TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Amhara

የኤፍራታ ግድም ወረዳ አስተዳዳሪ ተገደሉ።

በወረዳው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች የወረዳውን አስተዳዳሪ አቶ አልብስ አደፍራሽን ትለንትና በምሽት በመግባት እንደገደሏቸው ተሰምቷል።

ወረዳው ባወጣው የሀዘን መግለጫው ፥ " አቶ አልብስ ለዓመታት በቀውስ ነጋዴዎች ለችግር ተጋልጦ የሴራ ፖለቲካ መሸቀጫ የተደረገውን የጀውሃና አካባቢው ማህበረሰብ ቀርቦ በማወያየት መተማመን ፈጥሮና አደራጅቶ ወደ ቀደመ አካባቢውና ኑሮው እንዲመለስ በማድረግ ላይ ነበሩ " ሲል ገልጿል።

አክሎ " የወደሙትን የጤናና ሌሎች ተቋማትንም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት በመስራት መልሶ እያቋቋመ የነበረ ደከመኝን የማያውቅ፣ ለእውነት የቆመ ንፁህ የሕዝብ ልጅና አገልጋይ፤ እውነተኛ የአማራ ጀግና ነበር " ብሏል።

አቶ አልብስ አደፍራሽ ትላንትና ምሽት ቤታቸው በገቡ ታጣቂዎች ተገድለዋል።

@tikvahethiopia
👏559😭47080🕊56😢38🙏23😡20🥰18😱15🤔5