ነጥብ አንድ
“ሩዕያ”
አንደኛ መንገድ በሩዕያ ማናገር ነው፤ “ሩዕያ” رُّءْيَا ማለት “ራዕይ” ማለት ሲሆን ይህም ራዕይ በሪዕይ ውስጥ ሆነው የሚመጣላቸው ንግግር ነው፤ “ሪዕይ” رِءْي ማለት “እይታ” ማለት ሲሆን በሰመመን ወይም በተመስጦ ላይ ሆነው ሲሆን ነው፤ የራዕይ አንዱ ገፅታ “መናም” مَنَام ማለት “ህልም” ሲሆን ይህም በነውም ሆነው የሚመጣላቸው ንግግር ነው፤ “ነውም” نَوْم ማለት “እንቅልፍ” ማለት ነው፤ በዚህ ሁኔታ አላህ ወህይ ካወረደለት ነብይ መካከል የኢማን አባት የሆነው ኢብራሂም”አ.ሰ.” ነው፦
37፥102 ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ #በሕልሜ الْمَنَامِ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
37፥105 #ራእይቱን الرُّؤْيَا በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
ነጥብ ሁለት
“ተክሊም”
ሁለተኛ መንገድ በተክሊም ማናገር ነው፤ “ተክሊም” تَكْلِيم ማለት በሁለት ማንነት መካከል የሚደረግ “ምልልስ”conversation” ሲሆን አላህ ያለ ራዕይና ህልም ወይም ያለ መልአክ ሳይታይ ከግርዶ ወዲያ ሆና የሚያናግርበት መንገድ ነው፤ በዚህ መልኩ አላህ ያናገረው ነብይ ለናሙና ያክል ሙሳ”አ.ሰ.” ተጠቃሽ ነው፦
4:164 አላህም ሙሳን #ማነጋገርን #አነጋገረው وَكَلَّمَ اللَّهُ مُوسَىٰ تَكْلِيمًا ።
2:253 እነዚህን መልክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን፡፡ ከእነርሱ ውስጥ አላህ #ያነጋገረውَ” كَلَّمَ አልለ፡፡
19:51-52 በመጽሐፉ ዉስጥ ሙሳንም አዉሳ፤ እርሱ ምርጥ ነበርና መልክተኛ ነቢይም ነበር፤ ከጡር ቀኝ ጎን በኩልም #ጠራነው #ያነጋገርነዉም نَجِيًّا ሲኾን አቀረብነው።
28፥30 በመጣትም ጊዜ ከሸለቆው ቀኝ ዳርቻ ከዛፊቱ በኩል በተባረከችው ስፍራ ውስጥ «ሙሳ ሆይ! እኔ የዓለማት ጌታ አላህ እኔ ነኝ» በማለት #ተጠራ፡፡
20፥13-14 «እኔም መረጥኩህ፤ #የሚወረድልህንም يُوحَىٰ አዳምጥ፡፡ እኔ አላህ እኔ ነኝ ያለ እኔ አምላክ የለምና አምልከኝ፤ ሶላትንም እኔን ለማውሳት ስገድ፡፡
ነጥብ ሶስት
“መልአክ”
ሶስተኛ መንገድ በመልአክ ማናገር ነው፤ “ረሱል” رَسُول የሚለው ቃል “ተላላኪ” ማለት ሲሆን “መለክ” مَلَك ማለትም “መልአክ” የሚለው ቃል ተለዋዋጭ”inter-change” ሆኖ የመጣ ነው፤ ይህም የወህይ መልአክ ጂብሪል”አ.ሰ.” ነው፦
19:17 ከእነሱም መጋረጃን አደረገች፣ #መንፈሳችንንም (ጂብሪልን) ወደርሷ ላክን፤ ለርሷም ትክክለኛ ሰው ሆኖ ተመሰለላት።
19:19:፦ እኔ ንጹሕን ልጅ ለአንቺ ልሰጥሽ፣ የጌታሽ #መልክተኛ” رَسُولُ ነኝ አላት።
አላህ በዚህ መልአክ ነብያችንን”ﷺ” አናግሯል፦
2:97 #ለጂብሪል* ጠላት የኾነ ሰው በቁጭት ይሙት በላቸው፡፡ #እርሱ* ከበፊቱ ለነበሩት አረጋጋጭ ለምእመናን መሪና ብስራት ሲኾን #በአላህ #ፈቃድ* #በልብህ* ላይ #አውርዶታልና*፡፡
“ሩዕያ”
አንደኛ መንገድ በሩዕያ ማናገር ነው፤ “ሩዕያ” رُّءْيَا ማለት “ራዕይ” ማለት ሲሆን ይህም ራዕይ በሪዕይ ውስጥ ሆነው የሚመጣላቸው ንግግር ነው፤ “ሪዕይ” رِءْي ማለት “እይታ” ማለት ሲሆን በሰመመን ወይም በተመስጦ ላይ ሆነው ሲሆን ነው፤ የራዕይ አንዱ ገፅታ “መናም” مَنَام ማለት “ህልም” ሲሆን ይህም በነውም ሆነው የሚመጣላቸው ንግግር ነው፤ “ነውም” نَوْم ማለት “እንቅልፍ” ማለት ነው፤ በዚህ ሁኔታ አላህ ወህይ ካወረደለት ነብይ መካከል የኢማን አባት የሆነው ኢብራሂም”አ.ሰ.” ነው፦
37፥102 ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ #በሕልሜ الْمَنَامِ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
37፥105 #ራእይቱን الرُّؤْيَا በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
ነጥብ ሁለት
“ተክሊም”
ሁለተኛ መንገድ በተክሊም ማናገር ነው፤ “ተክሊም” تَكْلِيم ማለት በሁለት ማንነት መካከል የሚደረግ “ምልልስ”conversation” ሲሆን አላህ ያለ ራዕይና ህልም ወይም ያለ መልአክ ሳይታይ ከግርዶ ወዲያ ሆና የሚያናግርበት መንገድ ነው፤ በዚህ መልኩ አላህ ያናገረው ነብይ ለናሙና ያክል ሙሳ”አ.ሰ.” ተጠቃሽ ነው፦
4:164 አላህም ሙሳን #ማነጋገርን #አነጋገረው وَكَلَّمَ اللَّهُ مُوسَىٰ تَكْلِيمًا ።
2:253 እነዚህን መልክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን፡፡ ከእነርሱ ውስጥ አላህ #ያነጋገረውَ” كَلَّمَ አልለ፡፡
19:51-52 በመጽሐፉ ዉስጥ ሙሳንም አዉሳ፤ እርሱ ምርጥ ነበርና መልክተኛ ነቢይም ነበር፤ ከጡር ቀኝ ጎን በኩልም #ጠራነው #ያነጋገርነዉም نَجِيًّا ሲኾን አቀረብነው።
28፥30 በመጣትም ጊዜ ከሸለቆው ቀኝ ዳርቻ ከዛፊቱ በኩል በተባረከችው ስፍራ ውስጥ «ሙሳ ሆይ! እኔ የዓለማት ጌታ አላህ እኔ ነኝ» በማለት #ተጠራ፡፡
20፥13-14 «እኔም መረጥኩህ፤ #የሚወረድልህንም يُوحَىٰ አዳምጥ፡፡ እኔ አላህ እኔ ነኝ ያለ እኔ አምላክ የለምና አምልከኝ፤ ሶላትንም እኔን ለማውሳት ስገድ፡፡
ነጥብ ሶስት
“መልአክ”
ሶስተኛ መንገድ በመልአክ ማናገር ነው፤ “ረሱል” رَسُول የሚለው ቃል “ተላላኪ” ማለት ሲሆን “መለክ” مَلَك ማለትም “መልአክ” የሚለው ቃል ተለዋዋጭ”inter-change” ሆኖ የመጣ ነው፤ ይህም የወህይ መልአክ ጂብሪል”አ.ሰ.” ነው፦
19:17 ከእነሱም መጋረጃን አደረገች፣ #መንፈሳችንንም (ጂብሪልን) ወደርሷ ላክን፤ ለርሷም ትክክለኛ ሰው ሆኖ ተመሰለላት።
19:19:፦ እኔ ንጹሕን ልጅ ለአንቺ ልሰጥሽ፣ የጌታሽ #መልክተኛ” رَسُولُ ነኝ አላት።
አላህ በዚህ መልአክ ነብያችንን”ﷺ” አናግሯል፦
2:97 #ለጂብሪል* ጠላት የኾነ ሰው በቁጭት ይሙት በላቸው፡፡ #እርሱ* ከበፊቱ ለነበሩት አረጋጋጭ ለምእመናን መሪና ብስራት ሲኾን #በአላህ #ፈቃድ* #በልብህ* ላይ #አውርዶታልና*፡፡
አካል እና መንፈስ
ክፍል ሁለት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
17:85 ከሩሕም ይጠይቁሃል፤ ሩሕ *ከ* ጌታዬ ነገር مِنْ أَمْرِ رَبِّي ነው፤ ከዕውቀትም ጥቂትን እንጂ አልተሰጣችሁም፤ በላቸው።
ነጥብ ሁለት
“መንፈስ”
“ሩሕ” رُوح የሚለው ቃል “መንፈስ” ማለት ሲሆን በቁርአን 21 ጊዜ ተጠቅሷል፤ ይህም ቃል እንደየ አውዱ ለተለየየ አጠቃቀም ይጠቀምበታል፤ ለምሳሌ ቁርአን “መንፈስ” ተብሏል፦
42፥52 እንደዚሁም ወደ አንተ ከትእዛዛችን ሲኾን “መንፈስን” አወረድን፡፡ መጽሐፉም እምነቱም ምን እንደኾነ የምታውቅ አልነበርክም፡፡ ግን ከባሮቻችን የምንሻውን ሰው በእርሱ የምንመራበት “ብርሃን” አደረግነው፡፡ አንተም ወደ ቀጥተኛው መንገድ በእርግጥ ትመራለህ وَكَذَٰلِكَ أَوْحَيْنَآ إِلَيْكَ رُوحًۭا مِّنْ أَمْرِنَا ۚ مَا كُنتَ تَدْرِى مَا ٱلْكِتَٰبُ وَلَا ٱلْإِيمَٰنُ وَلَٰكِن جَعَلْنَٰهُ نُورًۭا نَّهْدِى بِهِۦ مَن نَّشَآءُ مِنْ عِبَادِنَا ۚ وَإِنَّكَ لَتَهْدِىٓ إِلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ ፡፡
እዚህ አንቀፅ ላይ “መንፈስ” እና “ብርሃን” ተለዋዋጭ ቃል ሆነው ገብተዋል፤ ብርሃን የሃይድሮጂን፣ የሂልየም እና የአርገን ብርሃን ማለት እንዳልሆን ሁሉ መንፈስ የተባለውም አካል ህያው የሚሆንበት ንጥረ-ነገር ሳይሆን ቁርአን ነው፤ “መንፈስ” እና “ብርሃን” እዚህ ጋር “ሒስሲይ” ማለትም “እማሬአዊ” ሳይሆን “መዕነዊይ” ማለትም “ፍካሬአዊ” ነው። በተጨማሪም ጂብሪል *ታማኙ መንፈስ* እና *ቅዱሱ መንፈስ* ተብላል፦
26:192-194 እርሱም ቁርአን በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡ እርሱን #ታማኙ* #መንፈስ* አወረደው፤ ከአስጠንቃቂዎቹ ትኾን ዘንድ #በልብህ* ላይ አወረደው፡፡
19:17 ከእነሱም መጋረጃን አደረገች፣ #መንፈሳችንንም (ጂብሪልን) ወደርሷ ላክን፤ ለእርሷም ትክክለኛ ሰው ሆኖ ተመሰለላት።
16:102 እነዚያን ያመኑትን ለማረጋጋት ሙስሊሞቹንም ለመምራትና ለማብሰር ቁርአንን #ቅዱሱ* #መንፈስ*(ጂብሪል) እውነተኛ ሲሆን #ከጌታህ* مِنْ رَبِّكَ *አወረደው* በላቸው።
ክፍል ሁለት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
17:85 ከሩሕም ይጠይቁሃል፤ ሩሕ *ከ* ጌታዬ ነገር مِنْ أَمْرِ رَبِّي ነው፤ ከዕውቀትም ጥቂትን እንጂ አልተሰጣችሁም፤ በላቸው።
ነጥብ ሁለት
“መንፈስ”
“ሩሕ” رُوح የሚለው ቃል “መንፈስ” ማለት ሲሆን በቁርአን 21 ጊዜ ተጠቅሷል፤ ይህም ቃል እንደየ አውዱ ለተለየየ አጠቃቀም ይጠቀምበታል፤ ለምሳሌ ቁርአን “መንፈስ” ተብሏል፦
42፥52 እንደዚሁም ወደ አንተ ከትእዛዛችን ሲኾን “መንፈስን” አወረድን፡፡ መጽሐፉም እምነቱም ምን እንደኾነ የምታውቅ አልነበርክም፡፡ ግን ከባሮቻችን የምንሻውን ሰው በእርሱ የምንመራበት “ብርሃን” አደረግነው፡፡ አንተም ወደ ቀጥተኛው መንገድ በእርግጥ ትመራለህ وَكَذَٰلِكَ أَوْحَيْنَآ إِلَيْكَ رُوحًۭا مِّنْ أَمْرِنَا ۚ مَا كُنتَ تَدْرِى مَا ٱلْكِتَٰبُ وَلَا ٱلْإِيمَٰنُ وَلَٰكِن جَعَلْنَٰهُ نُورًۭا نَّهْدِى بِهِۦ مَن نَّشَآءُ مِنْ عِبَادِنَا ۚ وَإِنَّكَ لَتَهْدِىٓ إِلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ ፡፡
እዚህ አንቀፅ ላይ “መንፈስ” እና “ብርሃን” ተለዋዋጭ ቃል ሆነው ገብተዋል፤ ብርሃን የሃይድሮጂን፣ የሂልየም እና የአርገን ብርሃን ማለት እንዳልሆን ሁሉ መንፈስ የተባለውም አካል ህያው የሚሆንበት ንጥረ-ነገር ሳይሆን ቁርአን ነው፤ “መንፈስ” እና “ብርሃን” እዚህ ጋር “ሒስሲይ” ማለትም “እማሬአዊ” ሳይሆን “መዕነዊይ” ማለትም “ፍካሬአዊ” ነው። በተጨማሪም ጂብሪል *ታማኙ መንፈስ* እና *ቅዱሱ መንፈስ* ተብላል፦
26:192-194 እርሱም ቁርአን በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡ እርሱን #ታማኙ* #መንፈስ* አወረደው፤ ከአስጠንቃቂዎቹ ትኾን ዘንድ #በልብህ* ላይ አወረደው፡፡
19:17 ከእነሱም መጋረጃን አደረገች፣ #መንፈሳችንንም (ጂብሪልን) ወደርሷ ላክን፤ ለእርሷም ትክክለኛ ሰው ሆኖ ተመሰለላት።
16:102 እነዚያን ያመኑትን ለማረጋጋት ሙስሊሞቹንም ለመምራትና ለማብሰር ቁርአንን #ቅዱሱ* #መንፈስ*(ጂብሪል) እውነተኛ ሲሆን #ከጌታህ* مِنْ رَبِّكَ *አወረደው* በላቸው።