TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ትኩረት‼️

የፌደራሉ መንግሥት #አጣዬ አካባቢ የተፈጣረው ችግር ሳይባባሥ #አስቸካይ መፍትሄ እንዲፈልግ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሠብ አባላት ጠይቀዋል።

ከአጣዬ••••

ለሰላም ሚኒስቴር
50 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ...

#በከሚሴ እና #አጣዬ አካባቢዎች ከወራት በፊት ተከስቶ በነበረው ግጭት በወንጀል የተጠረጠሩ 50 ሰዎች ከሕገ-ወጥ መሳሪዎች ጋር መያዛቸውን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ፡፡

ከኮሚሽኑ እና ከሕግ አካላት የተውጣጣ የመርማሪ ቡድን ተዋቅሮ ጉዳዩን ከቦታው ሲያጣራ መቆየቱንም የኮሚሽኑ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ሚዲያ ልማት ዋና መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር #ሰይድ_አህመድ ተናግረዋል፡፡

የምርመራ ቡድኑ በአጣራው መሠረትም በወንጀል ተጠርጥረው የተያዙት ግለሰቦች የተደራጀ ወንጀል ሲፈፅሙ ቆይተዋል ብለዋል ረዳት ኮሚሽነሩ፡፡

የምርመራ ቡድኑ በሕግ ጥላ ስር ያሉትን ጨምሮ ሌሎችንም በቁጥጥር ስር አውሎ ለሕግ ለማቅረብ እየሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡

በተጠቀሱት አካባቢዎች ከወራት በፊት ተከስቶ በነበረው ግጭት ከ4 ዓመት ህጻን እስከ 94 ዓመት አዛውንት ህይዎት ማለፉንም ረዳት ኮሚሽነሩ አስታውሰዋል፡፡

በሌሎች አካባቢዎች ተመሳሳይ ወንጀል የፈፀሙ አካላትን በቁጥጥር ስር የማዋሉ ተግባር እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አጣዬ

አጣዬ ዳግም ሰላም ርቋታል፤ የአጣዬ ቲክቫህ አባላት በላኩት የፅሁፍ መልዕክት ዳግም በተፈጠረው የፀጥታ መደፍረስ ሰዎች ሞተዋል ፣ ንብረት ተቃጥሏል፣ ሰዎች ሰላምን ፍለጋ ከገዛ ቤታቸውን ተፈናቅለው ሸሽተዋል።

ረቡዕ በአጣዬ ቤቶች መቃጠላቸውን ተከትሎ ከአምስት ሰዓት ጀምሮ የተኩስ እሩምታ የነበረ ሲሆን በሰዓት መከላከያ እና ፌዴራል ሁኔታውን መቆጣጠር ችለው ነበር።

አንድ የቲክቫህ አባል በአጣዬ ባለው ሁኔታ ሁለት በቅርብ የሚያውቃቸው ሰዎች መሞታቸውን ቢያረጋግጥም አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር በትክክል እንኳን እንደማይታውቀ ተናግሯል።

ሌላ የቲክቫህ አባል ፥ በቅድሚያ ወደዳር አካባቢ የነበረው የተኩስ እሩምታ ወደ መሃል ክፍልም ይሰማ እንደነበረ ተናግሮ በአካባቢው የሚኖሩ ቤተሰቦቹ ሰላምን ፍለጋ ቤታቸውን ጥለው ሸሽተዋል።

የፀጥታ ኃይሎች ያሉ ቢሆንም፥ በቂ አይደለም በታጠቁ ኃይሎች የሚፈፀመው ጥቃት / የሚሰማው ተኩስ በርካቶችን በደህንነት ስጋት ውስጥ ከቷቸውን ቤታቸው ለቀው እየሸሹ ናቸው።

በተጨማሪ በአንጻኪያ ወረዳ ውስጥ ባሉቱ የተለያዩ ቀበሌዎች ዳግም ግጭት ተቀስቅሶ ጉዳት እየደረሰ ይገኛል።

በእነዚህ አካባቢዎች በተፈጠረው የፀጥታ መደፍረስ ዋናው ዳግም መንገድ ተዘግቷል፤ወደ እና ከ አ/አ መሄድ አይቻልም መኪናዎችም ሸዋሮቢት ላይ ቆመዋል።

የሸዋሮቢት ቲክቫህ አባላት እንዴት ናችሁ ብለን ጠይቀናቸው ነበር?

ዛሬ በሸዋሮቢት ሁሉም መደበኛ እንቅስቃሴ መቀጠሉን አረጋግጠውልን፤ አጣዬ ላይ የተፈፀምጠረውን ሁኔታ ግን እንደሰሙት ገልፀዋል።

የአካባቢው አስተዳደር የጸጥታ ኃይል ችግር ቢፈጠር እንኳን ለመጠበቅና ለመከላከል ቦታ መያዙን፤ ምንም የሚያሳስብ ነገር እንደሌለ መግለፁን ነገርውናል።

ከሀሰተኛ መረጃና ውዥንብር ማህበረሰቡ እንዲቆጠብ ጥሪ መቅሩብን ነግረውናል።

@tikvahethiopia
1👍1