TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የኦነግ ሰራዊት አባላት‼️

ከ1 ሺህ በላይ የሚሆኑ የኦነግ ሰራዊት አባላት ወደ ተዘጋጀላቸው #ካምፕ ገብተዋል።

የሰራዊት አባላቱ ጦላይን ጨምሮ በኦሮሚያ ክልል በተዘጋጁ የተለያዩ ካምፖች በመግባት #ስልጠና እየወሰዱ ነው።

ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የሰራዊት አባላቱ፥ የተደረገላቸው የሰላም ጥሪና እየታየ ያለው የፖለቲካ ለውጥ ለሃገርና ህዝብ ጥቅም በሰላማዊ መንገድ እንዲታገሉ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።
በሃይል ትግል ማድረጉም ለህዝቡ ስለማይጠቅም ሰላማዊ የትግል መንገድ መምረጣቸውንም ነው የተናገሩት።

ከዚህ በተቃራኒው የትጥቅ ትግልን አማራጭ በማድረግ በሃይል የሚንቀሳቀስ ቡድን አካሄድ ተቀባይነት እንደሌለውም ገልጸዋል፤ ለውጡን ለማስቀጠል መናበብና መመካከር አስፈላጊ መሆኑን በመጥቀስ።

ከዚህ ባለፈም የበርካቶች ህይወት ያለፈበትን ትግል ማደናቀፍ እንደማይገባ የጠቀሱት አባላቱ፥ የአንድ ሃገር እድገትን ለማረጋገጥ በሰላማዊ መንገድ መታገል አስፈላጊ መሆኑንም አንስተዋል።

በትጥቅ ትግል ላይ ለሚገኙ ሌሎች ጓዶቻቸውም ትጥቃቸውን ፈተው ሰላማዊ ትግሉን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የጦላይ ስልጠና ማዕከል አስተባባሪ ኮሚሽነር ፀሃይ ነጋሽ በበኩላቸው አባላቱ በህገ መንግስቱ፣ በፌደራሊዝሙና በሃገራዊ ለውጡ ዙሪያ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን ገልጸዋል።

ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1