ነጥብ ሁለት
"ሴትና ጋብቻ"
በሙሴ ህግ አንድ ወንድ አንድ ሴት መፍታት የሚችለው የፍችዋን ወረቀት በመስጠት ነው፦
ዘዳግም 24፥1 ሰው ሴትን ወስዶ ቢያገባ፥ የእፍረት ነገር ስላገኘባት በእርሱ ዘንድ ሞገስ ባታገኝ፥ ""የፍችዋን ጽሕፈት ጽፎ በእጅዋ ይስጣት፥ ከቤቱም ይስደዳት""።
ዘዳግም 24፥3 ሁለተኛውም ባል ቢጠላት፥ ""የፍችዋንም ጽሕፈት ጽፎ በእጅዋ ቢሰጣት""፥ ከቤቱም ቢሰድዳት፥ ወይም ሚስት አድርጎ ያገባት ሁለተኛው ባልዋ ቢሞት፥
ነገር ግን በአዲስ ኪዳን አንድ ወንድ አንድ ሴት መፍታት የሚችለው ዝሙት ስትሰራ ብቻ ነው፦
ማቴዎስ 5: 31-32 ሚስቱን የሚፈታት ሁሉ የፍችዋን ጽሕፈት ይስጣት ተባለ። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ #አመንዝራ #ያደርጋታል፥ #የተፈታችውንም #የሚያገባ #ሁሉ #ያመነዝራል።
ማቴዎስ 19:9 እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን ፈትቶ ሌላዪቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል፥ #የተፈታችውንም #የሚያገባ #ያመነዝራል አላቸው።"
አንዲት ሴት በባህርይ አለመግባባት ቢኖር ወይም የፍቅር አለመጣጣም ቢኖር በዝሙት ካልሆነ መፈታት አትችልም። ከዚህ ሁሉ የሚገርመው ሚስቱን ፈትቶ ሌላ የሚያገባ አመንዝራ መባሉ ብቻ ሳይሆን የተፈታችው ሴት እርሱ በፈታት ሌላ ሰው እንዳያገባት እቀባ ተጥሎባታል። የተፈታች ሴት ሌላ ወንድ ካገባት አመንዝራ ይባላል።ሚስቱን ፈትቶ ሌላዪቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል፥ "የተፈታችውንም የሚያገባ ያመነዝራል አላቸው" የሚለው ይሰመርበት። እና ምን ትሆናለች? ሲባል ባልዋ እስኪሞት ድረስ ምንን ማግባት አትችልም፦
ሮሜ 7፥2-3"""ያገባች ሴት ባልዋ በሕይወት ሲኖር ከእርሱ ጋር በሕግ ታስራለችና""፤ ባልዋ ቢሞት ግን ስለ ባል ከሆነው ሕግ ተፈትታለች። """"ስለዚህ ባልዋ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ ትባላለች""""፤ ባልዋ ቢሞት ግን ከሕጉ አርነት ወጥታለችና ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ አይደለችም።
ልብ አድርጉ ""ባልዋ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ ትባላለች"" ባልዋ ቢሞት ግን ከሕጉ አርነት ወጥታለችና ሌላ ወንድ ማግባት ትችላለች። በተለይ የኢስላምን ህግ በምዕራባውያን ሚዛን ለሚመዝኑ ክርስቲያኖች ምን ይውጣቸው ይሆን? ዛሬስ በአገራችን ይህ የአዲስ ኪዳን ህግ ይኖር ይሆን? ፍርድ ቤቱን ያጨናነቀው የክርስቲያኑን ፍቺ ያለ ዝሙት ነው። ከዚህ ሁሉ የሚገርመው ኢየሱስ ባል ሚስቱ ያለ ዝሙት ምክንያት ከፈታ አመንዝራ ነው ሲል ጳውሎስ ደግሞ ሚስት ከባልዋ መለያየት ትችላለች ግን ሌላ ወንድ ሳታገባ ትኑር በማለት ይቃረናል፦
1ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች 7:10-11 " ሚስትም ከባልዋ አትለያይ፥ """ብትለያይ ግን ሳታገባ ትኑር"""" ወይም ከባልዋ ትታረቅ፥ ባልም ሚስቱን አይተዋት ብዬ የተጋቡትን አዛቸዋለሁ፥ እኔ ግን አላዝም፥ ጌታ እንጂ።
"ሴትና ጋብቻ"
በሙሴ ህግ አንድ ወንድ አንድ ሴት መፍታት የሚችለው የፍችዋን ወረቀት በመስጠት ነው፦
ዘዳግም 24፥1 ሰው ሴትን ወስዶ ቢያገባ፥ የእፍረት ነገር ስላገኘባት በእርሱ ዘንድ ሞገስ ባታገኝ፥ ""የፍችዋን ጽሕፈት ጽፎ በእጅዋ ይስጣት፥ ከቤቱም ይስደዳት""።
ዘዳግም 24፥3 ሁለተኛውም ባል ቢጠላት፥ ""የፍችዋንም ጽሕፈት ጽፎ በእጅዋ ቢሰጣት""፥ ከቤቱም ቢሰድዳት፥ ወይም ሚስት አድርጎ ያገባት ሁለተኛው ባልዋ ቢሞት፥
ነገር ግን በአዲስ ኪዳን አንድ ወንድ አንድ ሴት መፍታት የሚችለው ዝሙት ስትሰራ ብቻ ነው፦
ማቴዎስ 5: 31-32 ሚስቱን የሚፈታት ሁሉ የፍችዋን ጽሕፈት ይስጣት ተባለ። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ #አመንዝራ #ያደርጋታል፥ #የተፈታችውንም #የሚያገባ #ሁሉ #ያመነዝራል።
ማቴዎስ 19:9 እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን ፈትቶ ሌላዪቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል፥ #የተፈታችውንም #የሚያገባ #ያመነዝራል አላቸው።"
አንዲት ሴት በባህርይ አለመግባባት ቢኖር ወይም የፍቅር አለመጣጣም ቢኖር በዝሙት ካልሆነ መፈታት አትችልም። ከዚህ ሁሉ የሚገርመው ሚስቱን ፈትቶ ሌላ የሚያገባ አመንዝራ መባሉ ብቻ ሳይሆን የተፈታችው ሴት እርሱ በፈታት ሌላ ሰው እንዳያገባት እቀባ ተጥሎባታል። የተፈታች ሴት ሌላ ወንድ ካገባት አመንዝራ ይባላል።ሚስቱን ፈትቶ ሌላዪቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል፥ "የተፈታችውንም የሚያገባ ያመነዝራል አላቸው" የሚለው ይሰመርበት። እና ምን ትሆናለች? ሲባል ባልዋ እስኪሞት ድረስ ምንን ማግባት አትችልም፦
ሮሜ 7፥2-3"""ያገባች ሴት ባልዋ በሕይወት ሲኖር ከእርሱ ጋር በሕግ ታስራለችና""፤ ባልዋ ቢሞት ግን ስለ ባል ከሆነው ሕግ ተፈትታለች። """"ስለዚህ ባልዋ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ ትባላለች""""፤ ባልዋ ቢሞት ግን ከሕጉ አርነት ወጥታለችና ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ አይደለችም።
ልብ አድርጉ ""ባልዋ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ ትባላለች"" ባልዋ ቢሞት ግን ከሕጉ አርነት ወጥታለችና ሌላ ወንድ ማግባት ትችላለች። በተለይ የኢስላምን ህግ በምዕራባውያን ሚዛን ለሚመዝኑ ክርስቲያኖች ምን ይውጣቸው ይሆን? ዛሬስ በአገራችን ይህ የአዲስ ኪዳን ህግ ይኖር ይሆን? ፍርድ ቤቱን ያጨናነቀው የክርስቲያኑን ፍቺ ያለ ዝሙት ነው። ከዚህ ሁሉ የሚገርመው ኢየሱስ ባል ሚስቱ ያለ ዝሙት ምክንያት ከፈታ አመንዝራ ነው ሲል ጳውሎስ ደግሞ ሚስት ከባልዋ መለያየት ትችላለች ግን ሌላ ወንድ ሳታገባ ትኑር በማለት ይቃረናል፦
1ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች 7:10-11 " ሚስትም ከባልዋ አትለያይ፥ """ብትለያይ ግን ሳታገባ ትኑር"""" ወይም ከባልዋ ትታረቅ፥ ባልም ሚስቱን አይተዋት ብዬ የተጋቡትን አዛቸዋለሁ፥ እኔ ግን አላዝም፥ ጌታ እንጂ።