20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ጉዳይ!
በከተማ አስተዳደሩ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር በአቶ ደሳለኝ ተረፈ ፊርማ ሰሞኑን ለአሥሩም ክፍላተ ከተሞች የተላከው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው፣ ዕጣ የወጣባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች በተያዘው ወር ዕጣ ለወጣላቸው ሰዎች ይተላለፋሉ፡፡
ነገር ግን በኦሮሚያና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወሰን ላይ የተገነቡ ቤቶች ዕጣ ፈንታ ምን እንደሚሆን ተነጋግሮና መፍትሔ አስቀምጦ ስምምነት ላይ ሳይደረስ፣ ቤቶቹን ለዕድለኞቹ ለማስተላለፍ ውል መፈጸም በቀጣዩ ሒደት ላይ ችግር ሊፈጥር እንደሚችል ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የኮርፖሬሽኑ ኃላፊዎች ለሪፖርተር ጋዜጣ ገልጸዋል፡፡
More https://telegra.ph/Reporter-03-11
#ሪፖርተርጋዜጣ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በከተማ አስተዳደሩ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር በአቶ ደሳለኝ ተረፈ ፊርማ ሰሞኑን ለአሥሩም ክፍላተ ከተሞች የተላከው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው፣ ዕጣ የወጣባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች በተያዘው ወር ዕጣ ለወጣላቸው ሰዎች ይተላለፋሉ፡፡
ነገር ግን በኦሮሚያና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወሰን ላይ የተገነቡ ቤቶች ዕጣ ፈንታ ምን እንደሚሆን ተነጋግሮና መፍትሔ አስቀምጦ ስምምነት ላይ ሳይደረስ፣ ቤቶቹን ለዕድለኞቹ ለማስተላለፍ ውል መፈጸም በቀጣዩ ሒደት ላይ ችግር ሊፈጥር እንደሚችል ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የኮርፖሬሽኑ ኃላፊዎች ለሪፖርተር ጋዜጣ ገልጸዋል፡፡
More https://telegra.ph/Reporter-03-11
#ሪፖርተርጋዜጣ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
" ከባድ ተሽከርካሪዎች፣ ትራክተኖችና ማሽነሪዎችን እንዳናስገባ ተከልክለናል " - አስመጪዎች
ከባድ ተሽከርካሪዎችን ፣ ትራክተሮችን እና ማሽነሪዎችን ወደ አገር ውስጥ የሚያስገቡ አስመጪዎች ፣ መንግሥት ምንም ዓይነት መመርያ ሳያወጣ ማስገባት አትችሉም በመባላቸው በሥራቸው ላይ እንቅፋት መፈጠሩን ተናገሩ።
አስመጪዎቹ ይህን የተናገሩት ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ነው።
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ያለ ምንም በቂ ምክንያት " የመኪና ማስገቢያ ፈቃድ አልሰጣችሁም " እንዳላቸው ገልጸው ጉዳዩን ፦
- ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፣
- ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣
- ለገንዘብ ሚኒስቴርና ለጉምሩክ ኮሚሽን በአካል ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ከዚህ በፊት በነዳጅ የሚሠሩ አውቶሞቢሎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መከልከሉን መስማታቸውን ያስታወሱት አስመጪዎቹ፣ አውቶሞቢሎች እንዳይገቡ የተከለከለበት ዋነኛ ምክንያት እንደ አማራጭ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠሩ ተሸከርካሪዎችን ማስገባት እንደሚቻል በማመን ነው ብለዋል፡፡
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከባድ ተሸከርካሪዎችንና ትራክተሮችን ማስገባት አትችሉም ካለ ከሳምንት በላይ እንደሆነ ገልጸዋል።
ጉዳዩን በተመለከተ ለተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ቅሬታቸውን በአካል ሲያስረዱ፣ ተቋማቱም እንዲህ ዓይነት መመርያ አለመኖሩን እንደገለጹላቸው ተናግረዋል።
ስለጉዳዩ ዝርዝር መረጃም የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤትን ጠይቁ መባላቸውን አመልክተዋል።
ክልከላው ሥራ ላይ እንቅፋት እንደፈጠረባቸውና የተለያዩ ተሽከርካሪዎችንም ሆነ ትራክተሮችን የሚሸጡ ነጋዴዎች ዋጋ ጨምረው በመሸጥ ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
አስመጪዎቹ ፥ ከባድ ተሽከርካሪዎችና ትራክተሮችን ጨምሮ ሌሎች ተሽከርካሪዎች እንደ አውቶሞቢሎች በኤሌክትሪክ እንደማይሠሩ ተናግረው " ችግሩን መንግሥት በአፋጣኝ በመረዳት ክልከላው ሊያነሳልን ይገባል " ብለዋል፡፡
መንግሥት ከባድ ተሽከርካሪዎች ሆነ ትራክተሮች በመመርያ ቢከለክል በአገር የመጣ ጉዳይ መሆኑን በማመን ሌላ አማራጭ እንደሚፈልጉ የገለጹት አስመጪዎቹ ችግሩን የፈጠረው አንድ የመንግሥት ተቋም መሆኑ ሁኔታውን የተወሳሰበ እንዲሆን አድርጎታል በማለት አስረድተዋል።
ሪፖርተር ጋዜጣ ፥ ጉዳዩን በተመለከተ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርን በስልክ ለማነጋገር በተደጋጋሚ ጥረት ቢደረግም ሳይሳካ እንደቀረ አመልክቷል። #ሪፖርተርጋዜጣ
@tikvahethiopia
ከባድ ተሽከርካሪዎችን ፣ ትራክተሮችን እና ማሽነሪዎችን ወደ አገር ውስጥ የሚያስገቡ አስመጪዎች ፣ መንግሥት ምንም ዓይነት መመርያ ሳያወጣ ማስገባት አትችሉም በመባላቸው በሥራቸው ላይ እንቅፋት መፈጠሩን ተናገሩ።
አስመጪዎቹ ይህን የተናገሩት ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ነው።
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ያለ ምንም በቂ ምክንያት " የመኪና ማስገቢያ ፈቃድ አልሰጣችሁም " እንዳላቸው ገልጸው ጉዳዩን ፦
- ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፣
- ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣
- ለገንዘብ ሚኒስቴርና ለጉምሩክ ኮሚሽን በአካል ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ከዚህ በፊት በነዳጅ የሚሠሩ አውቶሞቢሎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መከልከሉን መስማታቸውን ያስታወሱት አስመጪዎቹ፣ አውቶሞቢሎች እንዳይገቡ የተከለከለበት ዋነኛ ምክንያት እንደ አማራጭ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠሩ ተሸከርካሪዎችን ማስገባት እንደሚቻል በማመን ነው ብለዋል፡፡
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከባድ ተሸከርካሪዎችንና ትራክተሮችን ማስገባት አትችሉም ካለ ከሳምንት በላይ እንደሆነ ገልጸዋል።
ጉዳዩን በተመለከተ ለተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ቅሬታቸውን በአካል ሲያስረዱ፣ ተቋማቱም እንዲህ ዓይነት መመርያ አለመኖሩን እንደገለጹላቸው ተናግረዋል።
ስለጉዳዩ ዝርዝር መረጃም የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤትን ጠይቁ መባላቸውን አመልክተዋል።
ክልከላው ሥራ ላይ እንቅፋት እንደፈጠረባቸውና የተለያዩ ተሽከርካሪዎችንም ሆነ ትራክተሮችን የሚሸጡ ነጋዴዎች ዋጋ ጨምረው በመሸጥ ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
አስመጪዎቹ ፥ ከባድ ተሽከርካሪዎችና ትራክተሮችን ጨምሮ ሌሎች ተሽከርካሪዎች እንደ አውቶሞቢሎች በኤሌክትሪክ እንደማይሠሩ ተናግረው " ችግሩን መንግሥት በአፋጣኝ በመረዳት ክልከላው ሊያነሳልን ይገባል " ብለዋል፡፡
መንግሥት ከባድ ተሽከርካሪዎች ሆነ ትራክተሮች በመመርያ ቢከለክል በአገር የመጣ ጉዳይ መሆኑን በማመን ሌላ አማራጭ እንደሚፈልጉ የገለጹት አስመጪዎቹ ችግሩን የፈጠረው አንድ የመንግሥት ተቋም መሆኑ ሁኔታውን የተወሳሰበ እንዲሆን አድርጎታል በማለት አስረድተዋል።
ሪፖርተር ጋዜጣ ፥ ጉዳዩን በተመለከተ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርን በስልክ ለማነጋገር በተደጋጋሚ ጥረት ቢደረግም ሳይሳካ እንደቀረ አመልክቷል። #ሪፖርተርጋዜጣ
@tikvahethiopia
😡457❤174🤔49👏37😢20🕊15😭14😱11🥰7🙏4
#ኢትዮጵያ #ባንኮች
የአገሪቱ ባንኮች ከአሠራር ጋር በተያያዙ ክፍተቶች በተለያዩ ሥልቶች ለሚፈጸሙ የማጭበርበር ድርጊቶች በከፍተኛ ደረጃ ተጋላጭ እየሆኑ መምጣታቸውን ፣ ይህ ሁኔታም በቀጣይ የአጭርና የመካከለኛ ጊዜ ውስጥ የበለጠ እንደሚጨምር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል።
ብሔራዊ ባንክ የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ጤናማነትን በመገምገም አንድ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
ሪፖርቱ ምን ይላል ?
➡️ የአገሪቱ ባንኮች በበይነ መረብ ማጭበርበርያ ሥልቶች፣ ከባንኮች የውስጥ ሠራተኞችና ከሦስተኛ ወገን በሚደርሱባቸው የምዝበራ ድርጊቶች በከፍተኛ ደረጃ እየተጋለጡ ናቸው።
➡️ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ ማለትም እስከ ሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ በሐሰተኛ ሰነዶችና በሌሎች የማጭበርበር ድርጊቶች ባንኮች 1 ቢሊዮን ብር አጥተዋል። የተመዘበሩት የገንዘብ መጠንም ከቀዳሚው ዓመት በእጥፍ ጨምሯል።
➡️ የባንክ ማጭበርበሮች በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ወደ 1 ቢሊዮን ብር ሲደርሱ፣ ከአምናው በእጥፍ አድጓል። እነዚህ ጉዳዮች የተከሰቱት በዋናነት ፦
° ሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶችንና ቼኮችን በመጠቀም ገንዘብ በማጭበርበር፣
° ያልተፈቀደ የባንክ ዋስትና በማቅረብ፣
° የተሰረቁ የኤቲኤም ካርዶችን በመጠቀም ገንዘብ በማውጣት ድርጊት
° በሐሰተኛ የስልክ ጥሪዎችና አጭር የጽሑፍ መልዕክቶችን በመጠቀም ነው። በተጠቀሱት የማጭበርበሪያ ሥልቶችም 20 ባንኮች ጉዳት ደርሶባቸዋል። በሰኔ ወር 2015 መጨረሻ ላይ 3 ባንኮች 200 ሚሊዮን ብር ተዘርፈዋል።
➡️ ባንኮች አዳዲስ ምርቶችንና አገልግሎቶችን ሲተዋወቁ በአሠራር ክፍተቶች ሳቢያ በከፍተኛ ደረጃ ለአደጋ እየተጋለጡ ናቸው።
➡️ ባንኮች ከአሠራር ጋር የተያያዙ አደጋዎችን ለመከላከልና የመጭበርበር ተጋላጭነታቸውን ለመቀነስ፣ ውጤታማ የቁጥጥር ሥልቶችንና አሠራርችን በመተግበር ላይ ሊያተኩሩ ይገባል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የ #ሪፖርተርጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
የአገሪቱ ባንኮች ከአሠራር ጋር በተያያዙ ክፍተቶች በተለያዩ ሥልቶች ለሚፈጸሙ የማጭበርበር ድርጊቶች በከፍተኛ ደረጃ ተጋላጭ እየሆኑ መምጣታቸውን ፣ ይህ ሁኔታም በቀጣይ የአጭርና የመካከለኛ ጊዜ ውስጥ የበለጠ እንደሚጨምር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል።
ብሔራዊ ባንክ የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ጤናማነትን በመገምገም አንድ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
ሪፖርቱ ምን ይላል ?
➡️ የአገሪቱ ባንኮች በበይነ መረብ ማጭበርበርያ ሥልቶች፣ ከባንኮች የውስጥ ሠራተኞችና ከሦስተኛ ወገን በሚደርሱባቸው የምዝበራ ድርጊቶች በከፍተኛ ደረጃ እየተጋለጡ ናቸው።
➡️ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ ማለትም እስከ ሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ በሐሰተኛ ሰነዶችና በሌሎች የማጭበርበር ድርጊቶች ባንኮች 1 ቢሊዮን ብር አጥተዋል። የተመዘበሩት የገንዘብ መጠንም ከቀዳሚው ዓመት በእጥፍ ጨምሯል።
➡️ የባንክ ማጭበርበሮች በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ወደ 1 ቢሊዮን ብር ሲደርሱ፣ ከአምናው በእጥፍ አድጓል። እነዚህ ጉዳዮች የተከሰቱት በዋናነት ፦
° ሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶችንና ቼኮችን በመጠቀም ገንዘብ በማጭበርበር፣
° ያልተፈቀደ የባንክ ዋስትና በማቅረብ፣
° የተሰረቁ የኤቲኤም ካርዶችን በመጠቀም ገንዘብ በማውጣት ድርጊት
° በሐሰተኛ የስልክ ጥሪዎችና አጭር የጽሑፍ መልዕክቶችን በመጠቀም ነው። በተጠቀሱት የማጭበርበሪያ ሥልቶችም 20 ባንኮች ጉዳት ደርሶባቸዋል። በሰኔ ወር 2015 መጨረሻ ላይ 3 ባንኮች 200 ሚሊዮን ብር ተዘርፈዋል።
➡️ ባንኮች አዳዲስ ምርቶችንና አገልግሎቶችን ሲተዋወቁ በአሠራር ክፍተቶች ሳቢያ በከፍተኛ ደረጃ ለአደጋ እየተጋለጡ ናቸው።
➡️ ባንኮች ከአሠራር ጋር የተያያዙ አደጋዎችን ለመከላከልና የመጭበርበር ተጋላጭነታቸውን ለመቀነስ፣ ውጤታማ የቁጥጥር ሥልቶችንና አሠራርችን በመተግበር ላይ ሊያተኩሩ ይገባል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የ #ሪፖርተርጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
😭126❤85👏42😱25🤔19😢10🕊7🥰6😡3🙏1
" የሃይማኖት ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ ምን ይዟል ?
በኢትዮጵያ አዲስ የተዘጋጀ " #የሃይማኖት_ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ አለ። ይህ ረቂቅ አዋጅ በርካታ ጉዳዮችን ይዟል።
አንዱ የአምልኮና የመቃብር ቦታን የተመለከተ ሲሆን ፥ ረቂቅ አዋጁ ለሃይማኖት ተቋማት የመሬት አቅርቦት በመሬት አጠቃቀምና የሊዝ ሕጎች መሠረት ይወሰናል ይላል።
ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቦታ በተጠየቀበት አካባቢ ለሃይማኖት ተቋሙ ለተመሳሳይ ዓላማ የተሰጠ ቦታ አለመኖሩ ወይም ደግሞ #ተጨማሪ_ቦታ መስጠት አስፈላጊ መሆኑ መረጋገጥ እንዳለበትም ይገልጻል።
በተለያዩ ቤተ እምነቶች መካከል ላይ የሚኖረው ርቀት ቢያንስ 500 ሜትር መሆን አለበትም ይደነግጋል።
ትምህርትና የሃይማኖት ተግባራትን በተመለከተ ረቂቁ ፥ መደበኛ ትምህርት በሚሰጡ የመንግሥት / የግል ተቋማት የሚሰጠው ትምህርት ሃይማኖታዊ ይዘት የሌለው መሆን አለበት ይላል።
በትምህርት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውስጥ ሃይማኖታዊ ትምህርትን ማስተማር ወይም በቡድን ማምለክ ፈጽሞ የተከለከለ ስለመሆኑ ይገልጻል።
ሌላውረቂቁ ማንነትን ለመለየት ሚያስችሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶችን ጥቅም ላይ ሊውሉ እንደማይገባ ይደነግጋል።
ከአለባበስን ጋር በተያያዘ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት " ሃይማኖታዊ ምልክቶችን እንደ ቤተ እምነቱ አስገዳጅ ሕግጋቶች #ልዩ_ሁኔታዎች እንደሚኖሩ መደንገግ ሲገባው፣ ሙሉ ለሙሉ ከትምህርትና ሥራ ገበታ የሚያስገድዱ ድንጋጌዎችን መያዙ አግባብ አይደለም " በማለት ለሰላም ሚኒስቴር አስተያየት ፣ ቅሬታ እና የመፍትሔ ሐሳብ ልኳል።
የመንግስት ስራ ኃላፊዎችን በተመለከተ መንግሥትን ወክለው በሃይማኖት በዓላት አከባበር ላይ መገኘት እንደማይችሉ ተቀምጧል።
በየት/ቤት ፣ በመኖሪያ ቤት እና በሕክምና ማዕከላት አካባቢ የሚደረግ አምልኮ በተመለከተም ፤ በአካባቢ ጥበቃ ሕግ የተቀመጠውን የድምፅ መጠን ያከበረ መሆን አለበት ይላል።
ካልተፈቀደ በስተቀር ማስተማርን ጨምሮ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎች መፈጸም እንደማይቻልም ተቀምጧል።
የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ይህ በልዩ ሁኔታ በወንጌል አማኞች ላይ ጫና የሚፈጥርና ሕገ መንግሥታዊ የሆነ መሠረት የሌለው በመሆኑን መስተካከል ይኖርበታል በማለት ለሰላም ሚኒስቴር ደብዳቤ ልኳል።
#ሪፖርተርጋዜጣ
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ አዲስ የተዘጋጀ " #የሃይማኖት_ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ አለ። ይህ ረቂቅ አዋጅ በርካታ ጉዳዮችን ይዟል።
አንዱ የአምልኮና የመቃብር ቦታን የተመለከተ ሲሆን ፥ ረቂቅ አዋጁ ለሃይማኖት ተቋማት የመሬት አቅርቦት በመሬት አጠቃቀምና የሊዝ ሕጎች መሠረት ይወሰናል ይላል።
ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቦታ በተጠየቀበት አካባቢ ለሃይማኖት ተቋሙ ለተመሳሳይ ዓላማ የተሰጠ ቦታ አለመኖሩ ወይም ደግሞ #ተጨማሪ_ቦታ መስጠት አስፈላጊ መሆኑ መረጋገጥ እንዳለበትም ይገልጻል።
በተለያዩ ቤተ እምነቶች መካከል ላይ የሚኖረው ርቀት ቢያንስ 500 ሜትር መሆን አለበትም ይደነግጋል።
ትምህርትና የሃይማኖት ተግባራትን በተመለከተ ረቂቁ ፥ መደበኛ ትምህርት በሚሰጡ የመንግሥት / የግል ተቋማት የሚሰጠው ትምህርት ሃይማኖታዊ ይዘት የሌለው መሆን አለበት ይላል።
በትምህርት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውስጥ ሃይማኖታዊ ትምህርትን ማስተማር ወይም በቡድን ማምለክ ፈጽሞ የተከለከለ ስለመሆኑ ይገልጻል።
ሌላውረቂቁ ማንነትን ለመለየት ሚያስችሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶችን ጥቅም ላይ ሊውሉ እንደማይገባ ይደነግጋል።
ከአለባበስን ጋር በተያያዘ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት " ሃይማኖታዊ ምልክቶችን እንደ ቤተ እምነቱ አስገዳጅ ሕግጋቶች #ልዩ_ሁኔታዎች እንደሚኖሩ መደንገግ ሲገባው፣ ሙሉ ለሙሉ ከትምህርትና ሥራ ገበታ የሚያስገድዱ ድንጋጌዎችን መያዙ አግባብ አይደለም " በማለት ለሰላም ሚኒስቴር አስተያየት ፣ ቅሬታ እና የመፍትሔ ሐሳብ ልኳል።
የመንግስት ስራ ኃላፊዎችን በተመለከተ መንግሥትን ወክለው በሃይማኖት በዓላት አከባበር ላይ መገኘት እንደማይችሉ ተቀምጧል።
በየት/ቤት ፣ በመኖሪያ ቤት እና በሕክምና ማዕከላት አካባቢ የሚደረግ አምልኮ በተመለከተም ፤ በአካባቢ ጥበቃ ሕግ የተቀመጠውን የድምፅ መጠን ያከበረ መሆን አለበት ይላል።
ካልተፈቀደ በስተቀር ማስተማርን ጨምሮ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎች መፈጸም እንደማይቻልም ተቀምጧል።
የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ይህ በልዩ ሁኔታ በወንጌል አማኞች ላይ ጫና የሚፈጥርና ሕገ መንግሥታዊ የሆነ መሠረት የሌለው በመሆኑን መስተካከል ይኖርበታል በማለት ለሰላም ሚኒስቴር ደብዳቤ ልኳል።
#ሪፖርተርጋዜጣ
@tikvahethiopia
😡1.03K❤389👏155🤔52😭40🕊36🙏22😱18😢12🥰8
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሃይማኖት ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ ምን ይዟል ? በኢትዮጵያ አዲስ የተዘጋጀ " #የሃይማኖት_ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ አለ። ይህ ረቂቅ አዋጅ በርካታ ጉዳዮችን ይዟል። አንዱ የአምልኮና የመቃብር ቦታን የተመለከተ ሲሆን ፥ ረቂቅ አዋጁ ለሃይማኖት ተቋማት የመሬት አቅርቦት በመሬት አጠቃቀምና የሊዝ ሕጎች መሠረት ይወሰናል ይላል። ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቦታ በተጠየቀበት አካባቢ ለሃይማኖት ተቋሙ ለተመሳሳይ…
#ኢትዮጵያ
በሀገሪቱ ውስጥ ያለ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርቱን ለሰላም ሚኒስቴር ማቅረብ እንደሚኖርበት ፤ ከውጭ አገር የሚመጣ የገንዘብ ዕርዳታ በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።
" የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ " የተሰኘው ረቂቅ አዋጁ የሃይማኖት ተቋማቱ ተቀባይነት ያለው የሒሳብ አያያዝና የኦዲት ሥርዓት መዘርጋት እንደሚኖርባቸው፣ የኦዲት ሪፖርታቸውን ለሰላም ሚኒስቴር ማቀረብ እንዳለባቸው ይደነግጋል፡፡
ረቂቅ አዋጁ ምን ይዟል ?
- የሃይማኖት ተቋማት የሚጠቀሙት የሒሳብ አያያዝ ሥርዓት የገቢ፣ የወጪና አጠቃላይ የንብረት ዝርዝር የያዘ መሆን አለበት።
- የገቢ አሰባሰብና የወጪ አስተዳደር በሕጋዊ መንገድ ማከናወን አለባቸው።
- የሃይማኖት ተቋም በራሱ #የገቢ_ማስገኛ ሥራዎችን በሚያከናውንበት ጊዜ ለዚሁ ሥራ ሲባል የተለየ የባንክ ሒሳብ መክፈትና የተለየ መዝገብ መያዝ አለበት።
- ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ከውጭ የሚላክለትን የገንዘብ ዕርዳታ፣ ስጦታ ወይም ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ አለበት። ሲያሳውቅም ፦
° የለጋሹን ድርጅት ወይም ግለሰብ ስም እና አድራሻ፣
° የተለገሰው የገንዘብ፣ ስጦታ ዓይነት እና መጠን ፣
° ስጦታው / ድጋፉ የተሰጠበት ልዩ ዓላማ መካተት አለበት።
- ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም የበጀት ዓመቱ ባለቀ በ3 ወር ውስጥ የፋይናንስ እንቅስቃሴውን በገለልተኛ ኦዲተር ማስመርመር አለበት። የኦዲተሩን አቋም እና የውሳኔ ሐሳብም መያዝ ይኖርበታል።
- የሰላም ሚኒስቴር የደረሰውን የኦዲት ሪፖርት አመቺ በሆነ መንገድ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ ይኖርበታል።
#ሪፖርተርጋዜጣ
@tikvahethiopia
በሀገሪቱ ውስጥ ያለ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርቱን ለሰላም ሚኒስቴር ማቅረብ እንደሚኖርበት ፤ ከውጭ አገር የሚመጣ የገንዘብ ዕርዳታ በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።
" የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ " የተሰኘው ረቂቅ አዋጁ የሃይማኖት ተቋማቱ ተቀባይነት ያለው የሒሳብ አያያዝና የኦዲት ሥርዓት መዘርጋት እንደሚኖርባቸው፣ የኦዲት ሪፖርታቸውን ለሰላም ሚኒስቴር ማቀረብ እንዳለባቸው ይደነግጋል፡፡
ረቂቅ አዋጁ ምን ይዟል ?
- የሃይማኖት ተቋማት የሚጠቀሙት የሒሳብ አያያዝ ሥርዓት የገቢ፣ የወጪና አጠቃላይ የንብረት ዝርዝር የያዘ መሆን አለበት።
- የገቢ አሰባሰብና የወጪ አስተዳደር በሕጋዊ መንገድ ማከናወን አለባቸው።
- የሃይማኖት ተቋም በራሱ #የገቢ_ማስገኛ ሥራዎችን በሚያከናውንበት ጊዜ ለዚሁ ሥራ ሲባል የተለየ የባንክ ሒሳብ መክፈትና የተለየ መዝገብ መያዝ አለበት።
- ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ከውጭ የሚላክለትን የገንዘብ ዕርዳታ፣ ስጦታ ወይም ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ አለበት። ሲያሳውቅም ፦
° የለጋሹን ድርጅት ወይም ግለሰብ ስም እና አድራሻ፣
° የተለገሰው የገንዘብ፣ ስጦታ ዓይነት እና መጠን ፣
° ስጦታው / ድጋፉ የተሰጠበት ልዩ ዓላማ መካተት አለበት።
- ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም የበጀት ዓመቱ ባለቀ በ3 ወር ውስጥ የፋይናንስ እንቅስቃሴውን በገለልተኛ ኦዲተር ማስመርመር አለበት። የኦዲተሩን አቋም እና የውሳኔ ሐሳብም መያዝ ይኖርበታል።
- የሰላም ሚኒስቴር የደረሰውን የኦዲት ሪፖርት አመቺ በሆነ መንገድ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ ይኖርበታል።
#ሪፖርተርጋዜጣ
@tikvahethiopia
😡1.88K👏1.18K❤327🤔145😭58🙏42🕊40🥰36😢34😱24