TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የሶማሊያ ጦር 41 የአልሸባብ ታጣቂዎችን ገደለ።

ጦሩ በዛሬው ዕለት በመዱግ ክልል ውስጥ የወሲል ከተማን ሊያጠቁ ነበር / ጥቃት ሊከፍቱ ነበር ያላቸውን 41 የአልሸባብ ታጣቂዎችን ገድሏል።

በነበረው ግጭት 3 ከሶማሊያ ጦር እንዲሁም 5 ከጋልሙዱግ የዳርዊሽ ኃይሎች መገደላቸው ተሰምቷል።

በሌላ መረጃ የሶማሊያዋ #ፑንትላንድ ዛሬ 21 የአልሸባብ አባላትን ዛሬ ረሽናለች።

አባላቱ ጋልካዮ፣ ቃርዶ እና ጋሮዊ በተባሉ የተለያዩ ሶስት አካባቢዎች ላይ መረሸናቸውን የፑንትላንድ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኛ ጄነራል መሃሙድ አብዲ መሃመድ አረጋግጠዋል፡፡

በፍርድ ቤቱ ውሳኔ የተገደሉት የአል ሸባብ አባላቱ ባለፉት 13 ዓመታት ውስጥ በተለያዩ የፑንትላንድ አካባቢዎች በተፈጸሙ ግድያዎች ጥፋተኛ ነበሩ ተብሏል፡፡

ከጎሳ መሪዎችን፣ ጋዜጠኞች፣ ከመንግስት ባለስልጣናት ግድያ ጀርባ እንደነበሩ ፍርድ ቤት ገልጿል።

መረጃው ከጎብጆግ ፣ አልዓይን ኒውስ ፣ SNTV (የሶማሊያ ብሄራዊ ቴሌቪዥን) የተውጣጣ ነው።

@tikvahethiopia