TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ህዝበ ወሳኔ እንዲካሄድ🔝

የሲዳማ ብሔር ክልል ሆኖ #እንዲደራጅ በቀረበው ጥያቄ መነሻ የክልሉ ምክርቤት ህገ መንግስቱ በሚፈቅደው መሰረት ህዝበ ውሳኔ እንዲያገኝ ለኢፌድሪ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት መፃፉን የተረጋገጠ ሲሆን ደብዳቤው በነገው እለት ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት ያደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከዚህ ቀጥሎ ህገመንግስቱ በሚፈቅደው መሰረት አስፈፃሚ ኮሚቴዎች #ሪፈረንደም ያካሂዳሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፦ የሲዳማ ዞን ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮምኒኬሽን መምሪያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሪፈረንደም

" ህዝብ የሚያቀራርብ ሌላ መፍትሄ ካለ መጠቆምና መነጋገር ይቻላል " - ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ ጥያቄ በሚነሳባቸው የአማራ እና ትግራይ አካባቢዎች ጉዳይ መንግሥት ይዞት ከመጣው መፍትሄ የተሻለና የተለየ መፍትሄ ያለው ማቅረብ ይችላል አሉ።

ዶ/ር ዐቢይ ፤ የፌደራል መንግስት በትግራይና አማራ ክልሎች አወዛጋቢ የሆኑ የወሰን ጉዳዮች #በህዘበ_ውሳኔ እንዲፈታ እንደሚፈልግ አሳውቀዋል።

ይህ የመፍትሄ ሀሳብ በክልሎቹ መካከል ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን እንዲሁም አንዱ ተደስቶ ሌላው እንዳያኮርፍ የሚያደርግ እንደሆነ ጠቁመዋል።

ለዚህም ፌዴራል መንግሥት ከሁለቱም ክልሎች አመራሮች ጋር ውይይት ማድረጉንና አቅጣጫ አስቀምጦ እየሰራበት እንደሆነ ተናግረዋል።

" የህዝበ ውሳኔው / ሪፈረንደም ብቸኛ አማራጭ አይደለም " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " የሁለቱንም ክልሎች ዘላቂ ሰላም የሚያመጣ፤ ህዝብ የሚያቀራርብ ሌላ መፍትሄ ካለ መጠቆምና መነጋገር ይቻላል " ብለዋል።

" የአማራ እና ትግራይ ምሁራን፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ተወያይተው ዘላቂ ሰላም የሚያመጣ መፍትሄ አለን ካሉ በደስታ እንቀበላልን " ሲሉ ገልጸዋል።

" መንግሥት ሪፈረንደም ይደረግና በህግ መሰረት በአካባቢዎቹ ዘላቂ ሰላም ይስፈን ብሎ እየሰራ ነው ፤ ከዚህ ውጭ አማራጭ ያለው ያቅርብ " ብለዋል።

መፍትሄ መጠቆም ሳይቻል ግን በመንግስት የቀረበውን የመፍትሄ ሃሳብ አለመቀበል ግን ተገቢ አይደለም፤ ወደ ሰላም አይወስድም ፤ ለአንዱ ቢመለስም ለሌላው ጥያቄ ሆኖ ይቀጥላል ሲሉ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
😡757369🕊53👏43😢15😱12🙏12🥰5