TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከዲላ...

"ከዲላ ነው እምፅፍልህ-የቤንዝል ችግር ከእለት ወደ እለት #እየተባባሰ መምጣቱ የአብዛኛውን ነዋሪ የኑሮ ሁኔታ #እያናጋ ነው። በተለያዪ መገናኛ ብዙሀን የምንሰማው የክምችት ችግር እንደሌለ እና ሰው ሰራሽ መሆኑ እየተገለፀ ነው። በከተማችን ቤንዝል በገባ በሰአታት ውስጥ መኪና ላይ በተጫነ በርሜል እየተገለበጠ ይጓጓዛል ወደየት እንደሚጫንም አናውቅም የመንግስት ባለስልጣናት ጉዳዪን እያዪ ባላየ ማለፍን መርጠዋል። ቸርቻሪዎች እንደ ህጋዊ ነጋዴ በየመንገዱ በፕላስቲክ ኮዳ እየሞሉ በሊትር 60 ብር እየሸጡ ነው። የሚመለከተው አካል ካለ አፋጣኝ ምላሽ እንሻለን፡፡"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
Alert‼️

የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የእሳት አደጋ አጋጥሞታል፤ ቃጠሎውም #እየተባባሰ እንደሆነ ነው የተሰማው። ከደባርቅ ከተማ ወጣቶች ተሰብስበው ወደ ፓርኩ ሄደው #ለማጥፋት ቢፈልጉም ተሽከርካሪ ማግኘት አለመቻላቸውን ለአብመድ ተናግረዋል።

እሳቱ #ሳንቃ_በር አካባቢም መከሰቱን ወጣቶቹ ተናግረዋል የደባርቅ ወረዳ ባሕልና ቱሪዝም ጽሕፈት ቤት የወጣቶችን #ጥቆማ ተጋርቷል።

ከፓርከ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መካከል አቶ #ታደሰ_ይግዛው እሳቱ እሜት ጎጎ እና ሳንቃበር አካባቢ #መባባሱን ገልጸው ወደ ቦታው ለማቅናት ተሽከርካሪ እያፈላለጉ መሆኑን ገልጸዋል። ጊዜው #በመምሸቱ ስልክ የሚያነሳላቸው ሰው ማጣታቸውንም ተናግረዋል። ከዞንና ክልል የሥራ ኃላፊዎች መረጃ ማግኘት አልቻልኩም ሲል አብመድ ዘግቧል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia