TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Sidama

" #አፊኒ " የተሰኘውና በሲዳማ ባህላዊ የእርቅ ስነስርአትና የግጭት አፈታት ላይ ትኩረቱን አድርጎ የተሰራው ፊልም ትላንት በሀዋሳ ከተማ ተመርቋል።

ፊልሙ የሲዳማ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ደስታ ሌዳሞን ጨምሮ በርካታ ባለስልጣናት የሀገር ሽማግሌዎች ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች በተገኙበት ነው የተመረቀው።

የፊልሙ ባለቤትና ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ኃላፊነቱን ወስዶ ሲሰራዉ የነበረው የሲዳማ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ነው ተብሏል።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ጃጎ አገኘሁ ፤ " አፊኒ ፊልም የሲዳማን ባህል ወግና ትውፊት የሚያንጸባርቅ ተንቀሳቃሽ ሙዚየም ነው " ብለውታል።

" አፊኒ " ፊልም የሲዳማን ባህል የማስተዋወቅ ዓላማ ያለዉና በኢንተርናሽናል ስታንዳርድ የተሰራ መሆኑ ከዚህ ቀደም መገለፁ ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቀናት በፊት " አፊኒ " ፊልም ከ7.5 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ መሰራቱን መግለጹን ተከትሎ ከፊልሙ አሰሪ ኮሚቴ " ትክክል አይደለም !! " የሚል ቅሬታ ቀርቦ ነበር።

ይሁንና ትክክለኛ የፊልሙ ወጭ ስንት እንደሆነና ከክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በተጨማሪ ፊልሙን በገንዘብ ስላገዙ አካላት መረጃ ለማግኘት በተደጋጋሚ ያደረግነው ሙከራ ሊሳካ አልቻለም።

ሌላው ከምርቃት ስርዓቱ ጋር በተያያዘ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ወጥቷል እየተባለ ስለሚነገረው በሚሊዮን የሚቆጠር የገንዘብ መጠን ምላሽ ለማግኘት ጥረት ብናደርግም ለጊዜው አልተሳካም።

በቀጣይ ከሚመለከተው አካል መረጃ የምናገኝ ከሆነ እናቀርባለን።

መረጃው በሀዋሳ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia
295😡49👏19🕊17🙏11😭10🥰6😱6😢4