TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አምነስቲ_ኢንተርናሽናል

የፕሪቶሪያ የ ' ሰላም ስምምነት ' ከተፈረመ በኋላ የ " ኤርትራ ወታደሮች " በትግራይ ወሲባዊ ባርነት ፣ ግድያዎችን እና ሌሎች ከባድ ጥሰቶች መፈጸማቸውን አምነስቲ ኢንተርናሽናል አዲስ ባወጣው ሪፖርት ይፋ አድርጓል።

ሪፖርቱ ምን ይላል ?

- ከሰላም ስምምነቱ በኃላ የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ ምድር ወሲባዊ ባርነት፣ ግድያ፣ ከባድ ጥሰቶችን ፈፅመዋል።

- የኤርትራ መከላከያ ሰራዊት መድፈር፣ ሴቶችን ለወራት ለወሲባዊ ባርነት መዳረግ፣ የዘፈቀደ ግድያ፣ ዘረፋዎችን እየፈጸሙም እንደሆነ ተገልጿል።

- የተፈፀሙት ጥሰቶች የጦር ወንጀሎች እንዲሁም በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል ሊሆን ይችላል።

- ሸዊቶ በተሰኘች ወረዳ ቢያንስ 20 ነዋሪዎች በዋነኝነት ወንዶች ከጥቅምት15 - ጥቅምት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ባለው ወቅት በኤርትራ መከላከያ ኃይል መገደላቸውን ገልጿል።

- የፕሪቶሪያው  ስምምነት ከተፈረመ በኃላ የኤርትራ መከላከያ ኃይል ወታደሮች 24 ሰላማዊ ነዋሪዎችን በኮኮብ ጽባህ ወረዳ መግደላቸውን ሪፖርት ተደርጓል።

- አምነስቲ በኮከብ ጽባህ የተደፈሩ እና ለወሲባዊ ባርነት ተዳርገው የነበሩ 11 ሴቶችን  አነጋግሯል። ከ40 በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎችም እንደተደፈሩ እና ለወሲባዊ ባርነት እንደተዳረጉ ለአካባቢው ለሚገኝ የሲቪል ማህበረሰብ መናገራቸውም ሪፖርቱ ላይ ሰፍሯል።

ሙሉ ሪፖርቱ በዚህ ይገኛል ፦ https://www.amnesty.org/en/latest/news/2023/09/eritrean-soldiers-committed-war-crimes-and-possible-crimes-against-humanity-in-the-tigray-region-after-signing-of-agreement-to-end-hostilities/

@tikvahethiopia
👍443😢372👎13364🕊15🙏10😱3🥰2