ጣዖታት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
22፥30 ከጣዖታትም ርክሰት ተጠንቀቁ! ሐሰትንም ቃል ራቁ!፡፡ فَاجْتَنِبُوا الرِّجْسَ مِنَ الْأَوْثَانِ وَاجْتَنِبُوا قَوْلَ الزُّورِ
“ጧጉት” طَّٰغُوت የሚለው ቃል “ጦጋ” طَغَىٰ ማለትም “ወሰን አለፈ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “በአሏህ ሐቅ ላይ ወሰን ማለፍ” ማለት ነው፦
79፥17 *ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ “ወሰን አልፏልና”*፡፡ اذْهَبْ إِلَىٰ فِرْعَوْنَ إِنَّهُ طَغَىٰ
79፥24 አለም፡- *«እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»* فَقَالَ أَنَا رَبُّكُمُ الْأَعْلَىٰ
“ወሰን አልፏል” ለሚለው አላፊ ግሥ የገባው ቃል “ጦጋ” طَغَىٰ መሆኑን ልብ አድርግ! ፊርዐውን በአሏህ ሐቅ ላይ ወሰን ያለፈው፦ “እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ” በማለት ነው፥ ስለዚህ በአሏህ ሐቅ ላይ ወሰን ማሳለፊያ ምንነት “ጣዖት” ይባላል። በአሏህ ሐቅ ላይ ወሰን ማሳለፊያ ምንነት “አስናም” እና “አውሳን” ናቸው፥ “አስናም” أَصْنَام ከእንጨት፣ ከብር፣ ከነሐስ፣ ከወርቅ ተሠርቶ አምልኮ የሚቀርብለት ጣዖት ሲሆን “አውሳን” أَوْثَٰن ደግሞ ከድንጋይ ተቀርፆ አምልኮ የሚቀርብለት ጣዖት ነው። ይህ ድርጊት የሚያስረክስ ስለሆነ "ራቁ" ተብሏል፦
74፥5 ጣዖትንም ራቅ፡፡ وَالرُّجْزَ فَاهْجُرْ
22፥30 ከጣዖታትም ርክሰት ተጠንቀቁ! ሐሰትንም ቃል ራቁ!፡፡ فَاجْتَنِبُوا الرِّجْسَ مِنَ الْأَوْثَانِ وَاجْتَنِبُوا قَوْلَ الزُّورِ
የተውሒድ አራማጅ ኢብራሂም፦ "እኔንም ልጆቼንም ጣዖታትን ከመገዛት አርቀን" በማለት ዱዓእ አርጎ ነበር፦
24፥35 ኢብራሂምም፦ "ጌታዬ ሆይ! ይህንን አገር (መካን) ጸጥተኛ አድርገው፡፡ እኔንም ልጆቼንም ጣዖታትን ከመገዛት አርቀን" ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ وَإِذْ قَالَ إِبْرَاهِيمُ رَبِّ اجْعَلْ هَـٰذَا الْبَلَدَ آمِنًا وَاجْنُبْنِي وَبَنِيَّ أَن نَّعْبُدَ الْأَصْنَامَ
ነገር ግን ከእርሱ እና ከልጆች ህልፈት በኃላ ዝርዮቹ የሷሊሕ ሰዎችን ምስል በድንጋይ በመቅረጽ ማምለክ ጀመሩ፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 64, ሐዲስ 401
አቢ ረጃእ አል-ዑጧሪዲይ እንደተረከው፦ "ድንጋይ እናመልክ ነበር፥ የተሻለ ድንጋይ ባገኘን ጊዜ የመጀመሪያውን እንተወው እና ከእርሱ የኃለኛውን እንይዝ ነበር። ነገር ግን ድንጋይ ካላገኘን ከአፈር ሬሳ እንሰበስብ ነበር፥ ከዚያም በእርሱ ላይ በበግ ወተት እንለውስ ነበር። ከዚያም በእርሱ(በሬሳው) እንዞር ነበር"። قَالَ سَمِعْتُ أَبَا رَجَاءٍ الْعُطَارِدِيَّ، يَقُولُ كُنَّا نَعْبُدُ الْحَجَرَ، فَإِذَا وَجَدْنَا حَجَرًا هُوَ أَخْيَرُ مِنْهُ أَلْقَيْنَاهُ وَأَخَذْنَا الآخَرَ، فَإِذَا لَمْ نَجِدْ حَجَرًا جَمَعْنَا جُثْوَةً مِنْ تُرَابٍ، ثُمَّ جِئْنَا بِالشَّاةِ فَحَلَبْنَاهُ عَلَيْهِ، ثُمَّ طُفْنَا بِهِ
ቁሬይሾች ከድንጋይ ተቀርፆ አምልኮ የሚቀርብለት አውሳን ሲያመልኩ አምላካችን አሏህ፦ "ለእናንተ ሲሳይን ሊሰጧችሁ አይችሉም፡፡ ስለዚህ ሲሳይን ከአላህ ዘንድ ብቻ ፈልጉ! አምልኩት" በማለት ነገራቸው፦
29፥17 ከአላህ ሌላ የምታመልኩት አውሳን ብቻ ነው፥ ውሸትንም ትቀጣጥፋላችሁ፡፡ እነዚያ ከአላህ ሌላ የምታመልኳቸው ለእናንተ ሲሳይን ሊሰጧችሁ አይችሉም፡፡ ስለዚህ ሲሳይን ከአላህ ዘንድ ብቻ ፈልጉ፣ አምልኩት፣ ለእርሱም አመሰግኑ!፡፡ ወደ እእርሱ ትመለሳላችሁ፡፡ إِنَّمَا تَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ أَوْثَانًا وَتَخْلُقُونَ إِفْكًا ۚ إِنَّ الَّذِينَ تَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ لَا يَمْلِكُونَ لَكُمْ رِزْقًا فَابْتَغُوا عِندَ اللَّهِ الرِّزْقَ وَاعْبُدُوهُ وَاشْكُرُوا لَهُ ۖ إِلَيْهِ تُرْجَعُونَ
ከሰማይ እና ከምድር ሲሳይ የሚሰጥ አሏህ እንጂ ድንጋይ አይሰማ፣ አይለማ፣ አይናገር፣ አይጋገር ምኑ ይመለካል? በእርግጥ እነዚያም ጣዖታትን የሚያመልኳት ከመኾን የራቁ ወደ አሏህ የዞሩ ለእነርሱ ብስራት አላቸው፦
39፥17 እነዚያም ጣዖታትን የሚያመልኳት ከመኾን የራቁ ወደ አላህም የዞሩ ለእነርሱ ብስራት አላቸው፡፡ ስለዚህ ባሮቼን አብስር፡፡ وَالَّذِينَ اجْتَنَبُوا الطَّاغُوتَ أَن يَعْبُدُوهَا وَأَنَابُوا إِلَى اللَّهِ لَهُمُ الْبُشْرَىٰ ۚ فَبَشِّرْ عِبَادِ
"ኑስብ" نُصْب ማለት “ሐውልት” ማለት ሲሆን የኑስብ ብዙ ቁጥር ደግሞ “ኑሱብ” نُصُب ወይም “አንሷብ” أَنْصَاب ነው። “አዝላም” أَزْلاَم ማለት ደግሞ “የጥንቆላ ቀስት” ማለት ነው፥ አንሷብ ሆነ አዝላም ከሰይጣን ሥራ የኾኑ እርኩስ ብቻ ናቸው፦
5፥90 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የሚያሰክር መጠጥ ቁማርም *”አንሷብም አዝላምም ከሰይጣን ሥራ የኾኑ እርኩስ ብቻ ናቸው”*፡፡ እርኩስን ራቁትም ልትድኑ ይከጀላልና፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا إِنَّمَا الْخَمْرُ وَالْمَيْسِرُ وَالْأَنصَابُ وَالْأَزْلَامُ رِجْسٌ مِّنْ عَمَلِ الشَّيْطَانِ فَاجْتَنِبُوهُ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
22፥30 ከጣዖታትም ርክሰት ተጠንቀቁ! ሐሰትንም ቃል ራቁ!፡፡ فَاجْتَنِبُوا الرِّجْسَ مِنَ الْأَوْثَانِ وَاجْتَنِبُوا قَوْلَ الزُّورِ
“ጧጉት” طَّٰغُوت የሚለው ቃል “ጦጋ” طَغَىٰ ማለትም “ወሰን አለፈ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “በአሏህ ሐቅ ላይ ወሰን ማለፍ” ማለት ነው፦
79፥17 *ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ “ወሰን አልፏልና”*፡፡ اذْهَبْ إِلَىٰ فِرْعَوْنَ إِنَّهُ طَغَىٰ
79፥24 አለም፡- *«እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»* فَقَالَ أَنَا رَبُّكُمُ الْأَعْلَىٰ
“ወሰን አልፏል” ለሚለው አላፊ ግሥ የገባው ቃል “ጦጋ” طَغَىٰ መሆኑን ልብ አድርግ! ፊርዐውን በአሏህ ሐቅ ላይ ወሰን ያለፈው፦ “እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ” በማለት ነው፥ ስለዚህ በአሏህ ሐቅ ላይ ወሰን ማሳለፊያ ምንነት “ጣዖት” ይባላል። በአሏህ ሐቅ ላይ ወሰን ማሳለፊያ ምንነት “አስናም” እና “አውሳን” ናቸው፥ “አስናም” أَصْنَام ከእንጨት፣ ከብር፣ ከነሐስ፣ ከወርቅ ተሠርቶ አምልኮ የሚቀርብለት ጣዖት ሲሆን “አውሳን” أَوْثَٰن ደግሞ ከድንጋይ ተቀርፆ አምልኮ የሚቀርብለት ጣዖት ነው። ይህ ድርጊት የሚያስረክስ ስለሆነ "ራቁ" ተብሏል፦
74፥5 ጣዖትንም ራቅ፡፡ وَالرُّجْزَ فَاهْجُرْ
22፥30 ከጣዖታትም ርክሰት ተጠንቀቁ! ሐሰትንም ቃል ራቁ!፡፡ فَاجْتَنِبُوا الرِّجْسَ مِنَ الْأَوْثَانِ وَاجْتَنِبُوا قَوْلَ الزُّورِ
የተውሒድ አራማጅ ኢብራሂም፦ "እኔንም ልጆቼንም ጣዖታትን ከመገዛት አርቀን" በማለት ዱዓእ አርጎ ነበር፦
24፥35 ኢብራሂምም፦ "ጌታዬ ሆይ! ይህንን አገር (መካን) ጸጥተኛ አድርገው፡፡ እኔንም ልጆቼንም ጣዖታትን ከመገዛት አርቀን" ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ وَإِذْ قَالَ إِبْرَاهِيمُ رَبِّ اجْعَلْ هَـٰذَا الْبَلَدَ آمِنًا وَاجْنُبْنِي وَبَنِيَّ أَن نَّعْبُدَ الْأَصْنَامَ
ነገር ግን ከእርሱ እና ከልጆች ህልፈት በኃላ ዝርዮቹ የሷሊሕ ሰዎችን ምስል በድንጋይ በመቅረጽ ማምለክ ጀመሩ፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 64, ሐዲስ 401
አቢ ረጃእ አል-ዑጧሪዲይ እንደተረከው፦ "ድንጋይ እናመልክ ነበር፥ የተሻለ ድንጋይ ባገኘን ጊዜ የመጀመሪያውን እንተወው እና ከእርሱ የኃለኛውን እንይዝ ነበር። ነገር ግን ድንጋይ ካላገኘን ከአፈር ሬሳ እንሰበስብ ነበር፥ ከዚያም በእርሱ ላይ በበግ ወተት እንለውስ ነበር። ከዚያም በእርሱ(በሬሳው) እንዞር ነበር"። قَالَ سَمِعْتُ أَبَا رَجَاءٍ الْعُطَارِدِيَّ، يَقُولُ كُنَّا نَعْبُدُ الْحَجَرَ، فَإِذَا وَجَدْنَا حَجَرًا هُوَ أَخْيَرُ مِنْهُ أَلْقَيْنَاهُ وَأَخَذْنَا الآخَرَ، فَإِذَا لَمْ نَجِدْ حَجَرًا جَمَعْنَا جُثْوَةً مِنْ تُرَابٍ، ثُمَّ جِئْنَا بِالشَّاةِ فَحَلَبْنَاهُ عَلَيْهِ، ثُمَّ طُفْنَا بِهِ
ቁሬይሾች ከድንጋይ ተቀርፆ አምልኮ የሚቀርብለት አውሳን ሲያመልኩ አምላካችን አሏህ፦ "ለእናንተ ሲሳይን ሊሰጧችሁ አይችሉም፡፡ ስለዚህ ሲሳይን ከአላህ ዘንድ ብቻ ፈልጉ! አምልኩት" በማለት ነገራቸው፦
29፥17 ከአላህ ሌላ የምታመልኩት አውሳን ብቻ ነው፥ ውሸትንም ትቀጣጥፋላችሁ፡፡ እነዚያ ከአላህ ሌላ የምታመልኳቸው ለእናንተ ሲሳይን ሊሰጧችሁ አይችሉም፡፡ ስለዚህ ሲሳይን ከአላህ ዘንድ ብቻ ፈልጉ፣ አምልኩት፣ ለእርሱም አመሰግኑ!፡፡ ወደ እእርሱ ትመለሳላችሁ፡፡ إِنَّمَا تَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ أَوْثَانًا وَتَخْلُقُونَ إِفْكًا ۚ إِنَّ الَّذِينَ تَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ لَا يَمْلِكُونَ لَكُمْ رِزْقًا فَابْتَغُوا عِندَ اللَّهِ الرِّزْقَ وَاعْبُدُوهُ وَاشْكُرُوا لَهُ ۖ إِلَيْهِ تُرْجَعُونَ
ከሰማይ እና ከምድር ሲሳይ የሚሰጥ አሏህ እንጂ ድንጋይ አይሰማ፣ አይለማ፣ አይናገር፣ አይጋገር ምኑ ይመለካል? በእርግጥ እነዚያም ጣዖታትን የሚያመልኳት ከመኾን የራቁ ወደ አሏህ የዞሩ ለእነርሱ ብስራት አላቸው፦
39፥17 እነዚያም ጣዖታትን የሚያመልኳት ከመኾን የራቁ ወደ አላህም የዞሩ ለእነርሱ ብስራት አላቸው፡፡ ስለዚህ ባሮቼን አብስር፡፡ وَالَّذِينَ اجْتَنَبُوا الطَّاغُوتَ أَن يَعْبُدُوهَا وَأَنَابُوا إِلَى اللَّهِ لَهُمُ الْبُشْرَىٰ ۚ فَبَشِّرْ عِبَادِ
"ኑስብ" نُصْب ማለት “ሐውልት” ማለት ሲሆን የኑስብ ብዙ ቁጥር ደግሞ “ኑሱብ” نُصُب ወይም “አንሷብ” أَنْصَاب ነው። “አዝላም” أَزْلاَم ማለት ደግሞ “የጥንቆላ ቀስት” ማለት ነው፥ አንሷብ ሆነ አዝላም ከሰይጣን ሥራ የኾኑ እርኩስ ብቻ ናቸው፦
5፥90 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የሚያሰክር መጠጥ ቁማርም *”አንሷብም አዝላምም ከሰይጣን ሥራ የኾኑ እርኩስ ብቻ ናቸው”*፡፡ እርኩስን ራቁትም ልትድኑ ይከጀላልና፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا إِنَّمَا الْخَمْرُ وَالْمَيْسِرُ وَالْأَنصَابُ وَالْأَزْلَامُ رِجْسٌ مِّنْ عَمَلِ الشَّيْطَانِ فَاجْتَنِبُوهُ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ
ነቢያችን"ﷺ" ነቢይ ሆነው ሲላኩ መካህ ውስጥ በአሏህ ቤት ዙሪያ ከድንጋይ የተሠሩ ሐውልቶች ነበሩ፥ እነዚህን 360 የሚደርሱ ጣዖታት ነቢያችን"ﷺ" ከመዲና ስደት በኃላ ወደ መካህ ድል አርገው ሲገቡ ሰባብረዋቸዋል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 64, ሐዲስ 320
ዐብደላህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ ”ነቢዩ”ﷺ” በመክፈት ቀን ወደ መካህ በገቡ ጊዜ ሦስት መቶ ስድሳ ኑሱብ በአላህ ቤት ዙሪያ ነበሩ። እርሳቸውም እነርሱን በእጃቸው መስበሪያ በመሰባበር ሲጀምሩ፦ “እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነውና” አሉ”። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ دَخَلَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم مَكَّةَ يَوْمَ الْفَتْحِ وَحَوْلَ الْبَيْتِ سِتُّونَ وَثَلاَثُمِائَةِ نُصُبٍ، فَجَعَلَ يَطْعُنُهَا بِعُودٍ فِي يَدِهِ وَيَقُولُ “ جَاءَ الْحَقُّ وَزَهَقَ الْبَاطِلُ، جَاءَ الْحَقُّ، وَمَا يُبْدِئُ الْبَاطِلُ وَمَا يُعِيدُ ”.
“ተህሊል” تَهْلِيل የሚለው ቃል “ሐለለ” هَلَّلَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ” لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه ማለት ነው፥ “ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ” لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ማለት “አምላክ የለም፥ ከአሏህ በስተቀር” ማለት ነው። ይህ ተህሊል ሁለት ማዕዘናት አሉት፥ እነርሱም፦ “ነፍይ” እና “ኢስባት” ናቸው። “ነፍይ” نَفْي ማለት “ማፍረስ” ማለት ሲሆን ነፍይ “ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ ማለትም “አምላክ የለም” በማለት ጣዖታትን የምናፈራርስበት አዋጅ ነው፥ “ኢስባት” إِثْبَات ማለት “ማፅደቅ” ሲሆን “ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه ማለትም “ከአሏህ በቀር” በማለት የምናጸድቅበት አዋጅ ነው፦
2፥256 “በጣዖትም የሚክድ እና በአላህ የሚያምን ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ዘለበት በእርግጥ ጨበጠ”፡፡ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا
“ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ ስንል በጣዖት መካዳችን ነው፥ “ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه ስንል ደግሞ በሐቅ የሚመለክ አሏህ ብቻ መሆኑን ማመናችን ነው። ስለዚህ ኢሥላም ሰው ሠራሽ ሕግና ሥርዓት ሳይሆን ዐቂደቱ አር-ረባንያህ ስንል አርቲ ቡርቲና ቶራ ቦራ የሆነ ስሑትና መሪር የቡና ወሬ ይዘን ሳይሆን ቁርኣንና ሐዲስን ያማከለ ስሙርና ጥዑም ማስረጃ ይዘን ነው። አምላካችን አሏህ እርሱ ባስቀመጠው መስፈርት እርሱን ብቻ የምናመልክ ባሮቹ ያርገን አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 64, ሐዲስ 320
ዐብደላህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ ”ነቢዩ”ﷺ” በመክፈት ቀን ወደ መካህ በገቡ ጊዜ ሦስት መቶ ስድሳ ኑሱብ በአላህ ቤት ዙሪያ ነበሩ። እርሳቸውም እነርሱን በእጃቸው መስበሪያ በመሰባበር ሲጀምሩ፦ “እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነውና” አሉ”። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ دَخَلَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم مَكَّةَ يَوْمَ الْفَتْحِ وَحَوْلَ الْبَيْتِ سِتُّونَ وَثَلاَثُمِائَةِ نُصُبٍ، فَجَعَلَ يَطْعُنُهَا بِعُودٍ فِي يَدِهِ وَيَقُولُ “ جَاءَ الْحَقُّ وَزَهَقَ الْبَاطِلُ، جَاءَ الْحَقُّ، وَمَا يُبْدِئُ الْبَاطِلُ وَمَا يُعِيدُ ”.
“ተህሊል” تَهْلِيل የሚለው ቃል “ሐለለ” هَلَّلَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ” لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه ማለት ነው፥ “ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ” لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ማለት “አምላክ የለም፥ ከአሏህ በስተቀር” ማለት ነው። ይህ ተህሊል ሁለት ማዕዘናት አሉት፥ እነርሱም፦ “ነፍይ” እና “ኢስባት” ናቸው። “ነፍይ” نَفْي ማለት “ማፍረስ” ማለት ሲሆን ነፍይ “ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ ማለትም “አምላክ የለም” በማለት ጣዖታትን የምናፈራርስበት አዋጅ ነው፥ “ኢስባት” إِثْبَات ማለት “ማፅደቅ” ሲሆን “ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه ማለትም “ከአሏህ በቀር” በማለት የምናጸድቅበት አዋጅ ነው፦
2፥256 “በጣዖትም የሚክድ እና በአላህ የሚያምን ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ዘለበት በእርግጥ ጨበጠ”፡፡ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا
“ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ ስንል በጣዖት መካዳችን ነው፥ “ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه ስንል ደግሞ በሐቅ የሚመለክ አሏህ ብቻ መሆኑን ማመናችን ነው። ስለዚህ ኢሥላም ሰው ሠራሽ ሕግና ሥርዓት ሳይሆን ዐቂደቱ አር-ረባንያህ ስንል አርቲ ቡርቲና ቶራ ቦራ የሆነ ስሑትና መሪር የቡና ወሬ ይዘን ሳይሆን ቁርኣንና ሐዲስን ያማከለ ስሙርና ጥዑም ማስረጃ ይዘን ነው። አምላካችን አሏህ እርሱ ባስቀመጠው መስፈርት እርሱን ብቻ የምናመልክ ባሮቹ ያርገን አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ጦዋፍ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
22፥29 በጥንታዊውም ቤት ይዙሩ፡፡ وَلْيَطَّوَّفُوا بِالْبَيْتِ الْعَتِيقِ
"ሐጅ" حَجّ የሚለው ቃል "ሐጀ" حَجَّ ማለትም "ጎበኘ" ከሚል ሥርወ-ቃል የተገኘ ሲሆን "ጉብኝት" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ ለኢብራሂም፦ "በሰዎችም ውስጥ በሐጅ ትእዛዝ ጥራ" አለው፦
22፥27 አልነውም፦ "በሰዎችም ውስጥ በሐጅ ትእዛዝ ጥራ!፡፡ وَأَذِّن فِي النَّاسِ بِالْحَجِّ يَأْتُوكَ رِجَالًا
3፥97 ለአላህም በሰዎች ላይ ወደ እርሱ መኼድን በቻለ ሁሉ ላይ ቤቱን መጎብኘት ግዴታ አለባቸው፡፡ وَلِلَّهِ عَلَى النَّاسِ حِجُّ الْبَيْتِ مَنِ اسْتَطَاعَ إِلَيْهِ سَبِيلًا
ሰዎች የአሏህን ቤት ሲጎበኙ በመዘዋወር ዙሪያውን ይዞራሉ፥ አምላካችን አሏህም፦ "በጥንታዊውም ቤት ይዙሩ" ብሎ ተናግሯል፦
22፥29 በጥንታዊውም ቤት ይዙሩ፡፡ وَلْيَطَّوَّفُوا بِالْبَيْتِ الْعَتِيقِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ይዙሩ" ለሚል የገባው የግሥ መደብ "የጦወፉ" يَطَّوَّفُوا እንደሆነ ልብ አድርግ! "ጦዋፍ" طَواف የሚለው ቃል "ጧፈ" طَافَ ማለትም "ዞረ" ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ዙረት" ማለት ነው፥ ቤቱን በመጎብኘት መዞር አምላካችን አሏህ ለኢብራሂም የሰጠው ትእዛዝ ነው፦
22፥26 ለኢብራሂምም፦ "የቤቱን” ስፍራ መመለሻ ባደረግንለት ጊዜ "በእኔ ምንንም አታጋራ! "ቤቴንም” ለሚዞሩት" እና ለሚቆሙበት፣ ለሚያጎነብሱትና በግንባራቸውም ለሚደፉት ንጹሕ አድርግላቸው፣ ”ባልነው ጊዜ አስታውስ”። وَإِذْ بَوَّأْنَا لِإِبْرَٰهِيمَ مَكَانَ ٱلْبَيْتِ أَن لَّا تُشْرِكْ بِى شَيْـًۭٔا وَطَهِّرْ بَيْتِىَ لِلطَّآئِفِينَ وَٱلْقَآئِمِينَ وَٱلرُّكَّعِ ٱلسُّجُودِ
"ሚዞሩት" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ጧዒፊን" طَّائِفِين ሲሆን "በእኔ ምንም አታጋራ" ብሎ የተናገረው "እኔነት" ያለው ነባቢ መለኮት ነው፥ ይህ ለኢብራሂም ጦዋፍን ያዘዘ ነባቢ መለኮት ለነቢያችን"ﷺ"፦ "ለኢብራሂምም ባልነው ጊዜ አስታውስ" በማለት ይናገራል። ነገር ግን ከኢብራሂም እና ከልጆች ህልፈት በኃላ ዝርዮቹ የሷሊሕ ሰዎችን ምስል በድንጋይ በመቅረጽ ማምለክ ጀመሩ፥ ይህም አልበቃ ብሏቸው ከአፈር ሬሳ በመሰብሰብ በእርሱ ላይ በበግ ወተት ለውሰው ይዞሩት ነበር፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 64, ሐዲስ 401
አቢ ረጃእ አል-ዑጧሪዲይ እንደተረከው፦ "ድንጋይ እናመልክ ነበር፥ የተሻለ ድንጋይ ባገኘን ጊዜ የመጀመሪያውን እንተወው እና ከእርሱ የኃለኛውን እንይዝ ነበር። ነገር ግን ድንጋይ ካላገኘን ከአፈር ሬሳ እንሰበስብ ነበር፥ ከዚያም በእርሱ ላይ በበግ ወተት እንለውስ ነበር። ከዚያም በእርሱ(በሬሳው) እንዞር ነበር"። قَالَ سَمِعْتُ أَبَا رَجَاءٍ الْعُطَارِدِيَّ، يَقُولُ كُنَّا نَعْبُدُ الْحَجَرَ، فَإِذَا وَجَدْنَا حَجَرًا هُوَ أَخْيَرُ مِنْهُ أَلْقَيْنَاهُ وَأَخَذْنَا الآخَرَ، فَإِذَا لَمْ نَجِدْ حَجَرًا جَمَعْنَا جُثْوَةً مِنْ تُرَابٍ، ثُمَّ جِئْنَا بِالشَّاةِ فَحَلَبْنَاهُ عَلَيْهِ، ثُمَّ طُفْنَا بِهِ
ቁረይሾች ሬሳን መዞራቸውን በአሉታዊ መልኩ የገለጸው ሐዲስ ሆነ ከጥንትም የአሏህ ቤት በመጎብኘት የመዞር ትእዛዝ መኖሩን በአውንታዊ መልኩ የገለጸው ቁርኣን የእኛ መጽሐፍት ናቸው፥ ስለዚህ ቁረይሾች ሬሳን ከመዞራቸው በፊት አሏህ ለኢብራሂም የሰጠው ትእዛዝ መሆኑን መቀበል ይኖርባችኃል እንጂ "ጦዋፍ የተጀመረው ከቁረይሾች ነው" ብላችሁ መቅጠፍ የለባችሁም። ኢሥላም በግልጠተ መለኮት የመጣ የአሏህ ዲን እንጂ ቁሬይሾች በጅህልናቸው በጃሂሊያህ ጊዜ የሚያደርጉት ድርጊት በፍጹም አይደለም፥ ቁርኣን ከመውረዱ በፊት የነበረውን የጃሂሊያህን ሥርዓት ኢሥላም ውስጥ መክተት አሏህ ዘንድ የተጠላ ሥራ መሆኑን ለሙሥሊም ሙበሽር አይነግረውም፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 87 ሐዲስ 21
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ "ነቢዩም፦ "ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ ዘንድ የተጠሉ ሦስት ሰዎች አሉ፦ "በተከበረው ቤት ውስጥ ያለ እምነት አልባ፣ የጃሂሊያህን ሥርዓት ኢሥላም ውስጥ ለማስቀረት የሚፈልግ እና ያለ ሕግ የአንድ ሰው ደም ማፍሰስ የሚፈልግ። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ أَبْغَضُ النَّاسِ إِلَى اللَّهِ ثَلاَثَةٌ مُلْحِدٌ فِي الْحَرَمِ، وَمُبْتَغٍ فِي الإِسْلاَمِ سُنَّةَ الْجَاهِلِيَّةِ، وَمُطَّلِبُ دَمِ امْرِئٍ بِغَيْرِ حَقٍّ لِيُهَرِيقَ دَمَهُ
፨በክርስትና ጽብሓውያን ኦርቶዶክስ፣ መለካውያን ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ እና አንግሊካን በቅዳሴ ጊዜ የሚዞሩት ቁርባን የሚፈተትበት "መሠዊያ"altar" አላቸው። ሩቅ ሳንሄድ ኦርቶዶክስ በአገራችን በጽጌ ፆም ውስጥ ማኅሌተ ጽጌ ላይ በሳምንት አንዴ ቅዳሜ ለእሑድ ሌሊት ቅኔ ማኅሌቱ ይዞራል፥ በተለይ የመጨረሻው ቀን "ተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌ" በማለት ይዞራል። ትዝታችንን አትቀስቅሱብና!
፨በአይሁዳውያን በዓመት ሦስት ጊዜ የዳስ በዓል፣ በዓለ ኃምሳ እና ፋሲካ ሊያከብሩ ሲሉ በወሩ ከ 15 እስከ 21 ለሥድስት ወይም ለሰባት ቀን ሲጎበኙ ይዞራሉ፥ "ሱካህ" סוכה ማለትም "ድንኳን" ማለት ሲሆን ድንኳኑን የሚዞሩት ዙረት "ሐካፋህ" ይባላል። "ሐካፋህ" הקפה ማለት "ዙረት" ማለት ሲሆን የሚዞሩት ሰባት ጊዜ ስለሆነ "ሐካፉት" הקפות ይሉታል፥ ይህም በሚንሃግ፣ በሚድራሽ እና በባቢሎን ታልሙድ ተዘግቧል።
፨በዳርሚክ ሃይማኖት በሂንዱ፣ በጃይኒዝም እና በቡዲዝም ውስጥ መቅደሱን መዞር "ፓሪክራማ" ይባላል፥ ይህም በ 3102 ቅድመ ልደት ክርሪሽና ለአርጁን ባስተላለፈው መልእክት በባጋድ ጊታ ውስጥ፣ በ 1500 ቅድመ ልደት ከአርያን ወደ ህንድ የሄዱት ነቢያት የቬዳስ ማለትም ያዙር ቬድ፣ ሪግ ቬድ፣ ሳም ቬድ እና አግራፋ ቬድ ውስጥ፣ በካልኪን ፑራራ፣ በቪሽኑ ፑራና፣ በብርሃማ ፑራና ውስጥ ተዘግቧል።
ስለዚህ ጦዋፍን ሳያውቁ መተቸት አለማወቃችሁን ያሳብቃል፥ ሳይቀመጡ እግር መዘርጋት ለመፈንገል ነውና ቅድሚያ ሃይማኖታችሁን አጥኑ! ሙሥሊም የሚያመልከው ሁሉንም ነገር የፈጠረውን፣ የዓለማቱ ጌታ፣ ከፍጥረት በላይ ያለውን አሏህን ብቻ መሆኑን ውስጣችሁ እያወቀ ባዕድ አምልኮ ለማስባል የምትቆፍሩት ጉድጓድ መቀበሪአችሁ ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ቤቱን ከሚጎበኙት ባሮቹ ያርገን አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
22፥29 በጥንታዊውም ቤት ይዙሩ፡፡ وَلْيَطَّوَّفُوا بِالْبَيْتِ الْعَتِيقِ
"ሐጅ" حَجّ የሚለው ቃል "ሐጀ" حَجَّ ማለትም "ጎበኘ" ከሚል ሥርወ-ቃል የተገኘ ሲሆን "ጉብኝት" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ ለኢብራሂም፦ "በሰዎችም ውስጥ በሐጅ ትእዛዝ ጥራ" አለው፦
22፥27 አልነውም፦ "በሰዎችም ውስጥ በሐጅ ትእዛዝ ጥራ!፡፡ وَأَذِّن فِي النَّاسِ بِالْحَجِّ يَأْتُوكَ رِجَالًا
3፥97 ለአላህም በሰዎች ላይ ወደ እርሱ መኼድን በቻለ ሁሉ ላይ ቤቱን መጎብኘት ግዴታ አለባቸው፡፡ وَلِلَّهِ عَلَى النَّاسِ حِجُّ الْبَيْتِ مَنِ اسْتَطَاعَ إِلَيْهِ سَبِيلًا
ሰዎች የአሏህን ቤት ሲጎበኙ በመዘዋወር ዙሪያውን ይዞራሉ፥ አምላካችን አሏህም፦ "በጥንታዊውም ቤት ይዙሩ" ብሎ ተናግሯል፦
22፥29 በጥንታዊውም ቤት ይዙሩ፡፡ وَلْيَطَّوَّفُوا بِالْبَيْتِ الْعَتِيقِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ይዙሩ" ለሚል የገባው የግሥ መደብ "የጦወፉ" يَطَّوَّفُوا እንደሆነ ልብ አድርግ! "ጦዋፍ" طَواف የሚለው ቃል "ጧፈ" طَافَ ማለትም "ዞረ" ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ዙረት" ማለት ነው፥ ቤቱን በመጎብኘት መዞር አምላካችን አሏህ ለኢብራሂም የሰጠው ትእዛዝ ነው፦
22፥26 ለኢብራሂምም፦ "የቤቱን” ስፍራ መመለሻ ባደረግንለት ጊዜ "በእኔ ምንንም አታጋራ! "ቤቴንም” ለሚዞሩት" እና ለሚቆሙበት፣ ለሚያጎነብሱትና በግንባራቸውም ለሚደፉት ንጹሕ አድርግላቸው፣ ”ባልነው ጊዜ አስታውስ”። وَإِذْ بَوَّأْنَا لِإِبْرَٰهِيمَ مَكَانَ ٱلْبَيْتِ أَن لَّا تُشْرِكْ بِى شَيْـًۭٔا وَطَهِّرْ بَيْتِىَ لِلطَّآئِفِينَ وَٱلْقَآئِمِينَ وَٱلرُّكَّعِ ٱلسُّجُودِ
"ሚዞሩት" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ጧዒፊን" طَّائِفِين ሲሆን "በእኔ ምንም አታጋራ" ብሎ የተናገረው "እኔነት" ያለው ነባቢ መለኮት ነው፥ ይህ ለኢብራሂም ጦዋፍን ያዘዘ ነባቢ መለኮት ለነቢያችን"ﷺ"፦ "ለኢብራሂምም ባልነው ጊዜ አስታውስ" በማለት ይናገራል። ነገር ግን ከኢብራሂም እና ከልጆች ህልፈት በኃላ ዝርዮቹ የሷሊሕ ሰዎችን ምስል በድንጋይ በመቅረጽ ማምለክ ጀመሩ፥ ይህም አልበቃ ብሏቸው ከአፈር ሬሳ በመሰብሰብ በእርሱ ላይ በበግ ወተት ለውሰው ይዞሩት ነበር፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 64, ሐዲስ 401
አቢ ረጃእ አል-ዑጧሪዲይ እንደተረከው፦ "ድንጋይ እናመልክ ነበር፥ የተሻለ ድንጋይ ባገኘን ጊዜ የመጀመሪያውን እንተወው እና ከእርሱ የኃለኛውን እንይዝ ነበር። ነገር ግን ድንጋይ ካላገኘን ከአፈር ሬሳ እንሰበስብ ነበር፥ ከዚያም በእርሱ ላይ በበግ ወተት እንለውስ ነበር። ከዚያም በእርሱ(በሬሳው) እንዞር ነበር"። قَالَ سَمِعْتُ أَبَا رَجَاءٍ الْعُطَارِدِيَّ، يَقُولُ كُنَّا نَعْبُدُ الْحَجَرَ، فَإِذَا وَجَدْنَا حَجَرًا هُوَ أَخْيَرُ مِنْهُ أَلْقَيْنَاهُ وَأَخَذْنَا الآخَرَ، فَإِذَا لَمْ نَجِدْ حَجَرًا جَمَعْنَا جُثْوَةً مِنْ تُرَابٍ، ثُمَّ جِئْنَا بِالشَّاةِ فَحَلَبْنَاهُ عَلَيْهِ، ثُمَّ طُفْنَا بِهِ
ቁረይሾች ሬሳን መዞራቸውን በአሉታዊ መልኩ የገለጸው ሐዲስ ሆነ ከጥንትም የአሏህ ቤት በመጎብኘት የመዞር ትእዛዝ መኖሩን በአውንታዊ መልኩ የገለጸው ቁርኣን የእኛ መጽሐፍት ናቸው፥ ስለዚህ ቁረይሾች ሬሳን ከመዞራቸው በፊት አሏህ ለኢብራሂም የሰጠው ትእዛዝ መሆኑን መቀበል ይኖርባችኃል እንጂ "ጦዋፍ የተጀመረው ከቁረይሾች ነው" ብላችሁ መቅጠፍ የለባችሁም። ኢሥላም በግልጠተ መለኮት የመጣ የአሏህ ዲን እንጂ ቁሬይሾች በጅህልናቸው በጃሂሊያህ ጊዜ የሚያደርጉት ድርጊት በፍጹም አይደለም፥ ቁርኣን ከመውረዱ በፊት የነበረውን የጃሂሊያህን ሥርዓት ኢሥላም ውስጥ መክተት አሏህ ዘንድ የተጠላ ሥራ መሆኑን ለሙሥሊም ሙበሽር አይነግረውም፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 87 ሐዲስ 21
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ "ነቢዩም፦ "ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ ዘንድ የተጠሉ ሦስት ሰዎች አሉ፦ "በተከበረው ቤት ውስጥ ያለ እምነት አልባ፣ የጃሂሊያህን ሥርዓት ኢሥላም ውስጥ ለማስቀረት የሚፈልግ እና ያለ ሕግ የአንድ ሰው ደም ማፍሰስ የሚፈልግ። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ أَبْغَضُ النَّاسِ إِلَى اللَّهِ ثَلاَثَةٌ مُلْحِدٌ فِي الْحَرَمِ، وَمُبْتَغٍ فِي الإِسْلاَمِ سُنَّةَ الْجَاهِلِيَّةِ، وَمُطَّلِبُ دَمِ امْرِئٍ بِغَيْرِ حَقٍّ لِيُهَرِيقَ دَمَهُ
፨በክርስትና ጽብሓውያን ኦርቶዶክስ፣ መለካውያን ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ እና አንግሊካን በቅዳሴ ጊዜ የሚዞሩት ቁርባን የሚፈተትበት "መሠዊያ"altar" አላቸው። ሩቅ ሳንሄድ ኦርቶዶክስ በአገራችን በጽጌ ፆም ውስጥ ማኅሌተ ጽጌ ላይ በሳምንት አንዴ ቅዳሜ ለእሑድ ሌሊት ቅኔ ማኅሌቱ ይዞራል፥ በተለይ የመጨረሻው ቀን "ተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌ" በማለት ይዞራል። ትዝታችንን አትቀስቅሱብና!
፨በአይሁዳውያን በዓመት ሦስት ጊዜ የዳስ በዓል፣ በዓለ ኃምሳ እና ፋሲካ ሊያከብሩ ሲሉ በወሩ ከ 15 እስከ 21 ለሥድስት ወይም ለሰባት ቀን ሲጎበኙ ይዞራሉ፥ "ሱካህ" סוכה ማለትም "ድንኳን" ማለት ሲሆን ድንኳኑን የሚዞሩት ዙረት "ሐካፋህ" ይባላል። "ሐካፋህ" הקפה ማለት "ዙረት" ማለት ሲሆን የሚዞሩት ሰባት ጊዜ ስለሆነ "ሐካፉት" הקפות ይሉታል፥ ይህም በሚንሃግ፣ በሚድራሽ እና በባቢሎን ታልሙድ ተዘግቧል።
፨በዳርሚክ ሃይማኖት በሂንዱ፣ በጃይኒዝም እና በቡዲዝም ውስጥ መቅደሱን መዞር "ፓሪክራማ" ይባላል፥ ይህም በ 3102 ቅድመ ልደት ክርሪሽና ለአርጁን ባስተላለፈው መልእክት በባጋድ ጊታ ውስጥ፣ በ 1500 ቅድመ ልደት ከአርያን ወደ ህንድ የሄዱት ነቢያት የቬዳስ ማለትም ያዙር ቬድ፣ ሪግ ቬድ፣ ሳም ቬድ እና አግራፋ ቬድ ውስጥ፣ በካልኪን ፑራራ፣ በቪሽኑ ፑራና፣ በብርሃማ ፑራና ውስጥ ተዘግቧል።
ስለዚህ ጦዋፍን ሳያውቁ መተቸት አለማወቃችሁን ያሳብቃል፥ ሳይቀመጡ እግር መዘርጋት ለመፈንገል ነውና ቅድሚያ ሃይማኖታችሁን አጥኑ! ሙሥሊም የሚያመልከው ሁሉንም ነገር የፈጠረውን፣ የዓለማቱ ጌታ፣ ከፍጥረት በላይ ያለውን አሏህን ብቻ መሆኑን ውስጣችሁ እያወቀ ባዕድ አምልኮ ለማስባል የምትቆፍሩት ጉድጓድ መቀበሪአችሁ ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ቤቱን ከሚጎበኙት ባሮቹ ያርገን አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የጁሙዓህ ሰዋብ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
62፥9 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በጁሙዓህ ቀን ለሶላት ጥሪ በተደረገ ጊዜ ወደ አላህ ማውሳት ኺዱ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا إِذَا نُودِيَ لِلصَّلَاةِ مِن يَوْمِ الْجُمُعَةِ فَاسْعَوْا إِلَىٰ ذِكْرِ اللَّهِ
"ሙሥተሐብ" مُسْتَحَبّ የሚለው ቃል "ኢሥተሐበ" اِسْتَحَبَّ ማለትም "አስወደደ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "የተወደደ"supererogatory" ማለት ነው፥ አንድን ነገር በማድረግ ምንዳ የሚያስገኝ በተቃራኒው ባለማድረግ ምንም ፍዳን የማያስገኝ መርሕ ሙሥተሐብ ይባላል። የጁሙዓህ ቀን ሙሉ ትጥበት ሙሥተሐብ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 11, ሐዲስ 2
ዐብደሏህ ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ከእናንተ ማንም ጁሙዓህ በመጣ ጊዜ ይታጠብ"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عُمَرَ ـ رضى الله عنهما ـ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " إِذَا جَاءَ أَحَدُكُمُ الْجُمُعَةَ فَلْيَغْتَسِلْ ".
እዚህ ሐዲስ ላይ "ይታጠብ" ለሚለው የገባው ቃል "የግተሢል" يَغْتَسِلْ እንደሆነ ልብ አድርግ! "ጉሥል" غُسْل የሚለው ቃል "ገሠለ" غَسَلَ ማለትም "ሙሉውን ታጠበ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ሙሉ ትጥበት"full ablution" ማለት ነው፥ ጉሥል በጁሙዓህ ቀን ማድረግ ዋጂብ ነው፦
ሡነን አቢ ዳድው መጽሐፍ 1, ሐዲስ 341
አቢ ሠዒድ አል-ኹድሪይ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ጉሥል በጁሙዓህ ቀን ማድረግ በሁሉም ጎልማሳ ላይ ዋጂብ ነው"። عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيِّ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " غُسْلُ يَوْمِ الْجُمُعَةِ وَاجِبٌ عَلَى كُلِّ مُحْتَلِمٍ " .
"ዋጂብ" وَاجِب የሚለው ቃል "ወጀበ" وَجَبَ ማለትም "አስፈለገ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "አስፈላጊ"compulsory" ማለት ነው፥ በጁሙዓህ ቀን በመልካም ውዱእ አድርጎ ጁሙዓህ መምጣት እና በጥሞና በቅጡ መስማት ያለው ሰዋብ በጁሙዓህ እና በጁሙዓህ መካከል ያለው ኃጢአት ይቅር መባል ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 7, ሐዲስ 38
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "በመልካም ውዱእ ያረገ፣ ከዚያም ጁሙዓህ የመጣ፣ በቅጡ የሰማ እና ያዳመጠ በጁሙዓህ እና በጁሙዓህ መካከል ያለው ኃጢአቱ ይቅር ይባልለታል"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " مَنْ تَوَضَّأَ فَأَحْسَنَ الْوُضُوءَ ثُمَّ أَتَى الْجُمُعَةَ فَاسْتَمَعَ وَأَنْصَتَ غُفِرَ لَهُ مَا بَيْنَهُ وَبَيْنَ الْجُمُعَةِ " .
"ሰዋብ" ثَوَاب ማለት "ትሩፋት" "ትርሲት" "ስርጉት" ማለት ነው። አምላካችን አሏህ በጁሙዓህ የሚገኘውን ሰዋብ ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
62፥9 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በጁሙዓህ ቀን ለሶላት ጥሪ በተደረገ ጊዜ ወደ አላህ ማውሳት ኺዱ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا إِذَا نُودِيَ لِلصَّلَاةِ مِن يَوْمِ الْجُمُعَةِ فَاسْعَوْا إِلَىٰ ذِكْرِ اللَّهِ
"ሙሥተሐብ" مُسْتَحَبّ የሚለው ቃል "ኢሥተሐበ" اِسْتَحَبَّ ማለትም "አስወደደ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "የተወደደ"supererogatory" ማለት ነው፥ አንድን ነገር በማድረግ ምንዳ የሚያስገኝ በተቃራኒው ባለማድረግ ምንም ፍዳን የማያስገኝ መርሕ ሙሥተሐብ ይባላል። የጁሙዓህ ቀን ሙሉ ትጥበት ሙሥተሐብ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 11, ሐዲስ 2
ዐብደሏህ ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ከእናንተ ማንም ጁሙዓህ በመጣ ጊዜ ይታጠብ"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عُمَرَ ـ رضى الله عنهما ـ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " إِذَا جَاءَ أَحَدُكُمُ الْجُمُعَةَ فَلْيَغْتَسِلْ ".
እዚህ ሐዲስ ላይ "ይታጠብ" ለሚለው የገባው ቃል "የግተሢል" يَغْتَسِلْ እንደሆነ ልብ አድርግ! "ጉሥል" غُسْل የሚለው ቃል "ገሠለ" غَسَلَ ማለትም "ሙሉውን ታጠበ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ሙሉ ትጥበት"full ablution" ማለት ነው፥ ጉሥል በጁሙዓህ ቀን ማድረግ ዋጂብ ነው፦
ሡነን አቢ ዳድው መጽሐፍ 1, ሐዲስ 341
አቢ ሠዒድ አል-ኹድሪይ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ጉሥል በጁሙዓህ ቀን ማድረግ በሁሉም ጎልማሳ ላይ ዋጂብ ነው"። عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيِّ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " غُسْلُ يَوْمِ الْجُمُعَةِ وَاجِبٌ عَلَى كُلِّ مُحْتَلِمٍ " .
"ዋጂብ" وَاجِب የሚለው ቃል "ወጀበ" وَجَبَ ማለትም "አስፈለገ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "አስፈላጊ"compulsory" ማለት ነው፥ በጁሙዓህ ቀን በመልካም ውዱእ አድርጎ ጁሙዓህ መምጣት እና በጥሞና በቅጡ መስማት ያለው ሰዋብ በጁሙዓህ እና በጁሙዓህ መካከል ያለው ኃጢአት ይቅር መባል ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 7, ሐዲስ 38
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "በመልካም ውዱእ ያረገ፣ ከዚያም ጁሙዓህ የመጣ፣ በቅጡ የሰማ እና ያዳመጠ በጁሙዓህ እና በጁሙዓህ መካከል ያለው ኃጢአቱ ይቅር ይባልለታል"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " مَنْ تَوَضَّأَ فَأَحْسَنَ الْوُضُوءَ ثُمَّ أَتَى الْجُمُعَةَ فَاسْتَمَعَ وَأَنْصَتَ غُفِرَ لَهُ مَا بَيْنَهُ وَبَيْنَ الْجُمُعَةِ " .
"ሰዋብ" ثَوَاب ማለት "ትሩፋት" "ትርሲት" "ስርጉት" ማለት ነው። አምላካችን አሏህ በጁሙዓህ የሚገኘውን ሰዋብ ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ተውሒደ አር-ሩቡቢያህ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
6፥164 በላቸው «እርሱ አላህ የሁሉ ጌታ ሲኾን ከአላህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን? قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْء
"ረብ" رَبّ የሚለው ቃል "ረበ" رَبَّ ማለትም "ገዛ" "አዘዘ" "አስተናበረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ገዥ" "ጌታ" "አዛዥ" "አስተናባሪ" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ የሁሉም ነገር ጌታ ነው፦
6፥164 በላቸው «እርሱ አላህ የሁሉ ጌታ ሲኾን ከአላህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን? قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْء
13፥16 የሰማያትና የምድር “ጌታ” ማን ነው? በላቸው! አላህ ነው በል። قُلْ مَن رَّبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ قُلِ ٱللَّهُ ۚ
19፥65 እርሱ የሰማያት እና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነው እና አምልከው! እርሱን በአምልኮ ላይ ታገስ! ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን?። رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا فَاعْبُدْهُ وَاصْطَبِرْ لِعِبَادَتِهِ ۚ هَلْ تَعْلَمُ لَهُ سَمِيًّا
እዚህ አንቀጽ ላይ "እርሱ የሰማያት እና የምድር፣ በሁለቱም መካካል ላለዉ ሁሉ “ጌታ” ነው" ሲል ተውሒደ አር-ሩቡቢያን ያሳያል፣ "አምልከው! እርሱን በአምልኮ ላይ ታገስ” ሲል ተውሒደል ኡሉሂያን ያሳያል፣ "ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን" ሲል ደግሞ ተውሒደል አሥማእ ወስ-ሲፋትን ያመለክታል።
"ተውሒድ" تَوْحِيد የሚለው ቃል "ዋሐደ" وَٰحَدَ ማለትም "አንድ አደረገ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "አንድነት"oneness" ማለት ነው፥ የስም መደቡ ደግሞ "ዋሒድ” وَٰحِد ነው። አሏህን በጌትነቱ ከፍጡራን ነጥሎ ስልጣኑን መቀበል "ተውሒደ አር-ሩቡቢያህ" تَوْحِيد الرُبُوبِيّة ይባላል፥ "ሩቡቢያህ" رُبُوبِيّة ማለት "ጌትነት" ማለት ሲሆን አሏህ ብቻውን ነገርን ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣ ጌታ መሆኑን እና ሕግ በማውጣት ጽንፈ ዓለማትን የሚያስተናብር ጌታ መሆኑን የሚያስረዳ ነው፦
39፥62 አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡ اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ ۖ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ
42፥21 ከሃይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነርሱ የደነገጉ ተጋሪዎች ለእነርሱ አሏቸውን? أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ شَرَعُوا لَهُم مِّنَ الدِّينِ مَا لَمْ يَأْذَن بِهِ اللَّهُ
“ሸሪክ” شَرِيك ማለት “ተጋሪ” ማለት ነው፥ የሸሪክ ብዙ ቁጥር ደግሞ “ሹረካእ” شُرَكَاء ሲሆን “ተጋሪዎች” ማለት ነው። አሏህ በእርሱ ያልፈቀደውን ነገር ሐላል ማድረግ ለእነርሱ የደነገጉ በአላህ ሐቅ ላይ ተጋሪዎች አሏቸው፥ "የደነገጉ" ለሚለው የገባው ቃል “ሸረዑ” شَرَعُوا ሲሆን ሸሪዓህ መደንገጋቸው የሚያሳይ ቃል ነው። ለዚህ ነው “ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው” ነው ያለው፥ አይሁዳውያን ሊቃውንቶቻቸውን እንዲሁ ክርስቲያኖች መነኮሳታቸውን በአሏህ ላይ በማጋራት ጌቶች አድርገው ያዙ፦
9፥31 ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለውን አንድን አምላክ ሊያመልኩ እንጂ ያልታዘዙ ሲኾኑ ሊቃውንቶቻቸውን እና መነኮሳታቸውን ከአላህ ሌላ አርባብ አድርገው ያዙ፥ እንዲሁ የመርየምን ልጅ አልመሲሕንም ያዙ። ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው፡፡ اتَّخَذُوا أَحْبَارَهُمْ وَرُهْبَانَهُمْ أَرْبَابًا مِّن دُونِ اللَّهِ وَالْمَسِيحَ ابْنَ مَرْيَمَ وَمَا أُمِرُوا إِلَّا لِيَعْبُدُوا إِلَـٰهًا وَاحِدًا ۖ لَّا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۚ سُبْحَانَهُ عَمَّا يُشْرِكُونَ
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 147
ዐዲይ ኢብኑ ሓቲም እንደተረከው፦ ”ወደ ነቢዩም”ﷺ” ስመጣ በአንገቴ ዙሪያ የወርቅሐራም መስቀል ነበረኝ፥ እርሳቸውም፦ “ዐዲይ ሆይ! ይህንን ጣዖት ከአንተ አስወግድ” አሉ። ሱረቱል በራኣህ "ሊቃውንቶቻቸውን እና መነኮሳታቸውን ከአሏህ ሌላ አርባብ አድርገው ያዙ" የሚለው ሲነበብ ሰማዋቸው። እርሳቸውም፦ ለእነርሱ አያመልኳቸውም፥ ነገር ግን ሐላል ባደረጉላቸው ጊዜ ሐላል አርገው ይቀበሉታል። ባደረጉላቸው ጊዜ ሐራም አርገው ይቀበሉታል” አሉ። عَنْ عَدِيِّ بْنِ حَاتِمٍ، قَالَ أَتَيْتُ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم وَفِي عُنُقِي صَلِيبٌ مِنْ ذَهَبٍ . فَقَالَ ” يَا عَدِيُّ اطْرَحْ عَنْكَ هَذَا الْوَثَنَ ” . وَسَمِعْتُهُ يَقْرَأُ فِي سُورَةِ بَرَاءَةََ : ( اتَّخَذُوا أَحْبَارَهُمْ وَرُهْبَانَهُمْ أَرْبَابًا مِنْ دُونِ اللَّهِ ) قَالَ ” أَمَا إِنَّهُمْ لَمْ يَكُونُوا يَعْبُدُونَهُمْ وَلَكِنَّهُمْ كَانُوا إِذَا أَحَلُّوا لَهُمْ شَيْئًا اسْتَحَلُّوهُ وَإِذَا حَرَّمُوا عَلَيْهِمْ شَيْئًا حَرَّمُوهُ
“አርባብ” أَرْبَاب የሚለው ቃል "ረብ" رَبّ ለሚለው ብዙ ቁጥር ሲሆን "ጌቶች" ማለት ነው፥ አንድን ነገር ፈድር፣ ሙስተሐብ፣ ሙባሕ፣ መክሩህ፣ እና ሐራም ማለት የሚችለው ብቸኛው ባለ ሥልጣን አሏህ ብቻ ነው። ነቢያችን”ﷺ” ሆኑ አሚሮቻችን አሏህ ባዘዘው ያዛሉ እንዲሁ በከለከለው ይከለክላሉ እንጂ የእራሳቸው ድንጋጌ አያወጡም፦
16፥116 በአላህም ላይ ውሸትን ልትቀጣጥፉ ምላሶቻችሁ በሚመጥኑት ውሸት «ይህ የተፈቀደ ነው፤ ይህም እርም ነው» አትበሉ፡፡ وَلَا تَقُولُوا لِمَا تَصِفُ أَلْسِنَتُكُمُ الْكَذِبَ هَـٰذَا حَلَالٌ وَهَـٰذَا حَرَامٌ لِّتَفْتَرُوا عَلَى اللَّهِ الْكَذِبَ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
6፥164 በላቸው «እርሱ አላህ የሁሉ ጌታ ሲኾን ከአላህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን? قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْء
"ረብ" رَبّ የሚለው ቃል "ረበ" رَبَّ ማለትም "ገዛ" "አዘዘ" "አስተናበረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ገዥ" "ጌታ" "አዛዥ" "አስተናባሪ" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ የሁሉም ነገር ጌታ ነው፦
6፥164 በላቸው «እርሱ አላህ የሁሉ ጌታ ሲኾን ከአላህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን? قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْء
13፥16 የሰማያትና የምድር “ጌታ” ማን ነው? በላቸው! አላህ ነው በል። قُلْ مَن رَّبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ قُلِ ٱللَّهُ ۚ
19፥65 እርሱ የሰማያት እና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነው እና አምልከው! እርሱን በአምልኮ ላይ ታገስ! ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን?። رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا فَاعْبُدْهُ وَاصْطَبِرْ لِعِبَادَتِهِ ۚ هَلْ تَعْلَمُ لَهُ سَمِيًّا
እዚህ አንቀጽ ላይ "እርሱ የሰማያት እና የምድር፣ በሁለቱም መካካል ላለዉ ሁሉ “ጌታ” ነው" ሲል ተውሒደ አር-ሩቡቢያን ያሳያል፣ "አምልከው! እርሱን በአምልኮ ላይ ታገስ” ሲል ተውሒደል ኡሉሂያን ያሳያል፣ "ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን" ሲል ደግሞ ተውሒደል አሥማእ ወስ-ሲፋትን ያመለክታል።
"ተውሒድ" تَوْحِيد የሚለው ቃል "ዋሐደ" وَٰحَدَ ማለትም "አንድ አደረገ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "አንድነት"oneness" ማለት ነው፥ የስም መደቡ ደግሞ "ዋሒድ” وَٰحِد ነው። አሏህን በጌትነቱ ከፍጡራን ነጥሎ ስልጣኑን መቀበል "ተውሒደ አር-ሩቡቢያህ" تَوْحِيد الرُبُوبِيّة ይባላል፥ "ሩቡቢያህ" رُبُوبِيّة ማለት "ጌትነት" ማለት ሲሆን አሏህ ብቻውን ነገርን ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣ ጌታ መሆኑን እና ሕግ በማውጣት ጽንፈ ዓለማትን የሚያስተናብር ጌታ መሆኑን የሚያስረዳ ነው፦
39፥62 አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡ اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ ۖ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ
42፥21 ከሃይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነርሱ የደነገጉ ተጋሪዎች ለእነርሱ አሏቸውን? أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ شَرَعُوا لَهُم مِّنَ الدِّينِ مَا لَمْ يَأْذَن بِهِ اللَّهُ
“ሸሪክ” شَرِيك ማለት “ተጋሪ” ማለት ነው፥ የሸሪክ ብዙ ቁጥር ደግሞ “ሹረካእ” شُرَكَاء ሲሆን “ተጋሪዎች” ማለት ነው። አሏህ በእርሱ ያልፈቀደውን ነገር ሐላል ማድረግ ለእነርሱ የደነገጉ በአላህ ሐቅ ላይ ተጋሪዎች አሏቸው፥ "የደነገጉ" ለሚለው የገባው ቃል “ሸረዑ” شَرَعُوا ሲሆን ሸሪዓህ መደንገጋቸው የሚያሳይ ቃል ነው። ለዚህ ነው “ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው” ነው ያለው፥ አይሁዳውያን ሊቃውንቶቻቸውን እንዲሁ ክርስቲያኖች መነኮሳታቸውን በአሏህ ላይ በማጋራት ጌቶች አድርገው ያዙ፦
9፥31 ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለውን አንድን አምላክ ሊያመልኩ እንጂ ያልታዘዙ ሲኾኑ ሊቃውንቶቻቸውን እና መነኮሳታቸውን ከአላህ ሌላ አርባብ አድርገው ያዙ፥ እንዲሁ የመርየምን ልጅ አልመሲሕንም ያዙ። ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው፡፡ اتَّخَذُوا أَحْبَارَهُمْ وَرُهْبَانَهُمْ أَرْبَابًا مِّن دُونِ اللَّهِ وَالْمَسِيحَ ابْنَ مَرْيَمَ وَمَا أُمِرُوا إِلَّا لِيَعْبُدُوا إِلَـٰهًا وَاحِدًا ۖ لَّا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۚ سُبْحَانَهُ عَمَّا يُشْرِكُونَ
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 147
ዐዲይ ኢብኑ ሓቲም እንደተረከው፦ ”ወደ ነቢዩም”ﷺ” ስመጣ በአንገቴ ዙሪያ የወርቅሐራም መስቀል ነበረኝ፥ እርሳቸውም፦ “ዐዲይ ሆይ! ይህንን ጣዖት ከአንተ አስወግድ” አሉ። ሱረቱል በራኣህ "ሊቃውንቶቻቸውን እና መነኮሳታቸውን ከአሏህ ሌላ አርባብ አድርገው ያዙ" የሚለው ሲነበብ ሰማዋቸው። እርሳቸውም፦ ለእነርሱ አያመልኳቸውም፥ ነገር ግን ሐላል ባደረጉላቸው ጊዜ ሐላል አርገው ይቀበሉታል። ባደረጉላቸው ጊዜ ሐራም አርገው ይቀበሉታል” አሉ። عَنْ عَدِيِّ بْنِ حَاتِمٍ، قَالَ أَتَيْتُ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم وَفِي عُنُقِي صَلِيبٌ مِنْ ذَهَبٍ . فَقَالَ ” يَا عَدِيُّ اطْرَحْ عَنْكَ هَذَا الْوَثَنَ ” . وَسَمِعْتُهُ يَقْرَأُ فِي سُورَةِ بَرَاءَةََ : ( اتَّخَذُوا أَحْبَارَهُمْ وَرُهْبَانَهُمْ أَرْبَابًا مِنْ دُونِ اللَّهِ ) قَالَ ” أَمَا إِنَّهُمْ لَمْ يَكُونُوا يَعْبُدُونَهُمْ وَلَكِنَّهُمْ كَانُوا إِذَا أَحَلُّوا لَهُمْ شَيْئًا اسْتَحَلُّوهُ وَإِذَا حَرَّمُوا عَلَيْهِمْ شَيْئًا حَرَّمُوهُ
“አርባብ” أَرْبَاب የሚለው ቃል "ረብ" رَبّ ለሚለው ብዙ ቁጥር ሲሆን "ጌቶች" ማለት ነው፥ አንድን ነገር ፈድር፣ ሙስተሐብ፣ ሙባሕ፣ መክሩህ፣ እና ሐራም ማለት የሚችለው ብቸኛው ባለ ሥልጣን አሏህ ብቻ ነው። ነቢያችን”ﷺ” ሆኑ አሚሮቻችን አሏህ ባዘዘው ያዛሉ እንዲሁ በከለከለው ይከለክላሉ እንጂ የእራሳቸው ድንጋጌ አያወጡም፦
16፥116 በአላህም ላይ ውሸትን ልትቀጣጥፉ ምላሶቻችሁ በሚመጥኑት ውሸት «ይህ የተፈቀደ ነው፤ ይህም እርም ነው» አትበሉ፡፡ وَلَا تَقُولُوا لِمَا تَصِفُ أَلْسِنَتُكُمُ الْكَذِبَ هَـٰذَا حَلَالٌ وَهَـٰذَا حَرَامٌ لِّتَفْتَرُوا عَلَى اللَّهِ الْكَذِبَ
"ሑክም" حُكْم ማለት "ፍርድ" "መርሕ" "ሕግ" ማለት ነው፥ የሑክም ብዙ ቁጥር ደግሞ "አሕካም" أَحْكَام ሲሆን "ሕግጋት" ማለት ነው። እነዚህም አሕካም አምስት ናቸው፥ እነርሱም፦
1ኛ. "ፈርድ" فَرْد ማለት "የታዘዘ" ግዴታ ማለት ሲሆን ብናደርገው አጅር የሚያሰጥ ባናደርገው የሚያስቀጣ ነው፥ ለምሳሌ፦ ሶላት፣ ፆም፣ ዘካህ፣ ወዘተ ፈርድ ናቸው።
2ኛ. "ሙስተሐብ" مُسْتَحَبّ ማለት "የተወደደ" ሡናህ ማለት ሲሆን ብናደርገው አጅር የሚያሰጥ ባናደርገው የማያስቀጣ ነው፥ ለምሳሌ፦ ማግባት፣ ልጅ መውለድ፣ ሶደቃህ መሶደቅ ወዘተ ሙስተሐብ ናቸው።
3ኛ. "ሙባሕ" مُبَاح ማለት "የተፈቀደ" ሐላል ማለት ሲሆን ብናደርገው አጅር የማያሰጥ ባናደርገው የማያስቀጣ ነው፥ ለምሳሌ፦ የግመል ሥጋ መብላት፣ የአህሉል ኪታብ ሥጋ መብላት ወዘተ ሙባሕ ናቸው።
4ኛ. "መክሩህ" مَكْرُوه ማለት "የተጠላ" ያልተወደደ ማለት ሲሆን ባናደርገው አጅር የማያሰጥ ብናደርገው የማያስቀጣ ነው፥ ለምሳሌ፦ ፍቺ መክሩህ ነው።
5ኛ. "ሐራም" حَرَام ማለት "የተከለከለ" ክልክል ማለት ሲሆን ባናደርገው አጅር የሚያሰጥ ብናደርገው የሚያስቀጣ ነው፥ ለምሳሌ፦ ዝሙት፣ ኸምር መጠጣት፣ የአሳማ ሥጋ መብላት ወዘተ ሐራም ናቸው።
"ጀዛእ" جَزَى ማለት "ዋጋ" ማለት ሲሆን ፍጥረትን ፈጥሮ እና አምስቱን አሕካም ሰጥቶ የሚያስተናብረው ጌታ በፍርዱ ቀን ለሁሉም ዋጋ በመስጠት ይፈርዳል፦
76፥22 «ይህ በእርግጥ ለእናንተ ዋጋ ኾነ፡፡ ሥራችሁም ምስጉን ኾነ» ይባላሉ፡፡ إِنَّ هَـٰذَا كَانَ لَكُمْ جَزَاءً وَكَانَ سَعْيُكُم مَّشْكُورًا
9፥95 ይሠሩትም በነበሩት ዋጋ መኖሪያቸው ገሀነም ነው፡፡ وَمَأْوَاهُمْ جَهَنَّمُ جَزَاءً بِمَا كَانُوا يَكْسِبُونَ
"ሰዋብ" ثَوَاب ወይም "አጅር" أَجْر ማለት "ሽልማት" "ትሩፋት" "ምንዳ" ማለት ሲሆን "ዒቃብ" عِقَاب ወይም "ዐዛብ" عَذَاب ማለት ደግሞ "ቅጣት" "ክስረት" "ፍዳ" ማለት ነው፥ የፍርዱ ቀን በአምስቱ አሕካም የሽልማት እና የቅጣት ዋጋ እንዲሁ የምንዳ እና የፍዳ ዋጋ የሚከፍለው አሏህ ብቻ ነው።
"ፍጥረትን የፈጠረው ብቻውን ነው" ብሎ መቀበል፣ በቁርኣኑ እና በመልእክተኛው የደነገገው የአሕካም ንግግር እና መልእክት ያለምንም ማቅማማት መቀበል፣ "በፍርዱ ቀን ዱንያህ ላይ በሰጠን አሕካም ብቻውን ይፈርዳል" ብሎ መቀበል የአሏህን ጌትነት በተውሒድ ማጽደቅ ነው፥ በተቃራኒው ከእርሱ ውጪ "ከእርሱ ጋር የፈጠሩ፣ ሕግ ያወጡ፣ የሚፈርዱ ማንነት ሆነ ምንነት አሉ" ብሎ መቀበል በእርሱ ላይ ማሻረክ ነው፦
6፥151 እንዲህም በላቸው፦ «ኑ ጌታችሁ በእናንተ ላይ እርም ያደርገውን ነገር ላንብብላችሁ፥ በእርሱ ምንንም ነገር አታጋሩ፡፡ قُلْ تَعَالَوْا أَتْلُ مَا حَرَّمَ رَبُّكُمْ عَلَيْكُمْ ۖ أَلَّا تُشْرِكُوا بِهِ شَيْئًا ۖ
በአሏህን ጌትነት ምንም ሳያሻርኩ የአሏህን ሥልጣን መቀበል ምንኛ መታደል ነው? ተውሒደ አር-ሩቡቢያህ ከፊላችንም ከፊሉን ከአሏህ ሌላ አርባብ አድርጎ ላይዝ ነው፦
3፥64 *የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! በእኛ እና በእናንተ መካከል ትክክል ወደ ኾነች ቃል ኑ፡፡ እርሷም አላህን እንጅ ሌላን ላናመልክ፣ በእርሱም ምንንም ላናጋራ፣ ከፊላችንም ከፊሉን ከአላህ ሌላ አርባብ አድርጎ ላይዝ ነው” በላቸው፡፡ قُلْ يَا أَهْلَ الْكِتَابِ تَعَالَوْا إِلَىٰ كَلِمَةٍ سَوَاءٍ بَيْنَنَا وَبَيْنَكُمْ أَلَّا نَعْبُدَ إِلَّا اللَّهَ وَلَا نُشْرِكَ بِهِ شَيْئًا وَلَا يَتَّخِذَ بَعْضُنَا بَعْضًا أَرْبَابًا مِّن دُونِ اللَّهِ ۚ
አሏህ በተውሒድ ጸንተው ከሚሞቱት ሙዋሒዱን ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
1ኛ. "ፈርድ" فَرْد ማለት "የታዘዘ" ግዴታ ማለት ሲሆን ብናደርገው አጅር የሚያሰጥ ባናደርገው የሚያስቀጣ ነው፥ ለምሳሌ፦ ሶላት፣ ፆም፣ ዘካህ፣ ወዘተ ፈርድ ናቸው።
2ኛ. "ሙስተሐብ" مُسْتَحَبّ ማለት "የተወደደ" ሡናህ ማለት ሲሆን ብናደርገው አጅር የሚያሰጥ ባናደርገው የማያስቀጣ ነው፥ ለምሳሌ፦ ማግባት፣ ልጅ መውለድ፣ ሶደቃህ መሶደቅ ወዘተ ሙስተሐብ ናቸው።
3ኛ. "ሙባሕ" مُبَاح ማለት "የተፈቀደ" ሐላል ማለት ሲሆን ብናደርገው አጅር የማያሰጥ ባናደርገው የማያስቀጣ ነው፥ ለምሳሌ፦ የግመል ሥጋ መብላት፣ የአህሉል ኪታብ ሥጋ መብላት ወዘተ ሙባሕ ናቸው።
4ኛ. "መክሩህ" مَكْرُوه ማለት "የተጠላ" ያልተወደደ ማለት ሲሆን ባናደርገው አጅር የማያሰጥ ብናደርገው የማያስቀጣ ነው፥ ለምሳሌ፦ ፍቺ መክሩህ ነው።
5ኛ. "ሐራም" حَرَام ማለት "የተከለከለ" ክልክል ማለት ሲሆን ባናደርገው አጅር የሚያሰጥ ብናደርገው የሚያስቀጣ ነው፥ ለምሳሌ፦ ዝሙት፣ ኸምር መጠጣት፣ የአሳማ ሥጋ መብላት ወዘተ ሐራም ናቸው።
"ጀዛእ" جَزَى ማለት "ዋጋ" ማለት ሲሆን ፍጥረትን ፈጥሮ እና አምስቱን አሕካም ሰጥቶ የሚያስተናብረው ጌታ በፍርዱ ቀን ለሁሉም ዋጋ በመስጠት ይፈርዳል፦
76፥22 «ይህ በእርግጥ ለእናንተ ዋጋ ኾነ፡፡ ሥራችሁም ምስጉን ኾነ» ይባላሉ፡፡ إِنَّ هَـٰذَا كَانَ لَكُمْ جَزَاءً وَكَانَ سَعْيُكُم مَّشْكُورًا
9፥95 ይሠሩትም በነበሩት ዋጋ መኖሪያቸው ገሀነም ነው፡፡ وَمَأْوَاهُمْ جَهَنَّمُ جَزَاءً بِمَا كَانُوا يَكْسِبُونَ
"ሰዋብ" ثَوَاب ወይም "አጅር" أَجْر ማለት "ሽልማት" "ትሩፋት" "ምንዳ" ማለት ሲሆን "ዒቃብ" عِقَاب ወይም "ዐዛብ" عَذَاب ማለት ደግሞ "ቅጣት" "ክስረት" "ፍዳ" ማለት ነው፥ የፍርዱ ቀን በአምስቱ አሕካም የሽልማት እና የቅጣት ዋጋ እንዲሁ የምንዳ እና የፍዳ ዋጋ የሚከፍለው አሏህ ብቻ ነው።
"ፍጥረትን የፈጠረው ብቻውን ነው" ብሎ መቀበል፣ በቁርኣኑ እና በመልእክተኛው የደነገገው የአሕካም ንግግር እና መልእክት ያለምንም ማቅማማት መቀበል፣ "በፍርዱ ቀን ዱንያህ ላይ በሰጠን አሕካም ብቻውን ይፈርዳል" ብሎ መቀበል የአሏህን ጌትነት በተውሒድ ማጽደቅ ነው፥ በተቃራኒው ከእርሱ ውጪ "ከእርሱ ጋር የፈጠሩ፣ ሕግ ያወጡ፣ የሚፈርዱ ማንነት ሆነ ምንነት አሉ" ብሎ መቀበል በእርሱ ላይ ማሻረክ ነው፦
6፥151 እንዲህም በላቸው፦ «ኑ ጌታችሁ በእናንተ ላይ እርም ያደርገውን ነገር ላንብብላችሁ፥ በእርሱ ምንንም ነገር አታጋሩ፡፡ قُلْ تَعَالَوْا أَتْلُ مَا حَرَّمَ رَبُّكُمْ عَلَيْكُمْ ۖ أَلَّا تُشْرِكُوا بِهِ شَيْئًا ۖ
በአሏህን ጌትነት ምንም ሳያሻርኩ የአሏህን ሥልጣን መቀበል ምንኛ መታደል ነው? ተውሒደ አር-ሩቡቢያህ ከፊላችንም ከፊሉን ከአሏህ ሌላ አርባብ አድርጎ ላይዝ ነው፦
3፥64 *የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! በእኛ እና በእናንተ መካከል ትክክል ወደ ኾነች ቃል ኑ፡፡ እርሷም አላህን እንጅ ሌላን ላናመልክ፣ በእርሱም ምንንም ላናጋራ፣ ከፊላችንም ከፊሉን ከአላህ ሌላ አርባብ አድርጎ ላይዝ ነው” በላቸው፡፡ قُلْ يَا أَهْلَ الْكِتَابِ تَعَالَوْا إِلَىٰ كَلِمَةٍ سَوَاءٍ بَيْنَنَا وَبَيْنَكُمْ أَلَّا نَعْبُدَ إِلَّا اللَّهَ وَلَا نُشْرِكَ بِهِ شَيْئًا وَلَا يَتَّخِذَ بَعْضُنَا بَعْضًا أَرْبَابًا مِّن دُونِ اللَّهِ ۚ
አሏህ በተውሒድ ጸንተው ከሚሞቱት ሙዋሒዱን ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ተውሒደል ኡሉሂያህ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥36 አላህን አምልኩ! በእርሱም ምንንም አታጋሩ፡፡ وَاعْبُدُوا اللَّهَ وَلَا تُشْرِكُوا بِهِ شَيْئًا
"ኢላህ" إِلَـٰه የሚለው ቃል "አለሀ" ألَهَ ማለትም "አመለከ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ተመላኪ" "አምላክ" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ ብቻውን አንዱ አምላክ ነው፦
4፥171 አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
6፥19 «እርሱ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ እኔም ከምታጋሩት ነገር ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا هُوَ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ وَإِنَّنِي بَرِيءٌ مِّمَّا تُشْرِكُونَ
2፥163 አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እርሱ እጅግ በጣም ርኅሩህ አዛኝ ነው፡፡ وَإِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ ۖ لَّا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الرَّحْمَـٰنُ الرَّحِيمُ
47፥19 እነሆ ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩንም ዕወቅ፡፡ فَاعْلَمْ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه
አንዱ አምላክ አሏህ ከነቢያችን"ﷺ" በፊት ለነበሩት መልእክተኞች፦ "እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወሕይ በማውረድ ይልካቸው ነበር፦
21፥25 ከአንተ በፊትም፦ "እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልእክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ
"አዕቡዱኒ" اعْبُدُونِ ማለት "አምልኩኝ" ማለት ሲሆን ጥንትም "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" የሚለው የነቢያት አምላክ ለነቢያችን"ﷺ" እና ለተከታዮቻቸው "አምልኩኝ" እያለ ይናገራል፦
21፥92 ይህች አንዲት መንገድ ስትሆን በእርግጥ ሃይማኖታችሁ ናት፡፡ እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ፡፡ إِنَّ هَـٰذِهِ أُمَّتُكُمْ أُمَّةً وَاحِدَةً وَأَنَا رَبُّكُمْ فَاعْبُدُونِ
29፥56 እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናትና ብትቸገሩ ተሰደዱ፥ እኔንም ብቻ አምልኩኝ፡፡ يَا عِبَادِيَ الَّذِينَ آمَنُوا إِنَّ أَرْضِي وَاسِعَةٌ فَإِيَّايَ فَاعْبُدُونِ
"ዒባዳህ" عِبَادَة የሚለው ቃል "ዓበደ" عَبَدَ ማለትም "አመለከ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "አምልኮ" ማለት ነው፥ ዒባዳህ በተመላኪ እና በአምላኪ መካከል ያለ መርሕ ነው፥ ይህም መርሕ የመጨረሻው ባለ ሥልጣን እና ባለቤት ለሆነው ማንነት እና ምንነት የሚቀርብ ነው። መዕቡድ" مَعْبُود ማለት "ተመላኪ" ማለት ሲሆን አምላካችን አሏህ በሚሠራው ሥራ ሁሉ የማይጠየቅ የአምልኮ ባለ መብት ስለሆነ ተመላኪ ነው፥ "ዐቢድ" عَابِد ደግሞ "አምላኪ" ማለት ሲሆን ሰው በሚሠራው ሥራ የሚጠየቅ የአምልኮ ባለ ዕዳ ስለሆነ አምላኪ ነው። ሰው የተፈጠረበት ዓላማ እና ዒላማ ተገዶ ሳይሆን ወዶ እና ፈቅዶ የፈጠረውን አሏህን በብቸኝነት እንዲያመልክ ነው፦
51፥56 ጂኒን እና ሰውንም ሊያመልኩኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም"፡፡ وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
19፥65 እርሱ የሰማያት እና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነው እና አምልከው! እርሱን በአምልኮ ላይ ታገስ! ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን?። رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا فَاعْبُدْهُ وَاصْطَبِرْ لِعِبَادَتِهِ ۚ هَلْ تَعْلَمُ لَهُ سَمِيًّا
እዚህ አንቀጽ ላይ "አምልከው! እርሱን በአምልኮ ላይ ታገስ” ሲል ተውሒደል ኡሉሂያን ያሳያል። "ተውሒድ" تَوْحِيد የሚለው ቃል "ዋሐደ" وَٰحَدَ ማለትም "አንድ አደረገ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "አንድነት"oneness" ማለት ነው፥ የስም መደቡ ደግሞ "ዋሒድ” وَٰحِد ነው። አሏህን በአምላክነቱ ከፍጡራን ነጥሎ ማምለክ "ተውሒደል ኡሉሂያህ" تَوْحِيد الأُلُوهِيَّة ይባላል፥ "ኡሉሂያህ" أُلُوهِيَّة ማለት "አምላክነት" ማለት ሲሆን አሏህ ብቻውን ያወጣውን አምስቱን አሕካም ፈርድ፣ ሙስተሐብ፣ ሙባሕ፣ መክሩህ እና ሐራም ተቀብለን በማሸርገድ፣ በመጎባደድ፣ በመተናነስ ለእርሱ ስንገዛ አምልኮ ነው። ይህ የአምልኮ መብት፣ ሐቅ እና ገንዘብ የአሏህ ብቻ ማድረግ ተውሒደል ኡሉሂያህ ነው፦
17፥22 ከአላህ ጋር ሌላን አምላክ አታድርግ የተወቀስክ ረዳት የሌለህ ትኾናለህና፤ لَّا تَجْعَلْ مَعَ اللَّهِ إِلَـٰهًا آخَرَ فَتَقْعُدَ مَذْمُومًا مَّخْذُولًا
17፥39 ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አታድርግ የተወቀስክ የተባረርክ ኾነህ በገሀነም ውስጥ ትጣላለህና፡፡ وَلَا تَجْعَلْ مَعَ اللَّهِ إِلَـٰهًا آخَرَ فَتُلْقَىٰ فِي جَهَنَّمَ مَلُومًا مَّدْحُورًا
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥36 አላህን አምልኩ! በእርሱም ምንንም አታጋሩ፡፡ وَاعْبُدُوا اللَّهَ وَلَا تُشْرِكُوا بِهِ شَيْئًا
"ኢላህ" إِلَـٰه የሚለው ቃል "አለሀ" ألَهَ ማለትም "አመለከ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ተመላኪ" "አምላክ" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ ብቻውን አንዱ አምላክ ነው፦
4፥171 አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
6፥19 «እርሱ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ እኔም ከምታጋሩት ነገር ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا هُوَ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ وَإِنَّنِي بَرِيءٌ مِّمَّا تُشْرِكُونَ
2፥163 አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እርሱ እጅግ በጣም ርኅሩህ አዛኝ ነው፡፡ وَإِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ ۖ لَّا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الرَّحْمَـٰنُ الرَّحِيمُ
47፥19 እነሆ ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩንም ዕወቅ፡፡ فَاعْلَمْ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه
አንዱ አምላክ አሏህ ከነቢያችን"ﷺ" በፊት ለነበሩት መልእክተኞች፦ "እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወሕይ በማውረድ ይልካቸው ነበር፦
21፥25 ከአንተ በፊትም፦ "እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልእክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ
"አዕቡዱኒ" اعْبُدُونِ ማለት "አምልኩኝ" ማለት ሲሆን ጥንትም "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" የሚለው የነቢያት አምላክ ለነቢያችን"ﷺ" እና ለተከታዮቻቸው "አምልኩኝ" እያለ ይናገራል፦
21፥92 ይህች አንዲት መንገድ ስትሆን በእርግጥ ሃይማኖታችሁ ናት፡፡ እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ፡፡ إِنَّ هَـٰذِهِ أُمَّتُكُمْ أُمَّةً وَاحِدَةً وَأَنَا رَبُّكُمْ فَاعْبُدُونِ
29፥56 እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናትና ብትቸገሩ ተሰደዱ፥ እኔንም ብቻ አምልኩኝ፡፡ يَا عِبَادِيَ الَّذِينَ آمَنُوا إِنَّ أَرْضِي وَاسِعَةٌ فَإِيَّايَ فَاعْبُدُونِ
"ዒባዳህ" عِبَادَة የሚለው ቃል "ዓበደ" عَبَدَ ማለትም "አመለከ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "አምልኮ" ማለት ነው፥ ዒባዳህ በተመላኪ እና በአምላኪ መካከል ያለ መርሕ ነው፥ ይህም መርሕ የመጨረሻው ባለ ሥልጣን እና ባለቤት ለሆነው ማንነት እና ምንነት የሚቀርብ ነው። መዕቡድ" مَعْبُود ማለት "ተመላኪ" ማለት ሲሆን አምላካችን አሏህ በሚሠራው ሥራ ሁሉ የማይጠየቅ የአምልኮ ባለ መብት ስለሆነ ተመላኪ ነው፥ "ዐቢድ" عَابِد ደግሞ "አምላኪ" ማለት ሲሆን ሰው በሚሠራው ሥራ የሚጠየቅ የአምልኮ ባለ ዕዳ ስለሆነ አምላኪ ነው። ሰው የተፈጠረበት ዓላማ እና ዒላማ ተገዶ ሳይሆን ወዶ እና ፈቅዶ የፈጠረውን አሏህን በብቸኝነት እንዲያመልክ ነው፦
51፥56 ጂኒን እና ሰውንም ሊያመልኩኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም"፡፡ وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
19፥65 እርሱ የሰማያት እና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነው እና አምልከው! እርሱን በአምልኮ ላይ ታገስ! ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን?። رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا فَاعْبُدْهُ وَاصْطَبِرْ لِعِبَادَتِهِ ۚ هَلْ تَعْلَمُ لَهُ سَمِيًّا
እዚህ አንቀጽ ላይ "አምልከው! እርሱን በአምልኮ ላይ ታገስ” ሲል ተውሒደል ኡሉሂያን ያሳያል። "ተውሒድ" تَوْحِيد የሚለው ቃል "ዋሐደ" وَٰحَدَ ማለትም "አንድ አደረገ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "አንድነት"oneness" ማለት ነው፥ የስም መደቡ ደግሞ "ዋሒድ” وَٰحِد ነው። አሏህን በአምላክነቱ ከፍጡራን ነጥሎ ማምለክ "ተውሒደል ኡሉሂያህ" تَوْحِيد الأُلُوهِيَّة ይባላል፥ "ኡሉሂያህ" أُلُوهِيَّة ማለት "አምላክነት" ማለት ሲሆን አሏህ ብቻውን ያወጣውን አምስቱን አሕካም ፈርድ፣ ሙስተሐብ፣ ሙባሕ፣ መክሩህ እና ሐራም ተቀብለን በማሸርገድ፣ በመጎባደድ፣ በመተናነስ ለእርሱ ስንገዛ አምልኮ ነው። ይህ የአምልኮ መብት፣ ሐቅ እና ገንዘብ የአሏህ ብቻ ማድረግ ተውሒደል ኡሉሂያህ ነው፦
17፥22 ከአላህ ጋር ሌላን አምላክ አታድርግ የተወቀስክ ረዳት የሌለህ ትኾናለህና፤ لَّا تَجْعَلْ مَعَ اللَّهِ إِلَـٰهًا آخَرَ فَتَقْعُدَ مَذْمُومًا مَّخْذُولًا
17፥39 ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አታድርግ የተወቀስክ የተባረርክ ኾነህ በገሀነም ውስጥ ትጣላለህና፡፡ وَلَا تَجْعَلْ مَعَ اللَّهِ إِلَـٰهًا آخَرَ فَتُلْقَىٰ فِي جَهَنَّمَ مَلُومًا مَّدْحُورًا
የአሏህን መብት፣ ሐቅ እና ገንዘብ ለሌላ ፍጡር ማድረግ ከአሏህ ጋር ሌላን አምላክ ማድረግ ነውና ሺርክ ነው። "ሺርክ" شِرْك የሚለው ቃል "ሸሪከ" شَرِكَ ማለትም "አጋራ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን በአሏህ መብት፣ ሐቅ እና ገንዘብ ላይ "ማጋራት" ማለት ነው፥ በሺርክ ድርጊት የተሰማራ ደግሞ "ሙሽሪክ" مُشْرِك ይባላል። ሁሉንም ነገር ሰሚ፣ ሁሉንም ነገር ተመልካች፣ ሁሉንም ነገር ዐዋቂ አሏህ ብቻ ስለሆነ ዱዓእ ማድረግ ለእርሱ ብቻ ነው፥ "ዱዓእ" دُعَآء የሚለው ቃል “ደዓ” دَعَا ማለትም "ለመነ" "ጠራ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ልመና" "መጣራት" ማለት ነው። ዱዓእ አምልኮ ነው፦
40፥60 ጌታችሁም አለ «ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና፡፡ እነዚያ እኔን ከማምለክ የሚኮሩት ተዋራጆች ኾነው ገሀነምን በእርግጥ ይገባሉ”*፡፡ وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ ۚ إِنَّ الَّذِينَ يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِي سَيَدْخُلُونَ جَهَنَّمَ دَاخِرِينَ
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 34, ሐዲስ 2
አን-ኑዕማን ኢብኑ በሺር እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” አሉ፦ "ዱዓእ ዒባዳህ ነው፥ ከዚያም፦ “ጌታችሁም አለ «ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና” የሚለውን አንቀጽ ቀሩ”። عَنِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ” إِنَّ الدُّعَاءَ هُوَ الْعِبَادَةُ ” . ثُمَّ قَرَأَ {وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ}
ሁሉንም ነገር መስማት፣ ሁሉንም ነገር ማየት፣ ሁሉንም ነገር ማወቅ የሚችል አንድ መለኮት ሆኖ ሳለ ወደ ፍጡራን መለመን፣ መለማመን፣ መጥራት ሺርክ ነው፦
4፥36 አላህን አምልኩ! በእርሱም ምንንም አታጋሩ፡፡ وَاعْبُدُوا اللَّهَ وَلَا تُشْرِكُوا بِهِ شَيْئًا
13፥36 «እኔ የታዘዝኩት አላህን ብቻ እንዳመልክ እና በእርሱም እንዳላጋራ ነው፥ ወደ እርሱ እጠራለሁ፤ መመለሻዬም ወደ እርሱ ነው» በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا أُمِرْتُ أَنْ أَعْبُدَ اللَّهَ وَلَا أُشْرِكَ بِهِ ۚ إِلَيْهِ أَدْعُو وَإِلَيْهِ مَآبِ
አምልኮ ለፍጡር መስጠት በአሏህ ላይ ባላንጣ ማድረግ ነው፥ ማንም ሰው ከአሏህ ሌላ ባላንጣ እየጠራ ከሞተ እሳት ውስጥ ይገባል። ማንም ሰው በአሏህ ላይ እያሻረከ አሏህን የተገናኘ እሳት ገባ፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 24
ዐብደሏህ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" አንድ ቃል ተናገሩ፥ እኔም ሌላ ተናገርኩኝ። "ነቢዩ"ﷺ"፦ "ማንም ሰው ከአሏህ ሌላ ባላንጣ እየጠራ ከሞተ እሳት ውስጥ ይገባል" አሉ። እኔም፦ "ማንም ሰው ያለ ባላንጣ አሏህ እየጠራ ከሞተ ጀናህ ውስጥ ይገባል" አልኩኝ። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم كَلِمَةً وَقُلْتُ أُخْرَى قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم " مَنْ مَاتَ وَهْوَ يَدْعُو مِنْ دُونِ اللَّهِ نِدًّا دَخَلَ النَّارَ ". وَقُلْتُ أَنَا مَنْ مَاتَ وَهْوَ لاَ يَدْعُو لِلَّهِ نِدًّا دَخَلَ الْجَنَّةَ.
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 176
ጃቢር ኢብኑ ዐብደሏህ ከአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" ሰምቶ እንደተረከው፦ "እርሳቸው እንዲህ አሉ፦ "ማንም ሰው በአሏህ ላይ ምንንም ነገር ሳያሻርክ አሏህን የተገናኘ ጀናህ ገባ፥ ማንም ሰው በአሏህ ላይ እያሻረከ አሏህን የተገናኘ እሳት ገባ። حَدَّثَنَا جَابِرُ بْنُ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ " مَنْ لَقِيَ اللَّهَ لاَ يُشْرِكُ بِهِ شَيْئًا دَخَلَ الْجَنَّةَ وَمَنْ لَقِيَهُ يُشْرِكُ بِهِ دَخَلَ النَّارِ "
በአሏህን አምላክነት ምንም ሳያሻርኩ አሏህን በብቸኝነት ማምለክ ምንኛ መታደል ነው? ማንም ሰው ያለ ባላንጣ አሏህ እየጠራ ከሞተ ጀናህ ውስጥ ይገባል፥ ማንም ሰው በአሏህ ላይ ምንንም ነገር ሳያሻርክ አሏህን የተገናኘ ጀናህ ገባ። አሏህ በተውሒድ ጸንተው ከሚሞቱት ሙዋሒዱን ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
40፥60 ጌታችሁም አለ «ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና፡፡ እነዚያ እኔን ከማምለክ የሚኮሩት ተዋራጆች ኾነው ገሀነምን በእርግጥ ይገባሉ”*፡፡ وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ ۚ إِنَّ الَّذِينَ يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِي سَيَدْخُلُونَ جَهَنَّمَ دَاخِرِينَ
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 34, ሐዲስ 2
አን-ኑዕማን ኢብኑ በሺር እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” አሉ፦ "ዱዓእ ዒባዳህ ነው፥ ከዚያም፦ “ጌታችሁም አለ «ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና” የሚለውን አንቀጽ ቀሩ”። عَنِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ” إِنَّ الدُّعَاءَ هُوَ الْعِبَادَةُ ” . ثُمَّ قَرَأَ {وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ}
ሁሉንም ነገር መስማት፣ ሁሉንም ነገር ማየት፣ ሁሉንም ነገር ማወቅ የሚችል አንድ መለኮት ሆኖ ሳለ ወደ ፍጡራን መለመን፣ መለማመን፣ መጥራት ሺርክ ነው፦
4፥36 አላህን አምልኩ! በእርሱም ምንንም አታጋሩ፡፡ وَاعْبُدُوا اللَّهَ وَلَا تُشْرِكُوا بِهِ شَيْئًا
13፥36 «እኔ የታዘዝኩት አላህን ብቻ እንዳመልክ እና በእርሱም እንዳላጋራ ነው፥ ወደ እርሱ እጠራለሁ፤ መመለሻዬም ወደ እርሱ ነው» በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا أُمِرْتُ أَنْ أَعْبُدَ اللَّهَ وَلَا أُشْرِكَ بِهِ ۚ إِلَيْهِ أَدْعُو وَإِلَيْهِ مَآبِ
አምልኮ ለፍጡር መስጠት በአሏህ ላይ ባላንጣ ማድረግ ነው፥ ማንም ሰው ከአሏህ ሌላ ባላንጣ እየጠራ ከሞተ እሳት ውስጥ ይገባል። ማንም ሰው በአሏህ ላይ እያሻረከ አሏህን የተገናኘ እሳት ገባ፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 24
ዐብደሏህ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" አንድ ቃል ተናገሩ፥ እኔም ሌላ ተናገርኩኝ። "ነቢዩ"ﷺ"፦ "ማንም ሰው ከአሏህ ሌላ ባላንጣ እየጠራ ከሞተ እሳት ውስጥ ይገባል" አሉ። እኔም፦ "ማንም ሰው ያለ ባላንጣ አሏህ እየጠራ ከሞተ ጀናህ ውስጥ ይገባል" አልኩኝ። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم كَلِمَةً وَقُلْتُ أُخْرَى قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم " مَنْ مَاتَ وَهْوَ يَدْعُو مِنْ دُونِ اللَّهِ نِدًّا دَخَلَ النَّارَ ". وَقُلْتُ أَنَا مَنْ مَاتَ وَهْوَ لاَ يَدْعُو لِلَّهِ نِدًّا دَخَلَ الْجَنَّةَ.
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 176
ጃቢር ኢብኑ ዐብደሏህ ከአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" ሰምቶ እንደተረከው፦ "እርሳቸው እንዲህ አሉ፦ "ማንም ሰው በአሏህ ላይ ምንንም ነገር ሳያሻርክ አሏህን የተገናኘ ጀናህ ገባ፥ ማንም ሰው በአሏህ ላይ እያሻረከ አሏህን የተገናኘ እሳት ገባ። حَدَّثَنَا جَابِرُ بْنُ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ " مَنْ لَقِيَ اللَّهَ لاَ يُشْرِكُ بِهِ شَيْئًا دَخَلَ الْجَنَّةَ وَمَنْ لَقِيَهُ يُشْرِكُ بِهِ دَخَلَ النَّارِ "
በአሏህን አምላክነት ምንም ሳያሻርኩ አሏህን በብቸኝነት ማምለክ ምንኛ መታደል ነው? ማንም ሰው ያለ ባላንጣ አሏህ እየጠራ ከሞተ ጀናህ ውስጥ ይገባል፥ ማንም ሰው በአሏህ ላይ ምንንም ነገር ሳያሻርክ አሏህን የተገናኘ ጀናህ ገባ። አሏህ በተውሒድ ጸንተው ከሚሞቱት ሙዋሒዱን ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ተውሒደል አሥማእ ወስ-ሲፋት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
7፥180 ለአላህ መልካም ስሞች አሉት፡፡ ስትጸልዩ በእርሷም ጥሩት፡፡ وَلِلَّهِ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ فَادْعُوهُ بِهَا
"ዛት" ذَات ማለት "ኑባሬ"being” ወይም "ህላዌ"essence” ማለት ሲሆን "ምንድን" ተብሎ የሚጠየቅ "ከዊነ-ምንነት" ነው። "ሲፋህ" صِفَة የሚለው ቃል "ወሰፈ" وَصَفَ ማለትም “ገጠለ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “መገለጫ”description” ወይም “ባሕርይ”attribute” ማለት ነው፥ የሲፋህ ብዙ ቁጥር ደግሞ “ሲፋት” صِفَات ነው። አሏህ የመናገር፣ የማየት፣ የመስማት፣ የማወቅ ባሕርይ አለው፥ እነዚህ ባሕርያት ከፍጡራን ጋር የማይመሳሰሉ ሲሆን እነዚህ ባሕርያት የተሰየሙበት "አል-አሥ ማኡል ሑሥና" الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ ማለትም "የተዋቡ ስሞች" አሉት፦
20፥8 አላህ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ለእርሱ መልካሞች የኾኑ ስሞች አሉት፡፡ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ
7፥180 ለአላህ መልካም ስሞች አሉት፡፡ ስትጸልዩ በእርሷም ጥሩት፡፡ وَلِلَّهِ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ فَادْعُوهُ بِهَا
እዚህ አንቀጽ ላይ "ጥሩ" ለሚለው የገባው ትእዛዛዊ ግሥ "ድዑ" دْعُو ሲሆን ዱዓእ የሚደረገው በአሏህ መልካም ስሞቹ ነው። "ኢሥም" اِسْم የሚለው ቃል “ሠማ” سَمَّى ማለትም “ጠራ” “ሰየመ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “መጠሪያ” ወይም “ስም" ማለት ነው፥ የኢሥም ብዙ ቁጥር “አሥማእ” أَسْمَاء ነው። እነዚህ ስሞቹ በቁርኣን ውስጥ “አል-ዐሊም” العَلِيم “አሥ-ሠሚዕ” السَّمِيع “አል-በሲር” الْبَصِير እያልን "ኢሥቲንባጥ" اِسْتِنْبَاطْ ስናረግ ዘጠና ዘጠኝ ስሞች እናገኛለን፥ እነዚህን ስሞች እያፈዘ አሏህን የሚጠራ መዳረሻው ጀነት ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 48, ሐዲስ 5
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “ነቢዩ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”አሏህ ዘጠና ዘጠኝ ስሞች አሉት፥ እነርሱን ያፈዘ ጀነት ገባ"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ” لِلَّهِ تِسْعَةٌ وَتِسْعُونَ اسْمًا مَنْ حَفِظَهَا دَخَلَ الْجَنَّةَ
“የአሏህ ስሞች ዘጠና ዘጠኝ ናቸው” ተብለው በቁጥር ስላልተወሰኑ “አሏህ ዘጠና ዘጠኝ ስሞች አሉት” ተብሎ ተቀምጧል፥ ምክንያቱም ከዘጠና ዘጠኝ ስሞቹ ሌላ በሐዲስ ደግሞ የተገለጡ ስሞች እንደ "አል-መናን" المَنَّان "አል-ጀሚል" الجَمِيل "አድ-ደህር" الدَّهْر "አል-ዊትር" الوِتْر ስሞች እና በቁርኣን ሆነ በሐዲስ ያልተገለጹ ግን እርሱ ብቻ የሚያውቃቸው ስሞች እንዳሉት እሙን እና ቅቡል ነው። ስሞቹ የተሰየሙበት ባሕርያቱ ከፍጡራን ጋር አይመሳሰሉም፥ አሏህን የሚመስለው ምንም ነገር የለም፦
42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሚስል" مِثْل በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ የገባው "ከ" كَ የሚል መስተዋድድ "በጭራሽ" ማለት ነው፥ "ነገር" በሚለው ቃል ውስጥ ሁሉም ፍጡራን የሚካተቱ ሲሆኑ ከፍጡራን መካከል እርሱን የሚመስል ብጤ በጭራሽ የለም፦
112፥4 «ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም፡፡» وَلَمْ يَكُن لَّهُ كُفُوًا أَحَدٌ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
7፥180 ለአላህ መልካም ስሞች አሉት፡፡ ስትጸልዩ በእርሷም ጥሩት፡፡ وَلِلَّهِ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ فَادْعُوهُ بِهَا
"ዛት" ذَات ማለት "ኑባሬ"being” ወይም "ህላዌ"essence” ማለት ሲሆን "ምንድን" ተብሎ የሚጠየቅ "ከዊነ-ምንነት" ነው። "ሲፋህ" صِفَة የሚለው ቃል "ወሰፈ" وَصَفَ ማለትም “ገጠለ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “መገለጫ”description” ወይም “ባሕርይ”attribute” ማለት ነው፥ የሲፋህ ብዙ ቁጥር ደግሞ “ሲፋት” صِفَات ነው። አሏህ የመናገር፣ የማየት፣ የመስማት፣ የማወቅ ባሕርይ አለው፥ እነዚህ ባሕርያት ከፍጡራን ጋር የማይመሳሰሉ ሲሆን እነዚህ ባሕርያት የተሰየሙበት "አል-አሥ ማኡል ሑሥና" الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ ማለትም "የተዋቡ ስሞች" አሉት፦
20፥8 አላህ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ለእርሱ መልካሞች የኾኑ ስሞች አሉት፡፡ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ
7፥180 ለአላህ መልካም ስሞች አሉት፡፡ ስትጸልዩ በእርሷም ጥሩት፡፡ وَلِلَّهِ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ فَادْعُوهُ بِهَا
እዚህ አንቀጽ ላይ "ጥሩ" ለሚለው የገባው ትእዛዛዊ ግሥ "ድዑ" دْعُو ሲሆን ዱዓእ የሚደረገው በአሏህ መልካም ስሞቹ ነው። "ኢሥም" اِسْم የሚለው ቃል “ሠማ” سَمَّى ማለትም “ጠራ” “ሰየመ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “መጠሪያ” ወይም “ስም" ማለት ነው፥ የኢሥም ብዙ ቁጥር “አሥማእ” أَسْمَاء ነው። እነዚህ ስሞቹ በቁርኣን ውስጥ “አል-ዐሊም” العَلِيم “አሥ-ሠሚዕ” السَّمِيع “አል-በሲር” الْبَصِير እያልን "ኢሥቲንባጥ" اِسْتِنْبَاطْ ስናረግ ዘጠና ዘጠኝ ስሞች እናገኛለን፥ እነዚህን ስሞች እያፈዘ አሏህን የሚጠራ መዳረሻው ጀነት ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 48, ሐዲስ 5
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “ነቢዩ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”አሏህ ዘጠና ዘጠኝ ስሞች አሉት፥ እነርሱን ያፈዘ ጀነት ገባ"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ” لِلَّهِ تِسْعَةٌ وَتِسْعُونَ اسْمًا مَنْ حَفِظَهَا دَخَلَ الْجَنَّةَ
“የአሏህ ስሞች ዘጠና ዘጠኝ ናቸው” ተብለው በቁጥር ስላልተወሰኑ “አሏህ ዘጠና ዘጠኝ ስሞች አሉት” ተብሎ ተቀምጧል፥ ምክንያቱም ከዘጠና ዘጠኝ ስሞቹ ሌላ በሐዲስ ደግሞ የተገለጡ ስሞች እንደ "አል-መናን" المَنَّان "አል-ጀሚል" الجَمِيل "አድ-ደህር" الدَّهْر "አል-ዊትር" الوِتْر ስሞች እና በቁርኣን ሆነ በሐዲስ ያልተገለጹ ግን እርሱ ብቻ የሚያውቃቸው ስሞች እንዳሉት እሙን እና ቅቡል ነው። ስሞቹ የተሰየሙበት ባሕርያቱ ከፍጡራን ጋር አይመሳሰሉም፥ አሏህን የሚመስለው ምንም ነገር የለም፦
42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሚስል" مِثْل በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ የገባው "ከ" كَ የሚል መስተዋድድ "በጭራሽ" ማለት ነው፥ "ነገር" በሚለው ቃል ውስጥ ሁሉም ፍጡራን የሚካተቱ ሲሆኑ ከፍጡራን መካከል እርሱን የሚመስል ብጤ በጭራሽ የለም፦
112፥4 «ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም፡፡» وَلَمْ يَكُن لَّهُ كُفُوًا أَحَدٌ
ሰው ዐዋቂ ነው፥ ነገር ግን ዕውቀቱ በጊዜ እና በቦታ ውስን ነው። ለማወቅ የሚታወቅ ነገር ያስፈልገዋል፣ ሰው ሰሚ ነው፥ መስማቱ በጊዜ እና በቦታ ውስን ነው። ለማስማት ድምጽ ያስፈልገዋል፣ ሰው ተመልካች ነው፥ ማየቱ በጊዜ እና በቦታ ውስን ነው። ለማየት ብርሃን ያስፈልገዋል። አሏህ ግን ለማወቅ የሚታወቅ ነገር አያስፈልገውም፥ የሚታወቀው ነገር ከመፈጠሩ በፊት ያውቀዋል፣ ለመስማት የሚሰማ ድምጽ አያስፈልገውም፥ የሚሰማ ድምጽ ከመፈጠሩ በፊት ሰሚ ነው፣ ለማየት የሚታይ ነገር አያስፈልገውም፥ ያለ ብርሃን በጨለማ ውስጥ የተደበቀውን የሚመለከት እና ፍጥረት ሳይኖር ተመልካች ነው። ስለዚህ “አል-ዐሊም” العَلِيم “አሥ-ሠሚዕ” السَّمِيع “አል-በሲር” الْبَصِير የሚባሉት የአሏህ መልካም ስሞች ሞክሼ የላቸውም፦
19፥65 እርሱ የሰማያት እና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነው እና አምልከው! እርሱን በአምልኮ ላይ ታገስ! ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን?። رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا فَاعْبُدْهُ وَاصْطَبِرْ لِعِبَادَتِهِ ۚ هَلْ تَعْلَمُ لَهُ سَمِيًّا
እዚህ አንቀጽ ላይ "ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን" ሲል ተውሒደል አሥማእ ወስ-ሲፋትን ያሳያል፥ አሏህን በስሙ እና በባሕርው ከፍጡራን ነጥሎ መረዳት እና መጠቀም "ተውሒደል አሥማእ ወስ-ሲፋት" تَوْحِيد الأَسْمَاء الصِفَات ይባላል። ሁሉን ነገር ዐዋቂ፣ ሰሚ እና ተመልካች አንድ መለኮት ብቻ ስሞቹን የትም መጥራት ሲቻል ሁሉን ነገር ማወቅ፣ መስማት እና መመልከት የምይችሉትን ስማቸውን መጥራት ሺርክ ነው፥ የፍጡር ስም ጠርቶ መለማመን፣ መማጸን፣ መጎባደድ፣ ማሸርገድ ማጋራት ነው። ወለደና ተወለደ፣ በላና ጠጣ፣ ተኛና ሞተ፣ ደከመና አደገ ማለት አሏህ የሌለውን ባሕርይ መወሰፍ ስለሆነ ሺርክ ነው፦
21፥22 የዐርሹ ጌታ አላህም “ከሚሉት” ሁሉ ጠራ። فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ
“ከሚሉት” ለሚለው ቃል የገባው “የሲፉነ” يَصِفُونَ ሲሆን "ባሕርይ ካደረጉለት"they attribute” ማለት ነው፥ ፍጡራን እራሱን ባልገለጸበት ሲፋህ መወሰፋቸው ሺርክ ነው። አሏህ ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው፦
53፥43 አላህ "ከሚያጋሩት" ሁሉ ጠራ፡፡ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يُشْرِكُونَ
ለአሏህ ቢጤ እና ሞክሼ ማድረግ ሺርክ ስለሆነ ጀናህ በሚያሻርከው ላይ እርም ናት፥ ማንም ምንንም ነገር በአሏህ ላይ ያላሻረከ ወደ ጀናህ ይገባል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 113
አቡ ዘር እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ጂብሪል ወደ እኔ መጥቶ፦ "ማንም ምንም ነገር በአሏህ ላይ ያላሻረከ ወደ ጀናህ ይገባል" ብሎ አበሰረኝ፥ እኔም፦ "ቢሰርቅም እና ቢያመነዝርም? ብዬ ጠየኩት። እርሱም፦ "ቢሰርቅም እና ቢያመነዝርም" አለኝ"። عَنِ الْمَعْرُورِ، قَالَ سَمِعْتُ أَبَا ذَرٍّ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " أَتَانِي جِبْرِيلُ فَبَشَّرَنِي أَنَّهُ مَنْ مَاتَ لاَ يُشْرِكُ بِاللَّهِ شَيْئًا دَخَلَ الْجَنَّةَ ". قُلْتُ وَإِنْ سَرَقَ وَإِنْ زَنَى قَالَ " وَإِنْ سَرَقَ وَإِنْ زَنَى
ሺርክ ትልቁ ዙልም ነው፥ አሏህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡ ከዚህ ሌላ ያለውንም ኀጢአት ለምሳሌ መስረቅ፣ ማመንዘር ወዘተ ቀጥቶ ይምራል፥ አንዳንድ የተውሒድ ባለቤት ከሺርክ ውጪ ያሉትን ወንጀሎች ንስሓ እስካልገቡ ድረስ ለሥራቸው ተመጣጣኝ ቅጣት ተቀብለው ወደ ጀነት ይገባሉ፦
31፥13 በአላህ ላይ አታጋራ! ማጋራት ታላቅ በደል ነው። لَا تُشْرِكْ بِاللَّهِ ۖ إِنَّ الشِّرْكَ لَظُلْمٌ عَظِيمٌ
4፥48 አላህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡ ከዚህ ሌላ ያለውንም ኀጢአት ለሚሻው ሰው ይምራል፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَغْفِرُ أَن يُشْرَكَ بِهِ وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَٰلِكَ لِمَن يَشَاءُ
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 40, ሐዲስ 33
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አንዳንድ የተውሒድ ባለቤቶች የሆኑ ሰዎች ከእሳት ይወጣሉ፥ ወደ ጀነት ይገባሉ"። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم أَنَّهُ قَالَ " سَيَخْرُجُ قَوْمٌ مِنَ النَّارِ مِنْ أَهْلِ التَّوْحِيدِ وَيَدْخُلُونَ الْجَنَّةَ "
ሙዋሒድ በአሏህ ጌትነት፣ አምላክነት እና ባሕርዮት ላይ ምንንም ነገር አያሻርኩም። ቁርኣን ከወረደበት ጭብጥ አንዱ አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት ነው፦
14፥52 ይህ ቁርኣን ለሰዎች ገላጭ ነው፡፡ በእርሱም ሊያስጠነቅቁበት፣ እርሱም አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት፣ የአእምሮ ባለቤቶችም ሊገሰጹበት የተወረደ ነው፡፡ هَـٰذَا بَلَاغٌ لِّلنَّاسِ وَلِيُنذَرُوا بِهِ وَلِيَعْلَمُوا أَنَّمَا هُوَ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ وَلِيَذَّكَّرَ أُولُو الْأَلْبَابِ
አሏህ በተውሒድ ጸንተው ከሚሞቱት ሙዋሒዱን ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
19፥65 እርሱ የሰማያት እና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነው እና አምልከው! እርሱን በአምልኮ ላይ ታገስ! ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን?። رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا فَاعْبُدْهُ وَاصْطَبِرْ لِعِبَادَتِهِ ۚ هَلْ تَعْلَمُ لَهُ سَمِيًّا
እዚህ አንቀጽ ላይ "ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን" ሲል ተውሒደል አሥማእ ወስ-ሲፋትን ያሳያል፥ አሏህን በስሙ እና በባሕርው ከፍጡራን ነጥሎ መረዳት እና መጠቀም "ተውሒደል አሥማእ ወስ-ሲፋት" تَوْحِيد الأَسْمَاء الصِفَات ይባላል። ሁሉን ነገር ዐዋቂ፣ ሰሚ እና ተመልካች አንድ መለኮት ብቻ ስሞቹን የትም መጥራት ሲቻል ሁሉን ነገር ማወቅ፣ መስማት እና መመልከት የምይችሉትን ስማቸውን መጥራት ሺርክ ነው፥ የፍጡር ስም ጠርቶ መለማመን፣ መማጸን፣ መጎባደድ፣ ማሸርገድ ማጋራት ነው። ወለደና ተወለደ፣ በላና ጠጣ፣ ተኛና ሞተ፣ ደከመና አደገ ማለት አሏህ የሌለውን ባሕርይ መወሰፍ ስለሆነ ሺርክ ነው፦
21፥22 የዐርሹ ጌታ አላህም “ከሚሉት” ሁሉ ጠራ። فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ
“ከሚሉት” ለሚለው ቃል የገባው “የሲፉነ” يَصِفُونَ ሲሆን "ባሕርይ ካደረጉለት"they attribute” ማለት ነው፥ ፍጡራን እራሱን ባልገለጸበት ሲፋህ መወሰፋቸው ሺርክ ነው። አሏህ ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው፦
53፥43 አላህ "ከሚያጋሩት" ሁሉ ጠራ፡፡ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يُشْرِكُونَ
ለአሏህ ቢጤ እና ሞክሼ ማድረግ ሺርክ ስለሆነ ጀናህ በሚያሻርከው ላይ እርም ናት፥ ማንም ምንንም ነገር በአሏህ ላይ ያላሻረከ ወደ ጀናህ ይገባል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 113
አቡ ዘር እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ጂብሪል ወደ እኔ መጥቶ፦ "ማንም ምንም ነገር በአሏህ ላይ ያላሻረከ ወደ ጀናህ ይገባል" ብሎ አበሰረኝ፥ እኔም፦ "ቢሰርቅም እና ቢያመነዝርም? ብዬ ጠየኩት። እርሱም፦ "ቢሰርቅም እና ቢያመነዝርም" አለኝ"። عَنِ الْمَعْرُورِ، قَالَ سَمِعْتُ أَبَا ذَرٍّ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " أَتَانِي جِبْرِيلُ فَبَشَّرَنِي أَنَّهُ مَنْ مَاتَ لاَ يُشْرِكُ بِاللَّهِ شَيْئًا دَخَلَ الْجَنَّةَ ". قُلْتُ وَإِنْ سَرَقَ وَإِنْ زَنَى قَالَ " وَإِنْ سَرَقَ وَإِنْ زَنَى
ሺርክ ትልቁ ዙልም ነው፥ አሏህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡ ከዚህ ሌላ ያለውንም ኀጢአት ለምሳሌ መስረቅ፣ ማመንዘር ወዘተ ቀጥቶ ይምራል፥ አንዳንድ የተውሒድ ባለቤት ከሺርክ ውጪ ያሉትን ወንጀሎች ንስሓ እስካልገቡ ድረስ ለሥራቸው ተመጣጣኝ ቅጣት ተቀብለው ወደ ጀነት ይገባሉ፦
31፥13 በአላህ ላይ አታጋራ! ማጋራት ታላቅ በደል ነው። لَا تُشْرِكْ بِاللَّهِ ۖ إِنَّ الشِّرْكَ لَظُلْمٌ عَظِيمٌ
4፥48 አላህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡ ከዚህ ሌላ ያለውንም ኀጢአት ለሚሻው ሰው ይምራል፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَغْفِرُ أَن يُشْرَكَ بِهِ وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَٰلِكَ لِمَن يَشَاءُ
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 40, ሐዲስ 33
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አንዳንድ የተውሒድ ባለቤቶች የሆኑ ሰዎች ከእሳት ይወጣሉ፥ ወደ ጀነት ይገባሉ"። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم أَنَّهُ قَالَ " سَيَخْرُجُ قَوْمٌ مِنَ النَّارِ مِنْ أَهْلِ التَّوْحِيدِ وَيَدْخُلُونَ الْجَنَّةَ "
ሙዋሒድ በአሏህ ጌትነት፣ አምላክነት እና ባሕርዮት ላይ ምንንም ነገር አያሻርኩም። ቁርኣን ከወረደበት ጭብጥ አንዱ አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት ነው፦
14፥52 ይህ ቁርኣን ለሰዎች ገላጭ ነው፡፡ በእርሱም ሊያስጠነቅቁበት፣ እርሱም አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት፣ የአእምሮ ባለቤቶችም ሊገሰጹበት የተወረደ ነው፡፡ هَـٰذَا بَلَاغٌ لِّلنَّاسِ وَلِيُنذَرُوا بِهِ وَلِيَعْلَمُوا أَنَّمَا هُوَ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ وَلِيَذَّكَّرَ أُولُو الْأَلْبَابِ
አሏህ በተውሒድ ጸንተው ከሚሞቱት ሙዋሒዱን ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በእርሱ ተፈጥረዋል
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
7፥191 ምንንም የማይፈጥሩትን እና እነርሱም የሚፈጠሩትን በአላህ ላይ ያጋራሉን? أَيُشْرِكُونَ مَا لَا يَخْلُقُ شَيْئًا وَهُمْ يُخْلَقُونَ
ክርስቲያኖች እራሳቸውን የሚያስጠጉበት ጳውሎስ የፈጣሪ ነቢይ ወይም ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት መካከል አይደለም፥ እርሱ ያስተላለፈው ትምህርት እስር ቤት ሆኖ የደረሰው ደብዳቤ እንጂ የፈጣሪ ንግግር ወይም "በል" ተብሎ የተላከው መልእክት አይደለም። "አንገሊያ" ἀγγελία ማለት "መልእክት"message" ማለት ሲሆን "ኢፕስቶሌን" ἐπιστολὴν ማለት ደግሞ "ደብዳቤ"letter" ማለት ነው፥ የጳውሎስ ትምህርት ከራሱ የፈለቀ ደብዳቤ"letter" ነው። እንደዛም ሆኖ ግን ጳውሎስ፦ "ኢየሱስ ፈጣሪ ነው" ብሎ በፍጹም አላስተማረም፥ ክርስቲያኖች "አስተምሯል" ብለው ድምዳሜ ላይ የደረሱበትን ጥቅስ ኢንሻሏህ ጥርስ እና ምላሱን እየነቀስንና እያደማን እንመልከት፦
ቆላስይስ 1፥15 እርሱም የማይታይ አምላክ መልክ እና የፍጥረት ሁሉ በኵር ነው። ὅς ἐστιν εἰκὼν τοῦ Θεοῦ τοῦ ἀοράτου, πρωτότοκος πάσης κτίσεως,
እዚህ ጥቅስ ላይ "የማይታየው አምላክ" ብቻውን አምላክ የሆነ አብን ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ አስቀምጦታል፥ ይህ የማይታየው አምላክ ኢየሱስ ሳይሆን ያልሞተ ብቻውን አምላክ የሚሆን እንደሆነ እንቅጩን ፍርጥ አርጎ ነግሮናል፦
1 ጢሞቴዎስ 1፥17 ብቻውን አምላክ ለሚሆን፣ ለማይሞተው፣ ለማይታየውም፣ ለዘመናት ንጉሥ ምስጋናና ክብር እስከ ዘላለም ድረስ ይሁን፤ አሜን።
1 ጢሞቴዎስ 6፥16 እርሱ ብቻ የማይሞት ነው፤ ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ይኖራል፤ አንድ ሰው እንኳ አላየውም ሊያይም አይቻለውም፤ ለእርሱ ክብርና የዘላለም ኃይል ይሁን፤ አሜን።
ይህ ብቻውን አምላክ የሆነ፣ የማይታይ እና የማይሞት ማንነት ከኢየሱስ ተነጥሎ ተቀምጧል፥ ኢየሱስ የዚያ የማይሞት፣ የማይታይ፣ የብቸኛ አምላክ መልክ ነው፥ "ኢኮን" εἰκὼν ማለት "መልክ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ ብቻ ሳይሆን ወንድ እራሱ የአምላክ መልክ ነው፦
1ኛ ቆሮንቶስ 11፥7 ወንድ የአምላክ መልክ እና ክብር ስለ ሆነ ራሱን መከናነብ አይገባውም። εἰκὼν καὶ δόξα Θεοῦ ὑπάρχων· ἡ γυνὴ δὲ δόξα ἀνδρός ἐστιν.
ወንድ የአምላክ መልክ ሆኖ እንደተፈጠረ ሁሉ ኢየሱስም የአምላክ መልክ ሆኖ ተፈጥሯል፦
ቆላስይስ 3፥10 የፈጠረውንም "መልክ" እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል። καὶ ἐνδυσάμενοι τὸν νέον τὸν ἀνακαινούμενον εἰς ἐπίγνωσιν κατ’ εἰκόνα τοῦ κτίσαντος αὐτόν,
"the image of him that created him" የሚለው ይሰመርበት! ዕውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው የሚመስለው "የፈጠረውንም መልክ" ኢየሱስን ነው፥ አዲሱ ሰው የተፈጠረው እንደ ኢየሱስ ነው፦
ኤፌሶን 4፥24 ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ። καὶ ἐνδύσασθαι τὸν καινὸν ἄνθρωπον τὸν κατὰ Θεὸν κτισθέντα ἐν δικαιοσύνῃ καὶ ὁσιότητι τῆς ἀληθείας.
ኢየሱስ የፍጥረት ሁሉ በኵር ነው፥ "ፓንታ" πάντα ወይም "ፓስ" πᾶς ማለት "ሁሉ" ማለት ሲሆን "ሁሉ" የሚለው ገላጭ ቅጽል አንጻራዊ ንግግር ነው፥ "በኵር" ማለት "መጀመሪያ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ መጀመሪያነቱ ዘፍጥረት ላይ ላለው ፍጥረት ሳይሆን የአዲስ ፍጥረት ሁሉ መጀመሪያ ነው። የዘፍጥረት ፍጥረት መጀመሪያ እኮ ሰማይ እና ምድር ነው፦
ዘፍጥረት 1፥1 በመጀመሪያ ኤሎሂም ሰማይንና ምድርን ፈጠረ። בְּרֵאשִׁ֖ית בָּרָ֣א אֱלֹהִ֑ים אֵ֥ת הַשָּׁמַ֖יִם וְאֵ֥ת הָאָֽרֶץ
እዚህ አንቀጽ ላይ "መጀመሪያ" ለሚለው የገባው ቃል "ረሺት" רֵאשִׁית ሲሆን ቤሕሞት "የአምላክ ፍጥረት መጀመሪያ" ለተባለበት የገባውም ቃል በተመሳሳይ "ረሺት" רֵאשִׁית ነው፥ ቤሕሞት "የአምላክ ፍጥረት መጀመሪያ" በተባለበት ሒሣብ ኢየሱስም "የአምላክ ፍጥረት መጀመሪያ" ተብሏል፦
ኢዮብ 40፥19 እርሱ የአምላክ ፍጥረት መጀመሪያ ነው። ה֖וּא רֵאשִׁ֣ית דַּרְכֵי־אֵ֑ל
τοῦτ᾿ ἔστιν ἀρχὴ πλάσματος Κυρίου,
ራእይ 3፥14 "የአምላክ ፍጥረት መጀመሪያ" የነበረው። ἡ ἀρχὴ τῆς κτίσεως τοῦ θεοῦ,
ግሪክ ሰፕቱአጀንት ላይ ቤሕሞት "መጀመሪያ" የተባለበት እና ራእይ ላይ ኢየሱስ "መጀመርያ" የተባለት "አርኬ" ἀρχὴ መሆኑን ልብ አርግ! ስለዚህ ቤሕሞት የአራዊት መጀመሪያ እንጂ የዘፍጥረት ፍጥረት መጀመሪያ እንዳልሆነ ሁሉ ኢየሱስም የአዲስ ፍጥረት ሁሉ መጀመሪያ እንጂ የዘፍጥረት ፍጥረት መጀመሪያ አይደለም። ቅሉን ግን በአዲስ ፍጥረት ውስጥ ዙፋናት፣ ጌትነት፣ አለቅነት፣ ሥልጣናት "በ"-ክርስቶስ ተፈጥረዋል፦
ቆላስይስ 1፥16 የሚታዩት እና የማይታዩትም፥ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት።
1. ዙፋናት የአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አገልግሎት ነው፦ ማቴዎስ 19፥28 ራእይ 20፥4
2. ጌትነት የጉባኤ ሽማግሌዎች አገልግሎት ነው፦ 2 ጴጥሮስ 2፥9 ይሁዳ 1፥8 1 ጴጥሮስ 5፥5 ዕብራውያን 13፥7 13፥17
3. አለቅነት የኤጲስ ቆጶሳት አገልግሎት ነው፦ ቆላስይስ 2፥15 ሉቃስ 12፥11 ኤፌሶን 3፥10
4. ሥልጣናት የአስተማሪዎች አገልግሎት ነው፦ 2 ጴጥሮስ 2፥10 ይሁዳ 1፥8
የቤተ ክርስቲያን ራስ ማለት የዙፋናት፣ የጌትነት፣ የአለቅነት፣ የሥልጣናት ራስ ማለት ነው፦
ቆላስይስ 1፥18 እርሱም የአካሉ ማለት የቤተ ክርስቲያን "ራስ" ነው።
ቆላስይስ 2፥10 ለአለቅነት እና ለሥልጣንም ሁሉ "ራስ" በሆነ በእርሱ ሆናችሁ ተሞልታችኋል።
የሚታዩት በምድር ያሉት እና የማይታዩት በሰማይ ያሉት የተባሉት አዲስ ፍጥረት ናቸው፥ "በሰማይ እና በምድር ያሉት ሁሉ" የሚለው ይሰመርበት! እስቲ፦
ቆላስይስ 1፥16 በሰማይ እና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋልና ነው። ὅτι ἐν αὐτῷ ἐκτίσθη τὰ πάντα ἐν τοῖς οὐρανοῖς καὶ ἐπὶ τῆς γῆς,
ልብ አርጋችሁ ከሆነ የሚለው "ሰማይ እና ምድር" ሳይሆን "በሰማይ እና በምድር ያሉት" ነው፥ "በሰማይ እና በምድር ያሉት ሁሉ" የተባሉት እዛው ዐውደ ንባቡ ላይ በክርስቶስ ከእግዚአብሔር ጋር የታረቁትን የሚያመለክት እንደሆነ አስረግጦ እና ረግጦ አስቀምጦታል፦
ቆላስይስ 1፥20 "በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ" ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዶአልና።
"በምድር ያሉት ሁሉ" ሲባል እንስሳት፣ እጽዋት፣ ማዕድናት በአዳም ከእግዚአብሔር ጋር ተጣልተው በክርስቶስ ታርቀዋልን? "በሰማያት ያሉት ሁሉ" ሲባል መላእክት፣ ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት በአዳም ከእግዚአብሔር ጋር ተጣልተው በክርስቶስ ታርቀዋልን? በሰማያት ያሉት በሚበልጥ መሥዋዕት እንደነጹ ይናገራል፦
ዕብራውያን 9፥23 "በሰማያት ያሉቱ" ራሳቸው ከእርሱ ይልቅ በሚበልጥ መሥዋዕት ሊነጹ የግድ ነበረ።
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
7፥191 ምንንም የማይፈጥሩትን እና እነርሱም የሚፈጠሩትን በአላህ ላይ ያጋራሉን? أَيُشْرِكُونَ مَا لَا يَخْلُقُ شَيْئًا وَهُمْ يُخْلَقُونَ
ክርስቲያኖች እራሳቸውን የሚያስጠጉበት ጳውሎስ የፈጣሪ ነቢይ ወይም ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት መካከል አይደለም፥ እርሱ ያስተላለፈው ትምህርት እስር ቤት ሆኖ የደረሰው ደብዳቤ እንጂ የፈጣሪ ንግግር ወይም "በል" ተብሎ የተላከው መልእክት አይደለም። "አንገሊያ" ἀγγελία ማለት "መልእክት"message" ማለት ሲሆን "ኢፕስቶሌን" ἐπιστολὴν ማለት ደግሞ "ደብዳቤ"letter" ማለት ነው፥ የጳውሎስ ትምህርት ከራሱ የፈለቀ ደብዳቤ"letter" ነው። እንደዛም ሆኖ ግን ጳውሎስ፦ "ኢየሱስ ፈጣሪ ነው" ብሎ በፍጹም አላስተማረም፥ ክርስቲያኖች "አስተምሯል" ብለው ድምዳሜ ላይ የደረሱበትን ጥቅስ ኢንሻሏህ ጥርስ እና ምላሱን እየነቀስንና እያደማን እንመልከት፦
ቆላስይስ 1፥15 እርሱም የማይታይ አምላክ መልክ እና የፍጥረት ሁሉ በኵር ነው። ὅς ἐστιν εἰκὼν τοῦ Θεοῦ τοῦ ἀοράτου, πρωτότοκος πάσης κτίσεως,
እዚህ ጥቅስ ላይ "የማይታየው አምላክ" ብቻውን አምላክ የሆነ አብን ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ አስቀምጦታል፥ ይህ የማይታየው አምላክ ኢየሱስ ሳይሆን ያልሞተ ብቻውን አምላክ የሚሆን እንደሆነ እንቅጩን ፍርጥ አርጎ ነግሮናል፦
1 ጢሞቴዎስ 1፥17 ብቻውን አምላክ ለሚሆን፣ ለማይሞተው፣ ለማይታየውም፣ ለዘመናት ንጉሥ ምስጋናና ክብር እስከ ዘላለም ድረስ ይሁን፤ አሜን።
1 ጢሞቴዎስ 6፥16 እርሱ ብቻ የማይሞት ነው፤ ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ይኖራል፤ አንድ ሰው እንኳ አላየውም ሊያይም አይቻለውም፤ ለእርሱ ክብርና የዘላለም ኃይል ይሁን፤ አሜን።
ይህ ብቻውን አምላክ የሆነ፣ የማይታይ እና የማይሞት ማንነት ከኢየሱስ ተነጥሎ ተቀምጧል፥ ኢየሱስ የዚያ የማይሞት፣ የማይታይ፣ የብቸኛ አምላክ መልክ ነው፥ "ኢኮን" εἰκὼν ማለት "መልክ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ ብቻ ሳይሆን ወንድ እራሱ የአምላክ መልክ ነው፦
1ኛ ቆሮንቶስ 11፥7 ወንድ የአምላክ መልክ እና ክብር ስለ ሆነ ራሱን መከናነብ አይገባውም። εἰκὼν καὶ δόξα Θεοῦ ὑπάρχων· ἡ γυνὴ δὲ δόξα ἀνδρός ἐστιν.
ወንድ የአምላክ መልክ ሆኖ እንደተፈጠረ ሁሉ ኢየሱስም የአምላክ መልክ ሆኖ ተፈጥሯል፦
ቆላስይስ 3፥10 የፈጠረውንም "መልክ" እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል። καὶ ἐνδυσάμενοι τὸν νέον τὸν ἀνακαινούμενον εἰς ἐπίγνωσιν κατ’ εἰκόνα τοῦ κτίσαντος αὐτόν,
"the image of him that created him" የሚለው ይሰመርበት! ዕውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው የሚመስለው "የፈጠረውንም መልክ" ኢየሱስን ነው፥ አዲሱ ሰው የተፈጠረው እንደ ኢየሱስ ነው፦
ኤፌሶን 4፥24 ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ። καὶ ἐνδύσασθαι τὸν καινὸν ἄνθρωπον τὸν κατὰ Θεὸν κτισθέντα ἐν δικαιοσύνῃ καὶ ὁσιότητι τῆς ἀληθείας.
ኢየሱስ የፍጥረት ሁሉ በኵር ነው፥ "ፓንታ" πάντα ወይም "ፓስ" πᾶς ማለት "ሁሉ" ማለት ሲሆን "ሁሉ" የሚለው ገላጭ ቅጽል አንጻራዊ ንግግር ነው፥ "በኵር" ማለት "መጀመሪያ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ መጀመሪያነቱ ዘፍጥረት ላይ ላለው ፍጥረት ሳይሆን የአዲስ ፍጥረት ሁሉ መጀመሪያ ነው። የዘፍጥረት ፍጥረት መጀመሪያ እኮ ሰማይ እና ምድር ነው፦
ዘፍጥረት 1፥1 በመጀመሪያ ኤሎሂም ሰማይንና ምድርን ፈጠረ። בְּרֵאשִׁ֖ית בָּרָ֣א אֱלֹהִ֑ים אֵ֥ת הַשָּׁמַ֖יִם וְאֵ֥ת הָאָֽרֶץ
እዚህ አንቀጽ ላይ "መጀመሪያ" ለሚለው የገባው ቃል "ረሺት" רֵאשִׁית ሲሆን ቤሕሞት "የአምላክ ፍጥረት መጀመሪያ" ለተባለበት የገባውም ቃል በተመሳሳይ "ረሺት" רֵאשִׁית ነው፥ ቤሕሞት "የአምላክ ፍጥረት መጀመሪያ" በተባለበት ሒሣብ ኢየሱስም "የአምላክ ፍጥረት መጀመሪያ" ተብሏል፦
ኢዮብ 40፥19 እርሱ የአምላክ ፍጥረት መጀመሪያ ነው። ה֖וּא רֵאשִׁ֣ית דַּרְכֵי־אֵ֑ל
τοῦτ᾿ ἔστιν ἀρχὴ πλάσματος Κυρίου,
ራእይ 3፥14 "የአምላክ ፍጥረት መጀመሪያ" የነበረው። ἡ ἀρχὴ τῆς κτίσεως τοῦ θεοῦ,
ግሪክ ሰፕቱአጀንት ላይ ቤሕሞት "መጀመሪያ" የተባለበት እና ራእይ ላይ ኢየሱስ "መጀመርያ" የተባለት "አርኬ" ἀρχὴ መሆኑን ልብ አርግ! ስለዚህ ቤሕሞት የአራዊት መጀመሪያ እንጂ የዘፍጥረት ፍጥረት መጀመሪያ እንዳልሆነ ሁሉ ኢየሱስም የአዲስ ፍጥረት ሁሉ መጀመሪያ እንጂ የዘፍጥረት ፍጥረት መጀመሪያ አይደለም። ቅሉን ግን በአዲስ ፍጥረት ውስጥ ዙፋናት፣ ጌትነት፣ አለቅነት፣ ሥልጣናት "በ"-ክርስቶስ ተፈጥረዋል፦
ቆላስይስ 1፥16 የሚታዩት እና የማይታዩትም፥ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት።
1. ዙፋናት የአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አገልግሎት ነው፦ ማቴዎስ 19፥28 ራእይ 20፥4
2. ጌትነት የጉባኤ ሽማግሌዎች አገልግሎት ነው፦ 2 ጴጥሮስ 2፥9 ይሁዳ 1፥8 1 ጴጥሮስ 5፥5 ዕብራውያን 13፥7 13፥17
3. አለቅነት የኤጲስ ቆጶሳት አገልግሎት ነው፦ ቆላስይስ 2፥15 ሉቃስ 12፥11 ኤፌሶን 3፥10
4. ሥልጣናት የአስተማሪዎች አገልግሎት ነው፦ 2 ጴጥሮስ 2፥10 ይሁዳ 1፥8
የቤተ ክርስቲያን ራስ ማለት የዙፋናት፣ የጌትነት፣ የአለቅነት፣ የሥልጣናት ራስ ማለት ነው፦
ቆላስይስ 1፥18 እርሱም የአካሉ ማለት የቤተ ክርስቲያን "ራስ" ነው።
ቆላስይስ 2፥10 ለአለቅነት እና ለሥልጣንም ሁሉ "ራስ" በሆነ በእርሱ ሆናችሁ ተሞልታችኋል።
የሚታዩት በምድር ያሉት እና የማይታዩት በሰማይ ያሉት የተባሉት አዲስ ፍጥረት ናቸው፥ "በሰማይ እና በምድር ያሉት ሁሉ" የሚለው ይሰመርበት! እስቲ፦
ቆላስይስ 1፥16 በሰማይ እና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋልና ነው። ὅτι ἐν αὐτῷ ἐκτίσθη τὰ πάντα ἐν τοῖς οὐρανοῖς καὶ ἐπὶ τῆς γῆς,
ልብ አርጋችሁ ከሆነ የሚለው "ሰማይ እና ምድር" ሳይሆን "በሰማይ እና በምድር ያሉት" ነው፥ "በሰማይ እና በምድር ያሉት ሁሉ" የተባሉት እዛው ዐውደ ንባቡ ላይ በክርስቶስ ከእግዚአብሔር ጋር የታረቁትን የሚያመለክት እንደሆነ አስረግጦ እና ረግጦ አስቀምጦታል፦
ቆላስይስ 1፥20 "በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ" ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዶአልና።
"በምድር ያሉት ሁሉ" ሲባል እንስሳት፣ እጽዋት፣ ማዕድናት በአዳም ከእግዚአብሔር ጋር ተጣልተው በክርስቶስ ታርቀዋልን? "በሰማያት ያሉት ሁሉ" ሲባል መላእክት፣ ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት በአዳም ከእግዚአብሔር ጋር ተጣልተው በክርስቶስ ታርቀዋልን? በሰማያት ያሉት በሚበልጥ መሥዋዕት እንደነጹ ይናገራል፦
ዕብራውያን 9፥23 "በሰማያት ያሉቱ" ራሳቸው ከእርሱ ይልቅ በሚበልጥ መሥዋዕት ሊነጹ የግድ ነበረ።
መቼም "በሚበልጥ መሥዋዕት የነጹት መላእክት፣ ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት ናቸው" የሚል ቂል ያለ አይመስለኝም። ስለዚህ በሰማይ እና በምድር ያሉት "ሁሉ" የሚለው አጻራዊ ንግግር እንጂ ፍጹማዊ ንግግር አይደለም፥ በሰማያት የተጻፉት የበኵራት ማኅበር እና በምድር ያሉት አማኞች በክርስቶስ አዲስ ፍጥረት ሆነዋል እንጂ ስለ ዘፍጥረት ፍጥረት በፍጹም አያወራም፦
ዕብራውያን 12፥23 በሰማያትም ወደ ተጻፉ ወደ በኵራት ማኅበር።
2 ቆሮንቶስ 5፥17 ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ "ሁሉም" አዲስ ሆኖአል። ὥστε εἴ τις ἐν Χριστῷ, καινὴ κτίσις· τὰ ἀρχαῖα παρῆλθεν, ἰδοὺ γέγονεν καινά.
አጠቃላይ ሥነ-ፍጥረት አዲስ ሆኗልን? እረ በፍጹም። ስለዚህ "ሁሉ" አንጻራዊ እንጂ ፍጹማዊ ስላልሆነ "ሁሉ አዲስ ሆኖአል" የተባለው አማኞችን ብቻ የሚመለከት ከሆነ "አዲስ ፍጥረት" የተባሉት አማንያን ብቻ ናቸው፦
ገላትያ 6፥15 በክርስቶስ ኢየሱስ "አዲስ ፍጥረት" መሆን ይጠቅማል እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና።
ኤፌሶን 2፥10 እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።
እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ የተፈጠሩት በክርስቶስ ኢየሱስ አዲስ ፍጥረት እንጂ መላው ፍጥረት እግዚአብሔር አስቀድሞ ባዘጋጀውን ውስጥ አይካተቱም። ደግሞም "በ-"እርሱ ተፈጥረዋል" ማለት ክርስቶስን ፈጣሪ አያደርገውም፦
ቆላስይስ 1፥16 "በ-"እርሱ ተፈጥረዋልና ὅτι ἐν αὐτῷ ἐκτίσθη
"በ" ለሚለው የገባው መስተዋድድ "ኤን" ἐν ሲሆን መሣሪያ"instrument" እንጂ እራሱ የድርጊቱ ፈጻሚ አይደለም፥ ለምሳሌ፦ ነገርን ሀሉ "በ" ጊዜ ውብ አድርጌ ሠራው" ይላል፦
መክብብ 3፥11 ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው። σύμπαντα, ἃ ἐποίησε, καλὰ ἐν καιρῷ αὐτοῦ,
"ጊዜ" ፍጡር ነው፥ "ነገርን ሁሉ" "በ"-ጊዜ ሠራው ማለት "ጊዜ" ፈጣሪ ነውን? "እርሱ" በሚለው መነሻ ላይ "ኤን" ἐν መስተዋድድ የሚል ስላለ "ኢየሱስ" ፈጣሪ ከሆነ "ጊዜ" በሚለው መነሻ ላይ "ኤን" ἐν የሚል መስተዋድድ ስላለ "ጊዜ" ፈጣሪ ነውን? ወንድ እኮ የተፈጠረው በሴት ነው፦
1 ቆሮንቶስ 11፥12 ሴት ከወንድ እንደ ሆነች እንዲሁ ወንድ ደግሞ "በ"-ሴት ነውና። ὥσπερ γὰρ ἡ γυνὴ ἐκ τοῦ ἀνδρός, οὕτως καὶ ὁ ἀνὴρ διὰ τῆς γυναικός·
እዚህ ጥቅስ ላይ "ሴት" በሚለው ቃል ላይ ለገባው "በ" ለሚለው መስተዋድድ የገባው "ዲያ" διὰ ሲሆን ወንድ በሴት በኩል መሆኑን እንጂ ሴት ፈጣሪ መሆኗን እንደማያሳይ ሁሉ "በ-"እርሱ ተፈጥረዋል ማለት እርሱ ፈጣሪ ነው ማለት አይደለም፦
ቆላስይስ 1፥16 ሁሉ በእርሱ እና "ለ"እርሱ ተፈጥሮአል። all things have been created through him and for him.(NIV)
"ለ-እርሱ"for him" የሚለው አዲስ ፍጥረት "ለ"-ኢየሱስ መፈጠሩን ያሳያል፥ "ለ"for" የሚለው መስተዋድድ ፍጡር ለፍጡር ይገባል። ለምሳሌ ሴት "ለ"-ወንድ ተፈጠረች፥ ሰንበት "ለ"ሰው ተፈጥሮአል፦
1 ቆሮንቶስ 11፥9 ሴት "ለ"-ወንድ ተፈጠረች እንጂ ወንድ "ለ"-ሴት አልተፈጠረምና። neither was man created "for" woman, but woman "for" man.(NIV)
ማርቆስ 2፥27 ደግሞ አላቸው፦ ሰንበት "ለ"ሰው ተፈጥሮአል እንጂ ሰው "ለ"-ሰንበት አልተፈጠረም። Then he said to them, “The Sabbath was made "for" man, not man for the Sabbath.(NIV)
ሴት ለወንድ ተፈጠረች ማለት ሴት አምላኪ ወንድ ተመላኪ ማለት ነውን? ሰንበት ለሰው ተፈጥሮአል ማለት ሰንበት አምላኪ ሰው ተመላኪ ማለት ነውን? ይህ ሙግት አያዋጣችሁም። "ተፈጥረዋል" የሚለው የግሪኩ ቃል "ኤክቲስቴ" ἐκτίσθη ሲሆን እድሳትን ወይም ከመንፈዊ ጨለማ ወደ መንፈሳዊ ብርሃን በመምጣት የሚገኝ ለውጥ"transformation" የሚያሳይ ነው፦
መዝሙር 51፥10 አቤቱ ንጹሕ ልብን "ፍጠርልኝ"፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ "አድስ"።
"ፍጠርልኝ" ሲል "አድስልኝ" ለማለት እንደሆነ ከተረዳን ዘንዳ "ተፈጥረዋል" ሲል "ታድሰዋል" ማለቱ ነው፦
የሐዋርያት ሥራ 3፥21 "ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት ዘመን" ድረስ ሰማይ ይቀበለው ዘንድ ይገባልና።
"ነገር ሁሉ" ታድሷል እንዴ? አይ አማንያን መታደሳቸውን የሚያሳይ ነው። እሩቅ ሳንሄድ "አዲስ ፍጥረት" የሚለው ቃል "አዲስ ልደት" በሚል እኮ መጥቷል፦
ቲቶ 3፥5 እንደ ምሕረቱ መጠን "ለአዲስ ልደት" በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን።
"አዲስ" በሚል ገላጭ ቅጽል ተስታኮ የመጣውን "ልደት" የሚለውን ቃል ከእናት እና አባት ውልደትን እንደማያመለክት ሁሉ "አዲስ" በሚል ገላጽ ቅጽል ተስታኮ የመጣውን "ፍጥረት" የሚለውን ቃል ሥነ-ፍጥረትን አያመለክትም። ሰማይ እና ምድርን ብቻውን የፈጠረ አንድ ማንነት ነው፥ ይህ አንድ ማንነት "እኔ" በሚል ነጠላ ተውላጠ ስም በመጠቀም አንድ ማንነት ብቻውን እንደፈጠረ ይናገራል፦
ኢሳይያስ 44፥24 ከማኅፀን የሠራህ፥ የሚቤዥህ ያህዌህ እንዲህ ይላል፦ ሁሉን የፈጠርሁ፥ ሰማያትን ለብቻዬ የዘረጋሁ ምድርንም ያጸናሁ ያህዌህ እኔ ነኝ፤ ከእኔ ጋር ማን ነበረ?
"እኔ" ለአንድ ማንነት"person" የምንጠቀምበት እንጂ "እኔ" ተብሎ ሁለት እና ከአንድ በላይ ማንነቶች አይባልም። "ማን ነበረ" ለሚለው ጥያቄ "ማንም" ከሆነ "ማን" የሚለውን "ማንነትን" ያሳያል፥ ከአንዱ እኔነት ጋር አብሮ የፈጠረ ማንነት ማንም የለም። ክርስቲያኖች ሆይ! የማይፈጥርን ይልቁንስ የሚፈጠርን አካል በአሏህ ላይ አታጋሩ! የጳውሎስ ደብዳቤ አሏህ ማስረጃን ያላወረደበት የራሱ የጳውሎስ ንግግር ነው፦
7፥191 ምንንም የማይፈጥሩትንና እነርሱም የሚፈጠሩትን በአላህ ላይ ያጋራሉን? أَيُشْرِكُونَ مَا لَا يَخْلُقُ شَيْئًا وَهُمْ يُخْلَقُونَ
22፥7 ከአላህ ሌላም በእርሱ ማስረጃን ያላወረደበትን ለእነርሱም በእርሱ ዕውቀት የሌላቸውን ነገር ያመልካሉ፡፡ ለባዳዮችም ምንም ረዳት የላቸውም፡፡ وَيَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ مَا لَمْ يُنَزِّلْ بِهِ سُلْطَانًا وَمَا لَيْسَ لَهُم بِهِ عِلْمٌ ۗ وَمَا لِلظَّالِمِينَ مِن نَّصِيرٍ
3፥151 በእነዚያ በካዱት ሰዎች ልቦች ውስጥ አላህ በእርሱ ማስረጃን ያላወረደበትን ነገር በአላህ ላይ በማጋራታቸው ምክንያት ፍርሃትን እንጥላለን፡፡ መኖሪያቸውም እሳት ናት፡፡ የበዳዮችም መኖሪያ ምን ትከፋ! سَنُلْقِي فِي قُلُوبِ الَّذِينَ كَفَرُوا الرُّعْبَ بِمَا أَشْرَكُوا بِاللَّهِ مَا لَمْ يُنَزِّلْ بِهِ سُلْطَانًا ۖ وَمَأْوَاهُمُ النَّارُ ۚ وَبِئْسَ مَثْوَى الظَّالِمِينَ
ሕዝበ ክርስትናው በውስጡ ሰላም የሌለው እና ፍርሃት ያለው አሏህ በእርሱ አስረጅ ያላወረደበትን ነገር በአሏህ ላይ በማጋራታቸው ምክንያት ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ዕብራውያን 12፥23 በሰማያትም ወደ ተጻፉ ወደ በኵራት ማኅበር።
2 ቆሮንቶስ 5፥17 ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ "ሁሉም" አዲስ ሆኖአል። ὥστε εἴ τις ἐν Χριστῷ, καινὴ κτίσις· τὰ ἀρχαῖα παρῆλθεν, ἰδοὺ γέγονεν καινά.
አጠቃላይ ሥነ-ፍጥረት አዲስ ሆኗልን? እረ በፍጹም። ስለዚህ "ሁሉ" አንጻራዊ እንጂ ፍጹማዊ ስላልሆነ "ሁሉ አዲስ ሆኖአል" የተባለው አማኞችን ብቻ የሚመለከት ከሆነ "አዲስ ፍጥረት" የተባሉት አማንያን ብቻ ናቸው፦
ገላትያ 6፥15 በክርስቶስ ኢየሱስ "አዲስ ፍጥረት" መሆን ይጠቅማል እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና።
ኤፌሶን 2፥10 እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።
እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ የተፈጠሩት በክርስቶስ ኢየሱስ አዲስ ፍጥረት እንጂ መላው ፍጥረት እግዚአብሔር አስቀድሞ ባዘጋጀውን ውስጥ አይካተቱም። ደግሞም "በ-"እርሱ ተፈጥረዋል" ማለት ክርስቶስን ፈጣሪ አያደርገውም፦
ቆላስይስ 1፥16 "በ-"እርሱ ተፈጥረዋልና ὅτι ἐν αὐτῷ ἐκτίσθη
"በ" ለሚለው የገባው መስተዋድድ "ኤን" ἐν ሲሆን መሣሪያ"instrument" እንጂ እራሱ የድርጊቱ ፈጻሚ አይደለም፥ ለምሳሌ፦ ነገርን ሀሉ "በ" ጊዜ ውብ አድርጌ ሠራው" ይላል፦
መክብብ 3፥11 ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው። σύμπαντα, ἃ ἐποίησε, καλὰ ἐν καιρῷ αὐτοῦ,
"ጊዜ" ፍጡር ነው፥ "ነገርን ሁሉ" "በ"-ጊዜ ሠራው ማለት "ጊዜ" ፈጣሪ ነውን? "እርሱ" በሚለው መነሻ ላይ "ኤን" ἐν መስተዋድድ የሚል ስላለ "ኢየሱስ" ፈጣሪ ከሆነ "ጊዜ" በሚለው መነሻ ላይ "ኤን" ἐν የሚል መስተዋድድ ስላለ "ጊዜ" ፈጣሪ ነውን? ወንድ እኮ የተፈጠረው በሴት ነው፦
1 ቆሮንቶስ 11፥12 ሴት ከወንድ እንደ ሆነች እንዲሁ ወንድ ደግሞ "በ"-ሴት ነውና። ὥσπερ γὰρ ἡ γυνὴ ἐκ τοῦ ἀνδρός, οὕτως καὶ ὁ ἀνὴρ διὰ τῆς γυναικός·
እዚህ ጥቅስ ላይ "ሴት" በሚለው ቃል ላይ ለገባው "በ" ለሚለው መስተዋድድ የገባው "ዲያ" διὰ ሲሆን ወንድ በሴት በኩል መሆኑን እንጂ ሴት ፈጣሪ መሆኗን እንደማያሳይ ሁሉ "በ-"እርሱ ተፈጥረዋል ማለት እርሱ ፈጣሪ ነው ማለት አይደለም፦
ቆላስይስ 1፥16 ሁሉ በእርሱ እና "ለ"እርሱ ተፈጥሮአል። all things have been created through him and for him.(NIV)
"ለ-እርሱ"for him" የሚለው አዲስ ፍጥረት "ለ"-ኢየሱስ መፈጠሩን ያሳያል፥ "ለ"for" የሚለው መስተዋድድ ፍጡር ለፍጡር ይገባል። ለምሳሌ ሴት "ለ"-ወንድ ተፈጠረች፥ ሰንበት "ለ"ሰው ተፈጥሮአል፦
1 ቆሮንቶስ 11፥9 ሴት "ለ"-ወንድ ተፈጠረች እንጂ ወንድ "ለ"-ሴት አልተፈጠረምና። neither was man created "for" woman, but woman "for" man.(NIV)
ማርቆስ 2፥27 ደግሞ አላቸው፦ ሰንበት "ለ"ሰው ተፈጥሮአል እንጂ ሰው "ለ"-ሰንበት አልተፈጠረም። Then he said to them, “The Sabbath was made "for" man, not man for the Sabbath.(NIV)
ሴት ለወንድ ተፈጠረች ማለት ሴት አምላኪ ወንድ ተመላኪ ማለት ነውን? ሰንበት ለሰው ተፈጥሮአል ማለት ሰንበት አምላኪ ሰው ተመላኪ ማለት ነውን? ይህ ሙግት አያዋጣችሁም። "ተፈጥረዋል" የሚለው የግሪኩ ቃል "ኤክቲስቴ" ἐκτίσθη ሲሆን እድሳትን ወይም ከመንፈዊ ጨለማ ወደ መንፈሳዊ ብርሃን በመምጣት የሚገኝ ለውጥ"transformation" የሚያሳይ ነው፦
መዝሙር 51፥10 አቤቱ ንጹሕ ልብን "ፍጠርልኝ"፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ "አድስ"።
"ፍጠርልኝ" ሲል "አድስልኝ" ለማለት እንደሆነ ከተረዳን ዘንዳ "ተፈጥረዋል" ሲል "ታድሰዋል" ማለቱ ነው፦
የሐዋርያት ሥራ 3፥21 "ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት ዘመን" ድረስ ሰማይ ይቀበለው ዘንድ ይገባልና።
"ነገር ሁሉ" ታድሷል እንዴ? አይ አማንያን መታደሳቸውን የሚያሳይ ነው። እሩቅ ሳንሄድ "አዲስ ፍጥረት" የሚለው ቃል "አዲስ ልደት" በሚል እኮ መጥቷል፦
ቲቶ 3፥5 እንደ ምሕረቱ መጠን "ለአዲስ ልደት" በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን።
"አዲስ" በሚል ገላጭ ቅጽል ተስታኮ የመጣውን "ልደት" የሚለውን ቃል ከእናት እና አባት ውልደትን እንደማያመለክት ሁሉ "አዲስ" በሚል ገላጽ ቅጽል ተስታኮ የመጣውን "ፍጥረት" የሚለውን ቃል ሥነ-ፍጥረትን አያመለክትም። ሰማይ እና ምድርን ብቻውን የፈጠረ አንድ ማንነት ነው፥ ይህ አንድ ማንነት "እኔ" በሚል ነጠላ ተውላጠ ስም በመጠቀም አንድ ማንነት ብቻውን እንደፈጠረ ይናገራል፦
ኢሳይያስ 44፥24 ከማኅፀን የሠራህ፥ የሚቤዥህ ያህዌህ እንዲህ ይላል፦ ሁሉን የፈጠርሁ፥ ሰማያትን ለብቻዬ የዘረጋሁ ምድርንም ያጸናሁ ያህዌህ እኔ ነኝ፤ ከእኔ ጋር ማን ነበረ?
"እኔ" ለአንድ ማንነት"person" የምንጠቀምበት እንጂ "እኔ" ተብሎ ሁለት እና ከአንድ በላይ ማንነቶች አይባልም። "ማን ነበረ" ለሚለው ጥያቄ "ማንም" ከሆነ "ማን" የሚለውን "ማንነትን" ያሳያል፥ ከአንዱ እኔነት ጋር አብሮ የፈጠረ ማንነት ማንም የለም። ክርስቲያኖች ሆይ! የማይፈጥርን ይልቁንስ የሚፈጠርን አካል በአሏህ ላይ አታጋሩ! የጳውሎስ ደብዳቤ አሏህ ማስረጃን ያላወረደበት የራሱ የጳውሎስ ንግግር ነው፦
7፥191 ምንንም የማይፈጥሩትንና እነርሱም የሚፈጠሩትን በአላህ ላይ ያጋራሉን? أَيُشْرِكُونَ مَا لَا يَخْلُقُ شَيْئًا وَهُمْ يُخْلَقُونَ
22፥7 ከአላህ ሌላም በእርሱ ማስረጃን ያላወረደበትን ለእነርሱም በእርሱ ዕውቀት የሌላቸውን ነገር ያመልካሉ፡፡ ለባዳዮችም ምንም ረዳት የላቸውም፡፡ وَيَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ مَا لَمْ يُنَزِّلْ بِهِ سُلْطَانًا وَمَا لَيْسَ لَهُم بِهِ عِلْمٌ ۗ وَمَا لِلظَّالِمِينَ مِن نَّصِيرٍ
3፥151 በእነዚያ በካዱት ሰዎች ልቦች ውስጥ አላህ በእርሱ ማስረጃን ያላወረደበትን ነገር በአላህ ላይ በማጋራታቸው ምክንያት ፍርሃትን እንጥላለን፡፡ መኖሪያቸውም እሳት ናት፡፡ የበዳዮችም መኖሪያ ምን ትከፋ! سَنُلْقِي فِي قُلُوبِ الَّذِينَ كَفَرُوا الرُّعْبَ بِمَا أَشْرَكُوا بِاللَّهِ مَا لَمْ يُنَزِّلْ بِهِ سُلْطَانًا ۖ وَمَأْوَاهُمُ النَّارُ ۚ وَبِئْسَ مَثْوَى الظَّالِمِينَ
ሕዝበ ክርስትናው በውስጡ ሰላም የሌለው እና ፍርሃት ያለው አሏህ በእርሱ አስረጅ ያላወረደበትን ነገር በአሏህ ላይ በማጋራታቸው ምክንያት ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ዘመናትን ባደረገበት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥71 የመጸሐፉ ሰዎች ሆይ! እዉነቱን በዉሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ? እዉነቱንም እናንተ የምታወቁ ስትሆኑ ለምን ትደብቃላችሁ? يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لِمَ تَلْبِسُونَ ٱلْحَقَّ بِٱلْبَٰطِلِ وَتَكْتُمُونَ ٱلْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ
የዘመናችን የባይብል ምሁራን፦ "የዕብራውያን ደብዳቤ ተናጋሪ እና ጸሐፊ ማን እንደሆነ ዐይታወቅም" በማለት ይናገራሉ፥ አንዳንዶች፦ "የዕብራውያን ደብዳቤ ተናጋሪ እና ጸሐፊ ጻውሎስ ነው" ሲሉ፣ ጥቂቶች ደግሞ "አቂላ እና ጵርስቅላ ናቸው" ሲሉ፣ አንዳንድ፦ "አጵሎስ ነው" የሚል መላምት ሰንዝረዋል። ሆነም ቀረ የዕብራውያን ደብዳቤ የነቢይ ወይም የፈጣሪ ንግግር ሳይሆን አንድ ማንነቱ የማይታወቅ ሰው ለዕብራውያን ሰዎች የጻፈው ደብዳቤ ነው፥ ይህ ደብዳቤ መክፈቻው ላይ እንዲህ ይላል፦
ዕብራውያን 1፥1 ከጥንት ጀምሮ አምላክ በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ። Πολυμερῶς καὶ πολυτρόπως πάλαι ὁ Θεὸς λαλήσας τοῖς πατράσιν ἐν τοῖς προφήταις
እዚህ ጥቅስ ላይ "አምላክ" ለሚለው የገባው ቃል "ቴዎስ" Θεὸς ሲሆን ከጥንት ጀምሮ ይህ አንድ አምላክ ለእስራኤላውያን በነቢያቱ፦ "ከእኔ በቀር ሌላ አምላክ የለም" እያለ ከተናገረ በኃላ ዘመናትን ባደረገበት በልጁ በዘመኑ መጨረሻ ተናገረ፦
ዕብራውያን 1፥2 ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዘመናትን ባደረገበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን። ἐπ’ ἐσχάτου τῶν ἡμερῶν τούτων ἐλάλησεν ἡμῖν ἐν Υἱῷ, ὃν ἔθηκεν κληρονόμον πάντων, δι’ οὗ καὶ ἐποίησεν τοὺς αἰῶνας·
"ሁሉን ወራሽ" ማለት ኢየሱስ ያለውን "ነገር ሁሉ" ከራሱ ያገኘው ሳይሆን አምላክ በጸጋ እና በስጦታ የሰጠው ወይም ያወረሰው ነው፥ ለኢየሱስ የተሰጠው ነገር ሁሉ ለአማኞችም እንደሚሰጥ ጳውሎስ ተናግሯል፦
ሉቃስ 10፥22 ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል።
ሮሜ 8፥32 ከእርሱ ጋር ደግሞ "ሁሉን ነገር" እንዲያው እንዴት አይሰጠንም?
ሮሜ 8፥17 መከራ ብንቀበል "ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን"።
"ከእርሱ ጋር ደግሞ "ሁሉን ነገር"ይሰጠናል" ካለ ኢየሱስ የሚወርሰው "ሁሉ ነገር" አንጻራዊ ነው። "ኮስሞስ" κόσμος ማለት "ዓለም" ወይም "ጽንፈ ዓለም"universe" ማለት ነው፥ ይህም ኮስሞስ የሚለው ቃል ሥነ-ፍጥረትን"cosmology" ያሳያል፦
ማቴዎስ 13፥35 "ዓለም" ከተፈጠረ ጀምሮ የተሰወረውንም እናገራለሁ"። ἐρεύξομαι κεκρυμμένα ἀπὸ καταβολῆς.
ዕብራውያን 9፥26 እንዲህ ቢሆንስ፥ "ዓለም" ከተፈጠረ ጀምሮ ብዙ ጊዜ መከራ ሊቀበል ባስፈለገው ነበር። ἐπεὶ ἔδει αὐτὸν πολλάκις παθεῖν ἀπὸ καταβολῆς κόσμου·
እነዚህ ጥቅስ ላይ "ዓለም" ለሚለው የገባው ቃል "ኮስሞስ" κόσμος ነው፥ ነገር ግን ዕብራውያን 1፥2 ላይ የገባው ቃል "ኮስሞስ" κόσμος ሳይሆን "አይኦን" αἰών ነው። "አይኦን" αἰών ማለት "ዘመን" ማለት ነው፥ ለምሳሌ፦ የብሉይ ዘመን ፍጻሜ ሲሆን "በዘመናት ፍጻሜ" ተብሎ ተቀምጧል፦
ዕብራውያን 9፥26 በዘመናት ፍጻሜ ራሱን በመሠዋት ኃጢአትን ሊሽር አንድ ጊዜ ተገልጦአል። νυνὶ δὲ ἅπαξ ἐπὶ συντελείᾳ τῶν αἰώνων εἰς ἀθέτησιν τῆς ἁμαρτίας διὰ τῆς θυσίας αὐτοῦ πεφανέρωται.
ኢየሱስ ሲገለጥ ፍጻሜ ያገኘው ዘመን በሙሴ የተጀመረው የብሉይ ኪዳን ዘመን ነው፥ "በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን" ሲል የተፈጸመው ዘመን ያ በሙሴ ተጀምሮ የነበረው ነው፦
1 ቆሮንቶስ 10፥11 "የዘመናት መጨረሻ" የደረሰብንን ሊገሥጸን ተጻፈ። εἰς οὓς τὰ τέλη τῶν αἰώνων κατήντηκεν.
እዚህ አንቀጽ ላይ "ዘመን" ለሚለው የገባው ቃል "አይኦን" αἰών መሆኑን ልብ አድርግ! በተጨማሪ፦
፨1 ጴጥሮስ 1፥21 ላይ "በዘመኑ መጨረሻ"
፨ማርቆስ 1፥15 ላይ "ዘመኑ ተፈጸመ"
፨ገላትያ 4፥4 ላይ "የዘመኑ ፍጻሜ"
የሚሉትን ተመልከት!
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥71 የመጸሐፉ ሰዎች ሆይ! እዉነቱን በዉሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ? እዉነቱንም እናንተ የምታወቁ ስትሆኑ ለምን ትደብቃላችሁ? يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لِمَ تَلْبِسُونَ ٱلْحَقَّ بِٱلْبَٰطِلِ وَتَكْتُمُونَ ٱلْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ
የዘመናችን የባይብል ምሁራን፦ "የዕብራውያን ደብዳቤ ተናጋሪ እና ጸሐፊ ማን እንደሆነ ዐይታወቅም" በማለት ይናገራሉ፥ አንዳንዶች፦ "የዕብራውያን ደብዳቤ ተናጋሪ እና ጸሐፊ ጻውሎስ ነው" ሲሉ፣ ጥቂቶች ደግሞ "አቂላ እና ጵርስቅላ ናቸው" ሲሉ፣ አንዳንድ፦ "አጵሎስ ነው" የሚል መላምት ሰንዝረዋል። ሆነም ቀረ የዕብራውያን ደብዳቤ የነቢይ ወይም የፈጣሪ ንግግር ሳይሆን አንድ ማንነቱ የማይታወቅ ሰው ለዕብራውያን ሰዎች የጻፈው ደብዳቤ ነው፥ ይህ ደብዳቤ መክፈቻው ላይ እንዲህ ይላል፦
ዕብራውያን 1፥1 ከጥንት ጀምሮ አምላክ በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ። Πολυμερῶς καὶ πολυτρόπως πάλαι ὁ Θεὸς λαλήσας τοῖς πατράσιν ἐν τοῖς προφήταις
እዚህ ጥቅስ ላይ "አምላክ" ለሚለው የገባው ቃል "ቴዎስ" Θεὸς ሲሆን ከጥንት ጀምሮ ይህ አንድ አምላክ ለእስራኤላውያን በነቢያቱ፦ "ከእኔ በቀር ሌላ አምላክ የለም" እያለ ከተናገረ በኃላ ዘመናትን ባደረገበት በልጁ በዘመኑ መጨረሻ ተናገረ፦
ዕብራውያን 1፥2 ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዘመናትን ባደረገበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን። ἐπ’ ἐσχάτου τῶν ἡμερῶν τούτων ἐλάλησεν ἡμῖν ἐν Υἱῷ, ὃν ἔθηκεν κληρονόμον πάντων, δι’ οὗ καὶ ἐποίησεν τοὺς αἰῶνας·
"ሁሉን ወራሽ" ማለት ኢየሱስ ያለውን "ነገር ሁሉ" ከራሱ ያገኘው ሳይሆን አምላክ በጸጋ እና በስጦታ የሰጠው ወይም ያወረሰው ነው፥ ለኢየሱስ የተሰጠው ነገር ሁሉ ለአማኞችም እንደሚሰጥ ጳውሎስ ተናግሯል፦
ሉቃስ 10፥22 ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል።
ሮሜ 8፥32 ከእርሱ ጋር ደግሞ "ሁሉን ነገር" እንዲያው እንዴት አይሰጠንም?
ሮሜ 8፥17 መከራ ብንቀበል "ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን"።
"ከእርሱ ጋር ደግሞ "ሁሉን ነገር"ይሰጠናል" ካለ ኢየሱስ የሚወርሰው "ሁሉ ነገር" አንጻራዊ ነው። "ኮስሞስ" κόσμος ማለት "ዓለም" ወይም "ጽንፈ ዓለም"universe" ማለት ነው፥ ይህም ኮስሞስ የሚለው ቃል ሥነ-ፍጥረትን"cosmology" ያሳያል፦
ማቴዎስ 13፥35 "ዓለም" ከተፈጠረ ጀምሮ የተሰወረውንም እናገራለሁ"። ἐρεύξομαι κεκρυμμένα ἀπὸ καταβολῆς.
ዕብራውያን 9፥26 እንዲህ ቢሆንስ፥ "ዓለም" ከተፈጠረ ጀምሮ ብዙ ጊዜ መከራ ሊቀበል ባስፈለገው ነበር። ἐπεὶ ἔδει αὐτὸν πολλάκις παθεῖν ἀπὸ καταβολῆς κόσμου·
እነዚህ ጥቅስ ላይ "ዓለም" ለሚለው የገባው ቃል "ኮስሞስ" κόσμος ነው፥ ነገር ግን ዕብራውያን 1፥2 ላይ የገባው ቃል "ኮስሞስ" κόσμος ሳይሆን "አይኦን" αἰών ነው። "አይኦን" αἰών ማለት "ዘመን" ማለት ነው፥ ለምሳሌ፦ የብሉይ ዘመን ፍጻሜ ሲሆን "በዘመናት ፍጻሜ" ተብሎ ተቀምጧል፦
ዕብራውያን 9፥26 በዘመናት ፍጻሜ ራሱን በመሠዋት ኃጢአትን ሊሽር አንድ ጊዜ ተገልጦአል። νυνὶ δὲ ἅπαξ ἐπὶ συντελείᾳ τῶν αἰώνων εἰς ἀθέτησιν τῆς ἁμαρτίας διὰ τῆς θυσίας αὐτοῦ πεφανέρωται.
ኢየሱስ ሲገለጥ ፍጻሜ ያገኘው ዘመን በሙሴ የተጀመረው የብሉይ ኪዳን ዘመን ነው፥ "በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን" ሲል የተፈጸመው ዘመን ያ በሙሴ ተጀምሮ የነበረው ነው፦
1 ቆሮንቶስ 10፥11 "የዘመናት መጨረሻ" የደረሰብንን ሊገሥጸን ተጻፈ። εἰς οὓς τὰ τέλη τῶν αἰώνων κατήντηκεν.
እዚህ አንቀጽ ላይ "ዘመን" ለሚለው የገባው ቃል "አይኦን" αἰών መሆኑን ልብ አድርግ! በተጨማሪ፦
፨1 ጴጥሮስ 1፥21 ላይ "በዘመኑ መጨረሻ"
፨ማርቆስ 1፥15 ላይ "ዘመኑ ተፈጸመ"
፨ገላትያ 4፥4 ላይ "የዘመኑ ፍጻሜ"
የሚሉትን ተመልከት!
አምላክ አዲሱ የአዲስ ኪዳን ዘመን ያደረገው በኢየሱስ ነው፥ "ባደረገበት" የሚለው የግሪኩ ቃል "ኤፖኤሴን" ἐποίησεν ሲሆን ኢየሱስ አሥራ ሁለቱን ተከታዮቹን "ሐዋርያ" ለማድረጉ ጥቅም ላይ ውሏል፦
ማርቆስ 3፥15 አሥራ ሁለት "አደረገ"። καὶ ἐποίησεν δώδεκα,
እዚህ አንቀጽ ላይ "አደረገ" ለሚለው የገባው ቃል በተመሳሳይ "ኤፖኤሴን" ἐποίησεν ነው፥ ስለዚህ ብዙ የባይብል ቨርዥኖች፦ "ዘመናትን ባደረገበት"through whom He made the Ages" ብለው አስቀምጠውታል። ዋቢ ቨርዥኖች ተመልከት፦
1. Berean Literal Bible,
2. Literal Standard Version,
3. New Heart English Bible,
4. Weymouth New Testament,
5. Young's Literal Translation፦
አምላክ በክርስቶስ ያደረገው አዲሱ ዘመን የመታደስ ዘመን ነው፥ "ነገር ሁሉ የሚታደስበት ዘመን" "የመታደስ ዘመን" የሚሉ ቃላት ይህንን ጉልኅ ማሳያ ነው፦
የሐዋርያት ሥራ 3፥21 "ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት ዘመን" ድረስ ሰማይ ይቀበለው ዘንድ ይገባልና።
ዕብራውያን 9፥10 እነዚህም "እስከ መታደስ ዘመን" ድረስ የተደረጉ።
"ዓለማትን በፈጠረበት" ቢባል እንኳን ችግር የለውም፥ ምክንያቱም "ዓለም" የሚለው ቃል "ዘመን" የሚለውን ለማመልከት በዕብራውያን 9፥26 ላይ ስለገባ እና "መፈጠር" የሚለው ቃል "መታደስ" የሚለውን ለማመልከት ስለሚገባ ነው፦
መዝሙር 51፥10 አቤቱ ንጹሕ ልብን "ፍጠርልኝ"፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ "አድስ"።
"ፍጠርልኝ" ሲል "አድስልኝ" ለማለት እንደሆነ ከተረዳን ዘንዳ "በፈጠረበት" ሲል "ባደሰበት" በማለት መረዳት ይቻላል፥ ስለዚህ ዕብራውያን 1፥2 ስለ ዘፍጥረት ፍጥረት በፍጹም አይናገርም። "አይኦን" αἰών የሚለውን "ዓለም" በሚል ቢመጣ እንኳን "ዓለም" የሚለው ቃል የብሉይን ሕግ ለማመልከት መጥቷል፦
ገላትያ 6፥14 ነገር ግን "ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት"።
ማቴዎስ 22፥40 በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም "ተሰቅለዋል"።
ቆላስይስ 2፥20 "ከዓለማዊ ከመጀመሪያ ትምህርት" ርቃችሁ ከክርስቶስ ጋር ከሞታችሁ፥
"ዓለም" ተሰቀለ ሲባል "ጽንፈ ዓለም" ተሰቀለ ማለት ሳይሆን የመጀመሪያውን ትምህርት ሕግ እና ነቢያት አክትመው ሁለተኛው ኪዳን "በ"-ክርስቶስ መምጣቱን የሚያሳይ ነው፦
ዕብራውያን 8፥13 አዲስ በማለቱ ፊተኛውን አስረጅቶአል።
ዕብራውያን 8፥7 ፊተኛው ኪዳን ነቀፋ ባይኖረው ለሁለተኛው ስፍራ ባልተፈለገም ነበር።
ዕብራውያን 10፥9 ሁለተኛውንም ሊያቆም የፊተኛውን ይሽራል።
በሙሴ የፊተኛው ኪዳን ሲመሠረት ያ ኪዳን ዘመኑ ሲፈጸም በክርስቶስ ሁለተኛው ኪዳን ሲመሠረት ያ ኪዳን ዘመኑ ጀመረ፥ ጥንት በብሉይ ለአባቶች በነቢያት በኩል ሲናገር የነበረው የብሉይ ዘመን ሲፈጸም በአዲስ ኪዳን በኢየሱስ በኩል ለአይሁዳውያን ተናገረ። አይሁዳውያን ኢየሱስን፦ "አባትህ ወዴት ነው" አሉት፥ አብም በኢየሱስ በኩል፦ "እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ" አላቸው። እነርሱም፦ "አንተ ማን ነህ" አሉት፥ አብም በኢየሱስ በኩል፦ "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ" አላቸው፦
ዮሐንስ 8፥19 እንግዲህ፦ አባትህ ወዴት ነው? አሉት።
ዮሐንስ 8፥24 እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁና።
ዮሐንስ 8፥25 እንግዲህ፦ አንተ ማን ነህ? አሉት። ኢየሱስም አላቸው፦ "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ"።
ኢየሱስ፦ "እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ" "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ" ያለው ከአብ ሰምቶ ነው፦
ዮሐንስ 8፥26 ዳሩ ግን የላከኝ እውነተኛ ነው እኔም ከእርሱ የሰማሁትን "ይህን" ለዓለም እናገራለሁ።
"ይህም" የሚለው አመልካች ይሰመርበት! "ይህም" የተባለው "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ" የሚለው ኃይለ-ቃል ሲሆን "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ" የሚለው አብ ስለሆነ "ከእርሱ የሰማሁትን እናገራለሁ" በማለት እርሱ መልእክተኛ እንዲሁ አብ የመልእክቱ ባለቤት መሆኑን ረግጦ እና አስረግጦ ተናግሯል፥ "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ" የሚለውን አይሁዳውያን ስለ አብ እንደ ነገራቸው አላስተዋሉም፦
ዮሐንስ 8፥27 ስለ አብ እንደ ነገራቸው አላስተዋሉም።
ኢየሱስ የሚናገረው "በል" እየተባለ ነው፥ ከአንዱ አምላክ እየሰማ ይናገር ነበር እንጂ ከራሱ ምንም አይናገርም ነበር፦
ዮሐንስ 5፥30 እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ "እንደ ሰማሁ" እፈርዳለሁ።
ዮሐንስ 8፥40 ነገር ግን አሁን "ከአምላክ የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን ሰው" ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ።
ኢየሱስ፦ "እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ" "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ" ብሎ የተናገረው ቃል የላከው እንጂ የራሱ በፍጹም አይደለም፦
ዮሐንስ 14፥24 የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም።
ዮሐንስ 14፥10 እኔ የምነግራችሁን ቃል ከራሴ አልናገረውም፤ ነገር ግን በእኔ የሚኖረው አብ እርሱ ሥራውን ይሠራል።
ዮሐንስ 12፥49 እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ።
ስለዚህ እግዚአብሔር በኢየሱስ የተናገረው በነቢያት በተናገረበት ስሌት ነው፥ የዕብራውያን ደብዳቤ ጸሐፊ "ጥንት በነቢያት ተናግሮ በልጁ ተናገረ" የሚለው ይህንኑ ነው።
ስንጠቀልለው የዕብራውያን ደብዳቤ የአምላክ ንግግር በፍጹም አይደለም፥ ክርስቲያኖች ከአሏህ ዘንድ የወረደውን እውነት በውሸት ቀላቅለዋል። ከአሏህ ዘንድ የወረደው እውነት ሆኖ ሳለ ውሸቱ ደግሞ እንደ የዕብራውያን ዓይነት ደብዳቤ በእጆቻቸው ጽፈው «ይህ ከአሏህ ዘንድ ነው» ማለታቸው ነው፦
3፥71 የመጸሐፉ ሰዎች ሆይ! እዉነቱን በዉሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ? እዉነቱንም እናንተ የምታወቁ ስትሆኑ ለምን ትደብቃላችሁ? يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لِمَ تَلْبِسُونَ ٱلْحَقَّ بِٱلْبَٰطِلِ وَتَكْتُمُونَ ٱلْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ
2፥79 ለነዚያም መጽሐፉን በእጆቻቸው ለሚጽፉ እና ከዚያም በርሱ ጥቂትን ዋጋ ሊገዙበት «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» ለሚሉ ወዮላቸው፡፡ ለእነርሱም ከዚያ እጆቻቸው ከጻፉት ወዮላቸው፡፡ ለእነርሱም ከዚያ ከሚያፈሩት ኃጢኣት ወዮላቸው፡፡ فَوَيْلٌۭ لِّلَّذِينَ يَكْتُبُونَ ٱلْكِتَٰبَ بِأَيْدِيهِمْ ثُمَّ يَقُولُونَ هَٰذَا مِنْ عِندِ ٱللَّهِ لِيَشْتَرُوا۟ بِهِۦ ثَمَنًۭا قَلِيلًۭا ۖ فَوَيْلٌۭ لَّهُم مِّمَّا كَتَبَتْ أَيْدِيهِمْ وَوَيْلٌۭ لَّهُم مِّمَّا يَكْسِبُونَ
አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ማርቆስ 3፥15 አሥራ ሁለት "አደረገ"። καὶ ἐποίησεν δώδεκα,
እዚህ አንቀጽ ላይ "አደረገ" ለሚለው የገባው ቃል በተመሳሳይ "ኤፖኤሴን" ἐποίησεν ነው፥ ስለዚህ ብዙ የባይብል ቨርዥኖች፦ "ዘመናትን ባደረገበት"through whom He made the Ages" ብለው አስቀምጠውታል። ዋቢ ቨርዥኖች ተመልከት፦
1. Berean Literal Bible,
2. Literal Standard Version,
3. New Heart English Bible,
4. Weymouth New Testament,
5. Young's Literal Translation፦
አምላክ በክርስቶስ ያደረገው አዲሱ ዘመን የመታደስ ዘመን ነው፥ "ነገር ሁሉ የሚታደስበት ዘመን" "የመታደስ ዘመን" የሚሉ ቃላት ይህንን ጉልኅ ማሳያ ነው፦
የሐዋርያት ሥራ 3፥21 "ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት ዘመን" ድረስ ሰማይ ይቀበለው ዘንድ ይገባልና።
ዕብራውያን 9፥10 እነዚህም "እስከ መታደስ ዘመን" ድረስ የተደረጉ።
"ዓለማትን በፈጠረበት" ቢባል እንኳን ችግር የለውም፥ ምክንያቱም "ዓለም" የሚለው ቃል "ዘመን" የሚለውን ለማመልከት በዕብራውያን 9፥26 ላይ ስለገባ እና "መፈጠር" የሚለው ቃል "መታደስ" የሚለውን ለማመልከት ስለሚገባ ነው፦
መዝሙር 51፥10 አቤቱ ንጹሕ ልብን "ፍጠርልኝ"፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ "አድስ"።
"ፍጠርልኝ" ሲል "አድስልኝ" ለማለት እንደሆነ ከተረዳን ዘንዳ "በፈጠረበት" ሲል "ባደሰበት" በማለት መረዳት ይቻላል፥ ስለዚህ ዕብራውያን 1፥2 ስለ ዘፍጥረት ፍጥረት በፍጹም አይናገርም። "አይኦን" αἰών የሚለውን "ዓለም" በሚል ቢመጣ እንኳን "ዓለም" የሚለው ቃል የብሉይን ሕግ ለማመልከት መጥቷል፦
ገላትያ 6፥14 ነገር ግን "ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት"።
ማቴዎስ 22፥40 በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም "ተሰቅለዋል"።
ቆላስይስ 2፥20 "ከዓለማዊ ከመጀመሪያ ትምህርት" ርቃችሁ ከክርስቶስ ጋር ከሞታችሁ፥
"ዓለም" ተሰቀለ ሲባል "ጽንፈ ዓለም" ተሰቀለ ማለት ሳይሆን የመጀመሪያውን ትምህርት ሕግ እና ነቢያት አክትመው ሁለተኛው ኪዳን "በ"-ክርስቶስ መምጣቱን የሚያሳይ ነው፦
ዕብራውያን 8፥13 አዲስ በማለቱ ፊተኛውን አስረጅቶአል።
ዕብራውያን 8፥7 ፊተኛው ኪዳን ነቀፋ ባይኖረው ለሁለተኛው ስፍራ ባልተፈለገም ነበር።
ዕብራውያን 10፥9 ሁለተኛውንም ሊያቆም የፊተኛውን ይሽራል።
በሙሴ የፊተኛው ኪዳን ሲመሠረት ያ ኪዳን ዘመኑ ሲፈጸም በክርስቶስ ሁለተኛው ኪዳን ሲመሠረት ያ ኪዳን ዘመኑ ጀመረ፥ ጥንት በብሉይ ለአባቶች በነቢያት በኩል ሲናገር የነበረው የብሉይ ዘመን ሲፈጸም በአዲስ ኪዳን በኢየሱስ በኩል ለአይሁዳውያን ተናገረ። አይሁዳውያን ኢየሱስን፦ "አባትህ ወዴት ነው" አሉት፥ አብም በኢየሱስ በኩል፦ "እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ" አላቸው። እነርሱም፦ "አንተ ማን ነህ" አሉት፥ አብም በኢየሱስ በኩል፦ "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ" አላቸው፦
ዮሐንስ 8፥19 እንግዲህ፦ አባትህ ወዴት ነው? አሉት።
ዮሐንስ 8፥24 እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁና።
ዮሐንስ 8፥25 እንግዲህ፦ አንተ ማን ነህ? አሉት። ኢየሱስም አላቸው፦ "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ"።
ኢየሱስ፦ "እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ" "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ" ያለው ከአብ ሰምቶ ነው፦
ዮሐንስ 8፥26 ዳሩ ግን የላከኝ እውነተኛ ነው እኔም ከእርሱ የሰማሁትን "ይህን" ለዓለም እናገራለሁ።
"ይህም" የሚለው አመልካች ይሰመርበት! "ይህም" የተባለው "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ" የሚለው ኃይለ-ቃል ሲሆን "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ" የሚለው አብ ስለሆነ "ከእርሱ የሰማሁትን እናገራለሁ" በማለት እርሱ መልእክተኛ እንዲሁ አብ የመልእክቱ ባለቤት መሆኑን ረግጦ እና አስረግጦ ተናግሯል፥ "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ" የሚለውን አይሁዳውያን ስለ አብ እንደ ነገራቸው አላስተዋሉም፦
ዮሐንስ 8፥27 ስለ አብ እንደ ነገራቸው አላስተዋሉም።
ኢየሱስ የሚናገረው "በል" እየተባለ ነው፥ ከአንዱ አምላክ እየሰማ ይናገር ነበር እንጂ ከራሱ ምንም አይናገርም ነበር፦
ዮሐንስ 5፥30 እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ "እንደ ሰማሁ" እፈርዳለሁ።
ዮሐንስ 8፥40 ነገር ግን አሁን "ከአምላክ የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን ሰው" ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ።
ኢየሱስ፦ "እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ" "ከመጀመሪያ ለእናንተ የተናገርሁት ነኝ" ብሎ የተናገረው ቃል የላከው እንጂ የራሱ በፍጹም አይደለም፦
ዮሐንስ 14፥24 የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም።
ዮሐንስ 14፥10 እኔ የምነግራችሁን ቃል ከራሴ አልናገረውም፤ ነገር ግን በእኔ የሚኖረው አብ እርሱ ሥራውን ይሠራል።
ዮሐንስ 12፥49 እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ።
ስለዚህ እግዚአብሔር በኢየሱስ የተናገረው በነቢያት በተናገረበት ስሌት ነው፥ የዕብራውያን ደብዳቤ ጸሐፊ "ጥንት በነቢያት ተናግሮ በልጁ ተናገረ" የሚለው ይህንኑ ነው።
ስንጠቀልለው የዕብራውያን ደብዳቤ የአምላክ ንግግር በፍጹም አይደለም፥ ክርስቲያኖች ከአሏህ ዘንድ የወረደውን እውነት በውሸት ቀላቅለዋል። ከአሏህ ዘንድ የወረደው እውነት ሆኖ ሳለ ውሸቱ ደግሞ እንደ የዕብራውያን ዓይነት ደብዳቤ በእጆቻቸው ጽፈው «ይህ ከአሏህ ዘንድ ነው» ማለታቸው ነው፦
3፥71 የመጸሐፉ ሰዎች ሆይ! እዉነቱን በዉሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ? እዉነቱንም እናንተ የምታወቁ ስትሆኑ ለምን ትደብቃላችሁ? يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لِمَ تَلْبِسُونَ ٱلْحَقَّ بِٱلْبَٰطِلِ وَتَكْتُمُونَ ٱلْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ
2፥79 ለነዚያም መጽሐፉን በእጆቻቸው ለሚጽፉ እና ከዚያም በርሱ ጥቂትን ዋጋ ሊገዙበት «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» ለሚሉ ወዮላቸው፡፡ ለእነርሱም ከዚያ እጆቻቸው ከጻፉት ወዮላቸው፡፡ ለእነርሱም ከዚያ ከሚያፈሩት ኃጢኣት ወዮላቸው፡፡ فَوَيْلٌۭ لِّلَّذِينَ يَكْتُبُونَ ٱلْكِتَٰبَ بِأَيْدِيهِمْ ثُمَّ يَقُولُونَ هَٰذَا مِنْ عِندِ ٱللَّهِ لِيَشْتَرُوا۟ بِهِۦ ثَمَنًۭا قَلِيلًۭا ۖ فَوَيْلٌۭ لَّهُم مِّمَّا كَتَبَتْ أَيْدِيهِمْ وَوَيْلٌۭ لَّهُم مِّمَّا يَكْسِبُونَ
አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
አምላክን ማየት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
5፥75 የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ
"እኔን ያየ አብን አይቶአል" የሚለውን ኃይለ-ቃል ይዘው የሐዋርያት ቤተክርስቲያን በተለምዶ ኢየሱስ ብቻ"only Jesus" የሚባሉት፦ "ኢየሱስ አብ ነው" ሲሉ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ፣ አንግሊካን እና ፕሮቴስታንት ደግሞ፦ "ኢየሱስ አምላክ ነው" የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል፥ እውን ይህ ኃይለ-ቃል "ኢየሱስ አብ ነው" ወይም "ኢየሱስ አምላክ ነው" ለሚለው ዶክትሪን ድምዳሜ ላይ ያደርሳልን? ጥቅሱን በሰከነ እና በሰላ አእምሮ እንመልከተው፦
ዮሐ14፥7 እኔንስ ብታውቁኝ አባቴን ደግሞ ባወቃችሁ ነበር። ከአሁንም ጀምራችሁ ታውቁታላችሁ አይታችሁትማል አለው።
ዮሐ14፥8 ፊልጶስ ጌታ ሆይ፥ አብን አሳየንና ይበቃናል አለው። ኢየሱስም አለው።
ዮሐ14፥9 አንተ ፊልጶስ፥ ይህን ያህል ዘመን ከእናንተ ጋር ስኖር አታውቀኝምን? እኔን ያየ አብን አይቶአል።
"እኔን ያየ አብን አይቶአል" ማለት እና "እኔ አብ ነኝ ወይም እኔ አምላክ ነኝ" ማለት አንድ የሚሆነው በምን ሒሣብ ታሥቦ ነው? ኢየሱስ፦ "እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል" ብሏል፥ እና ሐዋርያት ኢየሱስ ናቸውን? ተመሳሳይ ሰዋስው ነው፦
ማቴዎስ 10፥40 እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።
"እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል" ማለት "ሐዋርያትን መቀበል ኢየሱስን እንደ መቀበል ነው" ማለት ከሆነ እንግዲያውስ "እኔን ያየ አብን አይቶአል" ማለት "ወልድን ማየት አብን እንደ ማየት ነው" ማለት ነው፥ "እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል" ማለት "ወልድን መቀበል አብን እንደ መቀበል ነው" ማለት ከሆነ "ወልድን ማየት አብን እንደ ማየት ነው" ማለት ነው። ተመሳሳይ ሙግት እንመልከት፦
ሉቃ10፥16 እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል፤ እኔንም የጣለ የላከኝን ይጥላል።
"እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል" ማለት "ሐዋርያትን መጣል ኢየሱስን እንደ መጣል ነው" ማለት ከሆነ እንግዲያውስ "እኔን ያየ አብን አይቶአል ማለት ወልድን ማየት አብን እንደ ማየት ነው" ማለት ነው፥ "እኔንም የጣለ የላከኝን ይጥላል" ማለት "ወልድን መጣል አብን እንደ መጣል ነው" ማለት ከሆነ "ወልድን ማየት አብን እንደማየት ነው" ማለት ነው። እንቀጥል፦
ዮሐንስ 5፥46 ሙሴንስ ብታምኑት እኔን ባመናችሁ ነበር።
"ሙሴንስ ብታምኑት እኔን ባመናችሁ ነበር" ማለት ሙሴ ኢየሱስ ነውን? ወይስ "ሙሴን ማመን ኢየሱስ እንደ ማመን ነው" ማለት ነው? እንዲሁ ኢየሱስን ማየት አብን እንደ ማየት ነው፣ ኢየሱስን ማወቅ አብን እንደ ማወቅ ነው፣ ኢየሱስን መጥላት አብን እንደ መጥላት ነው፦
ዮሐንስ 12፥45 እኔንም የሚያይ የላከኝን ያያል።
ዮሐንስ 14፥7 እኔንስ ብታውቁኝ አባቴን ደግሞ ባወቃችሁ ነበር።
ዮሐንስ 15፥23 እኔን የሚጠላ አባቴን ደግሞ ይጠላል።
"እኔን" አንደኛ ማንነት "የላከኝ ወይም አባቴ" ሁለተኛ ማንነት፥ ስለዚህ ሁለት ማንነቶችን ቀልጭ አርጎ ያሳያል፦
ዮሐንስ 15፥24 አሁን ግን እኔንም አባቴንም አይተውማል ጠልተውማል።
ያዩት እና የጠሉት ሁለት ማንነት ነው፥ "እኔን" አንድ "አባቴን" ሁለት። አብን ታውቁታላችሁ አይታችሁትማል፦
ዮሐንስ 14፥7 ከአሁንም ጀምራችሁ ታውቁታላችሁ አይታችሁትማል" አለው።
"ማየት" ማለት በእማሬአዊ አብን በሥጋ ዓይን መመልከት ሳይሆን በመልእክተኛው ማንነት ውስጥ በፍካሬአዊ "መገንዘብ" ማለት ነው፦
ዮሐንስ 6፥46። አብን ያየ ማንም የለም፥ ከእግዚአብሔር ከሆነ በቀር እርሱ አብን አይቶአል።
"ከሆነ" የሚለው ቃል በቅጡ ይሰመርበት! "ከ"-እግዚአብሔር የሆነ መንፈሳዊ ሰው እርሱ አብን አይቷል፥ በሥጋ ዓይን ግን አብን ያየ ማንም የለም፦
ዮሐንስ 5፥37 የላከኝ አብም እርሱ ስለ እኔ መስክሮአል። ድምፁን ከቶ አልሰማችሁም፥ “መልኩንም አላያችሁም”፤
ዮሐንስ 1፥18 መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም።
1ኛ ዮሐንስ 4፥12 እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም።
1ኛ ጢሞቴዎስ 6፥16 አንድ ሰው እንኳ አላየውም ሊያይም አይቻለውም።
ከኢየሱስ እርገት በኃላ "እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም" ሲባል ኢየሱስ "አብን አይታችሁትማል" ከሚለው ጋር ለማስማማት የሚቻለው "ወልድን ማየት አብን እንደ ማየት ነው" በሚል ቀመር ብቻ ነው። ብሉይ ኪዳን ላይ መላእክት ሲገለጡ ሰዎች "እግዚአብሔር አይተናል" ይሉ ነበር።
ናሙና አንድ፦
ዘፍጥረት 16፥7 "የእግዚአብሔር መልአክም" በውኃ ምንጭ አጠገብ በበረሀ አገኛት።
ዘፍጥረት 16፥13 እርስዋም ይናገራት የነበረውን የእግዚአብሔርን ስም ኤልሮኢ ብላ ጠራች፤ የሚያየኝን በውኑ እዚህ ደግሞ አየሁትን? ብላለችና።
ናሙና ሁለት፦
ሆሴዕ 12፥4 "ከመልአኩም" ጋር ታግሎ አሸነፈ፤ አልቅሶም ለመነው።
ዘፍጥረት 32፥24 ያዕቆብ ግን ለብቻው ቀረ፤ አንድ "ሰውም" እስከ ንጋት ድረስ ይታገለው ነበር።
ዘፍጥረት 32፥30 ያዕቆብም፦ እግዚአብሔርን ፊት ለፊት አየሁ፥ ሰውነቴም ድና ቀረች" ሲል የዚያን ቦታ ስም ጵኒኤል ብሎ ጠራው።
ናሙና ሦስት፦
መሣፍንት 13፥21 ያን ጊዜም ማኑሄ "የእግዚአብሔር መልአክ" መሆኑን አወቀ።
መሣፍንት 13፥22 ማኑሄም ሚስቱን፦ እግዚአብሔርን አይተናልና ሞት እንሞታለን" አላት።
መላእክት መልእክተኞች ሲሆኑ በመላእክት የአምላክ መታየት "አስተርዮተ አምላክ"theophany" ሲሆን ይህም መታየት ፍካሬአዊ እንጂ እማሬአዊ አይደለም፦
ዘጸአት 33፥20 ደግሞም፦ ሰው አይቶኝ አይድንምና ፊቴን ማየት አይቻልህም፡ አለ።
መላእክትን ማየት እግዚአብሔር ማየት ከሆነ መልእክተኛውን "ኢየሱስን ማየት እግዚአብሔር ማየት ነው" ብሎ መረዳት እንጂ መልእክተኛው እራሱ አብ ወይም አምላክ ነው" ብሎ መደምደም የሾቀ ድምዳሜ ነው። የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፦
5፥75 የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ
ኢየሱስን የላከውን አንዱን አምላክ አሏህ እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አሏህን ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
5፥75 የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ
"እኔን ያየ አብን አይቶአል" የሚለውን ኃይለ-ቃል ይዘው የሐዋርያት ቤተክርስቲያን በተለምዶ ኢየሱስ ብቻ"only Jesus" የሚባሉት፦ "ኢየሱስ አብ ነው" ሲሉ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ፣ አንግሊካን እና ፕሮቴስታንት ደግሞ፦ "ኢየሱስ አምላክ ነው" የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል፥ እውን ይህ ኃይለ-ቃል "ኢየሱስ አብ ነው" ወይም "ኢየሱስ አምላክ ነው" ለሚለው ዶክትሪን ድምዳሜ ላይ ያደርሳልን? ጥቅሱን በሰከነ እና በሰላ አእምሮ እንመልከተው፦
ዮሐ14፥7 እኔንስ ብታውቁኝ አባቴን ደግሞ ባወቃችሁ ነበር። ከአሁንም ጀምራችሁ ታውቁታላችሁ አይታችሁትማል አለው።
ዮሐ14፥8 ፊልጶስ ጌታ ሆይ፥ አብን አሳየንና ይበቃናል አለው። ኢየሱስም አለው።
ዮሐ14፥9 አንተ ፊልጶስ፥ ይህን ያህል ዘመን ከእናንተ ጋር ስኖር አታውቀኝምን? እኔን ያየ አብን አይቶአል።
"እኔን ያየ አብን አይቶአል" ማለት እና "እኔ አብ ነኝ ወይም እኔ አምላክ ነኝ" ማለት አንድ የሚሆነው በምን ሒሣብ ታሥቦ ነው? ኢየሱስ፦ "እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል" ብሏል፥ እና ሐዋርያት ኢየሱስ ናቸውን? ተመሳሳይ ሰዋስው ነው፦
ማቴዎስ 10፥40 እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።
"እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል" ማለት "ሐዋርያትን መቀበል ኢየሱስን እንደ መቀበል ነው" ማለት ከሆነ እንግዲያውስ "እኔን ያየ አብን አይቶአል" ማለት "ወልድን ማየት አብን እንደ ማየት ነው" ማለት ነው፥ "እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል" ማለት "ወልድን መቀበል አብን እንደ መቀበል ነው" ማለት ከሆነ "ወልድን ማየት አብን እንደ ማየት ነው" ማለት ነው። ተመሳሳይ ሙግት እንመልከት፦
ሉቃ10፥16 እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል፤ እኔንም የጣለ የላከኝን ይጥላል።
"እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል" ማለት "ሐዋርያትን መጣል ኢየሱስን እንደ መጣል ነው" ማለት ከሆነ እንግዲያውስ "እኔን ያየ አብን አይቶአል ማለት ወልድን ማየት አብን እንደ ማየት ነው" ማለት ነው፥ "እኔንም የጣለ የላከኝን ይጥላል" ማለት "ወልድን መጣል አብን እንደ መጣል ነው" ማለት ከሆነ "ወልድን ማየት አብን እንደማየት ነው" ማለት ነው። እንቀጥል፦
ዮሐንስ 5፥46 ሙሴንስ ብታምኑት እኔን ባመናችሁ ነበር።
"ሙሴንስ ብታምኑት እኔን ባመናችሁ ነበር" ማለት ሙሴ ኢየሱስ ነውን? ወይስ "ሙሴን ማመን ኢየሱስ እንደ ማመን ነው" ማለት ነው? እንዲሁ ኢየሱስን ማየት አብን እንደ ማየት ነው፣ ኢየሱስን ማወቅ አብን እንደ ማወቅ ነው፣ ኢየሱስን መጥላት አብን እንደ መጥላት ነው፦
ዮሐንስ 12፥45 እኔንም የሚያይ የላከኝን ያያል።
ዮሐንስ 14፥7 እኔንስ ብታውቁኝ አባቴን ደግሞ ባወቃችሁ ነበር።
ዮሐንስ 15፥23 እኔን የሚጠላ አባቴን ደግሞ ይጠላል።
"እኔን" አንደኛ ማንነት "የላከኝ ወይም አባቴ" ሁለተኛ ማንነት፥ ስለዚህ ሁለት ማንነቶችን ቀልጭ አርጎ ያሳያል፦
ዮሐንስ 15፥24 አሁን ግን እኔንም አባቴንም አይተውማል ጠልተውማል።
ያዩት እና የጠሉት ሁለት ማንነት ነው፥ "እኔን" አንድ "አባቴን" ሁለት። አብን ታውቁታላችሁ አይታችሁትማል፦
ዮሐንስ 14፥7 ከአሁንም ጀምራችሁ ታውቁታላችሁ አይታችሁትማል" አለው።
"ማየት" ማለት በእማሬአዊ አብን በሥጋ ዓይን መመልከት ሳይሆን በመልእክተኛው ማንነት ውስጥ በፍካሬአዊ "መገንዘብ" ማለት ነው፦
ዮሐንስ 6፥46። አብን ያየ ማንም የለም፥ ከእግዚአብሔር ከሆነ በቀር እርሱ አብን አይቶአል።
"ከሆነ" የሚለው ቃል በቅጡ ይሰመርበት! "ከ"-እግዚአብሔር የሆነ መንፈሳዊ ሰው እርሱ አብን አይቷል፥ በሥጋ ዓይን ግን አብን ያየ ማንም የለም፦
ዮሐንስ 5፥37 የላከኝ አብም እርሱ ስለ እኔ መስክሮአል። ድምፁን ከቶ አልሰማችሁም፥ “መልኩንም አላያችሁም”፤
ዮሐንስ 1፥18 መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም።
1ኛ ዮሐንስ 4፥12 እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም።
1ኛ ጢሞቴዎስ 6፥16 አንድ ሰው እንኳ አላየውም ሊያይም አይቻለውም።
ከኢየሱስ እርገት በኃላ "እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም" ሲባል ኢየሱስ "አብን አይታችሁትማል" ከሚለው ጋር ለማስማማት የሚቻለው "ወልድን ማየት አብን እንደ ማየት ነው" በሚል ቀመር ብቻ ነው። ብሉይ ኪዳን ላይ መላእክት ሲገለጡ ሰዎች "እግዚአብሔር አይተናል" ይሉ ነበር።
ናሙና አንድ፦
ዘፍጥረት 16፥7 "የእግዚአብሔር መልአክም" በውኃ ምንጭ አጠገብ በበረሀ አገኛት።
ዘፍጥረት 16፥13 እርስዋም ይናገራት የነበረውን የእግዚአብሔርን ስም ኤልሮኢ ብላ ጠራች፤ የሚያየኝን በውኑ እዚህ ደግሞ አየሁትን? ብላለችና።
ናሙና ሁለት፦
ሆሴዕ 12፥4 "ከመልአኩም" ጋር ታግሎ አሸነፈ፤ አልቅሶም ለመነው።
ዘፍጥረት 32፥24 ያዕቆብ ግን ለብቻው ቀረ፤ አንድ "ሰውም" እስከ ንጋት ድረስ ይታገለው ነበር።
ዘፍጥረት 32፥30 ያዕቆብም፦ እግዚአብሔርን ፊት ለፊት አየሁ፥ ሰውነቴም ድና ቀረች" ሲል የዚያን ቦታ ስም ጵኒኤል ብሎ ጠራው።
ናሙና ሦስት፦
መሣፍንት 13፥21 ያን ጊዜም ማኑሄ "የእግዚአብሔር መልአክ" መሆኑን አወቀ።
መሣፍንት 13፥22 ማኑሄም ሚስቱን፦ እግዚአብሔርን አይተናልና ሞት እንሞታለን" አላት።
መላእክት መልእክተኞች ሲሆኑ በመላእክት የአምላክ መታየት "አስተርዮተ አምላክ"theophany" ሲሆን ይህም መታየት ፍካሬአዊ እንጂ እማሬአዊ አይደለም፦
ዘጸአት 33፥20 ደግሞም፦ ሰው አይቶኝ አይድንምና ፊቴን ማየት አይቻልህም፡ አለ።
መላእክትን ማየት እግዚአብሔር ማየት ከሆነ መልእክተኛውን "ኢየሱስን ማየት እግዚአብሔር ማየት ነው" ብሎ መረዳት እንጂ መልእክተኛው እራሱ አብ ወይም አምላክ ነው" ብሎ መደምደም የሾቀ ድምዳሜ ነው። የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፦
5፥75 የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ
ኢየሱስን የላከውን አንዱን አምላክ አሏህ እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አሏህን ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
አንዋዑል ዒባዳህ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
21፥92 ይህች አንዲት መንገድ ስትሆን በእርግጥ ሃይማኖታችሁ ናት፡፡ እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ፡፡ إِنَّ هَـٰذِهِ أُمَّتُكُمْ أُمَّةً وَاحِدَةً وَأَنَا رَبُّكُمْ فَاعْبُدُونِ
ቁርኣን ውስጥ "ኢሥቲንባጥ" اِسْتِنْبَاطْ ሲደረግ የዒባዳህ ዓይነቶች ፍንትው እና ቁልጭ ብለው ይወጣሉ። "ነውዕ" نَوْع የሚለው ቃል "ናዐ" نَاعَ ማለትም "መደበ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ምድብ" "ዓይነት" ማለት ነው፥ የነውዕ ብዙ ቁጥር ደግሞ "አንዋዕ" أنْوَاع ሲሆን "ዓይነቶች" ማለት ነው። በጥቅሉ "አንዋዑል ኢባዳህ" أنْوَاعُ العِبَادَة ማለት "የአምልኮ ዓይነቶች" ማለት ነው፥ አንዋዑል ኢባዳህ የሚባሉት ዒባደቱል ቀልቢያህ፣ ዒባደቱል ቀውሊያህ እና ዒባደቱል ዐመሊያህ ናቸው። እነዚህን ነጥብ በነጥብ እንመልከት፦
ነጥብ አንድ
"ቀልቢያህ"
"ዒባደቱል ቀልቢያ" عِبَادَة القَلْبِيَّة ማለት "የኃልዮ አምልኮ" ማለት ነው፥ "ቀልብ" قَلْب የሚለው ቃል "ቀለበ" قَلَبَ ማለትም "ለበወ" "ኀለየ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ልብ" "ኃልዮ" ማለት ነው። በልብ የሚፈጸሙ አምልኮ ዒልሚያህ፣ ኢማንያህ፣ ኢኽላስ፣ ኢሕሣን፣ ተወኩል፣ ተቅዋእ፣ ሶብር እና መሐባህ ናቸው፦
፨"ዒልሚያህ" عِلْمِيَّة ማለት "ዕውቀት" ማለት ሲሆን ይህም የዕውቀት ቁንጮ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه የሚለውን ዐቂዳህ ማወት ነው።
፨"ኢማንያህ" ِإِيمَانِيَّة ማለት "እምነት" ማለት ነው፥ ኢማን ከሰባ ወይም ከስልሳ በላይ ቅርንጫፎች ያሉት ሲሆን ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه የሚለው ቃል ነው።
፨"ኢኽላስ" إِخْلَاص ማለት እውነት ለማንገሥ ሐሠትን ለማርከሥ የሚደረግ "መተናነስ" ወይም ከሙገሳ እና ከወቀሳ ነጻ ሆኖ ለአሏህ ውዴታ የሚደረግ "ማጥራት" ማለት ነው።
፨"ኢሕሣን" ማለት "አሏህን እንደምታየው አርገህ ማምለክ፥ አሊያም አሏህ እንደሚያይህ አርገህ ማምለክ" ማለት ነው።
፨"ተወኩል" تَوَكُّل ማለት "አሏህን መጠጊያ፣ መመኪያ፣ መሸሸጊያ አድርገን የምንይዝበት ዐቅም" ማለት ነው።
፨"ተቅዋእ" تَقْوَا ማለት "አሏህ ሁሉን ዐዋቂ ነው” በልቤ የማስበውን ያውቃል፣ “አሏህ ሁሉን ነገር ሰሚ ነው” መስጥሬ የምናገረውን ይሰማል፣ “አሏህ ሁሉን ተመልካች ነው” ተደብቄ የማደርገውን ያያል ብሎ መጥፎ ከማሰብ፣ ከመናገር፣ ከማድረግ እድንቆጠብ የሚያደርገን ስሜት ነው።
፨"ተዋዱዕ تَوَاضُع ማለት "መተናነስ"humility" ማለት ሲሆን ለአሏህ የሚደረግ መጎባደድ ነው።
፨"ሶብር" صَّبْر ማለት "ሙሲባህ ሲመጣ ኢሥቲርጃዕ በማድረግ የምናሳልፍበትን ዐቅም የሚሰጥ ስሜት ነው።
፨"መሐባህ" مَحَبَّة አሏህን በፍጹም እና በሙሉ ሁለንተና ማፍቀር ነው።
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
21፥92 ይህች አንዲት መንገድ ስትሆን በእርግጥ ሃይማኖታችሁ ናት፡፡ እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ፡፡ إِنَّ هَـٰذِهِ أُمَّتُكُمْ أُمَّةً وَاحِدَةً وَأَنَا رَبُّكُمْ فَاعْبُدُونِ
ቁርኣን ውስጥ "ኢሥቲንባጥ" اِسْتِنْبَاطْ ሲደረግ የዒባዳህ ዓይነቶች ፍንትው እና ቁልጭ ብለው ይወጣሉ። "ነውዕ" نَوْع የሚለው ቃል "ናዐ" نَاعَ ማለትም "መደበ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ምድብ" "ዓይነት" ማለት ነው፥ የነውዕ ብዙ ቁጥር ደግሞ "አንዋዕ" أنْوَاع ሲሆን "ዓይነቶች" ማለት ነው። በጥቅሉ "አንዋዑል ኢባዳህ" أنْوَاعُ العِبَادَة ማለት "የአምልኮ ዓይነቶች" ማለት ነው፥ አንዋዑል ኢባዳህ የሚባሉት ዒባደቱል ቀልቢያህ፣ ዒባደቱል ቀውሊያህ እና ዒባደቱል ዐመሊያህ ናቸው። እነዚህን ነጥብ በነጥብ እንመልከት፦
ነጥብ አንድ
"ቀልቢያህ"
"ዒባደቱል ቀልቢያ" عِبَادَة القَلْبِيَّة ማለት "የኃልዮ አምልኮ" ማለት ነው፥ "ቀልብ" قَلْب የሚለው ቃል "ቀለበ" قَلَبَ ማለትም "ለበወ" "ኀለየ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ልብ" "ኃልዮ" ማለት ነው። በልብ የሚፈጸሙ አምልኮ ዒልሚያህ፣ ኢማንያህ፣ ኢኽላስ፣ ኢሕሣን፣ ተወኩል፣ ተቅዋእ፣ ሶብር እና መሐባህ ናቸው፦
፨"ዒልሚያህ" عِلْمِيَّة ማለት "ዕውቀት" ማለት ሲሆን ይህም የዕውቀት ቁንጮ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه የሚለውን ዐቂዳህ ማወት ነው።
፨"ኢማንያህ" ِإِيمَانِيَّة ማለት "እምነት" ማለት ነው፥ ኢማን ከሰባ ወይም ከስልሳ በላይ ቅርንጫፎች ያሉት ሲሆን ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه የሚለው ቃል ነው።
፨"ኢኽላስ" إِخْلَاص ማለት እውነት ለማንገሥ ሐሠትን ለማርከሥ የሚደረግ "መተናነስ" ወይም ከሙገሳ እና ከወቀሳ ነጻ ሆኖ ለአሏህ ውዴታ የሚደረግ "ማጥራት" ማለት ነው።
፨"ኢሕሣን" ማለት "አሏህን እንደምታየው አርገህ ማምለክ፥ አሊያም አሏህ እንደሚያይህ አርገህ ማምለክ" ማለት ነው።
፨"ተወኩል" تَوَكُّل ማለት "አሏህን መጠጊያ፣ መመኪያ፣ መሸሸጊያ አድርገን የምንይዝበት ዐቅም" ማለት ነው።
፨"ተቅዋእ" تَقْوَا ማለት "አሏህ ሁሉን ዐዋቂ ነው” በልቤ የማስበውን ያውቃል፣ “አሏህ ሁሉን ነገር ሰሚ ነው” መስጥሬ የምናገረውን ይሰማል፣ “አሏህ ሁሉን ተመልካች ነው” ተደብቄ የማደርገውን ያያል ብሎ መጥፎ ከማሰብ፣ ከመናገር፣ ከማድረግ እድንቆጠብ የሚያደርገን ስሜት ነው።
፨"ተዋዱዕ تَوَاضُع ማለት "መተናነስ"humility" ማለት ሲሆን ለአሏህ የሚደረግ መጎባደድ ነው።
፨"ሶብር" صَّبْر ማለት "ሙሲባህ ሲመጣ ኢሥቲርጃዕ በማድረግ የምናሳልፍበትን ዐቅም የሚሰጥ ስሜት ነው።
፨"መሐባህ" مَحَبَّة አሏህን በፍጹም እና በሙሉ ሁለንተና ማፍቀር ነው።
ነጥብ ሁለት
"ቀውልያ"
"ዒባደቱል ቀውልያ" عِبَادَة القَوْلِيَّة ማለት "የነቢብ አምልኮ" ማለት ነው፥ "ቀውል" قَوْل የሚለው ቃል "ቀወለ" قَوَّلَ ማለትም "ነበበ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ነቢብ" "አንደበት" ማለት ነው። በአንደበት የሚፈጸሙ አምልኮ ሸሃዳህ፣ ተውባህ፣ ዱዓእ፣ ደዕዋህ፣ ዚክር እና ቂርኣት ናቸው፦
፨"ሸሃዳህ" شَهَادَة ማለት "አሽሀዱ አነ ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" أَشْهَدُ أَنْ لَا إِلٰهَ إِلَّا ٱلله እና "አሽሀዱ አነ ሙሐመደን ረሡሉሏህ" أَشْهَدُ أَنَّ مُحَمَّدًا رَسُولُ ٱلله በማለት በአፍ የምናውጀው ቃለ-ምስክርነት ነው።
፨"ተውባህ" تَوْبَة ማለት ከልብ አሏህን ይቅርታ በመጠየቅ "ይቅር በለኝ" ብሎ መማጸን ነው።
፨"ዱዓእ" دُعَآء ማለት አሏህን በተለያዩ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ስሙን በመጥራት እየለመንን የምንጠይቀው ነው።
፨"ደዕዋህ" دَعْوَة ሰዎችን ከሺርክ፣ ከኩፍር፣ ከቢድዓህ፣ ከፈሣድ ወደ አሏህ የምንጠራበት አስተምህሮት ነው።
፨"ዚክር" ذِكْر የአሏህ ስም በተህሊል፣ በተክቢር፣ በተሕሚድ፣ በተሥቢሕ፣ በተምጂድ፣ በኢሥቲግፋር፣ በኢሥቲዓዛህ፣ በበስመሏህ፣ በሐስበላህ፣ በኢሥቲርጃህ እየጠራን የምንዘክረው ነው።
፨"ቂርኣት" قِرْاءَت ማለት ቁርኣንን በሙጀወድ ወይም በሙረተል ደንቡን ጠብቆ መቅራት ነው።
ነጥብ ሦስት
"ዐመል"
"ዒባደቱል ዐመልያ" عِبَادَة العَمَلِيَّة ማለት "የገቢር አምልኮ" ማለት ነው፥ "ዐመል"عَمَل የሚለው ቃል "ዐሚለ" عَمِلَ ማለትም "ገበረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ገቢር" "ድርጊት" ማለት ነው። በድርጊት የሚፈጸሙ አምልኮ ሶላት፤ ሶውም፣ ዘካህ፣ ሐጅ እና ጂሃድ ናቸው፦
፨"ሶላት" صَّلَات ማለት ቂያም፣ ሩኩዕ፣ ሡጁድ የያዘ "ጸሎት" ነው።
፨"ሶውም" صَوْم ማለት ከፈጅር እስከ መግሪብ ከምግብ እና ከመጠጥ ተከልክሎ ተቅዋእ መቀበያ ነው።
፨"ዘካህ" زَكَاة ማለት አሏህ ከሰጠን ሲሳይ ላይ መጥራራት ለማግኘት ለድኾች፣ ለምስኪኖችም፣ ለባለ ዕዳዎችም ወዘተ የሚሰጥ ምጽዋት ነው።
፨"ሐጅ" حَجّ ማለት የአሏህ ቤት በደንቡ መጎብኘት ነው።
፨"ጂሃድ" جِهَاد ማለት እውነት ለማንገሥ እና ሐሠትን ለማርከሥ ተብሎ በአሏህ መንገድ የሚደረግ ትግል ነው።
ስንጠቀልለው በቀልብ፣ በቀውል እና በዐመል የሚፈጸሙ የዒባዳህ ዓይነቶች አንዱ ከሌላው ጋር የተሰናሰነ እና የተሳሰረ ነው፥ ለምሳሌ ኢማንያህ ዒባደቱል ቀልቢያህ ቢሆንም በቀውል የምንመከክረው እና በዐመል የምንተገብረው ነው፣ ጂሃድ ዒባደቱል ዐመልያ ቢሆንም በቀውል የምናገረው እና በቀልብ የምናስበው ነው፣ ተውባህ ዒባደቱል ቀውልያ ቢሆንም በቀልብ የምንጸጸተው እና በዐመል መጥፎ ድርጊቱን የምንተወው ነው።
አምላካችን አሏህ በኢማን፣ በኢኽላስ፣ በኢትባዕ የምናመልከው ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
"ቀውልያ"
"ዒባደቱል ቀውልያ" عِبَادَة القَوْلِيَّة ማለት "የነቢብ አምልኮ" ማለት ነው፥ "ቀውል" قَوْل የሚለው ቃል "ቀወለ" قَوَّلَ ማለትም "ነበበ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ነቢብ" "አንደበት" ማለት ነው። በአንደበት የሚፈጸሙ አምልኮ ሸሃዳህ፣ ተውባህ፣ ዱዓእ፣ ደዕዋህ፣ ዚክር እና ቂርኣት ናቸው፦
፨"ሸሃዳህ" شَهَادَة ማለት "አሽሀዱ አነ ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" أَشْهَدُ أَنْ لَا إِلٰهَ إِلَّا ٱلله እና "አሽሀዱ አነ ሙሐመደን ረሡሉሏህ" أَشْهَدُ أَنَّ مُحَمَّدًا رَسُولُ ٱلله በማለት በአፍ የምናውጀው ቃለ-ምስክርነት ነው።
፨"ተውባህ" تَوْبَة ማለት ከልብ አሏህን ይቅርታ በመጠየቅ "ይቅር በለኝ" ብሎ መማጸን ነው።
፨"ዱዓእ" دُعَآء ማለት አሏህን በተለያዩ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ስሙን በመጥራት እየለመንን የምንጠይቀው ነው።
፨"ደዕዋህ" دَعْوَة ሰዎችን ከሺርክ፣ ከኩፍር፣ ከቢድዓህ፣ ከፈሣድ ወደ አሏህ የምንጠራበት አስተምህሮት ነው።
፨"ዚክር" ذِكْر የአሏህ ስም በተህሊል፣ በተክቢር፣ በተሕሚድ፣ በተሥቢሕ፣ በተምጂድ፣ በኢሥቲግፋር፣ በኢሥቲዓዛህ፣ በበስመሏህ፣ በሐስበላህ፣ በኢሥቲርጃህ እየጠራን የምንዘክረው ነው።
፨"ቂርኣት" قِرْاءَت ማለት ቁርኣንን በሙጀወድ ወይም በሙረተል ደንቡን ጠብቆ መቅራት ነው።
ነጥብ ሦስት
"ዐመል"
"ዒባደቱል ዐመልያ" عِبَادَة العَمَلِيَّة ማለት "የገቢር አምልኮ" ማለት ነው፥ "ዐመል"عَمَل የሚለው ቃል "ዐሚለ" عَمِلَ ማለትም "ገበረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ገቢር" "ድርጊት" ማለት ነው። በድርጊት የሚፈጸሙ አምልኮ ሶላት፤ ሶውም፣ ዘካህ፣ ሐጅ እና ጂሃድ ናቸው፦
፨"ሶላት" صَّلَات ማለት ቂያም፣ ሩኩዕ፣ ሡጁድ የያዘ "ጸሎት" ነው።
፨"ሶውም" صَوْم ማለት ከፈጅር እስከ መግሪብ ከምግብ እና ከመጠጥ ተከልክሎ ተቅዋእ መቀበያ ነው።
፨"ዘካህ" زَكَاة ማለት አሏህ ከሰጠን ሲሳይ ላይ መጥራራት ለማግኘት ለድኾች፣ ለምስኪኖችም፣ ለባለ ዕዳዎችም ወዘተ የሚሰጥ ምጽዋት ነው።
፨"ሐጅ" حَجّ ማለት የአሏህ ቤት በደንቡ መጎብኘት ነው።
፨"ጂሃድ" جِهَاد ማለት እውነት ለማንገሥ እና ሐሠትን ለማርከሥ ተብሎ በአሏህ መንገድ የሚደረግ ትግል ነው።
ስንጠቀልለው በቀልብ፣ በቀውል እና በዐመል የሚፈጸሙ የዒባዳህ ዓይነቶች አንዱ ከሌላው ጋር የተሰናሰነ እና የተሳሰረ ነው፥ ለምሳሌ ኢማንያህ ዒባደቱል ቀልቢያህ ቢሆንም በቀውል የምንመከክረው እና በዐመል የምንተገብረው ነው፣ ጂሃድ ዒባደቱል ዐመልያ ቢሆንም በቀውል የምናገረው እና በቀልብ የምናስበው ነው፣ ተውባህ ዒባደቱል ቀውልያ ቢሆንም በቀልብ የምንጸጸተው እና በዐመል መጥፎ ድርጊቱን የምንተወው ነው።
አምላካችን አሏህ በኢማን፣ በኢኽላስ፣ በኢትባዕ የምናመልከው ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የረመዷን ወር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
2፥185 እንድትጦሙ የተጻፈባችሁ ያ በእርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድ እና እውነትን ከውሸት ከሚለዩም ገላጮች አንቀጾች ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዳን ወር ነው፡፡ ከእናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጡመው፡፡ شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ ۚ فَمَن شَهِدَ مِنكُمُ الشَّهْرَ فَلْيَصُمْهُ
"ሸህር" شَهْر የሚለው ቃል "ሸሀረ" شَهَرَ ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ወር" ማለት ነው፥ "ሸህር" شَهْر የሚለው ቃል በቁርኣን ውስጥ በነጠላ የመጣው 12 ጊዜ ነው። የሚያጅበው የወሮች ቁጥር አሏህ ዘንድ በአሏህ መጽሐፍ አሥራ ሁለት ነው፥ እነዚህም፦
1ኛው ወር "ሙሐረም" مُحَرَّم
2ኛው ወር "ሶፈር" صَفَر
3ኛው ወር "ረቢዑል-አወል" رَبِيع ٱلْأَوَّل
4ኛው ወር "ረቢዑ አስ-ሳኒይ" رَبِيع ٱلثَّانِي
5ኛው ወር "ጁማዱል-አወል" جُمَادَىٰ ٱلْأَوَّل
6ኛው ወር። ጀማዱ አስ-ሳኒይ" جُمَادَىٰ ٱلثَّانِي
7ኛው ወር "ረጀብ" رَجَب
8ኛው ወር "ሸዕባን" شَعْبَان
9ኛው ወር "ረመዷን" رَمَضَان
10ኛው ወር "ሸዋል" شَوَّال
11ኛው ወር "ዙል-ቀዕዳህ" ذُو ٱلْقَعْدَة
12ኛው ወር "ዙል-ሒጃህ" ذُو ٱلْحِجَّة ናቸው፦
9፥36 የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ውስጥ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን ዐሥራ ሁለት ወር ነው፡፡ ከእነርሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው፡፡ إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِندَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65 ሐዲስ 4662
አቡበከር”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ ”ዘመን አላህ ሰማያትን እና ምድር በፈጠረበት ቀን የቀድሞ ሁኔታ ይመለሳል። አንድ ዓመት ዐሥራ ሁለት ወር ነው፥ ከእነርሱም አራቱ የተከበሩ ናቸው። ሦስቱ ተከታታይ ዙል-ቀዒዳህ፣ ዙል-ሒጃህ፣ ሙሐረም ናቸው፥ አራተኛው በጀማዱ-ሣኒ እና በሻዕባን መካከል ያለው ረጀብ ነው። عَنْ أَبِي بَكْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ إِنَّ الزَّمَانَ قَدِ اسْتَدَارَ كَهَيْئَتِهِ يَوْمَ خَلَقَ اللَّهُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضَ، السَّنَةُ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا مِنْهَا، أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ، ثَلاَثٌ مُتَوَالِيَاتٌ، ذُو الْقَعْدَةِ وَذُو الْحِجَّةِ وَالْمُحَرَّمُ وَرَجَبُ مُضَرَ الَّذِي بَيْنَ جُمَادَى وَشَعْبَانَ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
2፥185 እንድትጦሙ የተጻፈባችሁ ያ በእርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድ እና እውነትን ከውሸት ከሚለዩም ገላጮች አንቀጾች ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዳን ወር ነው፡፡ ከእናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጡመው፡፡ شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ ۚ فَمَن شَهِدَ مِنكُمُ الشَّهْرَ فَلْيَصُمْهُ
"ሸህር" شَهْر የሚለው ቃል "ሸሀረ" شَهَرَ ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ወር" ማለት ነው፥ "ሸህር" شَهْر የሚለው ቃል በቁርኣን ውስጥ በነጠላ የመጣው 12 ጊዜ ነው። የሚያጅበው የወሮች ቁጥር አሏህ ዘንድ በአሏህ መጽሐፍ አሥራ ሁለት ነው፥ እነዚህም፦
1ኛው ወር "ሙሐረም" مُحَرَّم
2ኛው ወር "ሶፈር" صَفَر
3ኛው ወር "ረቢዑል-አወል" رَبِيع ٱلْأَوَّل
4ኛው ወር "ረቢዑ አስ-ሳኒይ" رَبِيع ٱلثَّانِي
5ኛው ወር "ጁማዱል-አወል" جُمَادَىٰ ٱلْأَوَّل
6ኛው ወር። ጀማዱ አስ-ሳኒይ" جُمَادَىٰ ٱلثَّانِي
7ኛው ወር "ረጀብ" رَجَب
8ኛው ወር "ሸዕባን" شَعْبَان
9ኛው ወር "ረመዷን" رَمَضَان
10ኛው ወር "ሸዋል" شَوَّال
11ኛው ወር "ዙል-ቀዕዳህ" ذُو ٱلْقَعْدَة
12ኛው ወር "ዙል-ሒጃህ" ذُو ٱلْحِجَّة ናቸው፦
9፥36 የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ውስጥ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን ዐሥራ ሁለት ወር ነው፡፡ ከእነርሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው፡፡ إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِندَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65 ሐዲስ 4662
አቡበከር”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ ”ዘመን አላህ ሰማያትን እና ምድር በፈጠረበት ቀን የቀድሞ ሁኔታ ይመለሳል። አንድ ዓመት ዐሥራ ሁለት ወር ነው፥ ከእነርሱም አራቱ የተከበሩ ናቸው። ሦስቱ ተከታታይ ዙል-ቀዒዳህ፣ ዙል-ሒጃህ፣ ሙሐረም ናቸው፥ አራተኛው በጀማዱ-ሣኒ እና በሻዕባን መካከል ያለው ረጀብ ነው። عَنْ أَبِي بَكْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ إِنَّ الزَّمَانَ قَدِ اسْتَدَارَ كَهَيْئَتِهِ يَوْمَ خَلَقَ اللَّهُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضَ، السَّنَةُ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا مِنْهَا، أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ، ثَلاَثٌ مُتَوَالِيَاتٌ، ذُو الْقَعْدَةِ وَذُو الْحِجَّةِ وَالْمُحَرَّمُ وَرَجَبُ مُضَرَ الَّذِي بَيْنَ جُمَادَى وَشَعْبَانَ
“ረመዷን” رَمَضَان የሚለው ቃል "ረመዶ" رَمَضَ ማለትም "ደረቀ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ድርቀት” ወይም “ሞቃት” ማለት ነው፥ ረመዷን የወር ስም እንጂ የጦም ስም አይደለም። የተቆጠሩ ቀኖች የያዘው ረመዷን 9ኛው ወር ሲሆን ይህ ወር የሚጦምበት ምክንያት ቁርኣን ከጥብቁ ሰሌዳ ወደ ቅርቢቱ ሰማይ የወረደበት ወር ስለሆነ ነው፦
2፥185 እንድትጦሙ የተጻፈባችሁ ያ በእርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድ እና እውነትን ከውሸት ከሚለዩም ገላጮች አንቀጾች ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዳን ወር ነው፡፡ ከእናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጡመው፡፡ شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ ۚ فَمَن شَهِدَ مِنكُمُ الشَّهْرَ فَلْيَصُمْهُ
እዚህ አንቀጽ ላይ "የረመዷን ወር" ለሚለው የገባው ቃል “ሸህሩ ረመዷን” شَهْرُ رَمَضَان መሆኑን ልብ አድርግ! ይህ ወር የጸጋ ወር ስለሆነ በዒባዳህ ለሚዘወተሩ የጀነት ደጆች ክፍት የሆነበት፥ በተቃራኒው የእሳት ደጆች የሚዘጉበት ነው። እንዲሁ ማሪድ የሚባሉት ኩፋሩል ጂን የሚባሉት ሸያጢን የሚታሰሩበት ነው፦
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 30, ሐዲስ 9
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው የአላህም መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”የረመዷን ወር ሲጀመር የሰማይ ደጆች ይከፈታሉ፣ የጀሃነም ደጆች ይዘጋሉ፣ ሰይጣናትም ይታሰራሉ”። سَمِعَ أَبَا هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ يَقُولُ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم “ إِذَا دَخَلَ شَهْرُ رَمَضَانَ فُتِّحَتْ أَبْوَابُ السَّمَاءِ، وَغُلِّقَتْ أَبْوَابُ جَهَنَّمَ، وَسُلْسِلَتِ الشَّيَاطِينُ ”
“የሰማይ ደጆች ይከፈታሉ፥ የጀሃነም ደጆች ይዘጋሉ” ማለት "በዚህ ወር የሚሞት ሁሉ እሳት አይገባም፥ ሁሉም ጀነት ይገባል" ማለት ሳይሆን የወሩን ድባብ ታላቅነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፥ በዚህ ወር “የሰማይ ደጆች ይከፈታሉ” ማለት "ሌላውን 11 ወራት ዝግ ነበር" ማለት እንዳልሆነ ሁሉ፥ ሙእሚን ዘርፈ-ብዙ እና መጠነ-ሰፊ የአምልኮ ተግባራትን በማከናወን ወደ አሏህ የሚቀርቡበትን የጸጋ ወር ለማመልከት የተገለጸ ፈሊጣዊ አገላለጽ ነው። ለምሳሌ ሙሥሊም በሳምንት ውስጥ ሁለት ቀናት የሡናህ አጥዋማት ይፆማል፥ እነርሱም ሰኞ እና ሐሙስ ናቸው። ሰኞ እና ሐሙስ የጀነት ደጃፎች በአሏህ ላይ ምንም ነገር ላላሻረከ ሁሉ ይከፈታል፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 45, ሐዲስ 43
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛም እንዲህ አሉ፦ ”የጀነት ደጃፎች በአላህ ላይ ምንም ነገር ላላሻረከ ሁሉ ሰኞ ቀን እና ሐሙስ ቀን ይከፈታል፥ አንድ ሰው በውስጡ መራራነት በወንድሙ ላይ ካለበት በስተቀር”። እንዲህም ይባላል፦ “በሁለቱ መካከል ዕርቅ እስኪሆን ድረስ አጢኑ፣ በሁለቱ መካከል ዕርቅ እስኪሆን ድረስ አጢኑ፣ በሁለቱ መካከል ዕርቅ እስኪሆን ድረስ አጢኑ”። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ” تُفْتَحُ أَبْوَابُ الْجَنَّةِ يَوْمَ الاِثْنَيْنِ وَيَوْمَ الْخَمِيسِ فَيُغْفَرُ لِكُلِّ عَبْدٍ لاَ يُشْرِكُ بِاللَّهِ شَيْئًا إِلاَّ رَجُلاً كَانَتْ بَيْنَهُ وَبَيْنَ أَخِيهِ شَحْنَاءُ فَيُقَالُ أَنْظِرُوا هَذَيْنِ حَتَّى يَصْطَلِحَا أَنْظِرُوا هَذَيْنِ حَتَّى يَصْطَلِحَا أَنْظِرُوا هَذَيْنِ حَتَّى يَصْطَلِحَا
የጀነት ደጃፎች ሰኞ ቀን እና ሐሙስ ቀን ክፍት የሆነው ቂም ወይም ጥላቻ በሙሥሊም ወንድሙ ላይ በልቡ ላልቋጠረ ሙሥሊም ነው። ሰኞ እና ሐሙስ ሳምንታዊ መጠነ-ሰፊ የአምልኮ ጊዜ ለማመልከት እንጂ ሌላውን የአዘቦት ቀናት ሥራዎች አይቀርቡም ወይም አሏህ ይቅር አይልም አሊያም የጀነት ደጃፎች አይከፈቱም ማለትን እንደማያሲዝ ሁሉ በረመዷን ወር “የሰማይ ደጆች ይከፈታሉ” ማለት "ሌላውን 11 ወራት ዝግ ነበር" ማለት አይደለም፥ የሚያሳየው የወሩን ድባብ ታላቅነት ነው።
“አሏሁ አዕለም” اَللّٰهُ أَعْلَم
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
2፥185 እንድትጦሙ የተጻፈባችሁ ያ በእርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድ እና እውነትን ከውሸት ከሚለዩም ገላጮች አንቀጾች ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዳን ወር ነው፡፡ ከእናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጡመው፡፡ شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ ۚ فَمَن شَهِدَ مِنكُمُ الشَّهْرَ فَلْيَصُمْهُ
እዚህ አንቀጽ ላይ "የረመዷን ወር" ለሚለው የገባው ቃል “ሸህሩ ረመዷን” شَهْرُ رَمَضَان መሆኑን ልብ አድርግ! ይህ ወር የጸጋ ወር ስለሆነ በዒባዳህ ለሚዘወተሩ የጀነት ደጆች ክፍት የሆነበት፥ በተቃራኒው የእሳት ደጆች የሚዘጉበት ነው። እንዲሁ ማሪድ የሚባሉት ኩፋሩል ጂን የሚባሉት ሸያጢን የሚታሰሩበት ነው፦
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 30, ሐዲስ 9
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው የአላህም መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”የረመዷን ወር ሲጀመር የሰማይ ደጆች ይከፈታሉ፣ የጀሃነም ደጆች ይዘጋሉ፣ ሰይጣናትም ይታሰራሉ”። سَمِعَ أَبَا هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ يَقُولُ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم “ إِذَا دَخَلَ شَهْرُ رَمَضَانَ فُتِّحَتْ أَبْوَابُ السَّمَاءِ، وَغُلِّقَتْ أَبْوَابُ جَهَنَّمَ، وَسُلْسِلَتِ الشَّيَاطِينُ ”
“የሰማይ ደጆች ይከፈታሉ፥ የጀሃነም ደጆች ይዘጋሉ” ማለት "በዚህ ወር የሚሞት ሁሉ እሳት አይገባም፥ ሁሉም ጀነት ይገባል" ማለት ሳይሆን የወሩን ድባብ ታላቅነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፥ በዚህ ወር “የሰማይ ደጆች ይከፈታሉ” ማለት "ሌላውን 11 ወራት ዝግ ነበር" ማለት እንዳልሆነ ሁሉ፥ ሙእሚን ዘርፈ-ብዙ እና መጠነ-ሰፊ የአምልኮ ተግባራትን በማከናወን ወደ አሏህ የሚቀርቡበትን የጸጋ ወር ለማመልከት የተገለጸ ፈሊጣዊ አገላለጽ ነው። ለምሳሌ ሙሥሊም በሳምንት ውስጥ ሁለት ቀናት የሡናህ አጥዋማት ይፆማል፥ እነርሱም ሰኞ እና ሐሙስ ናቸው። ሰኞ እና ሐሙስ የጀነት ደጃፎች በአሏህ ላይ ምንም ነገር ላላሻረከ ሁሉ ይከፈታል፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 45, ሐዲስ 43
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛም እንዲህ አሉ፦ ”የጀነት ደጃፎች በአላህ ላይ ምንም ነገር ላላሻረከ ሁሉ ሰኞ ቀን እና ሐሙስ ቀን ይከፈታል፥ አንድ ሰው በውስጡ መራራነት በወንድሙ ላይ ካለበት በስተቀር”። እንዲህም ይባላል፦ “በሁለቱ መካከል ዕርቅ እስኪሆን ድረስ አጢኑ፣ በሁለቱ መካከል ዕርቅ እስኪሆን ድረስ አጢኑ፣ በሁለቱ መካከል ዕርቅ እስኪሆን ድረስ አጢኑ”። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ” تُفْتَحُ أَبْوَابُ الْجَنَّةِ يَوْمَ الاِثْنَيْنِ وَيَوْمَ الْخَمِيسِ فَيُغْفَرُ لِكُلِّ عَبْدٍ لاَ يُشْرِكُ بِاللَّهِ شَيْئًا إِلاَّ رَجُلاً كَانَتْ بَيْنَهُ وَبَيْنَ أَخِيهِ شَحْنَاءُ فَيُقَالُ أَنْظِرُوا هَذَيْنِ حَتَّى يَصْطَلِحَا أَنْظِرُوا هَذَيْنِ حَتَّى يَصْطَلِحَا أَنْظِرُوا هَذَيْنِ حَتَّى يَصْطَلِحَا
የጀነት ደጃፎች ሰኞ ቀን እና ሐሙስ ቀን ክፍት የሆነው ቂም ወይም ጥላቻ በሙሥሊም ወንድሙ ላይ በልቡ ላልቋጠረ ሙሥሊም ነው። ሰኞ እና ሐሙስ ሳምንታዊ መጠነ-ሰፊ የአምልኮ ጊዜ ለማመልከት እንጂ ሌላውን የአዘቦት ቀናት ሥራዎች አይቀርቡም ወይም አሏህ ይቅር አይልም አሊያም የጀነት ደጃፎች አይከፈቱም ማለትን እንደማያሲዝ ሁሉ በረመዷን ወር “የሰማይ ደጆች ይከፈታሉ” ማለት "ሌላውን 11 ወራት ዝግ ነበር" ማለት አይደለም፥ የሚያሳየው የወሩን ድባብ ታላቅነት ነው።
“አሏሁ አዕለም” اَللّٰهُ أَعْلَم
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የረመዷን ስጦታ
በስምንት አርስት የተሰደረ አርስት በረመዷን ወር እንካችሁ ብለናል። ሊንኩን በማስፈንጠር ያግኙት!
1. የረመዷን ወር፦
https://tttttt.me/Wahidcom/3107
2. የጨረቃ አቆጣጠር፦
https://tttttt.me/Wahidcom/2717
3. ጨረቃ እና ኮከብ፦
https://tttttt.me/Wahidcom/2360
4. የሚታሰሩ ሰይጣናት፦
https://tttttt.me/Wahidcom/2724
5. ሡሑር፦
https://tttttt.me/Wahidcom/2726
6. ተራዊህ፦
https://tttttt.me/Wahidcom/833
7. ኢዕቲካፍ፦
https://tttttt.me/Wahidcom/2286
8. ለይለቱል ቀድር፦
https://tttttt.me/Wahidcom/2289
ሁሉም ቦታ ለሁሉም ሰው እንዲዳረስ አሰራጩ!
ወጀዛኩሙሏህ ኸይራ!
በስምንት አርስት የተሰደረ አርስት በረመዷን ወር እንካችሁ ብለናል። ሊንኩን በማስፈንጠር ያግኙት!
1. የረመዷን ወር፦
https://tttttt.me/Wahidcom/3107
2. የጨረቃ አቆጣጠር፦
https://tttttt.me/Wahidcom/2717
3. ጨረቃ እና ኮከብ፦
https://tttttt.me/Wahidcom/2360
4. የሚታሰሩ ሰይጣናት፦
https://tttttt.me/Wahidcom/2724
5. ሡሑር፦
https://tttttt.me/Wahidcom/2726
6. ተራዊህ፦
https://tttttt.me/Wahidcom/833
7. ኢዕቲካፍ፦
https://tttttt.me/Wahidcom/2286
8. ለይለቱል ቀድር፦
https://tttttt.me/Wahidcom/2289
ሁሉም ቦታ ለሁሉም ሰው እንዲዳረስ አሰራጩ!
ወጀዛኩሙሏህ ኸይራ!