بِعِجْلٍ حَنِيذٍ
11፥70 *እጆቻቸውም ወደ እርሱ የማይደርሱ መኾነቸውን ባየ ጊዜ ሸሻቸው፡፡ ከእነርሱም ፍርሃት ተሰማው፡፡ «አትፍራ እኛ ወደ ሉጥ ሕዝቦች ተልከናልና» አሉት*፡፡ فَلَمَّا رَأَىٰ أَيْدِيَهُمْ لَا تَصِلُ إِلَيْهِ نَكِرَهُمْ وَأَوْجَسَ مِنْهُمْ خِيفَةً ۚ قَالُوا لَا تَخَفْ إِنَّا أُرْسِلْنَا إِلَىٰ قَوْمِ لُوطٍ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
እንፍጠር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
6፥102 *"ይህ ጌታችሁ አላህ ነው፥ ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፡፡ ነገርን ሁሉ ፈጣሪ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ተጠባባቂ ነው"*፡፡ ذَٰلِكُمُ اللَّهُ رَبُّكُمْ ۖ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ فَاعْبُدُوهُ ۚ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ
ከአንድ አይሁዳዊ ምሁር ጋር እየተጨዋወትን ቀበል አርጌ፦ "ኤሎሂም እነማንን ነው እንፍጠር ያለው? ብዬ ጠየኩት፥ እርሱ፦ "በዚህ አንቀጽ ላይ በአይሁድ ጥንታዊ ምሁራን እና ዘመናዊ ምሁራን ዘንድ የተለያየ መልስ ተሰቶበታል" አለኝ። ከተሰጡት መልሶች መካከል፦
1ኛ. ኤሎሂም ከመላእክት ጋር እየተነጋገረ ነው፣
2ኛ. ከምድር ጋር እየተነጋገረ ነው፣
3ኛ. እራሱ ለግነት የብዜት ግስ እየተጠቀመ ነው፣
4ኛ. እራሱ ከራሱ ባሕርያት ጋር በዜቢያዊ አነጋገር እየተናገረ ነው" የሚል ነው፦
ዘፍጥረት 1፥26 ኤሎሂምም አለ፦ *"ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር"*።
አራተኛው ሰምቼ የማላውቀው ስለሆነ ትኩረቴ ሳበው። አንዱ አምላክ ብቻውን ሁሉን ነገር ፈጥሯል፥ ሰውንም የፈጠረ አንድ አምላክ ብቻ ነው፦
ሚልክያስ 2፥10 ለሁላችን አንድ አባት ያለን አይደለምን? *"አንድ አምላክስ የፈጠረን አይደለምን?"*
አንዱ አምላክ ያህዌህ ኤሎሂም ሰውን ከምድር አፈር በእጆቹ ፈጠረው፦
ዘፍጥረት 2፥7 ያህዌህ ኤሎሂም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው"*።
ኢዮብ 33፥6 *"እኔ ደግሞ ከጭቃ የተፈጠርሁ ነኝ"*።
መዝሙር 119፥73 *”እጆችህ ሠሩኝ አበጃጁኝም”*።
ኤሎሂም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፥ ኤሎሂም እንፍጠር ያለው መፍጠር ለሚችሉ ለእጆቹ ነው። ዳዊት፦ "እጆችህ ሠሩኝ አበጃጁኝም" ሲል ሰውን ያበጃጁት እጆቹ ከሆኑ፥ ኤሎሂም እጆቹ የራሱ ባሕርያት እንጂ ከኤሎሂም ውጪ ያሉ አካላት አይደለም። ታዲያ አንድ ማንነት ከራሱ ባሕርያት ጋር እንዴት ይነጋገራል? ከተባለ ዳዊት ለራሱ ነፍስ እና አጥንቶች፦ "ነፍሴ ሆይ፥ ያህዌህን ባርኪ፥ አጥንቶቼም ሁሉ የተቀደሰ ስሙን ባርኩ" ብሏል፦
መዝሙር 103፥1 *"ነፍሴ ሆይ፥ ያህዌህን ባርኪ፥ አጥንቶቼም ሁሉ፥ የተቀደሰ ስሙን"*።
ዳዊት በሁለተኛ መደብ በትእዛዛዊ ግስ የራሱን ነፍስ እና አጥንቶች "ባርኩ" ካለ፥ የራሱን ነፍስ ነፍሴ ሆይ! ባርኪ፣ አመስግኚ፣ ታመኚ፣ አትርሺ፣ ተመለሺ ካለ ኤሎሂም ሰውን የሚሠሩትንና የሚያበጁትን የራሱን እጆች "እንፍጠር" ቢል ምን ይደንቃል? ፈጣሪ ብቻውን ሰማያትን እና ምድርን እንደፈጠረ እሙን እና ቅቡል ነው፦
ኢሳይያስ 44፥24 *"ሁሉን የፈጠርሁ፥ ሰማያትን ለብቻዬ የዘረጋሁ ምድርንም ያጸናሁ ያህዌህ እኔ ነኝ ከእኔ ጋር ማን ነበረ”*?
ከእኔ ጋር "ምን" ነበረ? ሳይሆን "ከእኔ ጋር "ማን" ነበረ? ነው ያለው። ከዚህ ከአንድ እኔነት ጋር አብረው የፈጠሩ ማንነቶች እንደሌሉ ቁልጭ እና ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ይህ ሆኖ ሳለ ሰማያት እና ምድርን የፈጠሩ አሉ፥ እነርሱም እጁ፣ ቀኙ፣ ጣቶቹ ወዘተ ናቸው፦
ኢሳይያስ 48:13 *”እጄም ምድርን መሥርታለች ቀኜም ሰማያትን ዘርግታለች”*።
መዝሙር 8፥3 *”የጣቶችህን ሥራ” ሰማዮችን ባየሁ ጊዜ"*።
እነዚህን ባሕርያት ሸንሽነን ማንነት ሰጥተን ከሦስቱ ሥላሴ በላይ ስንት አካላት ልናረጋቸው ነው? ያህዌህ በጥበቡ፣ በማስተዋሉ፣ በኃይሉ ሰማያትን እና ምድርን ፈጥሯል፦
ምሳሌ 3፥19 *"ያህዌህ በጥበብ ምድርን መሠረተ፥ በማስተዋልም ሰማያትን አጸና”*።
ኤርምያስ 10፥12 *"ምድርን ”በኃይሉ የፈጠረ፥ ዓለሙን በጥበቡ የመሠረተ ሰማያትንም በማስተዋሉ የዘረጋ” እርሱ ነው"*።
ጥበቡ፣ ማስተዋሉ፣ ኃይሉ የራሱ ባሕርያት እንጂ የሚያማክሩት አካላት በፍጹም አይደሉም። እርሱ ራሱ እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንጂ ከራሱ ውጪ የሆኑ አካላትን እንፍጠር እያለ እየተመካከረ የሚሠራ በፍጹም አይደለም፦
ኤፌሶን 1፥11 *"እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ"*።
ከላይ ያለው አራተኛው እይታ ከሥነ-አመክንዮ አንጻር ድንቅ እይታ ነው። በቁርኣን ከሄድን ነገርን ሁሉ የፈጠረ ፈጣሪ ጌታችን አላህ ነው፥ ነገርን ሁሉ ብቻውን ፈጥሯል። ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፥ እርሱን ብቻ በብቸኝነት እናመልካለን፦
6፥102 *"ይህ ጌታችሁ አላህ ነው፥ ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፡፡ ነገርን ሁሉ ፈጣሪ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ተጠባባቂ ነው"*፡፡ ذَٰلِكُمُ اللَّهُ رَبُّكُمْ ۖ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ فَاعْبُدُوهُ ۚ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
6፥102 *"ይህ ጌታችሁ አላህ ነው፥ ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፡፡ ነገርን ሁሉ ፈጣሪ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ተጠባባቂ ነው"*፡፡ ذَٰلِكُمُ اللَّهُ رَبُّكُمْ ۖ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ فَاعْبُدُوهُ ۚ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ
ከአንድ አይሁዳዊ ምሁር ጋር እየተጨዋወትን ቀበል አርጌ፦ "ኤሎሂም እነማንን ነው እንፍጠር ያለው? ብዬ ጠየኩት፥ እርሱ፦ "በዚህ አንቀጽ ላይ በአይሁድ ጥንታዊ ምሁራን እና ዘመናዊ ምሁራን ዘንድ የተለያየ መልስ ተሰቶበታል" አለኝ። ከተሰጡት መልሶች መካከል፦
1ኛ. ኤሎሂም ከመላእክት ጋር እየተነጋገረ ነው፣
2ኛ. ከምድር ጋር እየተነጋገረ ነው፣
3ኛ. እራሱ ለግነት የብዜት ግስ እየተጠቀመ ነው፣
4ኛ. እራሱ ከራሱ ባሕርያት ጋር በዜቢያዊ አነጋገር እየተናገረ ነው" የሚል ነው፦
ዘፍጥረት 1፥26 ኤሎሂምም አለ፦ *"ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር"*።
አራተኛው ሰምቼ የማላውቀው ስለሆነ ትኩረቴ ሳበው። አንዱ አምላክ ብቻውን ሁሉን ነገር ፈጥሯል፥ ሰውንም የፈጠረ አንድ አምላክ ብቻ ነው፦
ሚልክያስ 2፥10 ለሁላችን አንድ አባት ያለን አይደለምን? *"አንድ አምላክስ የፈጠረን አይደለምን?"*
አንዱ አምላክ ያህዌህ ኤሎሂም ሰውን ከምድር አፈር በእጆቹ ፈጠረው፦
ዘፍጥረት 2፥7 ያህዌህ ኤሎሂም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው"*።
ኢዮብ 33፥6 *"እኔ ደግሞ ከጭቃ የተፈጠርሁ ነኝ"*።
መዝሙር 119፥73 *”እጆችህ ሠሩኝ አበጃጁኝም”*።
ኤሎሂም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፥ ኤሎሂም እንፍጠር ያለው መፍጠር ለሚችሉ ለእጆቹ ነው። ዳዊት፦ "እጆችህ ሠሩኝ አበጃጁኝም" ሲል ሰውን ያበጃጁት እጆቹ ከሆኑ፥ ኤሎሂም እጆቹ የራሱ ባሕርያት እንጂ ከኤሎሂም ውጪ ያሉ አካላት አይደለም። ታዲያ አንድ ማንነት ከራሱ ባሕርያት ጋር እንዴት ይነጋገራል? ከተባለ ዳዊት ለራሱ ነፍስ እና አጥንቶች፦ "ነፍሴ ሆይ፥ ያህዌህን ባርኪ፥ አጥንቶቼም ሁሉ የተቀደሰ ስሙን ባርኩ" ብሏል፦
መዝሙር 103፥1 *"ነፍሴ ሆይ፥ ያህዌህን ባርኪ፥ አጥንቶቼም ሁሉ፥ የተቀደሰ ስሙን"*።
ዳዊት በሁለተኛ መደብ በትእዛዛዊ ግስ የራሱን ነፍስ እና አጥንቶች "ባርኩ" ካለ፥ የራሱን ነፍስ ነፍሴ ሆይ! ባርኪ፣ አመስግኚ፣ ታመኚ፣ አትርሺ፣ ተመለሺ ካለ ኤሎሂም ሰውን የሚሠሩትንና የሚያበጁትን የራሱን እጆች "እንፍጠር" ቢል ምን ይደንቃል? ፈጣሪ ብቻውን ሰማያትን እና ምድርን እንደፈጠረ እሙን እና ቅቡል ነው፦
ኢሳይያስ 44፥24 *"ሁሉን የፈጠርሁ፥ ሰማያትን ለብቻዬ የዘረጋሁ ምድርንም ያጸናሁ ያህዌህ እኔ ነኝ ከእኔ ጋር ማን ነበረ”*?
ከእኔ ጋር "ምን" ነበረ? ሳይሆን "ከእኔ ጋር "ማን" ነበረ? ነው ያለው። ከዚህ ከአንድ እኔነት ጋር አብረው የፈጠሩ ማንነቶች እንደሌሉ ቁልጭ እና ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ይህ ሆኖ ሳለ ሰማያት እና ምድርን የፈጠሩ አሉ፥ እነርሱም እጁ፣ ቀኙ፣ ጣቶቹ ወዘተ ናቸው፦
ኢሳይያስ 48:13 *”እጄም ምድርን መሥርታለች ቀኜም ሰማያትን ዘርግታለች”*።
መዝሙር 8፥3 *”የጣቶችህን ሥራ” ሰማዮችን ባየሁ ጊዜ"*።
እነዚህን ባሕርያት ሸንሽነን ማንነት ሰጥተን ከሦስቱ ሥላሴ በላይ ስንት አካላት ልናረጋቸው ነው? ያህዌህ በጥበቡ፣ በማስተዋሉ፣ በኃይሉ ሰማያትን እና ምድርን ፈጥሯል፦
ምሳሌ 3፥19 *"ያህዌህ በጥበብ ምድርን መሠረተ፥ በማስተዋልም ሰማያትን አጸና”*።
ኤርምያስ 10፥12 *"ምድርን ”በኃይሉ የፈጠረ፥ ዓለሙን በጥበቡ የመሠረተ ሰማያትንም በማስተዋሉ የዘረጋ” እርሱ ነው"*።
ጥበቡ፣ ማስተዋሉ፣ ኃይሉ የራሱ ባሕርያት እንጂ የሚያማክሩት አካላት በፍጹም አይደሉም። እርሱ ራሱ እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንጂ ከራሱ ውጪ የሆኑ አካላትን እንፍጠር እያለ እየተመካከረ የሚሠራ በፍጹም አይደለም፦
ኤፌሶን 1፥11 *"እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ"*።
ከላይ ያለው አራተኛው እይታ ከሥነ-አመክንዮ አንጻር ድንቅ እይታ ነው። በቁርኣን ከሄድን ነገርን ሁሉ የፈጠረ ፈጣሪ ጌታችን አላህ ነው፥ ነገርን ሁሉ ብቻውን ፈጥሯል። ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፥ እርሱን ብቻ በብቸኝነት እናመልካለን፦
6፥102 *"ይህ ጌታችሁ አላህ ነው፥ ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፡፡ ነገርን ሁሉ ፈጣሪ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ተጠባባቂ ነው"*፡፡ ذَٰلِكُمُ اللَّهُ رَبُّكُمْ ۖ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ فَاعْبُدُوهُ ۚ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም