TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ⬆️

"ዛሬ ከሰአት 202 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍነውን እና 4 ተሽከርካሪዎች በትይዩ ለማስተናገድ የሚያስችል 32 ሜትር ስፋት ያለውን የሞጆ - ሃዋሳ የፍጥነት መንገድ የግንባታ ሂደት ያለበትን ደረጃ መመልከት ችያለው መንገዱ ካለዉ አጠቃላይ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጠቀሜታ አኳያ በተያዘለት የግዜ ገደብ እና የጥራት ደረጃ #መጠናቀቅ እንደሚገባዉ የስራ #መመሪያ ሰጥተናል። በጉብኝቱ ከመንገዱ ባሻገር ኢትዮጲያውያን ሙያተኞች ከውጭ ሙያተኞች የሚቀስሙት ልምድ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር በላቀ ደረጃ አጠናክረው መሄድ እንደሚገባቸው ነው ያሳሰብኩት።

በተመሳሳይ ማምሻውን የኢትዮጲያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ የአዲስ-አዳማ የፍጥነት መንገድ ላይ የሚገኙት ቱሉዲምቱ እና የሞጆ የክፍያ ጣቢያ ላይ ያለውን የቁጥጥር እና የክፍያ ሲስተም ተመልክተናል። ዘመናዊ በሆነ ቴክኖሎጂ እና ብቃት ያለው የሰው ሃብት በመጠቀም ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎት መስጠት ተልኮውን ላደረገው ኢንተርፕራይዝ በቀጣይም ከዚህም በተሻለ ሁኔታ አገልግሎት እንዲሰጥ ሚንስትር መስሪያ ቤታችን ድጋፍና ክትትል ያደርጋል።"

@tsegabwolde @tikahethiopia