የተመድ ማስጠንቀቂያ‼️የአለም ሀገራት የምድራችን ሙቀት እንዳይጨምር አስፈላጊውን እርምጃ ካልወሰዱ እስከ አውሮፓዊያኑ 2030 ባለው ጊዜ የከፋ የአየር ንብረት ለውጥ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል የተባበሩት መንግስታቱ ድርጅት/ተመድ/ #አስጠነቀቀ፡፡
ድርጅቱ ይሄን ያስታወቀው ከአውሮፓዊያኑ 2030 ወዲህ የአለም ሙቀት ከ1 ነጥብ 5 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ #ሊጨምር እንደሚችል ከተነበየ በኋላ ነው ተብሏል፡፡
ይሄም ሁኔታ እውን ከሆነ በአለም በሚሊዮን በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ የከፋ ድርቅ፣ ሰደድ እሳት፣ ጎርፍ እና የምግብ እጥረት እንደሚከሰት የመንግስታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ፓናል ገልጿል፡፡
ድርጅቱ እዚህ መደምደሜያ ላይ የደረሰው ለአለም ሙቀት መጨመር ምክንያት የሆነው የሙቀት አማቂ ጋዝ ልቀት አሁን ያለበትን ደረጃ ጥናት በማድረግ እንደሆነ ተነግሯል፡፡
አሁን ላይ የአለም ሙቀት በ1 ዲግሪ ሴልሺየስ እየጨመረ ሲሆን ይህን ሁኔታ እንዳይባባስ በሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት የአለም መንግስታት አስፈላጊውን እርምጃ ሊወስዱ እንደሚገባ ተመልክቷል፡፡
የአለም ሙቀት ከ1 ነጥብ 5 ድግሪ ሴልሺየስ የዘለለ እንዳይሆን እስከ 2030 ባለው ጊዜ ውስጥ የአለም የካርቦን ዳይ ኦክሳይድ ልቀት በ45 በመቶ ሊቀንስ እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡
ምንጭ፦ ሲኤንኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ድርጅቱ ይሄን ያስታወቀው ከአውሮፓዊያኑ 2030 ወዲህ የአለም ሙቀት ከ1 ነጥብ 5 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ #ሊጨምር እንደሚችል ከተነበየ በኋላ ነው ተብሏል፡፡
ይሄም ሁኔታ እውን ከሆነ በአለም በሚሊዮን በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ የከፋ ድርቅ፣ ሰደድ እሳት፣ ጎርፍ እና የምግብ እጥረት እንደሚከሰት የመንግስታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ፓናል ገልጿል፡፡
ድርጅቱ እዚህ መደምደሜያ ላይ የደረሰው ለአለም ሙቀት መጨመር ምክንያት የሆነው የሙቀት አማቂ ጋዝ ልቀት አሁን ያለበትን ደረጃ ጥናት በማድረግ እንደሆነ ተነግሯል፡፡
አሁን ላይ የአለም ሙቀት በ1 ዲግሪ ሴልሺየስ እየጨመረ ሲሆን ይህን ሁኔታ እንዳይባባስ በሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት የአለም መንግስታት አስፈላጊውን እርምጃ ሊወስዱ እንደሚገባ ተመልክቷል፡፡
የአለም ሙቀት ከ1 ነጥብ 5 ድግሪ ሴልሺየስ የዘለለ እንዳይሆን እስከ 2030 ባለው ጊዜ ውስጥ የአለም የካርቦን ዳይ ኦክሳይድ ልቀት በ45 በመቶ ሊቀንስ እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡
ምንጭ፦ ሲኤንኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኮማንድ ፖስቱ ማስጠንቀቂያ!
<<በደቡብ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በመንግስት እውቅና ሳይሰጣቸው ተሰቅለው የሚገኙ አርማዎችና ሰንደቅ ዓላማዎች በአስቸኳይ እንዲነሱ>> ሲል የደቡብ ክልል ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስት #አስጠነቀቀ ።
ኮማንድ ፖስቱ ዛሬ በክልሉ መንግስት ራዲዮ ጣቢያ አማካኘነት ባስሳተላለፈው ማሳሰቢያ፤ ኮማንድ ፖስቱ በክልሉ አንዳንድ ዞኖች እና ወረዳዎች በህግ የማይታወቁ አርማዎችን፣ ሰንደቅ ዓላማዎችን፣ ባነሮችን እና የአድራሻ ማስታወቂያዎችን (ታፒላዎችን) የሰቀሉ አካላት ከዛሬ ጀምሮ ባሉት ሁለት ተከታታይ ቀናት ውስጥ በአስቸኳይ እንዲያነሱ ሲል አሳስቧል።
በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የክልሉን #ህጋዊ ሰንደቅ ዓላማ በማውረድና የመንግስት ተቋማት የአድራሻ ማስታወቂያዎችን በመንቀል በምትኩ እውቅና የሌላቸውን የመትከል ሙከራዎች መከናወናቸውን ኮማንድ ፖስቱ በመግለጫው አስታውቋል።
በመሆኑም «ህገ ወጥ»ያላቸውን አርማዎችን፣ ሰንደቅ ዓላማዎችን እና የአድራሻ ማስታወቂያዎችን በተሰጠው የሁለት ቀናት የጊዜ ገደብ ውስጥ በማንሳት ህጋዊ» የሆኑትን በአስቸኳይ ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ ሲል ኮማንድ ፖስቱ አሳስቧል።
በተጨማሪም መግለጫው ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በክልሉ ሁሉም ዞኖች ፣ ወረዳዎች ፣ በከተሞች አና በቀበሌዎች የመስተዳድር ክልል ውስጥ የሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ የግል ተቋማት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች #ትክክለኛ የአድራሻ ማስታወቂያዎችን (ታፒላዎችን) እና ህጋዊ የክልሉን ሰንደቅ ዓላማ ብቻ እንዲጠቀሙ አመልክቷል።
እንዲሁም በተለያዩ የህትመት ውጤቶች የተዘጋጁና በህግ የማይታወቁ አርማዎችንና ሰንደቅ ዓላማዎችን መልበስ ፣ ይዞ መዘዋወር ፣ መሰቀልም ሆነ መለጠፍ በጥብቅ የተከለከለ ነው ሲል አስታውቋል። በተጠቀሰው ቀናት ውስጥ መመሪያውን ተፈፃሚ በማያደርጉ ግለሰቦች፣ ተቋማት እና ድርጅቶች ላይ በየደረጃው በተዋቀሩ የኮማንድ ፖስት አማካኝነት #ህጋዊ_እርምጃ ይወሰዳል ሲል አስጠንቅቋል።
በደቡብ ክልል የሀዋሳ እና የወላይታ ሶዶ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በክልል መደራጀትን ለመጠየቅ በተዘጋጁ ሰልፎች ላይ ወደፊቱ ለሚመሰርቷቸው ክልሎች በሰንደቅ ዓላማነት ሊያገለግሉ ይችላሉ በሚል የዘጋጁቸውን አርማዎችን ሲያውለበልቡ እንደነበር አይዘነጋም። በተለይም በሲዳማ ዞን ከባለፈው ሐምሌ 11 ቀን 2011 ዓም ወዲህ በዞኑ የሚገኙ አንዳንድ የወረዳዎች መስተዳድር ፅህፈት ቤቶች የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የሚሉ የአድራሻ ማስታወቂያዎችን በጎዳናዎች በመትከል በማህበራዊ የመገናኛ ዘዴ አውታሮች እያሰራጩ እንደሚገኙ ይታወቃል።
ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
<<በደቡብ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በመንግስት እውቅና ሳይሰጣቸው ተሰቅለው የሚገኙ አርማዎችና ሰንደቅ ዓላማዎች በአስቸኳይ እንዲነሱ>> ሲል የደቡብ ክልል ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስት #አስጠነቀቀ ።
ኮማንድ ፖስቱ ዛሬ በክልሉ መንግስት ራዲዮ ጣቢያ አማካኘነት ባስሳተላለፈው ማሳሰቢያ፤ ኮማንድ ፖስቱ በክልሉ አንዳንድ ዞኖች እና ወረዳዎች በህግ የማይታወቁ አርማዎችን፣ ሰንደቅ ዓላማዎችን፣ ባነሮችን እና የአድራሻ ማስታወቂያዎችን (ታፒላዎችን) የሰቀሉ አካላት ከዛሬ ጀምሮ ባሉት ሁለት ተከታታይ ቀናት ውስጥ በአስቸኳይ እንዲያነሱ ሲል አሳስቧል።
በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የክልሉን #ህጋዊ ሰንደቅ ዓላማ በማውረድና የመንግስት ተቋማት የአድራሻ ማስታወቂያዎችን በመንቀል በምትኩ እውቅና የሌላቸውን የመትከል ሙከራዎች መከናወናቸውን ኮማንድ ፖስቱ በመግለጫው አስታውቋል።
በመሆኑም «ህገ ወጥ»ያላቸውን አርማዎችን፣ ሰንደቅ ዓላማዎችን እና የአድራሻ ማስታወቂያዎችን በተሰጠው የሁለት ቀናት የጊዜ ገደብ ውስጥ በማንሳት ህጋዊ» የሆኑትን በአስቸኳይ ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ ሲል ኮማንድ ፖስቱ አሳስቧል።
በተጨማሪም መግለጫው ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በክልሉ ሁሉም ዞኖች ፣ ወረዳዎች ፣ በከተሞች አና በቀበሌዎች የመስተዳድር ክልል ውስጥ የሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ የግል ተቋማት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች #ትክክለኛ የአድራሻ ማስታወቂያዎችን (ታፒላዎችን) እና ህጋዊ የክልሉን ሰንደቅ ዓላማ ብቻ እንዲጠቀሙ አመልክቷል።
እንዲሁም በተለያዩ የህትመት ውጤቶች የተዘጋጁና በህግ የማይታወቁ አርማዎችንና ሰንደቅ ዓላማዎችን መልበስ ፣ ይዞ መዘዋወር ፣ መሰቀልም ሆነ መለጠፍ በጥብቅ የተከለከለ ነው ሲል አስታውቋል። በተጠቀሰው ቀናት ውስጥ መመሪያውን ተፈፃሚ በማያደርጉ ግለሰቦች፣ ተቋማት እና ድርጅቶች ላይ በየደረጃው በተዋቀሩ የኮማንድ ፖስት አማካኝነት #ህጋዊ_እርምጃ ይወሰዳል ሲል አስጠንቅቋል።
በደቡብ ክልል የሀዋሳ እና የወላይታ ሶዶ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በክልል መደራጀትን ለመጠየቅ በተዘጋጁ ሰልፎች ላይ ወደፊቱ ለሚመሰርቷቸው ክልሎች በሰንደቅ ዓላማነት ሊያገለግሉ ይችላሉ በሚል የዘጋጁቸውን አርማዎችን ሲያውለበልቡ እንደነበር አይዘነጋም። በተለይም በሲዳማ ዞን ከባለፈው ሐምሌ 11 ቀን 2011 ዓም ወዲህ በዞኑ የሚገኙ አንዳንድ የወረዳዎች መስተዳድር ፅህፈት ቤቶች የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የሚሉ የአድራሻ ማስታወቂያዎችን በጎዳናዎች በመትከል በማህበራዊ የመገናኛ ዘዴ አውታሮች እያሰራጩ እንደሚገኙ ይታወቃል።
ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia