መከላከያ ሰራዊት🔝
የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግሥት ለፌዴራል መንግሥቱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት የመከላከያ ሠራዊቱ የአካባቢውን ሠላም ለማስከበር #ከዛሬ ጀምሮ እንደሚሠማራም ተገልጧል፡፡
በምዕራብ እና በማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች የተከሰተውን ግጭት ለማርገብ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን በተመለከተ የ33ኛ ዓባይ ክፍለ ጦር እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ጎንደር ላይ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ መግለጫውን የሰጡት የ33ኛ ዓባይ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል #አለምነው_አየነ እና የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር #ዘላለም_ልጃለም ናቸው፡፡
የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግሥት ለፌዴራል መንግሥቱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት የመከላከያ ሠራዊቱ የአካባቢውን ሠላም ለማስከበር ከዛሬ የካቲት10/2011 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሠማራም በመግለጫው ይፋ ተደርጓል፡፡
በፀጥታ ኃይሉ አስተማማኝ ሰላም እስኪገኝ ድረስ የተከለከለከሉ ተግባራትም በመግለጫው ይፋ ተደርገዋል፡፡
በዚህም መሠረት ከጎንደር-መተማ መስመር ከመንገድ 5 ኪ.ሜ ክልል በቡድንም ይሁን በግል ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ አይቻልም፤ በሁመራ መስመርም በተመሳሳይ #ክልከላ ተደርጓል፡፡ በጎንደር ከተማ ከፀጥታ አካላት ውጭ ማንኛውም ሰው መሣሪያ ታጥቆ መንቀሳቀስ እንደማይችልም ታውቋል፡፡
ማንኛውም በፀጥታ መደፍረስ ተሳትፎ ያደረገ ኃይል እርምጃ እንደሚወሰድበትና ‹‹ሰላም ለማስከበር›› በሚል ሰበብ ማንኛውም ግለሰብ ከኮሚሽኑ ፈቃድ ውጭ መሣሪያ ይዞ #እንዳይንቀሳቀስ እገዳ ተላልፏል፡፡
በመግለጫው የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጎንደር ወጣቶችና አክቲቪስቶች በጎንደር እና በአካባቢው ሰላም እንዲሰፍን ከፀጥታ ኃይሉ ጋር እንዲሠሩ ጥሪ ቀርቦላቸዋል፡፡
ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግሥት ለፌዴራል መንግሥቱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት የመከላከያ ሠራዊቱ የአካባቢውን ሠላም ለማስከበር #ከዛሬ ጀምሮ እንደሚሠማራም ተገልጧል፡፡
በምዕራብ እና በማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች የተከሰተውን ግጭት ለማርገብ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን በተመለከተ የ33ኛ ዓባይ ክፍለ ጦር እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ጎንደር ላይ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ መግለጫውን የሰጡት የ33ኛ ዓባይ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል #አለምነው_አየነ እና የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር #ዘላለም_ልጃለም ናቸው፡፡
የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግሥት ለፌዴራል መንግሥቱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት የመከላከያ ሠራዊቱ የአካባቢውን ሠላም ለማስከበር ከዛሬ የካቲት10/2011 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሠማራም በመግለጫው ይፋ ተደርጓል፡፡
በፀጥታ ኃይሉ አስተማማኝ ሰላም እስኪገኝ ድረስ የተከለከለከሉ ተግባራትም በመግለጫው ይፋ ተደርገዋል፡፡
በዚህም መሠረት ከጎንደር-መተማ መስመር ከመንገድ 5 ኪ.ሜ ክልል በቡድንም ይሁን በግል ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ አይቻልም፤ በሁመራ መስመርም በተመሳሳይ #ክልከላ ተደርጓል፡፡ በጎንደር ከተማ ከፀጥታ አካላት ውጭ ማንኛውም ሰው መሣሪያ ታጥቆ መንቀሳቀስ እንደማይችልም ታውቋል፡፡
ማንኛውም በፀጥታ መደፍረስ ተሳትፎ ያደረገ ኃይል እርምጃ እንደሚወሰድበትና ‹‹ሰላም ለማስከበር›› በሚል ሰበብ ማንኛውም ግለሰብ ከኮሚሽኑ ፈቃድ ውጭ መሣሪያ ይዞ #እንዳይንቀሳቀስ እገዳ ተላልፏል፡፡
በመግለጫው የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጎንደር ወጣቶችና አክቲቪስቶች በጎንደር እና በአካባቢው ሰላም እንዲሰፍን ከፀጥታ ኃይሉ ጋር እንዲሠሩ ጥሪ ቀርቦላቸዋል፡፡
ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
🙏1
ከሊቀመንበርነታቸው ወረዱ‼️
የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አልበሺር ከገዥው #ናሽናል_ኮንግረስ_ፓርቲ ሊቀመንበርነታቸው መውረዳቸው ተገልጿል። በምትካቸውም የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አህመድ ሞሃመድ ሃሩን ፓርቲው አጠቃላይ ጉባኤ እስከሚያካሂድ የአልበሺርን ቦታ መረከባቸው ነው የተነገረው። ሀሩን በዚህ ሳምንት የሱዳን ገዥ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው መመረጣቸው ይታወሳል።
በሱዳን ከታህሳስ ወር 2018 ጀምሮ እስከዛሬ ያልተቋረጠው የዜጎች ተቃውሞ አልበሺር ከፓርቲ ሃላፊነታቸው እንዲለቁ ማስገደዱን ተንታኞች እየገለጹ ቢሆንም ፕሬዚዳንቱ ከዚህ ቀደምበተቃውሞ ፍራቻ ሳይሆን በምርጫ ብቻ ስልጣናቸውን እንደሚለቁ መናገራቸው ይታወሳል። ሱዳን በ2020 ምርጭ እንደሚታካሂድ ይጠበቃል።
አልበሺር ባሳለፍነው ሳምንት ለአንድ ዓመት የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያወጡ ሲሆን እሰተዳደራዊ መዋቅሩን በመበተን አዳዲስ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ሹመት ሰጥተዋል። በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ #ክልከላ ቢደረግም #ተቃውሞው እስከዛሬ ድረስ መቀጠሉን መረጃዎች ያሳያሉ።
ምንጭ፦ሲጂቲኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አልበሺር ከገዥው #ናሽናል_ኮንግረስ_ፓርቲ ሊቀመንበርነታቸው መውረዳቸው ተገልጿል። በምትካቸውም የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አህመድ ሞሃመድ ሃሩን ፓርቲው አጠቃላይ ጉባኤ እስከሚያካሂድ የአልበሺርን ቦታ መረከባቸው ነው የተነገረው። ሀሩን በዚህ ሳምንት የሱዳን ገዥ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው መመረጣቸው ይታወሳል።
በሱዳን ከታህሳስ ወር 2018 ጀምሮ እስከዛሬ ያልተቋረጠው የዜጎች ተቃውሞ አልበሺር ከፓርቲ ሃላፊነታቸው እንዲለቁ ማስገደዱን ተንታኞች እየገለጹ ቢሆንም ፕሬዚዳንቱ ከዚህ ቀደምበተቃውሞ ፍራቻ ሳይሆን በምርጫ ብቻ ስልጣናቸውን እንደሚለቁ መናገራቸው ይታወሳል። ሱዳን በ2020 ምርጭ እንደሚታካሂድ ይጠበቃል።
አልበሺር ባሳለፍነው ሳምንት ለአንድ ዓመት የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያወጡ ሲሆን እሰተዳደራዊ መዋቅሩን በመበተን አዳዲስ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ሹመት ሰጥተዋል። በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ #ክልከላ ቢደረግም #ተቃውሞው እስከዛሬ ድረስ መቀጠሉን መረጃዎች ያሳያሉ።
ምንጭ፦ሲጂቲኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የግብረ ሰዶማውያኑ ጉብኝት...
ከኢትዮጵያ ባህልና ልማድ #የተቃረነ ነው ተብሎ በህግ #ክልከላ የተጣለበት፣ የተመሳሳይ ፆታ አፍቃሪያን ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት የሚያደርጉት ዝግጅት፣ የሚያወጡት መግለጫ የተቃውሞ መልስ እየተሰጠው ነው፡፡ ይህንንም የማይገባ ግብር የሚያደርገው ቡድን ወደ #ኢትዮጵያ መግባት እንደሌለበት እና ወደ ቅጣትም እንደሚገባ በዚሁ ጉዳይ ላይ ወደ ኋላ እንደማይል የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ እወቁልኝ ብሏል።
Via #ShegerFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከኢትዮጵያ ባህልና ልማድ #የተቃረነ ነው ተብሎ በህግ #ክልከላ የተጣለበት፣ የተመሳሳይ ፆታ አፍቃሪያን ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት የሚያደርጉት ዝግጅት፣ የሚያወጡት መግለጫ የተቃውሞ መልስ እየተሰጠው ነው፡፡ ይህንንም የማይገባ ግብር የሚያደርገው ቡድን ወደ #ኢትዮጵያ መግባት እንደሌለበት እና ወደ ቅጣትም እንደሚገባ በዚሁ ጉዳይ ላይ ወደ ኋላ እንደማይል የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ እወቁልኝ ብሏል።
Via #ShegerFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia