TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በ2 ቀን ውስጥ በጎሳ ግጭት 400 ሰዎች ሞቱ‼️

በዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ በታህሳስ ወር ላይ ተከስቶ በነበረ #የጎሳ_ግጭት የ400 ሰዎች ህይዎት ማለፉ ተገለፀ።

በሀገሪቱ ሰሜን ምስራቅ አካባቢ ባለፈው ታህሳስ ወር ላይ ተከስቶ በነበረው የጎሳ ግጭት በሁለት ቀናት ውስጥ ብቻ 400 የሚሆኑ ዜጎች ህይዎት አልፏል።

ግጭቱ የተፈጠረውም በዩምቢ ከተማና አካባቢው በሚገኙት #ባቴንድ እና #ባኑን በተሰኙ ጎሳዎች መካከል መሆኑ ነው የተገለፀው።

የግጭቱ ምክንያትም በአካባቢው ለመካሄድ ዝግጅት ላይ በነበረው ሀገራዊ ምርጫ ላይ በተፈጠረ አለመግባባት ነው ተብሏል።

የባቴንድ ጎሳዎች የገዢውን መንግስት መመረጥ #የሚደግፉ ሲሆን ፥ባኑኖች ደግሞ በአካባቢው እነሱን ወክሎ የሚወዳደረውን #የተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎች ነበሩ።

በተፈጠረው ግጭትም ከሞቱት ሰዎች በተጨማሪም በርካቶች ከባድና ቀላል የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል፡፡

እንዲሁም በግጭቱ ብዛት ያላቸው ሰዎች ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ መሆኑ በዘገባው ተመላክቷል።

ግጭቱን ተከትሎ የሀገሪቱ መንግስት ታህሳስ 30 ላይ በአካባቢው ሊካሄድ የነበረውን ምርጫ መሰረዙ ይታወሳል።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
1
“እኛ #ኢትዮጵያዊያን እርስ በርስ የሚያስተሳስሩ በርካታ ማንነቶች ያሉን፣ ለዘመናት የቆየ የሐይማኖት መከባበር ልምድ፣ የአኩሪ ባህል ባለቤቶች፣ አንገትን ከፍ አድርገን እንድንራመድ የሚያደርጉን የታሪክ ባለቤቶች መገኛ ነን፡፡ ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ እየተነሱ ያሉ #የዘርና #የጎሳ ግጭቶች ለእንደኛ አይነት ህዝቦች #ማይመጥኑ አስነዋሪ ተግባራት በመሆናቸው ሁላችንም በቃ ልንላቸው ያስፈልጋል” የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ዶ/ር #ሂሩት_ካሳው

@tsegabwolde @tikvahethiopia