ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.9K subscribers
68 photos
70 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
አስካሪ መጠጥ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

2፥219 አእምሮን ከሚቃወም መጠጥ እና ከቁማር ይጠይቁሃል፡፡ «በሁለቱም ውስጥ ታላቅ ኃጢኣት እና ለሰዎች ጥቅሞች አሉባቸው፡፡ ግን ኃጢኣታቸው ከጥቅማቸው በጣም ትልቅ ነው» በላቸው፡፡ يَسْأَلُونَكَ عَنِ الْخَمْرِ وَالْمَيْسِرِ ۖ قُلْ فِيهِمَا إِثْمٌ كَبِيرٌ وَمَنَافِعُ لِلنَّاسِ وَإِثْمُهُمَا أَكْبَرُ مِن نَّفْعِهِمَا ۗ

"ኸምር" خَمْرየሚለው ቃል "ኸመረ" خَمَرَ ማለትም "ሸፈነ" "ደበቀ" "ሰወረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ "የሚሸፍን" "የሚደብቅ" "የሚሰውር" ማለት ነው፥ እኅቶቻችን ከሚሰተሩበት ሒጃብ መካከል "ጉፍታ" እራሱ በቁርኣን "ኺማር" خِمَار ይባላል፦
24፥31 ጉፍታዎቻቸውንም በአንገትጌዎቻቸው ላይ ያጣፉ። وَلْيَضْرِبْنَ بِخُمُرِهِنَّ عَلَىٰ جُيُوبِهِنَّ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ጉፍታዎች" ለሚለው በብዜት የገባው ቃል "ኹሙር" خُمُر ሲሆን በነጠላ ደግሞ "ኺማር" خِمَار ነው፥ “ኺማር” خِمَار የሚለው ቃል ልክ እንደ “ኸምር” خَمْر ሥርወ-ቃሉ “ኸመረ” خَمَرَ ነው። ጉፍታ ራስን ስለሚሸፍን “ኺማር” خِمَار እንሚባል ሁሉ አእምሮን የሚቃወም ማንኛውም አስካሪ መጠጥ”alcohol" ሁሉ “ኸምር” خَمْر ይባላል፦
2፥219 አእምሮን ከሚቃወም መጠጥ እና ከቁማር ይጠይቁሃል፡፡ «በሁለቱም ውስጥ ታላቅ ኃጢኣትና ለሰዎች ጥቅሞች አሉባቸው፡፡ ግን ኃጢኣታቸው ከጥቅማቸው በጣም ትልቅ ነው» በላቸው፡፡ يَسْأَلُونَكَ عَنِ الْخَمْرِ وَالْمَيْسِرِ ۖ قُلْ فِيهِمَا إِثْمٌ كَبِيرٌ وَمَنَافِعُ لِلنَّاسِ وَإِثْمُهُمَا أَكْبَرُ مِن نَّفْعِهِمَا ۗ

ቁማር መሠረቱ ገንዘብ ስለሆነ ለሰዎች ጥቅም አለው፥ አስካሪ መጠጥ በህክምና አገልግሎት ለሰዎች ጥቅም አለው። ነገር ግን ኸምር ሆነ ቁማር ኃጢኣታቸው ከጥቅማቸው በጣም ትልቅ ስለሆነ ታላቅ ኃጢኣት አለባቸው፥ አስካሪ መጠጥ ውስጥ የሚካተቱት ጠላ፣ ጠጅ፣ አረቄ፣ ውስኪ፣ ቮድካ ወዘተ ናቸው፦
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 74, ሐዲስ 14
ኢብኑ ዑመር”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ “ዑመር በአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” አትሮንስ ላይ ኹጥባህ ሲያደርግ እንዲህ አለ፦ ”ኸምር ሐራም መሆኑ የሚናገረው የወረደው ከአምስት ነገር ማለትም ከወይን፣ ከተምር፣ ከስንዴ፣ ከገብስ እና ከማር ስለሚዘጋጁት ኸምር ናቸው። ዐቅልን የሚሰውር ሁሉ ኸምር ነው”። عَنِ ابْنِ عُمَرَ ـ رضى الله عنهما ـ قَالَ خَطَبَ عُمَرُ عَلَى مِنْبَرِ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم فَقَالَ إِنَّهُ قَدْ نَزَلَ تَحْرِيمُ الْخَمْرِ، وَهْىَ مِنْ خَمْسَةِ أَشْيَاءَ الْعِنَبِ وَالتَّمْرِ وَالْحِنْطَةِ وَالشَّعِيرِ وَالْعَسَلِ، وَالْخَمْرُ مَا خَامَرَ الْعَقْلَ

እዚህ ሐዲስ ላይ “የሚሰውር” ለሚለው የገባው ቃል “ኻመረ” خَامَرَ መሆኑ ልብ አድርግ! አስካሪ መጠጥ አእምሮን የሚያስት እስከሆነ ድረስ ሙሥኪር ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 36, ሐዲስ 95
ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ “ነቢዩ”ﷺ”፦ ”ሙሥኪር ሁሉ ኸምር ነው፥ ኸምር ሁሉ ሐራም ነው” ሲሉ እንጂ ሌላ ዐላውቅም”። عَنِ ابْنِ عُمَرَ، قَالَ وَلاَ أَعْلَمُهُ إِلاَّ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ كُلُّ مُسْكِرٍ خَمْرٌ وَكُلُّ خَمْرٍ حَرَامٌ ‏”‏
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 30, ሐዲስ 3514
ሙዓዊያህ የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ ሲሉ ሰምቼ ነበር፦ ”ሙሥኪር ሁሉ ለሁሉም ምእመናን ሐራም ነው”። سَمِعْتُ مُعَاوِيَةَ، يَقُولُ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ يَقُولُ ‏ “‏ كُلُّ مُسْكِرٍ حَرَامٌ عَلَى كُلِّ مُؤْمِنٍ ‏”‏

“ሙሥኪር” مُسْكِر የሚለው ቃል “ሠኪረ” سَكِرَ
ማለትም "ሰከረ" ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "የሚያሰክር" "የሚያነፍዝ" ማለት ነው፥ “ሠከር” سَكَر እራሱ “አስካሪ”intoxicant” ማለት ሲሆን “ሡክር” سُكْر ደግሞ “አስካሪነት”intoxication” ማለት ነው። ኸምር ከዘምባባ እና ከወይን ፍሬ የሚሠራ ጠጅ ነው፦
16፥67 ከዘምባባዎች እና ከወይኖችም ፍሬዎች እንመግባችኋለን፡፡ ከእርሱ ጠጅን እና መልካም ምግብንም ትሠራላችሁ፡፡ በዚህም ውስጥ ለሚያስቡ ሕዝቦች በእርግጥ ተዓምር አለ፡፡ وَمِن ثَمَرَاتِ النَّخِيلِ وَالْأَعْنَابِ تَتَّخِذُونَ مِنْهُ سَكَرًا وَرِزْقًا حَسَنًا ۗ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً لِّقَوْمٍ يَعْقِلُونَ

አሏህ ከዘንባባ እና ከወይን ፍሬ ማብቀሉ በእርግጥ ታምር አለበት፥ ከዚህም ሰው በሠናይ መልካም ምግብ ማለትም ጭማቂ ሲሠራ በተቃራኒው እኩይ የሆነውን አስካሪ ጠጅን ይሠራል። "ዛሊከ" ذَٰلِكَ ማለትም "በዚህም" የተባለው ኢሥሙል ኢሻራህ ከበፊቱ ያለው "ሁ" هُ ማለትም "እርሱ" የተባለው ዶሚሩል ሙንተሲል የሚያመለክት ነው፥ ይህም "እርሱ" የተባለው ፍራፍሬው ነው፦
16፥11 "በ"-"እርሱ" ለእናንተ አዝመራን፣ ወይራንም፣ ዘምባባዎችንም፣ ወይኖችንም፣ ከፍሬዎችም ሁሉ ያበቅልላችኋል፤ በዚህ ውስጥ ለሚያስተነትኑ ሕዝቦች በእርግጥ ታምር አለ። يُنبِتُ لَكُم بِهِ الزَّرْعَ وَالزَّيْتُونَ وَالنَّخِيلَ وَالْأَعْنَابَ وَمِن كُلِّ الثَّمَرَاتِ ۗ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً لِّقَوْمٍ يَتَفَكَّرُونَ
እዚህ አንቀጽ ላይ “ዛሊከ” ذَٰلِكَ የተባለው የአዝመራን፣ የወይራንም፣ የዘምባባዎችንም፣ የወይኖችንም ፍራፍሬ ነው። ተጨማሪ አናቅጽ፦ 6፥99 13፥3 ይመልከቱ!
ፍራፍሬ ሲቆይ ስኳርነቱ ወደ አሲድ ይቀየርና ቆምጣጣነት"Fermentation" ሢሠራ ወይም ጌሾና ብቅል ሲቀላቀልበት ፓስቸራዜሽን”Pasteurization” እና ኒዩትራላይዜሽን”Neutralization” በመሆን ያሰክራል፥ ቢራ ፣ ቮድካ፣ ውስኪ የመሳሰሉት የዛ ውጤት ናቸው። አስካሪ መጠጥ አዕምሮን የሚያደንዝ እና ለጥል፣ ለጥላቻ፣ ለዝሙት፣ ለጣዖት አምልኮ የሚዳርግ፣ ከሶላት እና አሏህ ከማውሳት የሚያዘናጋ እኩይ ነገር ስለሆነ ከሸይጧን ነው፦
5፥90 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የሚያሰክር መጠጥ ቁማርም ጣዖታትም አዝላምም ከሰይጣን ሥራ የኾኑ እርኩስ ብቻ ናቸው፡፡ እርኩስን ራቁትም ልትድኑ ይከጀላልና፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا إِنَّمَا الْخَمْرُ وَالْمَيْسِرُ وَالْأَنصَابُ وَالْأَزْلَامُ رِجْسٌ مِّنْ عَمَلِ الشَّيْطَانِ فَاجْتَنِبُوهُ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ
5፥91 ሰይጣን የሚፈልገው በሚያሰክር መጠጥና በቁማር በመካከላችሁ ጠብንና ጥላቻን ሊጥል፤ አላህን ከማውሳት እና ከስግደትም ሊያግዳችሁ ብቻ ነው፡፡ ታዲያ እናንተ ከእነዚህ ተከልካዮች ናችሁን ተከልከሉ፡፡ إِنَّمَا يُرِيدُ الشَّيْطَانُ أَن يُوقِعَ بَيْنَكُمُ الْعَدَاوَةَ وَالْبَغْضَاءَ فِي الْخَمْرِ وَالْمَيْسِرِ وَيَصُدَّكُمْ عَن ذِكْرِ اللَّهِ وَعَنِ الصَّلَاةِ ۖ فَهَلْ أَنتُم مُّنتَهُونَ

"ነቢዝ" نَّبِيذ ማለት ከዘምባባ እና ከወይን ፍሬ የሚጠጣ ጭማቂ"juice" ነው፥ እርሱን መጠጣት ሐላል ነው፦
ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 36, ሐዲስ 81
ዐብደላህ ኢብኑ ቡረይዳህ አባቱ እንዳለው የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” አሉ፦ "በኮዳ በስተቀር ከነቢዝ የሚዘጋጅ ነገር እንዳትጠጡ ከልክያችሁ ነበር፥ ግን አሁን በሁሉም ሰፍነግ መጠጣት ትችላላችሁ። ነገር ግን አስካሪ መጠጥ እንዳትጠጡ። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ بُرَيْدَةَ، عَنْ أَبِيهِ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ نَهَيْتُكُمْ عَنِ النَّبِيذِ إِلاَّ فِي سِقَاءٍ فَاشْرَبُوا فِي الأَسْقِيَةِ كُلِّهَا وَلاَ تَشْرَبُوا مُسْكِرًا ‏”‏

ይህ ጭማቂ ከሁለት ቀናት አሊያም ከሦስት ቀናት በኃላ ስለሚቆመጥጥ ሙሥኪር ይሆናል፥ ሙሥኪር መጠጣት ሐራም ነው። አይደለም ኸምር ጠጪው ይቅርና ቀጂውን፣ ሻጩንም፣ ገዢውንም፣ ጨማቂውን፣ አስጨማቂውን፣ ተሸካሚውን እና የሚሸከሙለትንም ሁሉ ተጠያቂዎች ናቸው፦
ሡነንን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 27, ሐዲስ 6:
ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር”ረ.ዐ.” እንዳስተላለፈው የአላህ መልክተኛም”ﷺ” አሉ፦ ”አላህ ኸምርን ጠጪውን፣ ቀጂውን፣ ሻጩንም፣ ገዢውንም፣ ጨማቂውን፣ አስጨማቂውን፣ ተሸካሚውን እና የሚሸከሙለትንም ሁሉ ረግሟቸዋል"። أَنَّهُمَا سَمِعَا ابْنَ عُمَرَ، يَقُولُ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ لَعَنَ اللَّهُ الْخَمْرَ وَشَارِبَهَا وَسَاقِيَهَا وَبَائِعَهَا وَمُبْتَاعَهَا وَعَاصِرَهَا وَمُعْتَصِرَهَا وَحَامِلَهَا وَالْمَحْمُولَةَ إِلَيْهِ ‏”‏
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 74, ሐዲስ 1:
ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር”ረ.ዐ.” እንደተረከው የአላህ መልክተኛም”ﷺ” አሉ፦ "የሚያሰክር ነገር ሁሉ ኸምር ነው፤ የሚያሰክር ነገር ሁሉ ሐራም ነው፡፡ በዱኒያህ ኸምርን የጠጣ እና በእሷም ላይ ዘውትሮ ሳይቶብት የሞተ ሰው በአኺራ የጀነቷን አይጠጣትም"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عُمَرَ ـ رضى الله عنهما ـ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ مَنْ شَرِبَ الْخَمْرَ فِي الدُّنْيَا، ثُمَّ لَمْ يَتُبْ مِنْهَا، حُرِمَهَا فِي الآخِرَةِ ‏”‌‏.‏

አሏህ ከአስካሪ መጠጥ እና በአስካሪ መጠጥ ከሚመጣ ጥፋት ይጠብቀን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሪያእ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

107፥6 ለእነዚያ እነርሱ ይዩልኝ ባዮች ለኾኑት ወዮላቸው፡፡ ٱلَّذِينَ هُمْ يُرَآءُونَ

"ሪያእ" رِيَاء የሚለው ቃል "ራኣ" رَاءَى ማለትም "አሳየ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "እዩልኝ" ማለት ሲሆን መልካም ሥራን የሰዎችን ፊት ተከጅሎ ከተሠራ "ሪያእ" رِيَاء ይባላል፦
2፥264 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እንደዚያ ገንዘቡን ለሰዎች ማሳየት ሲል እንደሚሰጠውና በአላህና በመጨረሻውም ቀን እንደማያምነው ሰው ምጽዋቶቻችሁን በመመጻደቅ እና በማስከፋት አታበላሹ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا لَا تُبْطِلُوا صَدَقَاتِكُم بِالْمَنِّ وَالْأَذَىٰ كَالَّذِي يُنفِقُ مَالَهُ رِئَاءَ النَّاسِ وَلَا يُؤْمِنُ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ማሳየት" ለሚለው ግሣዊ ስም የገባው ቃል "ሪያእ" رِيَاء መሆኑን ልብ አድርግ! መልካም ሥራን ለሰዎች ለማሳየት መሥራት "መን" ነው፥ "መን" مَنّ ማለት "መመጻደቅ" ማለት ነው። ያለመመጻደቅ የአሏህን ፊት ከጅለው መልካም ሥራ የሚሠሩ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው፥ በእነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም። እነርሱም አያዝኑም፦
2፥262 እነዚያ ገንዘቦቻቸውን በአላህ መንገድ የሚለግሱ ከዚያም የሰጡትን ነገር መመጻደቅን እና ማስከፋትን የማያስከትሉ ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው፡፡ በእነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም፤ እነርሱም አያዝኑም፡፡ الَّذِينَ يُنفِقُونَ أَمْوَالَهُمْ فِي سَبِيلِ اللَّهِ ثُمَّ لَا يُتْبِعُونَ مَا أَنفَقُوا مَنًّا وَلَا أَذًى ۙ لَّهُمْ أَجْرُهُمْ عِندَ رَبِّهِمْ وَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
49፥17 በመሥለማቸው በአንተ ላይ ይመጻደቃሉ። «በእሥምናችሁ በእኔ ላይ አትመጻደቁ! ይልቁንም አላህ ወደ እምነት ስለ መራችሁ ይመጸደቅባችኋል። እውነተኞች ብትኾኑ መመጻደቅ ለአላህ ነው» በላቸው፡፡ يَمُنُّونَ عَلَيْكَ أَنْ أَسْلَمُوا ۖ قُل لَّا تَمُنُّوا عَلَيَّ إِسْلَامَكُم ۖ بَلِ اللَّهُ يَمُنُّ عَلَيْكُمْ أَنْ هَدَاكُمْ لِلْإِيمَانِ إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ

መመጻደቅ የአሏህ ሐቅ ብቻ ነው፥ "ሥራዬን ዓይታችሁ ተፈኩር እና ተደቡር አርጉ" ማለት የእርሱ መብት ብቻ ነው። ሪያእ የኢኽላስ ተቃራኒ ነው፥ "ኢኽላስ" إِخْلَاص‎ የሚለው ቃል "አኽለሶ" أَخْلَصَ‎ ማለትም "አጠራ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን እውነት ለማንገሥ ሐሠትን ለማርከሥ የሚደረግ “መተናነስ” ወይም ከሙገሳ እና ከወቀሳ ነጻ ሆኖ ለአሏህ ውዴታ የሚደረግ “ማጥራት” ማለት ነው። እዩልኝ ባዮች ወዮላቸው የተባለባቸው ሥራቸው ሺርክ ለሆነ ነው፦
107፥4 ወዮላቸው ለሰጋጆች፡፡ فَوَيْلٌۭ لِّلْمُصَلِّينَ
107፥6 ለእነዚያ እነርሱ ይዩልኝ ባዮች ለኾኑት ወዮላቸው፡፡ ٱلَّذِينَ هُمْ يُرَآءُونَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ይዩልኝ ባዮች" ለሚለው የገባው ቃል "ዩራኡን" يُرَآءُون ሲሆን በሪያእ ድርጊት የተሰማሩ ሰዎች አመላካች ነው፥ "ሺርኩል ኸፊይ" شِّرْكُ الْخَفِي ማለት "ድብቁ ሺርክ" ማለት ሲሆን ሪያእ በሰው ልብ ውስጥ ተደብቆ ያለ ድብቁ ሺርክ ነው፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 4344
አቢ ሠዒድ እንደተናገረው፦ "ስለ መሢሑል ደጃል በተወያየንበት ጊዜ የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” ወደ እኛ መጥተው፦ "ከመሢሑል ደጃል የባሰ የምፈራላችሁን ነገር ልንገራችሁን? አሉን፥ እኛም አዎ አልን። እርሳቸውም፦ "አንድ ሰው ሶላት ሲቆምና በሰው ፊት ጥሩ አድርጎ ለሰው እንዲያይለት ማድረግ ድብቁ ሺርክ ነው። عَنْ أَبِي سَعِيدٍ، قَالَ خَرَجَ عَلَيْنَا رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ وَنَحْنُ نَتَذَاكَرُ الْمَسِيحَ الدَّجَّالَ فَقَالَ ‏”‏ أَلاَ أُخْبِرُكُمْ بِمَا هُوَ أَخْوَفُ عَلَيْكُمْ عِنْدِي مِنَ الْمَسِيحِ الدَّجَّالِ ‏”‏ ‏.‏ قَالَ قُلْنَا بَلَى ‏.‏ فَقَالَ ‏”‏ الشِّرْكُ الْخَفِيُّ أَنْ يَقُومَ الرَّجُلُ يُصَلِّي فَيُزَيِّنُ صَلاَتَهُ لِمَا يَرَى مِنْ نَظَرِ رَجُلٍ ‏”‏ ‏.‏

"ሽርኩል አስገር" شِّرْكُ اَلْأَصْغَر ማለት "ትንሹ ሺርክ" ማለት ሲሆን በሰው ልብ ተደብቆ ያለ ድብቁ ሺርክ ሪያእ "ሽርኩል አስገር" شِّرْكُ اَلْأَصْغَر ነው፦
ቡሉጉል መራም መጽሐፍ 8 ሐዲስ 1035
መሕሙድ ለቢድ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ትንሹ ሺርክ የሆነውን ሪያእን እፈራላችኃለው"። وَعَنْ مَحْمُودِ بْنِ لَبِيدٍ ‏- رضى الله عنه ‏- قَالَ: قَالَ رَسُولُ اَللَّهِ ‏- صلى الله عليه وسلم ‏-{ إِنَّ أَخْوَفَ مَا أَخَافُ عَلَيْكُمْ اَلشِّرْكُ اَلْأَصْغَرُ: اَلرِّيَاءُ }

አሏህ ከሪያእ ይጠብቀን! መልካም ሥራዎቻችንን በኢኽላስ ይቀበለን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የጀናህ ኸምር

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

32፥17 ይሠሩትም በነበሩት ለመመንዳት ከዓይኖች መርጊያ ለእነርሱ የተደበቀላቸውን ጸጋ ማንኛይቱም ነፍስ አታውቅም፡፡ فَلَا تَعْلَمُ نَفْسٌ مَّا أُخْفِيَ لَهُم مِّن قُرَّةِ أَعْيُنٍ جَزَاءً بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ

“ጀናህ” جَنَّة የሚለው ቃል “ጀነ” جَنَّ ማለትም “ተሰወረ” ወይም “ተደበቀ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን “ድብቅ” ወይም “ስውር” ማለት ነው፥ በጀነት ውስጥ ያለው ለሙሥሊሞች የተደበቀላቸውን ፀጋ ደግሞ ማንኛይቱም ነፍስ ስለማያውቅ ድብቅ እና ስውር ነው። በሐዲሰል ቁድሢይ ላይ የተዘጋጀው የጀነት ጸጋ ዓይን ዓይቶት፣ ጆሮ ሰምቶት፣ ልብ አስቦት የማያውቅ መሆኑ ተገልጿል፦
32፥17 ይሠሩትም በነበሩት ለመመንዳት ከዓይኖች መርጊያ ለእነርሱ የተደበቀላቸውን ጸጋ ማንኛይቱም ነፍስ አታውቅም፡፡ فَلَا تَعْلَمُ نَفْسٌ مَّا أُخْفِيَ لَهُم مِّن قُرَّةِ أَعْيُنٍ جَزَاءً بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 123:
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ ነብዩ”ﷺ” እንዲህ ብለው አሉ፦ "አላህም እንዲህ አለ፦ እኔ ለደጋግ ባሮቼ ዓይን ዓይቶት የማያውቅ፣ ጆሮ ሰምቶት የማያውቅ እና በሰው ልቦና ውል ብሎ የማያውቅ ጸጋን አዘጋጅቻለው”። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ قَالَ اللَّهُ أَعْدَدْتُ لِعِبَادِي الصَّالِحِينَ مَا لاَ عَيْنٌ رَأَتْ، وَلاَ أُذُنٌ سَمِعَتْ، وَلاَ خَطَرَ عَلَى قَلْبِ بَشَرٍ ‏”

ስለዚህ በጀነት ውስጥ ያሉትን አሏህ ለባሮቹ ያዘጋጃቸው ፀጋዎች ዓይን ዓይቶት፣ ጆሮ ሰምቶት፣ ልብ አስቦት የማያውቅ ከሆነ ሙዝ፣ ዘንባባ፣ ወይን፣ ተምር የመሳሰሉት የስም መመሳሰል እንጂ ቅርጽና ይዘቱ አሊያም ጥፍጥናውና ጣዕሙ ከዚህ ዓለም ጋር አንድ አይደለም፥ ይህንን አምላካችን አሏህ እንዲህ ይለናል፦
47፥15 የዚያች ጥንቁቆች ተስፋ የተሰጧት ገነት “ምሳሌ” በውስጧ ሺታው ከማይለወጥ ውሃ ወንዞች ጣዕሙ ከማይለውጥ ወተትም ወንዞች ለጠጪዎች ሁሉ ጣፋጭ ከኾነች የወይን ጠጅም ወንዞች፤ ከተነጠረ ማርም ወንዞች አሉባት፤ ለእነሱም በውስጧ ከፍሬዎች ሁሉ በያይነቱ ከጌታቸው ምሕረትም አላቸው። مَّثَلُ الْجَنَّةِ الَّتِي وُعِدَ الْمُتَّقُونَ ۖ فِيهَا أَنْهَارٌ مِّن مَّاءٍ غَيْرِ آسِنٍ وَأَنْهَارٌ مِّن لَّبَنٍ لَّمْ يَتَغَيَّرْ طَعْمُهُ وَأَنْهَارٌ مِّنْ خَمْرٍ لَّذَّةٍ لِّلشَّارِبِينَ وَأَنْهَارٌ مِّنْ عَسَلٍ مُّصَفًّى ۖ وَلَهُمْ فِيهَا مِن كُلِّ الثَّمَرَاتِ وَمَغْفِرَةٌ مِّن رَّبِّهِمْ ۖ كَمَنْ هُوَ خَالِدٌ فِي النَّارِ وَسُقُوا مَاءً حَمِيمًا فَقَطَّعَ أَمْعَاءَهُمْ
2፥25 ከእርሷ ከፍሬ ዓይነት ሲሳይን በተመገቡ ቁጥር ፍሬዎችዋ ስለሚመሳሰሉ «ይህ ያ ከአሁን በፊት የተገመብነው ነው» ይላሉ፡፡ እርሱንም ተመሳሳይ ኾኖ ተሰጣቸው*፡፡ ۖ كُلَّمَا رُزِقُوا مِنْهَا مِن ثَمَرَةٍ رِّزْقًا ۙ قَالُوا هَـٰذَا الَّذِي رُزِقْنَا مِن قَبْلُ ۖ وَأُتُوا بِهِ مُتَشَابِهًا ۖ وَلَهُمْ فِيهَا أَزْوَاجٌ مُّطَهَّرَةٌ ۖ وَهُمْ فِيهَا خَالِدُونَ

“መሰል” مَثَل ማለት “ምሳሌ” ማለት ሲሆን እዚህ ላይ የተዘረዘሩት ውኃ፣ ወተት፣ የወይን ጠጅም፣ ማር፣ ፍሬዎች “ምሳሌ” ናቸው፥ ምክንያቱም የዚህ ዓለም ውኃ ሲቆይ ይሸታል፣ ወተት ሲቆይ ረግቶ ይቀየራል፣ ማርና ወይንም ጥፍጥናው ይሰለቻል። ነገር ግን የጀነት ውኃ፣ ወተት፣ የወይን ጠጅም፣ ማር፣ ፍሬዎች ግን የተለየ ነው፥ የዚህ ዓለም ወይን ከቆየ ይቆመጥጥና ያሰክራል። ነገር ግን የጀነት ወይን ጠጅ አያሰክርም፦
56፥19 ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም። لَّا يُصَدَّعُونَ عَنْهَا وَلَا يُنزِفُونَ
37፥47 በእርሷ ዉስጥም ራስ ምታት የለባትም። እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም። لَا فِيهَا غَوْلٌ وَلَا هُمْ عَنْهَا يُنزَفُونَ

"ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! ስካር ራስምታ ያመጣል ወይም ውድቅ ንግግር ያናግራል አሊያም ወንጀል ያሠራል፥ ጀነት ውስጥ ያለው ወይን ግን ራስምታት የለውም፣ ውድቅ ንግግር አያናግርም እና ወንጀልም አያሠራም። ምክንያቱም ምንም አልኮል የሌለበት “ንጹህ” የሆነ ነው፦
52፥23 በውስጧ መጠጥን ይሰጣጣሉ፤ በውስጧ ውድቅ ንግግር እና ወንጀልም የለም። يَتَنَازَعُونَ فِيهَا كَأْسًا لَّا لَغْوٌ فِيهَا وَلَا تَأْثِيمٌ
76፥21 ጌታቸውም ንጹህ የሆኑን መጠጥ ያጠጣቸዋል። رَبُّهُمْ شَرَابًا طَهُورًا
የመጨረሻው አንቀጽ ላይ "ንጹህ" ለሚለው ቃል የገባው "ጦሁር" طَهُور ሲሆን ይህም ከአልኮልነት ነጻ የሆነ የተጣራ ወይን መሆኑን ቁልጭ አርጎ ያሳያል፥ ይህ ምንም አልኮል የሌለበት ወይን "ረሒቅ" رَّحِيق ይባላል፦
83፥25 ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ። يُسْقَوْنَ مِن رَّحِيقٍ مَّخْتُومٍ

"ተጣርቶ" ለሚለው ቃል የገባው "ጦሁር" طَهُور ሲሆን ይህም ንጹህ ወይን መበረጃው "ካፉር" ነው፥ "ካፉር" كَافُور የሚለው ቃል "ከፈረ" كَفَّرَ ማለትም "ሸፈነ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ሽፍን" ማለት ነው፦
76፥5 በጎ አድራጊዎች መበረዣዋ ካፉርው ከሆነች ጠጅ ይጠጣሉ። إِنَّ الْأَبْرَارَ يَشْرَبُونَ مِن كَأْسٍ كَانَ مِزَاجُهَا كَافُورًا

ጀነት ውስጥ ያለው ወይን ዓይን ዓይቶት፣ ጆሮ ሰምቶት፣ ልብ አስቦት የማያውቅ ስለሆነ ካፉር ተብሏል፥ በተጨማሪም "ኸምር" خَمْرየሚለው ቃል "ኸመረ" خَمَرَ ማለትም "ሸፈነ" "ደበቀ" "ሰወረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ "ሽፍን" "ድብቅ" "ስውር" መሆኑ በራሱ የጀናህ ወይን ዓይን ዓይቶት፣ ጆሮ ሰምቶት፣ ልብ አስቦት የማያውቅ መሆኑን አመላካች ነው። እኅቶቻችን ከሚሰተሩበት ሒጃብ መካከል "ጉፍታ" እራሱ በቁርኣን "ኺማር" خِمَار ይባላል፦
24፥31 ጉፍታዎቻቸውንም በአንገትጌዎቻቸው ላይ ያጣፉ። وَلْيَضْرِبْنَ بِخُمُرِهِنَّ عَلَىٰ جُيُوبِهِنَّ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ጉፍታዎች" ለሚለው በብዜት የገባው ቃል "ኹሙር" خُمُر ሲሆን በነጠላ ደግሞ "ኺማር" خِمَار ነው፥ “ኺማር” خِمَار የሚለው ቃል ልክ እንደ “ኸምር” خَمْر ሥርወ-ቃሉ “ኸመረ” خَمَرَ ነው። ጉፍታ ራስን ስለሚሸፍን “ኺማር” خِمَار እንሚባል ሁሉ ጀነት ውስጥ ያለው ወይን ከሰው ዕውቀት የተደበቀ ስለሆነ "ኸምር" خَمْر ይባላል። በተመሳሳይ ይህ ወይን መበረጃው "ዘንጀቢል" زَنجَبِيل “እና "ተሥኒም" تَسْنِيم ነው፦
76፥17 በእርሷም መበረዣዋ ዘንጀቢል የሆነችን ጠጅ ይጠጣሉ። وَيُسْقَوْنَ فِيهَا كَأْسًا كَانَ مِزَاجُهَا زَنجَبِيلًا
83፥27 መበረዣውም ከተሥኒም ነው። وَمِزَاجُهُ مِن تَسْنِيمٍ

ሚሽነሪዎች፦ "እሺ የጀነት ወይን የማያሳክር ከሆነ እንዴት ጀነት ውስጥ ይኖራል?" ብለው ይጠይቃሉ፥ ምነው በእናንተ መንግሥተ ሰማይ ውስጥ የሚበላ ዛፍ እና የሚጠጣ ወይን የለም እንዴ? አንብቡት፦
ማቴዎስ 26፥29 ነገር ግን እላችኋለሁ በአባቴ መንግሥት ከእናንተ ጋር አዲሱን ወይን ፍሬ እስከምጠጣበት እስከዚያ ቀን ድረስ ከዛሬ ጀምሬ ከዚህ ከወይን ፍሬ አልጠጣም። But I say unto you, I will not drink henceforth of this fruit of the vine, until that day when I drink it new vine with you in my Father’s kingdom.
ራእይ 2፥7 ድል ለነሣው በእግዚአብሔር ገነት ካለው ከሕይወት ዛፍ እንዲበላ እሰጠዋለሁ።

በመንግሥተ ሰማይ ወይም በገነት መብላት እና መጠጣት ብቻ ሳይሆን መብል እና መጠጥ መኖሩ በራሱ ቁርኣንን ለመተቸት ሞራል እና ዐቅም ያሳጣችኃል። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የጣዖታውያን ዲን

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

109፥6 ለእናንተ ሃይማኖታችሁ አላችሁ፡፡ ለእኔም ሃይማኖቴ አለኝ፡፡ لَكُمْ دِينُكُمْ وَلِيَ دِينِ

አምላካችን አሏህ ለነቢያች"ﷺ" "ለእናንተ ሃይማኖታችሁ አላችሁ፡፡ ለእኔም ሃይማኖቴ አለኝ" በል በማለት ለከሓዲዎች እንዲናገሩ አዟቸዋል፦
109፥1 በላቸው፦ "እናንተ ከሓዲዎች ሆይ! قُلْ يَا أَيُّهَا الْكَافِرُونَ
109፥6 ለእናንተ ሃይማኖታችሁ አላችሁ፡፡ ለእኔም ሃይማኖቴ አለኝ፡፡ لَكُمْ دِينُكُمْ وَلِيَ دِينِ

"ለእኔም ሃይማኖቴ አለኝ" ሲሉ ይህ ሃይማኖት ዲኑል ኢሥላም ነው፥ "ለእናንተ ሃይማኖታችሁ አላችሁ" ሲሉ ጣዖታውያኑ የነበራቸው ሃይማኖት ምንድን ነው? "ዲን" دِين የሚለው ቃል "ዳነ" دَانَ ማለትም "ፈረደ" "ደነገገ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ፍርድ" "ሕግ" ማለት ነው፦
1፥4 የፍርዱ ቀን ባለቤት ለኾነው፡፡ مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ
12፥76 አላህ ባልሻ ኖሮ በንጉሡ "ሕግ" ወንድሙን ሊይዝ አይገባውም ነበር፡፡ كَانَ لِيَأْخُذَ أَخَاهُ فِي دِينِ الْمَلِكِ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ

እነዚህ አናቅጽ ላይ "ፍርድ" "ሕግ" ለሚለው የገባው ቃል "ዲን" دِين መሆኑ ልብ አድርግ! ጣዖታውያን የነበራቸው ፍርድ እና ሕግ የሚያገኙት ከሸያጢን ነበር፦
6፥121 በእርሱም ላይ የአላህ ስም ካልተጠራበት ነገር አትብሉ፡፡ እርሱም በእርግጥ አመጽ ነው፡፡ ሰይጣናትም ወደ ወዳጆቻቸው በክትን በመብላት ይከራከሯችሁ ዘንድ ያሾከሹካሉ፡፡ ብትታዘዙዋቸውም እናንተ በእርግጥ አጋሪዎች ናችሁ፡፡ وَلَا تَأْكُلُوا مِمَّا لَمْ يُذْكَرِ اسْمُ اللَّهِ عَلَيْهِ وَإِنَّهُ لَفِسْقٌ ۗ وَإِنَّ الشَّيَاطِينَ لَيُوحُونَ إِلَىٰ أَوْلِيَائِهِمْ لِيُجَادِلُوكُمْ ۖ وَإِنْ أَطَعْتُمُوهُمْ إِنَّكُمْ لَمُشْرِكُونَ

ሸያጢን ለወዳጆቻቸው መገለጥ በመስጠት በክትን እንዲበሉ ይነግሯቸው ነበር፥ እነዚህም ወዳጆቻቸው ጣዖታውያን ናቸው። "ያሾከሹካሉ" ለሚለው የገባው ቃል "ለዩሑነ" لَيُوحُونَ ሲሆን ሥርወ-ቃሉ "አውሓ" أَوْحَىٰٓ ማለትም "ገለጠ" ነው፥ የጣዖታውያኑ ዲን ከሸያጢን የተገለጠ ነው፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 121
ዐብደሏህ ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ "ጥቂት ሰዎች ወደ ነቢዩ"ﷺ" በመምጣት፦ "የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! የገደልነውን መብላት እንችላለን፥ ነገር ግን አሏህ የገደለውን የማንበላው ለምንድን ነው? አሉ፥ አሏህም፦ "በእርሱም ላይ የአላህ ስም ካልተጠራበት ነገር አትብሉ" የሚለውን አንቀጽ "ብትታዘዙዋቸውም እናንተ በእርግጥ አጋሪዎች ናችሁ" እስከሚለው አወረደ"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ أَتَى أُنَاسٌ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم فَقَالُوا يَا رَسُولَ اللَّهِ أَنَأْكُلُ مَا نَقْتُلُ وَلاَ نَأْكُلُ مَا يَقْتُلُ اللَّهُ فَأَنْزَلَ اللَّهُ ‏(‏ وَلَا تَأْكُلُوا مِمَّا لَمْ يُذْكَرِ اسْمُ اللَّهِ عَلَيْهِ)‏ إِلَى قَوْلِهِ ‏:‏ ‏(‏وَإِنْ أَطَعْتُمُوهُمْ إِنَّكُمْ لَمُشْرِكُونَ ‏)‏ ‏.‏

ጣዖታውያኑ "በክትን ብሉ" የሚል ሑክም የሚቀበሉት ከሸያጢን ስለሆነ የጣዖታውያኑ ዲን ይህ ነው፥ ጣዖታውያኑ ከሸያጢን የሚቀበሉትን ሑክም የሚታዘዝ ሰው በአሏህ ሐቅ ማሻረክ ስለሆነ ጣዖታውያኑን የሚታዘዝ በእርግጥ "ሙሽሪክ" مُشْرِك ነው። ታዲያ ዛሬ ያሉትን ምዕራባውያን "ወንድ እና ወንድ፣ ሴት እና ሴት፣ ወላጅ እና ልጅ መጋባት ሐላል ነው" ሲሉ እሺ ማለት አያስከፍርምን? ይህስ መገለጥ ከሸያጢን አይደለምን? "ሰው እና እንስሳ መጋባት ሐላል ይሁንልን" የሚል ወረቀት በፓርላማ ገብቷል፥ ከጸደቀ ደግሞ ምን ዓይነት ፍጥረት ሊፈጠር እንደሚችል አስቡት! ይህ ጣጉት ቤተሰብ ለማፈራረስ የተነሳ ነው፦
42፥21 ከሃይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነርሱ የደነገጉ ተጋሪዎች ለእነርሱ አሏቸውን? أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ شَرَعُوا لَهُم مِّنَ الدِّينِ مَا لَمْ يَأْذَن بِهِ اللَّهُ

"ሸሪክ" شَرِيك ማለት "ተጋሪ" ማለት ነው፥ የሸሪክ ብዙ ቁጥር ደግሞ "ሹረካእ" شُرَكَاء ሲሆን "ተጋሪዎች" ማለት ነው፥ አሏህ በእርሱ ያልፈቀደውን ነገር ሐላል ማድረግ ለእነርሱ የደነገጉ በአላህ ሐቅ ላይ ተጋሪዎች አሏቸው። "የደነገጉ" ለሚለው የገባው ቃል "ሸረዑ" شَرَعُوا ሲሆን ሸሪዓህ መደንገጋቸው የሚያሳይ ቃል ነው፥ ለዚህ ነው "ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው" ነው ያለው። አሏህ ከዲሞክራሲያህ ጣጉት ይጠብቀን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ነፍስ መግደል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

17፥33 ያቺንም አላህ እርም ያረጋትን ነፍስ ያለ ሕግ አትግደሉ፡፡ وَلَا تَقْتُلُوا النَّفْسَ الَّتِي حَرَّمَ اللَّهُ إِلَّا بِالْحَقِّ

ኢሥላም ሰም እና ወርቅ የያዘ ቅኔ ነው፥ ሰሙ ሐቅ ሲሆን ወርቁ ፍትሕ ነው። “ቂሷስ” قِصَاص የሚለው ቃል “ቋሶ” قَاصَّ ማለትም “አመሳሰለ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ማመሳሰል” ማለት ነው፥ በቂሷስ ነፍስ ያጠፋ ነፍሱ ይጠፋል፣ ዓይን ያጠፋ ዓይኑ ይጠፋል፣ አፍንጫም ያጠፋ አፍንጫው ይጠፋል፣ ጆሮም ያጠፋ ጆሮው ይጠፋል፣ ጥርስ የሰበረ ጥርሱ ይሰበራል። እነዚህ ቁስሎችን በቂሷስ ይፈታሉ፦
5፥45 *”በእነርሱም ላይ በውስጧ፦ «ነፍስ በነፍስ ዓይንም በዓይን አፍንጫም በአፍንጫ ጆሮም በጆሮ ጥርስም በጥርስ ይያዛል፥ ቁስሎችንም “ማመሳሰል” አለባቸው» ማለትን ጻፍን*፡፡ وَكَتَبْنَا عَلَيْهِمْ فِيهَا أَنَّ النَّفْسَ بِالنَّفْسِ وَالْعَيْنَ بِالْعَيْنِ وَالْأَنفَ بِالْأَنفِ وَالْأُذُنَ بِالْأُذُنِ وَالسِّنَّ بِالسِّنِّ وَالْجُرُوحَ قِصَاصٌ

አሁንም እዚህ አንቀጽ ላይ “ማመሳሰል” ለሚለው ቃል የገባው “ቂሷስ” قِصَاص መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። መጥፎ ለሠሩ ሠዎች መጥፎ ቅጣት መቅጣት ቂሷስ ነው፥ የአሏህ መጽሐፍ ጭብጡ ቂሷስ ነው፦
42፥40 *የመጥፎም ነገረ ዋጋ ብጤዋ መጥፎ ናት፡፡ ይቅርም ያለና ያሳመረ ሰው ምንዳው በአላህ ላይ ነው፡፡ እርሱ በደለኞችን አይወድም*፡፡ وَجَزَاءُ سَيِّئَةٍ سَيِّئَةٌ مِّثْلُهَا ۖ فَمَنْ عَفَا وَأَصْلَحَ فَأَجْرُهُ عَلَى اللَّهِ ۚ إِنَّهُ لَا يُحِبُّ الظَّالِمِينَ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 26
አነሥ እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”የአሏህ መጽሐፍ ቂሷስ ነው”*። أَنَّ أَنَسًا، حَدَّثَهُمْ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ كِتَابُ اللَّهِ الْقِصَاصُ ‏”‌‏.‏

ከዚህ ሕግ ውጪ ነፍስን መግደል አሏህ እርም አድርጓል፥ ያለ ቂሷስ ነፍስን መግደል ሐራም እና ከዐበይት ኃጢአቶች አንዱ ነው፦
17፥33 *”ያቺንም አላህ እርም ያረጋትን ነፍስ ያለ ሕግ አትግደሉ”*፡፡ وَلَا تَقْتُلُوا النَّفْسَ الَّتِي حَرَّمَ اللَّهُ إِلَّا بِالْحَقِّ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 83, ሐዲስ 53
ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምሪው እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ *”ዐበይት ኃጢአቶች በአሏህ ላይ ማሻረክ፣ ወላጆችን አለማክበር፣ ነፍስን መግደል እና የውሸት መሓላ ናቸው”*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ الْكَبَائِرُ الإِشْرَاكُ بِاللَّهِ، وَعُقُوقُ الْوَالِدَيْنِ، وَقَتْلُ النَّفْسِ، وَالْيَمِينُ الْغَمُوسُ ‏”‌‏.‏
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 86, ሐዲስ 80
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ሰባት አጥፊ ወንጀሎችን አስወግዱ! ሶሓባዎችም፦ "የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! እነርሱ ምንድን ናቸው? አሉ። እርሳቸውም፦ "በአሏህ ላይ ማጋራት፣ መተት፣ አሏህ እርም ያረጋትን ነፍስ ያለ ሕግ መግደል፣ ወለድ መብላት፣ የየቲሞችን ገንዘብ መብላት፣ በፍልሚያ ወቅት ማፈግፈግ እና ጥብቅ የሆኑ ምእመናትን በዝሙት መወንጀል ነው" አሉ*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏"‏ اجْتَنِبُوا السَّبْعَ الْمُوبِقَاتِ ‏"‌‏.‏ قَالُوا يَا رَسُولَ اللَّهِ وَمَا هُنَّ قَالَ ‏"‏ الشِّرْكُ بِاللَّهِ، وَالسِّحْرُ، وَقَتْلُ النَّفْسِ الَّتِي حَرَّمَ اللَّهُ إِلاَّ بِالْحَقِّ، وَأَكْلُ الرِّبَا، وَأَكْلُ مَالِ الْيَتِيمِ، وَالتَّوَلِّي يَوْمَ الزَّحْفِ، وَقَذْفُ الْمُحْصَنَاتِ الْمُؤْمِنَاتِ الْغَافِلاَتِ ‏"‌‏.‏

“እርም ያረጋት” ለሚለው የገባው ቃል “ሐረመ” حَرَّمَ መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። “ሐራም” حَرَام የሚለው ቃል እራሱ “ሐረመ” حَرَّمَ ማለትም “ከለከለ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “የተከለከለ” ማለት ነው፥ እንደውም ያለጥፋት አንድን ሰው መግደል ሰዎችን ሁሉ እንደገደለ ነው፦
5፥32 *”በዚህ ምክንያት በእስራኤል ልጆች ላይ እነሆ ያለ ነፍስ መግደል ወይም በምድር ላይ ያለማጥፋት ካልሆነ በስተቀር ነፍስን የገደለ ሰው ሰዎቹን ሁሉ እንደገደለ ነው፥ ሕያው ያደረጋትም ሰው ሰዎቹን ሁሉ ሕያው እንዳደረገ ነው”* ማለትን ጻፍን፡፡ مِنْ أَجْلِ ذَٰلِكَ كَتَبْنَا عَلَىٰ بَنِي إِسْرَائِيلَ أَنَّهُ مَن قَتَلَ نَفْسًا بِغَيْرِ نَفْسٍ أَوْ فَسَادٍ فِي الْأَرْضِ فَكَأَنَّمَا قَتَلَ النَّاسَ جَمِيعًا وَمَنْ أَحْيَاهَا فَكَأَنَّمَا أَحْيَا النَّاسَ جَمِيعًا

ከዚህ ውጪ ወሰን ታልፎባቸው ለእነዚያ ለሚገደሉት ምእመናን እነርሱ የተበደሉ በመኾናቸው መጋደል ተፈቀደላቸው፦
22፥39 *”ለእነዚያ ለሚገደሉት ምእመናን እነርሱ የተበደሉ በመኾናቸው መጋደል ተፈቀደላቸው፡፡ አላህም እነርሱን በመርዳት ላይ በእርግጥ ቻይ ነው”*፡፡ أُذِنَ لِلَّذِينَ يُقَاتَلُونَ بِأَنَّهُمْ ظُلِمُوا ۚ وَإِنَّ اللَّهَ عَلَىٰ نَصْرِهِمْ لَقَدِيرٌ

አንቀጹ ይቀጥልና ሲበደሉ በቂሷስ ፍትሕ የሚያስተካክሉ አካላት ከሌሉ ገዳማት፣ ቤተክርስቲያኖችም፣ ምኩራቦችም እና በውስጣቸው የአላህ ስም በብዛት የሚወሳባቸው መስጊዶችም ይፈርሳሉ፦
22፥40 ለእነዚያ «ጌታችን አላህ ነው» ከማለታቸው በስተቀር ያለ አግባብ ከአገራቸው የተባረሩ ለሆኑት ተፈቀደ፡፡ *”አላህ ሰዎችን ከፊላቸውን በከፊሉ መገፍተሩ ባልነበረ ኖሮ ገዳማት፣ ቤተክርስቲያኖችም፣ ምኩራቦችም እና በውስጣቸው የአላህ ስም በብዛት የሚወሳባቸው መስጊዶችም በተፈረሱ ነበር*”፡፡ አላህም ሃይማኖቱን የሚረዳውን ሰው በእርግጥ ይረዳዋል፡፡ አላህ ብርቱ አሸናፊ ነውና፡፡ الَّذِينَ أُخْرِجُوا مِن دِيَارِهِم بِغَيْرِ حَقٍّ إِلَّا أَن يَقُولُوا رَبُّنَا اللَّهُ ۗ وَلَوْلَا دَفْعُ اللَّهِ النَّاسَ بَعْضَهُم بِبَعْضٍ لَّهُدِّمَتْ صَوَامِعُ وَبِيَعٌ وَصَلَوَاتٌ وَمَسَاجِدُ يُذْكَرُ فِيهَا اسْمُ اللَّهِ كَثِيرًا ۗ وَلَيَنصُرَنَّ اللَّهُ مَن يَنصُرُهُ ۗ إِنَّ اللَّهَ لَقَوِيٌّ عَزِيزٌ
ስለዚህ ገዳማት፣ ቤተክርስቲያኖችም፣ ምኩራቦችም እና መስጊዶች ማፍረስ ወሰን ማለፍ ነው። “አላህ ሰዎችን ከፊላቸውን በከፊሉ መገፍተሩ” የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! አንደኛው በሌላኛ ፍትሕ ለማስከበር መገፍተሩ ማለትም መጋደል ከሌለ ወሰን አላፊዎች ምድሩቱን ያበላሻሉ። በቂሷስ እነዚያንም ወሰን አላፊዎች በአላህ መንገድ ተጋደሉ! ወሰንንም አትለፉ! አላህ ወሰን አላፊዎን አይወድምና፦
2፥190 *እነዚያንም የሚጋደሉዋችሁን በአላህ መንገድ ተጋደሉ፡፡ ወሰንንም አትለፉ፤ አላህ ወሰን አላፊዎን አይወድምና*፡፡ وَقَاتِلُوا فِي سَبِيلِ اللَّهِ الَّذِينَ يُقَاتِلُونَكُمْ وَلَا تَعْتَدُوا ۚ إِنَّ اللَّهَ لَا يُحِبُّ الْمُعْتَدِينَ

የአልረሕማንም ባሮች ያችንም አላህ እርም ያደረጋትን ነፍስ ያለ ቂሷስ ሕግ የማይገድሉ ናቸው፥ ነገር ግን ያችንም አላህ እርም ያደረጋትን ነፍስ ያለ ቂሷስ ሕግ በመግደል ይህንንም የሚሠራ ሰው ከዱንያ ፍርድ ቢያመልጥ በአኺራ ከአሏህ ቅጣትን ያገኛል፦
25፥68 *”እነዚያም ምእመናን ከአላህ ጋር ሌላን አምላክ የማይገዙት፣ ያችንም አላህ እርም ያደረጋትን ነፍስ ያለ ሕግ የማይገድሉት፣ የማያመነዝሩትም ናቸው፡፡ ይህንንም የሚሠራ ሰው ግን ቅጣትን ያገኛል”*፡፡ وَالَّذِينَ لَا يَدْعُونَ مَعَ اللَّهِ إِلَـٰهًا آخَرَ وَلَا يَقْتُلُونَ النَّفْسَ الَّتِي حَرَّمَ اللَّهُ إِلَّا بِالْحَقِّ وَلَا يَزْنُونَ ۚ وَمَن يَفْعَلْ ذَٰلِكَ يَلْقَ أَثَامًا

የእሥልምና አስተምህሮት ይህ ነው። ሰሞኑን በሁለቱም ጽንፈኞች በፋኖ እና በሾኔ እየተገደለ ያለው ሙሥሊሙ መሆኑ በጣም ቢያምም ቅሉ ግን ማንም ሰው ያለ ሕግ መገደል ይቅርና ጉንፋን እንዲያመው እሥልምናችን አያስተምርም።
አሏህ ለሁላችንም ሂዳያህ ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ብርዘት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

2፥75 ከእነርሱ የኾኑ ጭፍሮች የአላህን ንግግር የሚሰሙ እና ከዚያም ከተረዱት በኋላ እነርሱ እያወቁ “የሚለውጡት” ሲኾኑ ለእናንተ ማመናቸውን ትከጅላላችሁን?” أَفَتَطْمَعُونَ أَن يُؤْمِنُوا لَكُمْ وَقَدْ كَانَ فَرِيقٌ مِّنْهُمْ يَسْمَعُونَ كَلَامَ اللَّهِ ثُمَّ يُحَرِّفُونَهُ مِن بَعْدِ مَا عَقَلُوهُ وَهُمْ يَعْلَمُون

"ተሕሪፍ" تَحْرِيف የሚለው ቃል "ሐረፈ" حَرَّفَ ማለትም "በረዘ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ብርዘት"corruption" ማለት ነው፥ የመጽሐፉ ሰዎች አይሁዳውያን እና ክርስቲያኖች ከአሏህ ዘንድ የወረደውን እውነት በውሸት መቀላቀላቸው ብርዘት ይባላል፦
3፥71 የመጸሐፉ ሰዎች ሆይ! እዉነቱን በዉሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ? እዉነቱንም እናንተ የምታወቁ ስትሆኑ ለምን ትደብቃላችሁ? يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لِمَ تَلْبِسُونَ ٱلْحَقَّ بِٱلْبَٰطِلِ وَتَكْتُمُونَ ٱلْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ

ከአሏህ ዘንድ የወረደው እውነት ሆኖ ሳለ ውሸቱ ደግሞ መጽሐፉን በእጆቻቸው ጽፈው «ይህ ከአሏህ ዘንድ ነው» ማለታቸው ነው፦
2፥79 ለነዚያም መጽሐፉን በእጆቻቸው ለሚጽፉ እና ከዚያም በርሱ ጥቂትን ዋጋ ሊገዙበት «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» ለሚሉ ወዮላቸው፡፡ ለእነርሱም ከዚያ እጆቻቸው ከጻፉት ወዮላቸው፡፡ ለእነርሱም ከዚያ ከሚያፈሩት ኃጢኣት ወዮላቸው፡፡ فَوَيْلٌۭ لِّلَّذِينَ يَكْتُبُونَ ٱلْكِتَٰبَ بِأَيْدِيهِمْ ثُمَّ يَقُولُونَ هَٰذَا مِنْ عِندِ ٱللَّهِ لِيَشْتَرُوا۟ بِهِۦ ثَمَنًۭا قَلِيلًۭا ۖ فَوَيْلٌۭ لَّهُم مِّمَّا كَتَبَتْ أَيْدِيهِمْ وَوَيْلٌۭ لَّهُم مِّمَّا يَكْسِبُونَ

"ለሚጽፉ" የሚለው ቃል "የክቱቡነ" يَكْتُبُونَ ሲሆን ከላይ ያለውን ሲያቅ ስንከተል የአሏህን ንግግር እያወቁ መበረዛቸውን ያሳያል፥ "ሢያቅ" سِيَاق ማለት "ዐውድ"context" ማለት ሲሆን የሡረቱል በቀራህ 2፥79 ዐውደ ንባቡን"contextual passege" እና ክፍለ ንባቡን"paragraphical passage" ስንከተል የበረዙት የአሏህን ንግግር መሆኑን በቀላሉ እንረዳለን፦
2፥75 ከእነርሱ የኾኑ ጭፍሮች የአላህን ንግግር የሚሰሙ እና ከዚያም ከተረዱት በኋላ እነርሱ እያወቁ “የሚለውጡት” ሲኾኑ ለእናንተ ማመናቸውን ትከጅላላችሁን?” أَفَتَطْمَعُونَ أَن يُؤْمِنُوا لَكُمْ وَقَدْ كَانَ فَرِيقٌ مِّنْهُمْ يَسْمَعُونَ كَلَامَ اللَّهِ ثُمَّ يُحَرِّفُونَهُ مِن بَعْدِ مَا عَقَلُوهُ وَهُمْ يَعْلَمُون

እዚህ አንቀጽ ላይ "የሚለውጡ" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ዩሐረፉነ" يُحَرِّفُونَ ሲሆን "የሚበርዙት" ማለት ነው፥ "ዩሐረፉ" يُحَرِّفُ የሚለው በሙሥተቅበል የመጣ አላፊ ግሥ "ሐረፈ" حَرَّفَ ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ እንደሆነ አንባቢ ልብ ይለዋል። "ዩሐረፉነ" يُحَرِّفُونَ በሚል መዳረሻ ላይ "ሁ" هُ የሚለው ተሳቢ ተውላጠ ስም "ከላመል ሏህን" ያመለክታል፥ "ከላመል ሏህን" كَلَامَ اللَّه ማለት "የአሏህ ንግግር" ማለት ነው። በተዛማች ሙግት"textual approach" ስንመለከት ደግሞ የአሏህን ንግግር ከሥፍራው በሌላ የሰው ቃል ይበርዛሉ፦
5፥13 ቃል ኪዳናቸውንም በማፍረሳቸው ረገምናቸው፡፡ ልቦቻቸውንም ደረቆች አደረግን፡፡ ቃላትን ከቦታዎቻቸው ይለውጣሉ፡፡ فَبِمَا نَقْضِهِم مِّيثَاقَهُمْ لَعَنَّاهُمْ وَجَعَلْنَا قُلُوبَهُمْ قَاسِيَةً ۖ يُحَرِّفُونَ الْكَلِمَ عَن مَّوَاضِعِهِ

"ከሊም" كَلِم የሚለው ቃል "ከሊማህ" كَلِمَة ለሚለው ጀምዕ እና "ከላም" كَلَام ለሚለው ቃል ሙአነስ ነው። ይህ የብርዘት ሂደት "አት-ተሕሪፉል ለፍዝ" ٱلْتَحْرِيف ٱلْلَفْظ ይባላል፥ "ለፍዝ" لَفْظ ማለት "ቃል"Verbatim” ማለት ነው።

የመጽሐፉ ሰዎች ብርዘታቸው በዚህ አላበቃም፥ በመጽሐፉ ያለውን ንግግር ለማለት ያልፈለገውን "እንዲህ ለማለት ፈልጎ ነው" በማለት እየተረጎሙ ቋንቋውን ያጣምማሉ፦
3፥78 ከእነሱም እርሱ ከመጽሐፉ ያይደለ ሲኾን ከመጽሐፉ መኾኑን እንድታስቡ በመጽሐፉ ምላሶቻቸውን የሚያጣምሙ ክፍሎች አሉ፡፡ እርሱ ከአላህ ዘንድ ያልኾነ ሲኾን «እርሱ ከአላህ ዘንድ ነውም» ይላሉ፡፡ እነርሱ የሚያውቁ ሲኾኑም በአላህ ላይ ውሸትን ይናገራሉ፡፡ وَإِنَّ مِنْهُمْ لَفَرِيقًا يَلْوُونَ أَلْسِنَتَهُم بِالْكِتَابِ لِتَحْسَبُوهُ مِنَ الْكِتَابِ وَمَا هُوَ مِنَ الْكِتَابِ وَيَقُولُونَ هُوَ مِنْ عِندِ اللَّهِ وَمَا هُوَ مِنْ عِندِ اللَّهِ وَيَقُولُونَ عَلَى اللَّهِ الْكَذِبَ وَهُمْ يَعْلَمُونَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ምላስ" ለሚለው የገባው ቃል "ሊሣን" لِسَان ሲሆን "ቋንቋ" ማለት ነው፥ ቃሉ የወረደበትን ቋንቋ ወደ ሌላ ቋንቋ በመተርጎም እና ሙዳየ ቃላት"dictionary" በማበጀት መልእክቱን በትርጉም"interpretation" ያጣምማሉ። ሁለተኛ "ሊሣን" لِسَان ማለት "ምላስ" ማለት ሲሆን ዐውደ-ንባቡ ለማለት ያልፈለገውን እጁን ጠምዝዞ "እንዲህ ለማለት ነው" ብሎ በምላስ ማጣመም “ስሑት ትርጓሜ” ወይም “ሰጊጎት”Eisegesis” ይባላል። በምላስ ሆነ በቋንቋ የሚተረጎመውን አተረጓጎም ከአሏህ ዘንድ ያልኾነ ሲኾን «እርሱ ከአሏህ ዘንድ ነው» ይላሉ፡፡ ይህ የብርዘት ሂደት "አት-ተሕሪፉል መዕና" ٱلْتَحْرِيف ٱلْمَعْنًى ይባላል፥ "መዕና" مَعْنًى ማለት "መልእክት" "እሳቤ" "አሳብ"notion" ማለት ነው። የመጽሐፉ ሰዎች ክርስቲያን እና አይሁድ አሳላጭ በመሆን በመጻሕፍት ውስጥ ስርዋጽ በማሳለጥ አስገብተዋል፥ ስርዋጽ ማለት በመቀነስ እና በመጨመር እንዲሁ የሌለን እንዳለ በማስመሰል መበረዝ ነው። አሏህ ከመጽሐፉ ሰዎች ፈሣድ ይጠብቀን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ማዛጋት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

24፥21 እርሱ በመጥፎ እና በሚጠላ ነገር ያዛልና፡፡ فَإِنَّهُ يَأْمُرُ بِالْفَحْشَاءِ وَالْمُنكَرِ

አምላካችን አሏህ መጥፎ ነገር እንድናደርግ አያዝም፥ ከዚያ ይልቅ በመልካም ነገር ያዛል። በተቃራኒው ከፈሕሻእ እና ከሙንከር ይከለክላል፦
7፥28 «አላህ በመጥፎ ነገር አያዝም፡፡ በአላህ ላይ የማታውቁትን ትናገራላችሁን» በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّ اللَّهَ لَا يَأْمُرُ بِالْفَحْشَاءِ ۖ أَتَقُولُونَ عَلَى اللَّهِ مَا لَا تَعْلَمُونَ
16፥90 አላህ በማስተካከል፣ በማሳመርም እና ለዝምድና ባለቤት በመስጠትም ያዛል፡፡ ከመጥፎ እና ከሚጠላም ነገር ሁሉ፣ ከመበደልም ይከለክላል፡፡ إِنَّ اللَّهَ يَأْمُرُ بِالْعَدْلِ وَالْإِحْسَانِ وَإِيتَاءِ ذِي الْقُرْبَىٰ وَيَنْهَىٰ عَنِ الْفَحْشَاءِ وَالْمُنكَرِ وَالْبَغْيِ

"ፈሕሻእ" فَحْشَاء ማለት "መጥፎ" ማለት ሲሆን "ሙንከር" مُنكَر ደግሞ "የሚጠላ" ማለት ነው፥ ፈሕሻእ እና ሙንከር የሸይጧን እርምጃዎች ናቸው። ሸይጧን በፈሕሻእ እና በሙንከር ያዛልና፦
24፥21 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የሰይጣንን እርምጃዎች አትከተሉ፡፡ የሰይጣንንም እርምጃዎች የሚከተል ሰው ኀጢአትን ተሸከመ፡፡ እርሱ(ሰይጣን) በመጥፎ እና በሚጠላ ነገር ያዛልና፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا لَا تَتَّبِعُوا خُطُوَاتِ الشَّيْطَانِ ۚ وَمَن يَتَّبِعْ خُطُوَاتِ الشَّيْطَانِ فَإِنَّهُ يَأْمُرُ بِالْفَحْشَاءِ وَالْمُنكَرِ ۚ

ስለዚህ አንድ ድርጊት "ከአሏህ ነው" ማለት "ሐላል ነው" ማለት ሲሆን "ከሸይጧን ነው" ማለት ደግሞ "ሐራም ነው" ማለት ነው። እዚህ ድረስ ከተግባባን ማስነጠስ ከአሏህ ነው፥ ማዛጋት ደግሞ ግን ከሸይጧን ነው፦
ጃሚዒ አት-ተርሚዚይ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 16
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ ሲሉ አሉ፦ "ማስነጠስ ከአሏህ ነው፥ ማዛጋት ግን ከሸይጧን ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ الْعُطَاسُ مِنَ اللَّهِ وَالتَّثَاؤُبُ مِنَ الشَّيْطَانِ

"ማዛጋት ግን ከሸይጧን ነው" ማለት "ማዛጋት ሐራም ነው" ማለት ሲሆን ማዛጋት ክልክልነቱ ኢሥቲስናእ ሆኖ የመጣ ነው፥ ኢሥቲስናእ" اِسْتِثْنَاء‏ ማለት "ፍትቅታ"exceptional" ማለት ሲሆን ማዛጋት ክልክልነቱ በሶላት ውስጥ ነው፦
ጃሚዒ አት-ተርሚዚይ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 222
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ አሉ፦ "ማዛጋት በሶላት ውስጥ ከሸይጧን ነው፥ ከእናንተ አንደኛችሁ የሚያዛጋ በተቻለ መጠን ያፍነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ التَّثَاؤُبُ فِي الصَّلاَةِ مِنَ الشَّيْطَانِ فَإِذَا تَثَاءَبَ أَحَدُكُمْ فَلْيَكْظِمْ مَا اسْتَطَاعَ ‏"‏ ‏

ሶላት ክቡር እና ክቡድ ሲሆን በሶላት ውስጥ የሚረብሽ ነገር መቆጣጠር አለብን፥ ማዛጋት በማፈን የምንጎዳን የጤና እክል ስለሌለው እና በሶላት ውስጥ ማፈን ለሶላታችን ጥቅም አለው። በሶላት ውስጥ ማዛጋትን ማፈን ሲቻል ማስነጠስን ማፈን ግን ፈጽሞ ከባድ ነው፥ ማስነጠስን ማፈን ከጤና አንጻር ወደ ታምቡር ስብራት ሊያመራ ይችላል። ምክንያቱም ማስነጠስን ማፈን ኃይለኛ የአየር ፍሰት በአፍንጫው በኩል አይወጣም፣ ወደ ውጭ ያልወጡ በሽታ አምጪ ተህዋሲያን ማይክሮቦች ወደ ጆሮው ክፍል ውስጥ ይገባሉ፣ የደም ሥሮች መሰባበር እና አልፎ አልፎም ዓይነ ስውርነትን ያስከትላል። ይህ ጉዳት ስላለው በሶላት ውስጥ ማስነጠስ እና "አል-ሓምዱ ሊሏህ" ማለት ሐላል ነው፥ ዋቢ ማስረጃዎች ይመልከቱ፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 5, ሐዲስ 192
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 15, ሐዲስ 126

እንግዲህ ኢሥልምና ዱር ሙሥሊሙ ሐሩር እንዲሆን ቀን ከሌሊት ደፋ ቀና እና ጠብ እርግፍ የሚሉት አግድም አደግ ዕውቀት ያላቸው ሚሽነሪዎች በኢሥላም ላይ ለሚቀጥፉት ቅጥፈት እኛ ዐቃቢያነ እሥልምና የኢሥላምን መሠረትና ውቅር፣ ዋልታና ማገር፣ ጥልቀትና ስፋት፣ ድርና ማግ በቅጡ ተረድተን ለሚቀጥፉት ቀጣፊዎች በምንተ አፍረት ሳይሆን በምንተ እዳ እንዲህ መልስ መስጠት እና የታሪክ ምፀት ከዐሊሞቻችን ለሚቀጥለው ትውልድ የሚሆን ሰፊ ምዕላድ ትተን መሄድ ግድ ይለናል።
አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ታላቁ ስም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥2 አላህ ከእርሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እርሱ "ሕያው" ሁሉን ነገር አስተናባሪ ነው፡፡ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الْحَيُّ الْقَيُّومُ

በአንድ ወቅት ሙሴ አምላክን፦ "እነሆ እኔ ወደ እስራኤል ልጆች በመጣሁ ጊዜ፦ "የአባቶቻችሁ አምላክ ወደ እናንተ ላከኝ" ባልሁም ጊዜ፦ "ስሙስ ማን ነው? ባሉኝ ጊዜ፥ ምን እላቸዋለሁ? አለው፦
ዘጸአት 3፥13 ሙሴም ኤሎሂምን፦ "እነሆ እኔ ወደ እስራኤል ልጆች በመጣሁ ጊዜ፦ "የአባቶቻችሁ አምላክ ወደ እናንተ ላከኝ" ባልሁም ጊዜ፦ "ስሙስ ማን ነው? ባሉኝ ጊዜ፥ ምን እላቸዋለሁ? አለው። ויאמר משה אל־האלהים הנה אנכי בא אל־בני ישראל ואמרתי להם אלהי אבותיכם שלחני אליכם ואמרו־לי מה־שמו מה אמר אלהם׃

አምላክም ሙሴን፦ «ኤህዬህ አሼር ኤህዬህ» አለው፥ እንዲህ ለእስራኤል ልጆች፦ «ኤህዬህ» ወደ እናንተ ላከኝ" ትላለህ" አለው፦
ዘጸአት 3፥14 ኤሎሂምም ሙሴን፦ «ኤህዬህ አሼር ኤህዬህ» አለው፤ እንዲህ ለእስራኤል ልጆች፦ «ኤህዬህ» ወደ እናንተ ላከኝ ትላለህ" አለው። וַיֹּ֤אמֶר אֱלֹהִים֙ אֶל־מֹשֶׁ֔ה אֶֽהְיֶ֖ה אֲשֶׁ֣ר אֶֽהְיֶ֑ה וַיֹּ֗אמֶר כֹּ֤ה תֹאמַר֙ לִבְנֵ֣י יִשְׂרָאֵ֔ל אֶֽהְיֶ֖ה שְׁלָחַ֥נִי אֲלֵיכֶֽם׃

በዚህ ዐውድ መሠረት "ኤህዬህ" אֶֽהְיֶ֖ה የአምላክ ስም ነው፥ "ኤህዬህ" אֶֽהְיֶ֖ה ማለት "እሆናለው" "እኖራለው" "እኔ ነኝ" ማለት ነው፦
ዘጸአት 3፥12 በእውነት እኔ ከአንተ ጋር "እሆናለሁ"። וַיֹּ֙אמֶר֙ כִּֽי־אֶֽהְיֶ֣ה עִמָּ֔ךְ

እዚህ አንቀጽ ላይ "እሆናለሁ" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ኤህዬህ" אֶֽהְיֶ֖ה ነው፥ "ኤህዬህ አሼር ኤህዬህ" אֶֽהְיֶ֖ה אֲשֶׁ֣ר אֶֽהְיֶ֑ה ማለት "እኔ ነኝ ማን እኔ ነኝ"I am who i am" ማለት ነው። በግዕዝ ንባባት ውስጥ "አህያ ሸራህያ" "ዘሀሎ ወይሄሉ" "እሄሉ ዘይሄሉ" "እከውን ዘእከውን" ይሉታል። በብሉይ ከተገለጹ ሌላው ስሙ "የህ" ወይም "ያህ" ነው፦
መዝሙረ ዳዊት 68፥4 ወደ ደመናዎች ለወጣም መንገድ አድርጉ! ስሙ "ያህ" ነው። סֹ֡לּוּ לָרֹכֵ֣ב בָּ֭עֲרָבֹות בְּיָ֥הּ שְׁמֹ֗ו וְעִלְז֥וּ לְפָנָֽיו׃

"ያህ" יָהּ የሚለው ስም "ያህዌህ" יְהוָ֔ה ለሚለው ስም ምጻረ-ቃል ነው፥ "ያህ" יָהּ በተለይ በሰዎች የተጸውዖ ስም ላይ በመነሻ ቅጥያ አሊያም በመድረሻ ቅጥያ ይመጣል። ለምሳሌ፦ "ኤል-ያህ" אֵלִיָּה በግዕዝ "ኤል-ያስ" በዐረቢኛ "ኢል-ያሥ" إِلْيَاس ሲሆን በመድረሻ ቅጥያ ላይ አለ፥ "ያህ-ሁ" יֵהוּא በግዕዝ "ኢዩ" በዐረቢኛ "ያ-ሁወ" يَاهُو ሲሆን በመነሻ ቅጥያ ላይ አለ። ቁርኣን ውስጥ "ያሥ" يَاس ወይም "ያ" يَّا ይህንኑ ምጻረ ቃል የሚያሳይ ነው፦
37፥123 ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡ وَإِنَّ إِلْيَاسَ لَمِنَ الْمُرْسَلِينَ
19፥2 ይህ ጌታህ ባሪያውን ዘከሪያን በችሮታው ያወሳበት ነው፡፡ ذِكْرُ رَحْمَتِ رَبِّكَ عَبْدَهُ زَكَرِيَّا

"ኢል-ያሥ" إِلْيَاس ማለት "ያህ አምላክ ነው" ማለት ሲሆን "ዘከሪ-ያ" زَكَرِيَّا ማለት ደግሞ "ያህ ያወሳው" ማለት ነው። ያህ ምጻረ-ቃል የሆነበት ስም "ቴትራግራማተን" ወይም "ቴትራግራማቶን" τετραγράμματος ይባላል፥ "ቴትራስ" τέτταρες ማለት "አራት" ማለት ሲሆን "ግራማ" γράμμα ደግሞ "ፊደል" ማለት ነው። ከቀኝ ወደ ግራ የሚነበቡ አራቱ ተነባቢ ፊደላት "ዮድ" י‎ "ሔ" ה‎ "ዋው" ו‎ "ሔ" ה ወይም "የሐዋሐ" ሲሆኑ የፈጣሪ ታላቅ ስም ነው፦
ኢሳይያስ 42፥8 እኔ ያህዌህ ነኝ፥ ስሜ ይህ ነው። אֲנִ֥י יְהוָ֖ה ה֣וּא שְׁמִ֑י
ኤርምያስ 44፥26 "እነሆ በታላቅ ስሜ ምያለሁ" ይላል ያህዌህ፡፡הִנְנִ֨י נִשְׁבַּ֜עְתִּי בִּשְׁמִ֤י הַגָּדֹול֙ אָמַ֣ר יְהוָ֔ה

"ሃሼም" השם‌‎ ማለት "ስሙ" ማለት ሲሆን ይህ ታላቅ ስም በማሶሬት ጽሑፍ ውስጥ 6,518 ቦታ ተጠቅሷል፥ ቅሉ ግን አይሁዳውያን ይህንን ታላቅ ስም በከንቱ ላለመጥራት "አዶናይ" אֲדֹנָ֥י የሚለውን ስም ይጠቀሙ ነበር። "አዶናይ" אֲדֹנָ֥י ከሚለው ቃል "አታፍ ባታህን" א "ኦላም" o "ቃሜጽ" o‌ የሚባቡትን አናባቢ ፊደላት በ "ዮድ-ሄ-ዋው-ሄ" י‎ה‎ו‎ה ላይ ሲደቅሉት "ያህዌህ" יְהוָ֔ה የሚባል ስም ተፈጠረ፥ ይህንን የተለያዩ መድብለ ዕውቀቶች ያትታሉ፦
፨"ያህዌህ፦ ባዕድ ከሆነ ድምጽ ሰጪ ፊደላት ተዋቅሮ ያህዌህ በመባል በስህተት የተነበበ ነው"። Encyclopedia international volume 9, 1974 Edition.
፨"ያህዌህ፦ የቴትራግራማቶን የተሳሳተ አነባነብ ነው"። The universal jewish encyclopedia volume 6, 1948 Edition.
፨"ያህዌህ፦ ለእስራኤል አምላክ የተሳሳተ ስም ነው"። Encyclopedia Americana volume 16, 1976 Edition.

ላቲኖቹ ደግሞ "የ" የሚለውን "ጀ" እንዲሁ "ወ" የሚለውን "ቨ" በመጠቀም "ጆሆቫህ" በማለት ይጠቀማሉ። ከመነሻው ነቢያት ሲጠቀሙበት የነበረው ዕብራይስጥ ፓሌዎ ዕብራይስጥ እንጂ ማሶሬት ዕብራይስጥ አይደለም፥ ስለዚህ በፓሌዎ ዕብራይስጥ የተቀመጠው "ዮድ-ሄ-ዋው-ሄ" 𐤉𐤄𐤅𐤄 አጠራሩ በትክክል አይታወቅም። ሆነም ቀረ "ዮድ-ሄ-ዋው-ሄ" י‎ה‎ו‎ה የሚለው ቃል "ሀ-ወ-ሀ" הוה ማለትም "ኖረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ሐዋሕ" חַוָּה ማለትም "ሕያው"the living one" ማለት ነው።
እዚህ ድረስ ካየን ዘንዳ አምላካችን አሏህ እራሱን በቁርኣን የወሰፈበትን ወስፍ የነገረን ሲሆን የእርሱ ሲፋህ የተሰየመበት ስሞች በቁርኣን ውስጥ የተገለጹት ዘጠና ዘጠኝ ናቸው፥ ከእነዚህ ስሞች ውስጥ ታላቁ ስም ተገልጿል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 34, ሐዲስ 30
አል-ቃሲም እንደተረከው፦ "የአሏህ ታላቁ ስም በእርሱ በተማጸኑት ጊዜ የሚቀበልበት ነው፥ ይህም በሦስት ሡራዎች በበቀራህ፣ በአለ-ዒምራን እና በጧሀ ውስጥ ይገኛል"። عَنِ الْقَاسِمِ، قَالَ اسْمُ اللَّهِ الأَعْظَمُ الَّذِي إِذَا دُعِيَ بِهِ أَجَابَ فِي سُوَرٍ ثَلاَثٍ الْبَقَرَةِ وَآلِ عِمْرَانَ وَطَهَ ‏.‏

"አልሐይ" الْحَيّ ማለት "ሕያው"the living one" ማለት ነው፥ "አልሐይ" الْحَيّ ማለት "እንዲሆን የሚያደርግ"He Causes to Become" የሚል ትርጉምም አለው፦
18፥16 ከነገራችሁም ለእናንተ መጠቃቀሚያን ያደርግላችኋል፡፡ وَيُهَيِّئْ لَكُم مِّنْ أَمْرِكُم مِّرْفَقًا

እዚህ አንቀጽ "ያደርጋል" ለሚለው የግሥ መደብ የገባው ቃል "ዩሐዪ" يُهَيِّئْ ሲሆን "እንዲሆን ያደረጋል" ማለት እንደሆነ ልብ አድርግ! ይህ ታላቅ ስም በሡረቱል በቀራህ፣ በሡረቱል አለ-ዒምራን እና በሡረቱ አጥ-ጧሀ ውስጥ በግልጽ ተቀምጧል፦
2፥255 አላህ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ "ሕያው" ራሱን ቻይ ነው፡፡ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الْحَيُّ الْقَيُّومُ
3፥2 አላህ ከእርሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እርሱ "ሕያው" ሁሉን ነገር አስተናባሪ ነው፡፡ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الْحَيُّ الْقَيُّومُ
20፥111 ፊቶችም ሁሉ "ሕያው" አስተናባሪ ለኾነው አላህ ተዋረዱ፡፡ በደልንም የተሸከመ ሰው በእርግጥ ከሰረ፡፡ وَعَنَتِ الْوُجُوهُ لِلْحَيِّ الْقَيُّومِ ۖ وَقَدْ خَابَ مَنْ حَمَلَ ظُلْمًا
ተፍሢር ኢብኑ ከሲር 2፥255
"አቡ ኡማማህ እንደተረከው ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "የአሏህ ታላቁ ስም በእርሱ በተማጸኑት ጊዜ የሚቀበልበት ነው፥ ይህም በሦስት ቦታ በሱረቱል በቀራህ፣ አለ-ዒምራን እና ጣሃ ውስጥ ይገኛል"። «اسْمُ اللهِ الْأَعْظَمُ، الَّذِي إِذَا دُعِيَ بِهِ أَجَابَ، فِي ثَلَاثٍ: سُورَةِ الْبَقَرَةِ وَآلِ عِمْرَانَ وَطه»

ዛሬ በመላው ዓለም የምንገኘው ሙሥሊሞች ጠዋት እና ማታ አያቱል ኩርሢይን ስንቀራ ይህንን ታላቅ ስም በመጥራት ጥንት ነቢያት ሲያመልኩት የነበረውን አንዱን አምላክ አሏህን ለማምለካችን በቂ ማሳያ ነው። ኢሥላም ዐቂደቱ አር-ረባንያህ ስንል አርቲ ቡርቲና ቶራ ቦራ የሆነ ስሑትና መሪር የቡና ወሬ ይዘን ሳይሆን ስሙርና ጥዑም ማስረጃ ይዘን ነው። አምላካችን አሏህ ታላቁ ስሙን በመጥራት ዱዓቸው መቅቡል ከሆኑት ያርገን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የአሏህ ባሪያ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

19፥30 ሕፃኑም አለ «እኔ የአላህ ባሪያ ነኝ፡፡ መጽሐፍን ሰጥቶኛል ነቢይም አድርጎኛል፡፡» قَالَ إِنِّي عَبْدُ اللَّهِ آتَانِيَ الْكِتَابَ وَجَعَلَنِي نَبِيًّا

"መዕቡድ" مَعْبُود‎ ማለት "ተመላኪ" ማለት ሲሆን "ዓቢድ" عَابِد‎ ማለት ደግሞ "አምላኪ" ማለት ነው፥ በተመላኪ እና በአምላኪ መካከል ያለው ሥርዓት "ዒባዳህ" عِبَادَة‎ ነው። ለአሏህ አምልኮን የሚያቀርብ "ባሪያ" በቁርኣን "ዐብድ" عَبْد ይባላል፥ ዒሣ አሏህን በብቸኝነት ስለሚያመልክ "ዐብዱሏህ" عَبْدُ اللَّه ማለትም "የአሏህ አምላኪ" "የአሏህ ባሪያ" ተብሏል፦
4፥172 አልመሲሕ ለአላህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ
19፥30 ሕፃኑም አለ «እኔ የአላህ ባሪያ ነኝ፡፡ መጽሐፍን ሰጥቶኛል ነቢይም አድርጎኛል፡፡» قَالَ إِنِّي عَبْدُ اللَّهِ آتَانِيَ الْكِتَابَ وَجَعَلَنِي نَبِيًّا
43፥59 እርሱ በርሱ ላይ የለገስንለት ለእስራኤለም ልጆች ተዓምር ያደረግነው የኾነ ባሪያ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ إِنْ هُوَ إِلَّا عَبْدٌ أَنْعَمْنَا عَلَيْهِ وَجَعَلْنَاهُ مَثَلًا لِّبَنِي إِسْرَائِيلَ

በዕብራይስጥ "ዔቤድ" עֶבֶד ማለት "ባሪያ" ወይም "አምላኪ" ማለት ሲሆን "ዐባድ" עָבַד ማለትም "አምልኮ" ከሚል የመጣ ቃል ነው፥ ኢየሱስ የአንዱ አምላክ ባሪያ መሆኑን በግልጽ እና በማያሻማ መልኩ ተቀምጧል፦
ኢሳይያስ 42፥1 እነሆ ደግፌ የያዝሁት ባሪያዬ፤ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ምርጤ፤ በእርሱ ላይ መንፈሴን አድርጌአለሁ፥ እርሱም ለአሕዛብ ፍርድን ያወጣል። הֵ֤ן עַבְדִּי֙ אֶתְמָךְ־בֹּ֔ו בְּחִירִ֖י רָצְתָ֣ה נַפְשִׁ֑י נָתַ֤תִּי רוּחִי֙ עָלָ֔יו מִשְׁפָּ֖ט לַגֹּויִ֥ם יֹוצִֽיא׃
ማቴዎስ 12፥18 እነሆ የመረጥሁት "ባሪያዬ" ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ወዳጄ፤ መንፈሴን በእርሱ ላይ አኖራለሁ፥ ፍርድንም ያወራል። Ἰδοὺ ὁ παῖς μου ὃν ᾑρέτισα, ὁ ἀγαπητός μου ὃν εὐδόκησεν ἡ ψυχή μου· θήσω τὸ πνεῦμά μου ἐπ' αὐτόν, καὶ κρίσιν τοῖς ἔθνεσιν ἀπαγγελεῖ.

ልብ ብላችሁ ከሆነ የብሉይ ግሪክ ሰፕቱአጀንት በኢሳይያስ 42፥1 "ባሪያ" ለሚለው የተጠቀመው ቃል "ፓይስ" παῖς ሲሆን የማቴዎስ ጸሐፊም ከኢሳይያስ 42፥1 ላይ ጠቅሶ በግሪክ ኮይኔ ያስቀመጠውም ቃል "ፓይስ" παῖς ነው፥ ፈጣሪ ኢየሱስን በአገናዛቢ ተውላጠ ስም "ባሪያዬ"my servant" ማለቱ ብቻ ሳይሆን ሐዋርያትም ኢየሱስ ባርነቱ ለአንድ አምላክ ስለሆነ በአገናዛቢ ተውላጠ ስም "ባርያው"his servant" ብለው አስቀምጠዋል፦
የሐዋርያት ሥራ 3፥13 የአብርሀም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ አምላክ እና የአባቶቻችን አምላክ እናንተ አሳልፋችሁ የሰጣችሁትንና ሊፈታው ቈርጦ ሳለ በጲላጦስ ፊት የካዳችሁትን "ባሪያዬውን" ኢየሱስን አከበረው። ὁ θεὸς Ἀβραὰμ καὶ Ἰσαὰκ καὶ Ἰακώβ, ὁ θεὸς τῶν πατέρων ἡμῶν, ἐδόξασεν τὸν παῖδα αὐτοῦ Ἰησοῦν, ὃν ὑμεῖς μὲν παρεδώκατε καὶ ἠρνήσασθε κατὰ πρόσωπον Πειλάτου, κρίναντος ἐκείνου ἀπολύειν·

እዚህ አንቀጽ ላይ "ባሪያ" ለሚለው የገባው ቃል "ፓይዳ" Παῖδα ሥረ-መሠረቱ "ፓይስ" παῖς ሲሆን በግልጽ "ባሪያ" ማለት ስለሆነ New International Version ላይ ሳያቅማሙ "ባሪያ"servant" ብለውታል፥ ዐውዱ ላይም አምላክ ለእስራኤል ያስነሳው ነቢዩ ኢየሱስ "ፓይዳ" Παῖδα ተብሏል፦
የሐዋርያት ሥራ 3፥26 ለእናንተ አስቀድሞ አምላክ "ባሪያዬውን" አስነሥቶ እያንዳንዳችሁን ከክፋታችሁ እየመለሰ ይባርካችሁ ዘንድ ላከው። ὑμῖν πρῶτον ἀναστήσας ὁ θεὸς τὸν παῖδα αὐτοῦ ἀπέστειλεν αὐτὸν εὐλογοῦντα ὑμᾶς ἐν τῷ ἀποστρέφειν ἕκαστον ἀπὸ τῶν πονηριῶν ὑμῶν.

እዚህ አንቀጽ ላይ ደግሞ ኢየሱስን በነቢይነት ያስነሳው አምላክ ተመላኪ ሲሆን ኢየሱስ ግን የተላከ ባሪያ ነው። ሚሽነሪዎች ሆይ! እናንተ "ባሪያ" መባል ያፈራችሁበትን ነቢያት እና ሐዋርያት ኢየሱስን "ባሪያ" ብለውታና ለአንዱ አምላክ ባሪያ ትሆኑ ዘንድ ጥሪአችን ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ላት፣ ዑዛ፣ መናት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

7፥180 ለአላህም መልካም ስሞች አሉት፡፡ ስትጸልዩ በእርሷም ጥሩት! እነዚያንም ስሞቹን የሚያጣምሙትን ተዋቸው፡፡ ይሠሩት የነበሩትን ነገር በእርግጥ ይመነዳሉ፡፡ وَلِلَّهِ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ فَادْعُوهُ بِهَا ۖ وَذَرُوا الَّذِينَ يُلْحِدُونَ فِي أَسْمَائِهِ ۚ سَيُجْزَوْنَ مَا كَانُوا يَعْمَلُونَ

አምላካችን አሏህ ከፍጡራን ጋር የማይመሳሰሉ "አል-አሥ ማኡል ሑሥና" الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ ማለትም "የተዋቡ ስሞች" አሉት፦
20፥8 አላህ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ለእርሱ መልካሞች የኾኑ ስሞች አሉት፡፡ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ
7፥180 ለአላህም መልካም ስሞች አሉት፡፡ ስትጸልዩ በ-"እርሷም" ጥሩት! እነዚያንም ስሞቹን የሚያጣምሙትን ተዋቸው፡፡ ይሠሩት የነበሩትን ነገር በእርግጥ ይመነዳሉ፡፡ وَلِلَّهِ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ فَادْعُوهُ بِهَا ۖ وَذَرُوا الَّذِينَ يُلْحِدُونَ فِي أَسْمَائِهِ ۚ سَيُجْزَوْنَ مَا كَانُوا يَعْمَلُونَ

"እርሷ" ለሚለው ተሳቢ ተውላጠ ስም የገባው "ሃ" هَا ሲሆን "አሥማእ" أَسْمَاء የሚለውን ስም ተክቶ የመጣ ነው፥ ሙአነስ አንዳንዴ ጀምዕን ለማመልከት እንደሚመጣ በነሕው ደርሥ ግልጽ ነው። ነገር ግን ቁሬይሾች የአሏህ ስሞችን በማጣመም ነፍሶች የሚዘነበሉበትን ጥርጣሬ ተከትለዋል፥ "አሏህ" اللَّه ከሚለው ስም "ላት" لَّات በማለት፣ "ዐዚዝ" عَزِيزِ ከሚለው ስም "ዑዛ" عُزَّىٰ በማለት፣ "መናን" مَنَّان ከሚለው ስም "መናት" مَنَاة በማለት አጣመዋል፦
53፥19 ላትን እና ዑዛን አያችሁን? أَفَرَأَيْتُمُ اللَّاتَ وَالْعُزَّىٰ
53፥20 ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን አያችሁን? وَمَنَاةَ الثَّالِثَةَ الْأُخْرَىٰ

፨የመጀመሪያይቱ ጣዖት በግሪክ "አቴና" በሮም "ሚነርቫ" በከነዓ "አናት" በግብጽ "ኔዝ" ትባል ነበር፥ ይህቺ የጥበብ፣ የእጅ ሥራ፣ የፍትሕ፣ የሕግ፣ የድል አምላክ ተብላ የምትጠራውን ጣዖት ወደ ጧዒፍ ከተማ በወጅ ሸለቆ አምጥተው ስሟን "አሏህ" اللَّه ከሚለው ስም በማጣመም "ላት" لَّات አሏት። ላት በላይዋ ላይ የተቀረጹ ጽሑፎች ያሏ ነጭ ድንጋይ ነበረች፥ ላት ብለው በአንስታይ የሰየሟት ጣዖት ጥንት በአሏህ ቤት ሐጅ ለሚያደርጉ ሑጃጅ የገብስ ሾርባ የሚያቀርብ ሷሊሕ ሰው ሲሆን እርሱ ሲሞት እሳቤውን ከፓጋን በመውሰድ በእርሱን መቃብር ማምለክ ጀመሩ፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 380
ኢብኑ ዐባሥ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "ላት እና ዑዛ" ስለሚለውን ንግግር፦ "ላት ለሐጅ ሰዎች የገብስ ሾርባ የሚያቀርብ ሰው ነበር" አለ። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، رضى الله عنهما فِي قَوْلِهِ ‏{‏اللاَّتَ وَالْعُزَّى‏}‏ كَانَ الَّلاَتُ رَجُلاً يَلُتُّ سَوِيقَ الْحَاجِّ‏.‏

ይህቺን ጣዖት በ 9 የሒጅራህ አቆጣጠር ወይም በ 630 የጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በጥቅም ወር ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" አቡ ሡፍያን ኢብኑ ሐርብን እና አል-ሙጊራህ ኢብኑ ሹዕባህን ልከዋቸው አፈራርሰዋታል።

፨ሁለተኛይቱን በከነዓን "አስታሮት" በባቢሎን "ኤሽታር" በሮም "ቬኑስ" በግሪክ "አፍሮዳይት" በግብጽ "አዞር" ትባል ነበር፥ ይህቺ የጦርነት፣ የፍቅር፣ የአደን አምላክ ተብላ የምትታመን ጣዖትን በመካህ እና በጧዒፍ መካከል ባለው በነኽላህ አምጥተው ስሟን "ዐዚዝ" عَزِيزِ ከሚለው ስም በማጣመም "ዑዛ" عُزَّىٰ አሏት። ዑዛ በመጋረጃ የተኖረች እና በመታሰቢያ ሐውልት የተለወሰች ዛፍ ነበረች፥ በ 8 የሒጅራህ አቆጣጠር ወይም በ 630 የጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በጥር ወር ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ኻሊድ ኢብኑል ወሊድን ልከውት ዑዛ የተባለችውን ጣዖት አፈራርሷል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 11, ሐዲስ 8
ሠዕድ እንደተረከው፦ ስለ ላት እና ዑዛ የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ከአሏህ በቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም፥ ለእርሱ አንድም ተጋሪ የለውም"። عَنْ سَعْدٍ، قَالَ حَلَفْتُ بِاللاَّتِ وَالْعُزَّى فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ "‏ قُلْ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ وَحْدَهُ لاَ شَرِيكَ لَهُ

፨ሦስተኛይቱ በመካህ እና በመዲናህ መካከል በሚገኘው በሙሸለል አካባቢ የምትመለከው የእጣ፣ የዕድል፣ የጊዜ እና የመዳረሻ አምላክ ተብላ የምትታመነበው የነበረችው መናት ከላት እና ዑዛ በፊት የነበረች ስትሆን ስሟን "መናን" مَنَّان ከሚለው ስም በማጣመም "መናት" مَنَاة አሏት። "ሐናን" حَنَان ማለት "ርኅራኄ" ማለት ሲሆን ከአሏህ የሚሰጥ ነው፦
19፥13 ከእኛም የሆነን ርኅራኄ ንጽሕናንም ሰጠነው፡፡ ጥንቁቅም ነበር፡፡ وَحَنَانًا مِّن لَّدُنَّا وَزَكَاةً ۖ وَكَانَ تَقِيًّا

እዚህ አንቀጽ ላይ "ርኅራኄ" ለሚለው የገባው ቃል "ሐናን" حَنَان ነው። "አል-መናን" الْمَنَّان ደግሞ "ርኅራኄ ሰጪ" ማለት ሲሆን በሐዲስ የተገለጸ የአሏህ ስም ነው፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 34, ሐዲስ 32
Iአነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አንድ ሰው(ጂብሪል)፦ "አሏህ ሆይ! በእውነት በጎነት ምስጋና ሁሉ ለአንተ እንዲሆን እለምንሃለው፥ ከአንተ በቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም፥ ለአንተ አንድም ተጋሪ የለህም። አንተ አል-መናን፣ የሰማያት እና የምድር አስገኚ፣ የግርማ እና የክብር ባለቤት ነህ" ሲል ሰምቻለው"። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ، قَالَ سَمِعَ النَّبِيُّ ـ صلى الله عليه وسلم ـ رَجُلاً يَقُولُ اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ بِأَنَّ لَكَ الْحَمْدَ لاَ إِلَهَ إِلاَّ أَنْتَ وَحْدَكَ لاَ شَرِيكَ لَكَ الْمَنَّانُ بَدِيعُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضِ ذُو الْجَلاَلِ وَالإِكْرَامِ"‏ ‏

በ 8 የሒጅራህ አቆጣጠር ወይም በ 630 የጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ሠዒድ ኢብኑ ዘይድ አል-አሽሀሊይን ልከውት መናህ የተባለችውን ይህቺን ጣዖት አፈራርሷል።
እነዚህ ዐረብ ጣዖታውያን "መላእክት የአሏህ ሴቶች ልጀች ናቸው" በማለት መላእክትን ሴቶች በማድረግ ለአሏህ የማይገባውን ነገር ተናገሩ፦
53፥27 እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡ إِنَّ الَّذِينَ لَا يُؤْمِنُونَ بِالْآخِرَةِ لَيُسَمُّونَ الْمَلَائِكَةَ تَسْمِيَةَ الْأُنثَىٰ
37፥150 ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን? أَمْ خَلَقْنَا الْمَلَائِكَةَ إِنَاثًا وَهُمْ شَاهِدُونَ
43፥19 መላእክትንም እነርሱ የአልረሕማን ባሮች የኾኑትን ሴቶች አደረጉ፡፡ ሲፈጠሩ ነበሩን? መመስከራቸው በእርግጥ ትጻፋለች፡፡ ይጠየቃሉም፡፡ وَجَعَلُوا الْمَلَائِكَةَ الَّذِينَ هُمْ عِبَادُ الرَّحْمَـٰنِ إِنَاثًا ۚ أَشَهِدُوا خَلْقَهُمْ ۚ سَتُكْتَبُ شَهَادَتُهُمْ وَيُسْأَلُونَ
17፥40 ጌታችሁ በወንዶች ልጆች መረጣችሁ እና ከመላእክት ሴቶችን ልጆች ያዝን? እናንተ ከባድን ቃል በእርግጥ ትናገራላችሁ፡፡ أَفَأَصْفَاكُمْ رَبُّكُم بِالْبَنِينَ وَاتَّخَذَ مِنَ الْمَلَائِكَةِ إِنَاثًا ۚ إِنَّكُمْ لَتَقُولُونَ قَوْلًا عَظِيمًا
16፥57 ለአላህም ከመላእክት ሴቶች ልጆችን ያደርጋሉ። ጥራት ተገባው፡፡ ለእነርሱም የሚፈልጉትን ወንዶች ልጆችን ያደርጋሉ፡፡ وَيَجْعَلُونَ لِلَّهِ الْبَنَاتِ سُبْحَانَهُ ۙ وَلَهُم مَّا يَشْتَهُونَ

ከእነርሱ አንዳቸው ግን ለአልረሕማን ምሳሌ ባደረጉለት ነገር በሴት ልጅ በተበሰረ ጊዜ የተቆጨ ኾኖ ፊቱ ጠቁሮ ይውላል፥ ነገር ግን ለአሏህ መላእክትን ሴቶች ልጆች በማድረግ በአሏህ ላይ ቀጠፉ፦
43፥16 ከሚፈጥረው ውስጥ ሴቶች ልጆችን ያዘን? በወንዶች ልጆችም እናንተን መረጣችሁን? أَمِ اتَّخَذَ مِمَّا يَخْلُقُ بَنَاتٍ وَأَصْفَاكُم بِالْبَنِينَ
52፥39 ወይስ ለእርሱ ሴቶች ልጆች አሉትን? ለእናንተም ወንዶች ልጆች አሏችሁን? أَمْ لَهُ الْبَنَاتُ وَلَكُمُ الْبَنُونَ
16፥58 አንዳቸውም በሴት ልጅ በተበሰረ ጊዜ እርሱ የተቆጨ ኾኖ ፊቱ ጠቁሮ ይውላል፡፡ وَإِذَا بُشِّرَ أَحَدُهُم بِالْأُنثَىٰ ظَلَّ وَجْهُهُ مُسْوَدًّا وَهُوَ كَظِيمٌ
43፥17 አንዳቸውም ለአልረሕማን ምሳሌ ባደረጉለት ነገር በሴት ልጅ በተበሰረ ጊዜ እርሱ በቁጭት የተመላ ኾኖ ፊቱ የጠቆረ ይኾናል፡፡ وَإِذَا بُشِّرَ أَحَدُهُم بِمَا ضَرَبَ لِلرَّحْمَـٰنِ مَثَلًا ظَلَّ وَجْهُهُ مُسْوَدًّا وَهُوَ كَظِيمٌ

እነርሱ ወንድ ልጅ ሲወለድ ለራሳቸው ደስ ሲላቸው በተቃራኒው ሴት ስትወለድ የሚከፋቸው ሲሆን ለአሏህ መላእክትን ሴቶች ልጆች ማድረጋቸው አድሏዊ ንግግር ነው፥ አሏህም፦ "ለእናንተ ወንድ ልጅ ለእርሱም ሴት ልጅ ይኖራልን? ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት" በማለት መልስ ሰጣቸው፦
53፥21 ለእናንተ ወንድ ልጅ ለእርሱም ሴት ልጅ ይኖራልን? أَلَكُمُ الذَّكَرُ وَلَهُ الْأُنثَىٰ
53፥22 ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት፡፡ تِلْكَ إِذًا قِسْمَةٌ ضِيزَىٰ

እነዚህን ጣዖታት ሙሽሪኮች እና አባቶቻቸው "ላት፣ ዑዛ እና መናህ" ብለው የሰየሟቸው ስሞች እንጂ መጥቀም ሆነ መጉዳት የሚችሉ አይደሉም፥ አሏህን ሰዎች እነዚህን ጣዖታት እንዲያመልኩ ማስረጃ አላወረደም፦
53፥23 እነርሱንም እናንተ እና አባቶቻችሁ የሰየማኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፥ አላህ በእርሷ ምንም ማስረጃ አላወረደም። إِنْ هِيَ إِلَّا أَسْمَاءٌ سَمَّيْتُمُوهَا أَنتُمْ وَآبَاؤُكُم مَّا أَنزَلَ اللَّهُ بِهَا مِن سُلْطَانٍ

"አህዋእ" أَهْوَآء ማለት "ዝንባሌ"inclination" ማለት ነው፥ ይህ ዝንባሌ ከነፍሢያህ ሲሆን አሏህን ሰዎች እነዚህን ጣዖታት እንዲያመልኩ ማስረጃ ያላወረደበትን ነገር በዝንባሌአቸው ጥርጣሬን እንዲከተሉ ሆነዋል፥ በእርግጥም ከአሏህ ዘንድ የመጣው መመሪያ ቁርኣን አሏህ አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት የመጣ ነው፦
53፥23 ነፍሶች የሚዘነበሉበትን ጥርጣሬን እንጅ ሌላ አይከተሉም፥ በእርግጥ ከጌታቸውም መምሪያ መጥቶላቸዋል። إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا الظَّنَّ وَمَا تَهْوَى الْأَنفُسُ ۖ وَلَقَدْ جَاءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ الْهُدَىٰ
45፥11 ይህ ቁርኣን መመሪያ ነው፡፡ እነዚያም በጌታቸው አንቀጾች የካዱት ለእነርሱ ከብርቱ ቅጣት የኾነ አሳማሚ ስቃይ አላቸው፡፡ هَـٰذَا هُدًى ۖ وَالَّذِينَ كَفَرُوا بِآيَاتِ رَبِّهِمْ لَهُمْ عَذَابٌ مِّن رِّجْزٍ أَلِيمٌ
14፥52 ይህ ቁርኣን ለሰዎች ገላጭ ነው፡፡ በእርሱም ሊያስጠነቅቁበት፣ እርሱም አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት፣ የአእምሮ ባለቤቶችም ሊገሰጹበት የተወረደ ነው፡፡ هَـٰذَا بَلَاغٌ لِّلنَّاسِ وَلِيُنذَرُوا بِهِ وَلِيَعْلَمُوا أَنَّمَا هُوَ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ وَلِيَذَّكَّرَ أُولُو الْأَلْبَابِ

አምላካችን አሏህ በተውሒድ የምንጸና ሙዋሒድ ያርገን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
መምህር ምሕረተ አብ፦ "ሰካራሞች የኦርቶዶክስ ተከታዮች ናቸው" የሚል ምጸታዊ ቃላት ተጠቅሟል። ይህ ነውር አይደለምን እንዴ? መምህር ተው! እንዲህ አይባል።

በነገራችን ላይ በኦርቶዶክስ ዶግማ አስካሪ መጠጥ መጠጣት ሐላል ነው፥ እነርሱ ግን አስካሪ መጠጥ ይጨልጣሉ እንጂ አይጠጡም እኮ።

ይህንን ድርጊት እንዲያወግዙ ሼር አርጉላቸው!
የጀነት ዛፍ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

76፥14 ዛፎችዋም በእነርሱ ላይ የቀረበች እና ፍሬዎችዋም ለለቃሚዎች መግገራትን የተገራች ስትኾን ገነትን መነዳቸው፡፡ وَدَانِيَةً عَلَيْهِمْ ظِلَالُهَا وَذُلِّلَتْ قُطُوفُهَا تَذْلِيلًا

“ጀናህ” جَنَّة የሚለው ቃል “ጀነ” جَنَّ ማለትም “ተሰወረ” ወይም “ተደበቀ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን “ድብቅ” ወይም “ስውር” ማለት ነው፥ በጀነት ውስጥ ያለው ለሙሥሊሞች የተደበቀላቸውን ፀጋ ደግሞ ማንኛይቱም ነፍስ ስለማያውቅ ድብቅ እና ስውር ነው። በሐዲሰል ቁድሢይ ላይ የተዘጋጀው የጀነት ጸጋ ዓይን ዓይቶት፣ ጆሮ ሰምቶት፣ ልብ አስቦት የማያውቅ መሆኑ ተገልጿል፦
32፥17 ይሠሩትም በነበሩት ለመመንዳት ከዓይኖች መርጊያ ለእነርሱ የተደበቀላቸውን ጸጋ ማንኛይቱም ነፍስ አታውቅም፡፡ فَلَا تَعْلَمُ نَفْسٌ مَّا أُخْفِيَ لَهُم مِّن قُرَّةِ أَعْيُنٍ جَزَاءً بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 123:
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ ነብዩ”ﷺ” እንዲህ ብለው አሉ፦ “አላህም እንዲህ አለ፦ እኔ ለደጋግ ባሮቼ ዓይን ዓይቶት የማያውቅ፣ ጆሮ ሰምቶት የማያውቅ እና በሰው ልቦና ውል ብሎ የማያውቅ ጸጋን አዘጋጅቻለው”። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ قَالَ اللَّهُ أَعْدَدْتُ لِعِبَادِي الصَّالِحِينَ مَا لاَ عَيْنٌ رَأَتْ، وَلاَ أُذُنٌ سَمِعَتْ، وَلاَ خَطَرَ عَلَى قَلْبِ بَشَرٍ ‏”

ስለዚህ በጀነት ውስጥ ያሉትን አሏህ ለባሮቹ ያዘጋጃቸው ፀጋዎች ዓይን ዓይቶት፣ ጆሮ ሰምቶት፣ ልብ አስቦት የማያውቅ ከሆነ ጀነት ውስጥ ያለው ሙዝ፣ ዘንባባ፣ ወይን፣ ተምር እንዲሁ ዛፍ ከዱንያው ውስጥ ካለው ነገር ጋር የስም መመሳሰል እንጂ ቅርጽና ይዘቱ አሊያም ጥፍጥናውና ጣዕሙ አንድ አይደለም፦
76፥14 ዛፎችዋም በእነርሱ ላይ የቀረበች እና ፍሬዎችዋም ለለቃሚዎች መግገራትን የተገራች ስትኾን ገነትን መነዳቸው፡፡ وَدَانِيَةً عَلَيْهِمْ ظِلَالُهَا وَذُلِّلَتْ قُطُوفُهَا تَذْلِيلًا
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 53 ሐዲስ 7
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "በጀናህ ውስጥ በጥላ ሥር ፈረሰኛ መቶ ዓመት የሚምታስጓዝ ዛፍ አለች"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنْ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم أَنَّهُ قَالَ ‏ "‏ إِنَّ فِي الْجَنَّةِ لَشَجَرَةً يَسِيرُ الرَّاكِبُ فِي ظِلِّهَا مِائَةَ سَنَةٍ ‏"‏ ‏.‏

ጊዜ የሚለካው በሰከንድ፣ በደቂቃ፣ በሰዓት፣ በቀን፣ በወር፣ በዓመት ሲሆን በተመሳሳይ ከሜትር ቁጥጥር ውጪ ያለ ርዝመት የሚለካው በዓመት ነው፥ በፈረሰኛ መቶ ዓመት መገለጹ በራሱ ጀናህ ምን ያክል ሰፊ እንደሆነች በቀላሉ መረዳት ይቻላል። ቀለብ እንጂ ቀልብ የሌላቸው ሚሽነሪዎች በጀናህ ውስጥ ዛፍ መኖሩ ለመሳቅ እና ለመሳለቅ ሲቃታቸው ዓይተን ነበር፥ እንዚህ ዘንጋታዎች እየተጎማለሉ እና ዘንፈል እያሉ ቁርኣን እና ሐዲስ ውስጥ እንደገቡ እኛም እንዲማሩበት በጨዋ ደንብ እና ሥርዓት ከባይብል በጀነት ውስጥ ዛፍ እንዳለ ጠቅሰንና አጣቅሰን እናቀርባለን፦
ሕዝቅኤል 31፥ 9 በእግዚአብሔርም ገነት በዔድን የነበሩ "ዛፎች" ሁሉ ቀኑበት።
ራእይ 2፥7 ድል ለነሣው በእግዚአብሔር ገነት ካለው ከሕይወት "ዛፍ" እንዲበላ እሰጠዋለሁ።
ራእይ 22፥2 በወንዙም ወዲያና ወዲህ በየወሩ እያፈራ አሥራ ሁለት ፍሬ የሚሰጥ የሕይወት "ዛፍ" ነበረ፥ የዛፉም ቅጠሎች ለሕዝብ መፈወሻ ነበሩ።

እነዚህ ሦስት አናቅጽ ላይ በገነት ውስጥ ዛፎች እንዳሉ አስረግጠውና ረግጠው ያስረዳሉ፥ "የሕይወት ዛፍ" ማለት አዳም እና ሔዋን በገነት እያሉ እንዲበሉት የበቀለ ዛፍ ነው፦
ዘፍጥረት 2፥9 በገነትም መካከል "የሕይወትን ዛፍ"፥ መልካምንና ክፉን የሚያስታውቀውንም ዛፍ አበቀለ።
ዘፍጥረት 2፥16 እግዚአብሔር አምላክም ሰውን እንዲህ ብሎ አዘዘው፦ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ፤

እሥልምና እንዲጠፋ ሙሥሊም እንዲገፋ ቀን ከሌሊት የሚዋትሩ እነዚህ እብሪተኞች እና ዳተኞች የሚሰበሰቡበት አዳራሽ ክበብ ይሁን ክለብ ለይተው ሳያውቁ እነዚህ አናቅጽ ያነቡአቸዋል ብለን አናስብም፥ ሚሽነሪዎች ሆይ! መቅኖ አጥታችሁ መቀመቅ ከመውረዳችሁ በፊት ጨርቄን እና ማቄን ሳትሉ ወደ ዱኑል ኢሥላም እንድትመጡ ጥሪአችን ነው። አምላካችን አሏህ ለኢሥላም ጸር እና አጽራር ከመሆን አርነት አውጥቶ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የኢብራሂም ሣራህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

51፥29 ሚስቱም እየጮኸች መጣች፥ ፊቷንም መታች፡፡ «መካን አሮጊት ነኝ» አለችም። فَأَقْبَلَتِ امْرَأَتُهُ فِي صَرَّةٍ فَصَكَّتْ وَجْهَهَا وَقَالَتْ عَجُوزٌ عَقِيمٌ

ኢብራሂም የአሏህ ነቢይ ሲሆን ሚስቱ ደግሞ ሣራህ ትባላለች፥ የኢብራሂም ሚስት ሣራህ ማንነቷ እንጂ ስሟ በቁርኣን አልተጠቀሰም። ቅሉ ግን በሐዲስ ላይ ኢብራሂም ከከለዳውያን ወደ ከነዓን በነበረው ስደት ትረካ ላይ ስሟን ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ነግረውናል፦
ቡኻርይ መጽሐፍ 51, ሐዲስ 67
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ኢብራሂም ከሣራህ ጋር ተሰደደ"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏"‏ هَاجَرَ إِبْرَاهِيمُ بِسَارَةَ،

አሏህ ለተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" የኢብራሂም እንግዶች ወሬ በቁርኣን ተርኮላቸዋል፥ አምላካችን አሏህ መላእክትን ወደ ኢብራሂም በመላክ በኢሥሐቅ አበሰረው፦
51፥24 የተከበሩት የኢብራሂም እንግዶች ወሬ መጥቶሃልን? هَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ ضَيْفِ إِبْرَاهِيمَ الْمُكْرَمِينَ
37፥112 በኢሥሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡ وَبَشَّرْنَاهُ بِإِسْحَاقَ نَبِيًّا مِّنَ الصَّالِحِينَ
11፥69 መልክተኞቻችንም ኢብራሂምን በልጅ ብስራት በእርግጥ መጡለት፡፡ ሰላም አሉት፡፡ ሰላም አላቸው፡፡ ጥቂትም ሳይቆይ ወዲያውኑ የተጠበሰን የወይፈን ስጋ አመጣ፡፡ وَلَقَدْ جَاءَتْ رُسُلُنَا إِبْرَاهِيمَ بِالْبُشْرَىٰ قَالُوا سَلَامًا ۖ قَالَ سَلَامٌ ۖ فَمَا لَبِثَ أَن جَاءَ بِعِجْلٍ حَنِيذٍ
51፥28 ከእነርሱ መፍራትንም በልቡ አሳደረ፡፡ «አትፍራ» አሉት፡፡ በዐዋቂ ወጣት ልጅም አበሰሩት፡፡ فَأَوْجَسَ مِنْهُمْ خِيفَةً ۖ قَالُوا لَا تَخَفْ ۖ وَبَشَّرُوهُ بِغُلَامٍ عَلِيمٍ

መላእክት ስለ ኢሥሐቅ ለኢብራሂም ያበሰሩትን ብስራት ሣራህ ቆማ ታዳምጥ ስለነበር፦ "መካን አሮጊት ነኝ" በማለት የማይሆን መስሏት በስላቅ ሳቀች፥ አሏህም እርሱ ጥበበኛ ዐዋቂ መሆኑን በመናገር አበሰራት፦
51፥29 ሚስቱም እየጮኸች መጣች፥ ፊቷንም መታች፡፡ «መካን አሮጊት ነኝ» አለችም። فَأَقْبَلَتِ امْرَأَتُهُ فِي صَرَّةٍ فَصَكَّتْ وَجْهَهَا وَقَالَتْ عَجُوزٌ عَقِيمٌ
11፥71 ሚስቱም የቆመች ስትኾን ሳቀችም፡፡ በኢስሐቅ አበሰርናት፡፡ ከኢስሐቅም በኋላ በያዕቁብ አበሰርናት፡፡ وَامْرَأَتُهُ قَائِمَةٌ فَضَحِكَتْ فَبَشَّرْنَاهَا بِإِسْحَاقَ وَمِن وَرَاءِ إِسْحَاقَ يَعْقُوبَ
51፥30 ጌታሽ እንደዚህ ብሏል፦ «እነሆ እርሱ ጥበበኛ ዐዋቂ ነውና» አሏት፡፡ قَالُوا كَذَٰلِكِ قَالَ رَبُّكِ ۖ إِنَّهُ هُوَ الْحَكِيمُ الْعَلِيمُ

ከሳቀች በኃላ በኢሥሐቅ ስለተበሰረች ሚሽነሪዎች፦ "ከምን አንጻር እንደ ሳቀች ቅድመ ተከተሉን አልጠበቀም" በማለት ይተቻሉ፥ ቆማ የሳቀችውማ ለእርሷ ከመበሰሩ በፊት ለኢብራሂም በተበሰረው ብስራት ነው። ይህንን በተመሳሳይ ባይብል ላይ አለ፦
ዘፍጥረት 18፥9-11 እነርሱም፦ ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት? አሉት። እርሱም፦ በድንኳኑ ውስጥ ናት፡ አላቸው። እርሱም፦ የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለሁ፤ ሚስትህ ሣራም ልጅን ታገኛለች" አለ። ሣራም በድንኳን ደጃፍ በስተ ኋላው ሳለች ይህንን ሰማች።

ፈጣሪ በመላእክቱ ለአብርሃም ስለ ልጅ ሲነግረው ሣራ በድንኳን ደጃፍ በስተ ኋላው ሆኖ ትሰማ ነበር፥ ሣራ የሳቀችበት ልክ እንደ ቁርኣኑ፦ "ካረጀሁ በኋላ በውኑ ፍትወት ይሆንልኛልን? ጌታዬም ፈጽሞ ሸምግሎአል" በማለት ነበር፦
ዘፍጥረት 18፥12 ሣራም በራሷ፦ "ካረጀሁ በኋላ በውኑ ፍትወት ይሆንልኛልን? ጌታዬም ፈጽሞ ሸምግሎአል" ስትል ሳቀች"። וַתִּצְחַ֥ק שָׂרָ֖ה בְּקִרְבָּ֣הּ לֵאמֹ֑ר אַחֲרֵ֤י בְלֹתִי֙ הָֽיְתָה־לִּ֣י עֶדְנָ֔ה וַֽאדֹנִ֖י זָקֵֽן׃

ባይብሉ ታሪኩን ያቀረበው ሣራ የሳቀችው መላእክት ለአብርሃም ስለ ልጅ በነገሩት መሠረት እንደሆነ ሁሉ ቁርኣኑም ያስቀመጠው መላእክት ለኢብራሂም ስለ ልጅ በነገሩት መሠረት እንደሆነ በተዛማች ሙግት"textual approach" የሥነ-አፈታት ጥናት"hermeneutics" መረዳት ይቻላል፥ የተዛማች ሙግት ማለት አንዱ ሡራህ ላይ የተንጠለጠለ አሳብ በሌላ ሡራህ ላይ የሚጨርሰው ሲሆን ከቁርኣን የአነጋገር ውበት አንዱ ነው። አምላካችን አሏህ ስለዚህ እሳቦት እንዲህ ይነግረናል፦
39፥23 አላህ ከዜና ሁሉ መልካምን፣ ተመሳሳይ፣ ተደጋጋሚ የኾነን መጽሐፍ አወረደ፡፡ اللَّهُ نَزَّلَ أَحْسَنَ الْحَدِيثِ كِتَابًا مُّتَشَابِهًا مَّثَانِيَ تَقْشَعِرُّ

አሏህ ጥንት የተከናወኑትን ድርጊቶች በዜና የሚተርክልን ሙተሻቢህ በማድረግ አንዱ ሡራህ ላይ ተናግሮ ያንጠለጠለውን በሌላ ሡራህ ላይ የቀረውን ተመሳሳይ በማምጣት እና መሳኒይ በማድረግ አንዱ ሡራህ ላይ ተናግሮ ያንጠለጠለውን በሌላ ሡራህ ላይ የቀረውን በመድገም ነው፥ "ሙተሻቢህ" مُتَشَٰبِه ማለት "ተመሳሳይ" ማለት ሲሆን "መሳኒይ" مَّثَانِى ማለት "ተደጋጋሚ" ማለት ነው። አምላካችን አሏህ ቀደም ብለው የተከሰቱትን ክስተቶች የሚተርክልን መልካም፣ ተመሳሳይ እና ተደጋጋሚ ዜና ለእኛ እንድንማርበት ግሳጼ እና ማስታወሻ ነው፦
11፥120 ከመልክተኞቹም ዜናዎች ሁሉንም ልብህን በእርሱ የምናረካበትን እንተርክልሃለን፡፡ በዚህችም እውነቱ ነገር ለምእምናን ግሳጼ እና ማስታወሻ መጥቶልሃል፡፡ وَكُلًّا نَّقُصُّ عَلَيْكَ مِنْ أَنبَاءِ الرُّسُلِ مَا نُثَبِّتُ بِهِ فُؤَادَكَ ۚ وَجَاءَكَ فِي هَـٰذِهِ الْحَقُّ وَمَوْعِظَةٌ وَذِكْرَىٰ لِلْمُؤْمِنِينَ

"ለምእምናን ግሳጼ እና ማስታወሻ መጥቶልሃል" የሚለው ይሰመርበት! ሲጀመር ቁርኣን ላይ የሚመጣ ትረካ "እከሌ እከሌን ወለደ" የሚል የቀበሌ እና የእድር መጽሐፍ አይደለም። ሲቀጥል ለነቢያችን"ﷺ" የወረደላቸው የኢብራሂም ወሬ ኩረጃ ሳይሆን የሁሉን ዓዋቂው፣ በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለን ምስጢር የሚያውቀው የአሏህ ንግግር ነው፦
33፥54 አላህ ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው። فَإِنَّ اللَّهَ كَانَ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا
25፥6 «ያ በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለን ምስጢር የሚያውቀው አወረደው፡፡ እርሱ መሓሪ አዛኝ ነውና» በላቸው፡፡ قُلْ أَنزَلَهُ الَّذِي يَعْلَمُ السِّرَّ فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ إِنَّهُ كَانَ غَفُورًا رَّحِيمًا

ስለዚህ ከላይ ያለው የእናንተ የሚሽነሪዎች ኂስ ያልተጠና ኂስ ነው፥ ያልተጠና ኂስ የሚኃይስ ኃያሲ ለማሳለጥ ከሆነ መጥኔ ያጣ መኳተት ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
"ምላጭ ከምሣር እጅጉን የበለጠ ስለት አለው። ነገር ግን እንጨትን ለመቁረጥ አልታደለም አይሳካለትም። ምሣርም ቢሆን የራሱ ስለትና ብርቱ ጉልበት መኖሩ ፀጉርን ለመቁረጥ አይሳካለትም"
ወንድም ዑሥማን(አቡ ማሂራህ)
https://tttttt.me/AbuMahira55
ነቢዩ ኢሥማዒል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

19፥54 በመጽሐፉ ኢሥማዒልን አውሳ፡፡ እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና፡፡ መልክተኛ ነቢይም ነበር፡፡ وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِسْمَاعِيلَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صَادِقَ الْوَعْدِ وَكَانَ رَسُولًا نَّبِيًّا

አምላካችን አሏህ ወደ ኢሥማዒል ወሕይ አውርዷል፥ አሏህ ስለ ኢሥማዒል ሲናገር "በኢሥማዒል... ላይ በተወረደው አመንን በሉ" በማለት ግህደተ-መለኮት ወርዶለት እንደነበር በሡረቱል አለ ዒምራን 3፥84 በሡረቱል በቀራህ 2፥136 እና በሡረቱ አን-ኒስሳእ 4፥163 ላይ ይናገራል። ኢሥማዒል መልክተኛ እና ነቢይ ነበር፥ ቤተሰቦቹንም በሶላት እና በዘካህ ያዝ ነበር፦
19፥54 በመጽሐፉ ኢሥማዒልንም አውሳ፡፡ እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና፡፡ መልእክተኛ ነቢይም ነበር፡፡ وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِسْمَاعِيلَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صَادِقَ الْوَعْدِ وَكَانَ رَسُولًا نَّبِيًّا
19፥55 ቤተሰቦቹንም በሶላት እና በዘካህ ያዝ ነበር፡፡ እጌታውም ዘንድ ተወዳጅ ነበር፡፡ وَكَانَ يَأْمُرُ أَهْلَهُ بِالصَّلَاةِ وَالزَّكَاةِ وَكَانَ عِندَ رَبِّهِ مَرْضِيًّا

"እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረ" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! ይህም ቀጠሮ ኢብራሂም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፤ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፤ እርሱም «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አሏህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፦
37፥102 ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡ فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعْىَ قَالَ يَٰبُنَىَّ إِنِّىٓ أَرَىٰ فِى ٱلْمَنَامِ أَنِّىٓ أَذْبَحُكَ فَٱنظُرْ مَاذَا تَرَىٰ ۚ قَالَ يَٰٓأَبَتِ ٱفْعَلْ مَا تُؤْمَرُ ۖ سَتَجِدُنِىٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّٰبِرِينَ

ይህ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፥ አሏህ ኢብራሂምን ልጁን እንዲሠዋ በጠየቀው ቃላት ፈተነው፦
37፥106 ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلْبَلَٰٓؤُا۟ ٱلْمُبِينُ
2፥124 ኢብራሂምንም ጌታው በቃላት በፈተነው እና በፈጸማቸው ጊዜ አስታውስ! «እኔ ለሰዎች መሪ አድራጊህ ነኝ» አለው፡፡ «ከዘሮቼም አድርግ» አለ፡፡ ቃል ኪዳኔ በዳዮቹን አያገኝም አለው፡፡ وَإِذِ ٱبْتَلَىٰٓ إِبْرَٰهِـۧمَ رَبُّهُۥ بِكَلِمَٰتٍۢ فَأَتَمَّهُنَّ ۖ قَالَ إِنِّى جَاعِلُكَ لِلنَّاسِ إِمَامًۭا ۖ قَالَ وَمِن ذُرِّيَّتِى ۖ قَالَ لَا يَنَالُ عَهْدِى ٱلظَّٰلِمِينَ

ኢብራሂም የተፈተነበት ልጅ ኢሥማዒልን ስለመሆኑ 2፥124 እና 37፥106 ከላይ እና ከታች ዐውደ ንባቡ ያስረዳል፥ "ኢሥማዒል" إِسْمَٰعِيْل የሚለው ስም የሁለት ቃላት ውቅር ነው፥ "ኢሥም" إِسْم የሚለው ቃል "አሥመዐ" أَسْمَعَ‎ ማለት "ሰማ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ይሰማል" ማለት ነው። "ዒል" عِيْل ደግሞ "ኢላህ" إِلَـٰهً ለሚል ምጻረ-ቃል ሲሆን "አምላክ" ማለት ነው፥ በጥቅሉ "ኢሥማዒል" إِسْمَٰعِيْل ማለት "አምላክ ይሰማል" ማለት ነው። ኢብራሂም፦ "ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን ልጅ ስጠኝ" ብሎ አሏህ ጠይቆ አሏህም ዱዓውን በመስማት ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅ አበሰረው፦
37፥100 ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን ልጅ ስጠኝ፡፡ رَبِّ هَبْ لِى مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
37፥101 *ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው*፡፡ فَبَشَّرْنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٍۢ
14፥39 ጌታዬ ልመናን በእርግጥ ሰሚ ነውና፡፡ إِنَّ رَبِّي لَسَمِيعُ الدُّعَاءِ

ኢብራሂም፦ "ጌታዬ ልመናን በእርግጥ ሰሚ ነው" ማለቱ በራሱ ኢብራሂም አሏህን ለምኖ ያገኘው እና ለዕርድ ሲጠየቅ የታገሰ ትእግስተኛ ልጁ ኢሥማዒል መሆኑን ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ ያሳያል። አሏህ በልጅ ጉዳይ ኢብራሂም ያበሰረው ሁለት ጊዜ ነው፥ የመጀመሪያው ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም ሲሆን ሁለተኛው በኢሥሐቅ ነው፦
37፥101 ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡ فَبَشَّرْنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٍۢ
37፥112 በኢሥሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡ وَبَشَّرْنَٰهُ بِإِسْحَٰقَ نَبِيًّۭا مِّنَ ٱلصَّٰلِحِينَ

"በኢሥሐቅ-"ም" የሚለው ይሰመርበት! "ም" የሚለው ጥገኛ ምዕላድ በዐማርኛ ተጨማሪ ነገርን ያሳያል፥ "አበሰርነው" የሚለው ቃል አንድ ዐውድ ላይ ሁለቴ መምጣቱ ኢሥሐቅ እና ከላይ የተጠቀሰው በዱዓ የመጣው ልጅ ይለያያሉ። በተጨማሪም "ወ" وَ የሚለው አርፉል አጥፍ ብስራቱ ሁለት ጊዜ መሆኑን ያሳያል፥ አንደኛው ረድፍ “ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅ” ሲሆን ሁለተኛው ረድፍ “በኢሥሐቅም አበሰርነው” የሚለው ነው። ኢሥሐቅ ደግሞ ኢብራሂም አሏህን ለምኖ የተሰጠ ልጅ ሳይሆን እርሱ እና ሣራህ አንወልድም ብለው ተስፋ በቆረጡበት የተበሰሩት ልጅ ነው፦
15፥53 «አትፍራ፤ እኛ ዐዋቂ በኾነ ወንድ ልጅ እናበስርሃለን» አሉት፡፡ قَالُوا۟ لَا تَوْجَلْ إِنَّا نُبَشِّرُكَ بِغُلَٰمٍ عَلِيمٍۢ
15፥54 «እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ» አለ፡፡ قَالَ أَبَشَّرْتُمُونِى عَلَىٰٓ أَن مَّسَّنِىَ ٱلْكِبَرُ فَبِمَ تُبَشِّرُونَ
15፥55 «በእውነት አበሰርንህ፡፡ ከተሰፋ ቆራጮችም አትኹን» አሉ፡፡ قَالُوا۟ بَشَّرْنَٰكَ بِٱلْحَقِّ فَلَا تَكُن مِّنَ ٱلْقَٰنِطِينَ
51፥29 ሚስቱም እየጮኸች መጣች፥ ፊቷንም መታች፡፡ «መካን አሮጊት ነኝ» አለችም። فَأَقْبَلَتِ امْرَأَتُهُ فِي صَرَّةٍ فَصَكَّتْ وَجْهَهَا وَقَالَتْ عَجُوزٌ عَقِيمٌ
11፥71 ሚስቱም የቆመች ስትኾን አትፍራ አሉት፤ ሳቀችም፡፡ በኢሥሐቅም አበሰርናት፡፡ ከኢስሐቅም በኋላ በልጁ በያዕቁብ አበሰርናት፡፡ وَٱمْرَأَتُهُۥ قَآئِمَةٌۭ فَضَحِكَتْ فَبَشَّرْنَٰهَا بِإِسْحَٰقَ وَمِن وَرَآءِ إِسْحَٰقَ يَعْقُوبَ