TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሰበር_ዜና

የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) የሀዋሳ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ የሲዳማ እና የሀድያ ዞን ከፍተኛ ባለስልጣናትን ከኃላፊነት #ማገዱን አስታወቀ።

#ደኢህዴን ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር እና የሲዳማ ዞን አመራሮች የታገዱት ሰሞኑን በሀዋሳ ከተማና እና በሲዳማ ዞን የገጠር አካባቢዎች በተከሰተው ግጭት የራሳቸው ሚና ነበራቸው በሚል ነው። የሃድያ ዞን አመራሮች በዞኑ የህዝቡን ሰላም እና ደህንነት አደጋ ላይ ከሚጥሉ እንቅስቃሴዎች ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ የማገድ እርምጃ መወሰዱን አመልክቷል።

ድርጅቱ ከስልጣን አግጃቸዋለሁ ያላቸውን የሲዳማና የሀድያ ዞን ባለስልጣናት ''የፊት አመራሮች '' ከማለት ውጪ ቁጥራቸውንም ሆነ ማንነታቸውን አልጠቀሰም። በደቡብ ክልል በከፋ እና በወላይታ ዞኖች የተስተዋሉት ተመሳሳይ ድርጊቶችም የህግ ተጠያቂነትን የሚያስከትሉ ናቸው ሲል ድርጅቱ በመግለጫው ጠቁሟል።

ምንጭ: የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia