TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የጤናባለሙያዎችድምጽ

° “ የ3 ወራት የትርፍ ሰዓት ክፍያ አልተሰጠንም ” - የጤና ባለሙያዎች

° “ ለጉዳዩ ምላሽ መስጠት ያለበት ወረዳው ነው ” - የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጤና መምሪያ

° “ የጀበት ችግር ገጥሞን ነው ” - የኪንፋዝ በገላ ጤና ጽ/ቤት
  

በአማራ ክልል፤ ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ኪንፋዝ በገላ ወረዳ የሚገኙ ጤና ባለሙያዎች ከሚያዚያ 2016 ዓ/ም ጀምሮ የትርፍ ሰዓት ክፍያ እንዳልተፈጸመላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አማረዋል።

የጤና ባለሙያዎቹ፣ “ የ3 ወራት የትርፍ ሰዓት ክፍያ አልተሰጠንም። ስንጠይቃቸውም ‘ አንከፍልም ’ ነው የሚሉት ” ብለው፣ ክፍያው እንዲፈጸምላቸው ጠይቀዋል።

የቅሬታ አቅራቢዎቹ ብዛት ከ30 በላይ እንደሆነ፣ የክፍያ መጠኑ እንደዬደረጃቸው እንደሚለያይ ገልጸው፣ ይህ ቅሬታ የተፈጠረው ፦ 
- በስላሬ 
- በጭቅቂ 
- በሮቢት በገላ በተሰኙ 3 የወረዳው ጤና ጣቢያዎች መሆኑን አስረድተዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የጸጥታ ችግር ባለባቸው ቦታዎች የጤና ኤክስቴንሽን፣ ጤና ሙያተኞች ደህንነታችን ዋስትና ሳይሰጠው ‘ የክትባት ዘመቻ ካልዘመታችሁ ’ እየተባልን በስጋት ውስጥ ነው ያለነው ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎቹን ቅሬታ ይዞ የዞኑን ጤና መምሪያ አነጋግሯል።

ለምን ብራቸውን አትከፍሏቸውም ? ስንል ለጠየቅነው ጥያቄ ፤  “ለጉዳዩ ምላሽ መስጠት ያለበት ወረዳ ነው። በወረዳው በጀት ዞን ጤና መምሪያው የሚመለከተው ስላልሆነ ” ብሏል።

ተመሳሳይ ጥያቄ የቀረበላቸው የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መላኩ ገ/ህይወት በሰጡት ቃል፣ “ የበጀት እጥረት ገጥሞን ነው ” ብለዋል።

ታዲያ ችግሩን ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተነጋግራችሁ ነበር ? ለሚለው ጥያቄ፣ “ በሚቀጥው በአዲሱ በጀት ተይዞ ይከፈላቸዋል ” ነው ያሉት።

“ ለዚህም ደግሞ አስተዳደሩ ደብዳቤ ጽፏል። ‘በቀጣይ እከፍላለሁ’ የሚል ” ሲሉ አክለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ባለሙያዎቹ ' የጸጥታ ችግር ባለበት ለክትባት ውጡ ተብለናል ' የሚል ቅሬታ አላቸው፤ ለመሆኑ ይህን ስታደርጉ ለደህንነታቸው ከለላ ታደርጉላቸዋላችሁ ? ሲል ጥያቄ አቅርቧል።

ኃላፊው በምላሻቸው፣ “ የጸጥታ ችግር የሌለበት የለም። ዞሮ ዞሮ ግን በሚቻለው አግባብ የአገር ሽማግሌዎችን ይዘን እንሰራለን ” ነው ያሉት።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😢13957😡21🕊9😭8🙏5😱3🥰2👏2🤔2
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈#የጤናባለሙያዎችድምፅ " ከ15 ወራት በላይ የዱቲ ገንዘብ አልተከፈለንም በዚህ ኑሮ ውድነት በብድር በዬ ወሩ ተሰቃየን " - ጤና ባለሙያዎች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፣ በጌዴኦ ዞን በዲላ ዙሪያ ወረዳ የሚገኙ ጤና ባለሙያዎች የ15 ቀናት የዘመቻ አበልና ከአንድ አመት በላይ የትርፍ ሰዓት ክፍያ ባለመፈጸሙ ችግር ላይ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። የጤና ባለሙያዎቹ ዝርዝር ቅሬታ ምንድን ነው…
🔈#የጤናባለሙያዎችድምጽ

🔵 " ቸግሮናልጠምቶናል፣ ርቦናል፣ ሰልችቶናል፣ ከኑሮ ውድነቱ ጋር ተያይዞ የዱቲ ሳይከፈለን ለ17 ወራት ስንሰራ ከመንግስት አካል ማንም ያሰበን የለም " - ጤና ባለሞያዎች

🔴 " ምንም ምላሽ የለንም። ቢሮ መጥተው ይጠይቁን " - ወናጎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት

በጌዴኦ ዞን ወናጎ ወረዳ ያሉ ጤና ባለሙያዎች የወራት ያልተከፈለ የዱቲ ክፍያ እንዲፈጸምላቸው በመጠየቃቸው ከደመወዛቸው እንዲቆረጥባቸው መወሰኑን በመግለጽ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

" ዱቲ ስላልከፈሉን የሰራነውን ገንዘብ ስለጠየቅን ብቻ ከሦስት ወራት በላይ ደሞዛችን ከ960 ብር ጀምሮ በስኬል  እየተቆረጠ ይገኛል " ብለው፣ ደመወዛቸው እንዲቆረጥ የተወሰነው የዱቲ ሥራ በማቆማቸው መሆኑን ገልጸዋል።

የዱቲ ሥራ በመቆሙ ህዝቡም ችግር ላይ ስለሆነ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀው፣ " ካልሆነ ለሚፈጠር ችግር ተጠያቂ አንሆንም " ሲሉ አስጠይቅቀዋል።

በዞኑ ዲላ ዙሪያ ወረዳ ጪጩ ጤና ጣቢያ ያሉ ባለሙያዎቹ በበኩላቸው፣ የ17 ወራት የዱቲ ክፍያ እንዳልተፈጸመላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ያማረራቸውን ቅሬታ በተመለከተ በዝርዝር ምን አሉ ?

" በጌዴኦ ዞን በዲላ ዙሪያ ወረዳ የ17 ወራት የዱቲ ክፍያ ባለመከፈሉ የጪጩ ጤና ጣቢያ ከመስከረም 1 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ የዱቲ ሥራ በማቆም ሕዝቡ ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል።

በተደጋጋሚ ለዞኑና ለወረዳው ቅሬታ ብናቀርብም ምላሽ በመስጠት ፈንታ ባለሞያዎችን ለእስር ሲዳርግ ቆይቷል። ለሦስት ዓመት ያክል በዱቲ ክፍያ እየተከራተተ የሚገኝ የዲላ ዙሪያ ወረዳ ጤና ባለሞያ እስከ ዛሬ ተገቢ ምላሽ አላገኘም።

በጌዴኦ ዞን በወናጎ ወረዳ የሚገኙ ጤና ባለሞያዎች የዱቲ ጥያቄ አቅርበው ተገቢ ምላሽ ባለማግኘታቸው መብታቸው ለማስከበር የዱቲ ሥራ በማቆማቸው በየወሩ ከደሞዛዝ እንዲቆረጥ ተወስኗል።

ዱቲ ስላልከፈሉን የሰራነውን ገንዘብ ስለጠየቅን ብቻ ከሦስት ወር በላይ ደሞዛችን ከ960 ብር ጀምሮ በየወሩ እየተቆረጠ ይገኛል። መንግስት አፋጣኝ ምላሽ ይስጠን።

ቸግሮናል፣ ጠምቶናል፣ ርቦናል ሰልችቶናል ሞራላችን ተነክቷል መውጫ ቀዳዳ አሳጥቶናል ከኑሮ ውድነት ጋር የዱቲ ሳይከፈለን ለ17 ወራት ስንሰራ ከመንግስት አካል ማንም ያሰበን የለም " ብለዋል።


ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የጠየቀው የወናጎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ቀጥተኛ ማብራሪያ በመስጠት ፋንታ፣ " ምንም ምላሽ የለንም። ቢሮ መጥተው ይጠይቁን " ብሏል።

ሰሞኑን በተደጋጋሚ ስልክ ለማሳት ፈቃደኛ ባይሆኑም የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አንዱዓለም ማሞ ከዚህ ቀደም ጉዳዩን በተመለከተ በሰጡትን ምላሽ ችግሩን ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ገልጸውልን ነበር።

"ጉዳዩ በእርግጥ ያለ ነው። መሠረታዊ ችግሩ የበጀት ችግር ነው፤ የካሽ እጥረት ነው ያለው። ያን ለመፍታት በጋራ እየሰራን ነው" የሚል ቃል ነበር የሰጡን።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
😭580😡10578😢44🙏23🕊19👏6🥰5🤔4😱4
🔈 #የጤናባለሙያዎችድምጽ

🚨“ የሐምሌ 2016 ዓ/ም ደመወዝና፣ የ23 ወራት የዱቲ ክፍያ ስላልተከፈለን የዱቲ ሥራ ለማቆም ተገደናል” - የሀላለ ሆስፒታል ጤና ባለሞያዎች

🔴 “ የ23 ወራት ባይሆንም የ20 ወራት የዱቲ ክፍያ አልተከፈላቸውም ” - ሆስፒታሉ

🔵 “ የአንድ ወይም ሁለት ወራት እንጂ የዚህን ያክል የተወዘፈ ክፍያ የለም ” - የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ

በወላይታ ዞን ኪንዶ ዲዳዬ ወረዳ ሀላለ ሆስፒታል የሚገኙ 78 ጤና ባለሞያዎችና ሌሎች ሠራተኞች የአንድ ወር ደመወዝና የ3 ዓመት የዱቲ ክፍያ ስላልተከፈላቸው የትርፍ ሰዓቱን ሥራ ለማቆም መገደዳቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።

ጤና ባለሞያዎቹ በሰጡን ቃል ምን አሉ?

“መንግስት ከሚመድበው በጀት ክፈሉ ብለን በደብዳቤ ብንጠይቅም ‘እንከፍላለን አሁን ግን የካሽ እጥረት አለብን’ አሉን። ከዚህ ባለፈ ማስፈራሪያ፣ እስራት፣ ድብደባ ይደርስብናል።

የመጀመሪያ የስምነት ወራት የዱቲ ክፍያ በተመለከተ ተካስሰን ፍርድ ቤት እንዲከፈለን ውሳኔ ቢሰጠንም በፖለቲካ ሰዎች ጣልቃ ገብነት ውሳኔ ባለመከበሩ አልተከፈለንም።
 
ከዚያ ወዲህ የሰራነውን የ15 ወራት የትርፍ ሰዓት ክፍያንም ቢሆን ባለመክፈላቸው፣ ለመክፈልም ፍላጎት የሌላቸው በመሆኑ ከሆስፒታሉ ሠራተኞች ኃላፊ ውጪ በአጠቃላይ ተፈራሪመን የትርፍ ሰዓት ሥራ ለማቆም ተገደናል።

በደላችንን፣ ድምፃችንን ለህዝብ እና ለመንግስት አሰሙልን። ጤና ሚንስቴር በህይወት ካለ መብታችንን ያስከብርልን” ሲሉ አሳስበዋል።


ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የአንድ ወር ደመወዝና የ23 ወራት ወራት የትርፍ ሰዓት ክፍያ ያልተፈጸመበት ምክንያት ምንድን ነው? ሲል ለሆስፒታሉ ጥያቄ አቅርቧል።

የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ በረከት ሌራ ምን ምላሽ ሰጡ?

“የኛ ተቋም የሚያስተዳድረው ገንዘብ የለም ስራዎች ከተሰሩ በኋላ ለወረዳ ፋይናንስ ሪፓርት ቀርቦ ያንን መሠረት በማድረግ ነው ክፍያ የሚፈጸመው። 

የ2016 ዓ/ም የሐምሌ ደመወዝ 13% ብቻ ነው የሚቀረው 87% ተከፍሏል። የ23 ወራት ባይሆንም የ20 ወራት የትርፍ ሰዓት ክፍያ አልተከፈላቸውም። ሰፊ ነው ችግሩ። የካሽ እጥረት በሚል ብዙ ነገር እየተባለ ነበር።

የዱቲ ክፍያ በተመለከተ ፍርድ ቤት ክፍያ እንዲፈጸም የሚል ውሳኔ ሰጥቷል። የወረዳው መንግስት ከክስ ሂደቱ በኋላ መክፈል ከጀመረ በኋላ ነው የቆመው።

‘በንግግር ችግሮችን እየፈታን እንመጣለን’ በሚል ቃል ከተገባልን በኋላ ነው በመካከል ክፍያው የቆመው።  የሚያዚያ ወር በከፊል መከፈል ከተጀመረ በኋላ ነው ቆመ”
ብለዋል።

የዱቲ ሥራ በመቆሙ በማታ የሚመጡ ወላድ እናቶችን ብቻቸውን እያከሙ መሆኑን የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፣ የሚመለከታቸው አካላት ትኩረት እንዲሰጡ አሳስበዋል።

ባለሙያዎቹ የ23 ወራት የዱቲ ክፍያ እንዳልተፈጸመላቸው ቅሬታ አቅርበዋል፣ ሆስፒታሉም የ20 ወራት የዱቲ፣ የሐምሌ ደመወዝ 13 በመቶ ክፍያ አለመፈጸሙን ገልጿል፣ ይህ ለምን ሆነ? ጉዳዩን ተመልክታችሁት ነበር? ስንል ለወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ጥያቄ አቅርበናል።

የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ምን አለ?

የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ኤካ፣ “የ23 ወራት እንዳልተከፈለ መረጃው የለኝም። ተከፍሎ ነው እየተሰራ ያለው። ትክክል ነው ለማለት እቸገራለሁ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ ሰጥተዋል።

የ20 ወራት የዱቲ ክፍያ እንዳልተከፈላቸው ሆስፒታሉም እንዳረጋገጠ ስንገልጽላቸውም፣ “20 ወራት አይደርስም እኔ እንደማውቀው። ማጣራት ይጠይቃል” ነው ያሉት።

“የአንድ ወይም ሁለት ወራት እንጂ የዚህን ያክል የተወዘፈ ክፍያ የለም” ያሉት ኃላፊው፣ ጉዳዩን አጣርተው ተጨማሪ ማብራሪያ ለመስጠት ቃል ገብተዋል።

ሆስፒታሉ ያልተከፈላችሁ የ20 ወራት የዱቲ ክፍያ መሆኑን ገልጿል፣ እናንተ ደግሞ ያልተከፈላችሁ የ23 ወራት እንደሆነ ገልጻችኋል ፣ የትኛው ነው ትክክል ? ስንል የጠየቅናቸው ቅሬታ አቅራቢዎቹ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

“ ከ23 ወራት የዱቲ የ3 ወሯን ለተወሰኑ ሰዎች ነበር የከፈሉት። በትምህርት፣ በዝውዝውር፣ ሥራ በመልቀቅ ሄዱት ሳይከፊሉ ነው ‘ከፍለናል’ የሚሉት ነገር ግን እነዚህ ባለሙያዎች ደከመን ሰለቸን ሳይሉ ህብረተሰቡን እንዳገለገሉ መረሳት አልነበረበትም ” ነው ያሉት።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
😭583194😡81🙏64🕊28😢25👏21🤔17🥰6😱2