TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.4K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
Audio
#ለጥንቃቄ⚠️

እንዲህ ካሉ አጭበርባሪዎች ተጠንቀቁ።

ከላይ የምትሰሙት የድምፅ ቅጂ ከአንድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የተላከ ነው።

አጭበርባሪው ደዋይ ግለሰብ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ #ዋናው_ቢሮ እንደደወለ በማስመሰል በኦንላይን ዘረፋ ለመፈፀም ሞክሯል።

የደወለው #የባንክ_ሰራተኛ ጋር መሆኑን አላወቀም ነበር።

ሰራተኛው ግለሰቡ የሚለፈልፈውን ሁሉ እስከ መጨረሻ ድረስ አዳመጠው።

በኃላም የአንድ የባንኩን ቅርንጫፍ ዋና ስራ አስኪያጅ ስምን ይጠይቀዋል።

በዚህ ግዜ ከዋናው መ/ቤት ነኝ ያለው አጭበርባሪ ምን ይዋጠው ? መቀባጠር ይጀምራል።

በመጨረሻ ውርደቱን ተከናንቦ ስልኩን ዘግቷል።

እንዲህ ያሉ የማጭበርበር ስልቶች አንድ ሰሞን እንደጉድ ተበራክተው ነበር። አሁን ደግሞ ሰሞነኛውን የንግድ ባንክን ሁኔታ ተከትሎ እንደ አዲስ ተስፋፍተዋል።

ውድ ቤተሰቦቻችን ፦
* የማታውቋቸው የግል ስልኮችን ባለማንሳት ፣
* #የሚስጥር_ቁጥሮችን ባለመስጠት እራሳችሁን ከአጭበርባሪዎች ጠብቁ። የሚመለከታቸው አካላትም ይህን ነገር እንደ ቀላል ከማየት የማጭበርበር ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች #በደወሉበት_ስልክ ክትትል በማድረግ ወደ ህግ ማቀረብ አለባቸው።

(የድምፅ ቅጂውን ለላከው የቤተሰባችን አባል ምስጋና እናቀርባለን)

@tikvahethiopia
🙏1.25K👏321192😡99🤔69😱57😭42🕊34🥰33😢24
Audio
#ለጥንቃቄ⚠️

" ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መስሪያ ቤት ነው " እየተባለ ወደ ተለያዩ የባንኩ ደንበኞች ስልክ እየተደወለ የግል መረጃ መውሰድና የኦንላይን ዝርፊያ እየተሞከረ ይገኛል።

ቀደም ብሎ አንድ #አጭበርባሪ ግለሰብ (ጾታ - ወንድ) ሳያውቀው ለባንክ ሰራተኛ ደውሎ ያጋጠመውን ክስተት አጋርተናል።

የዜጎችን ሀቅና ገንዘብ አታለው ለመዝረፍ ስልክ ከሚደውሉት መካከል #ሴቶችም ስለሚገኙበት ጥንቃቄ አድርጉ።

ከላይ ባለው የድምፅ ቅጂ የምትሰሟት አጭበርባሪ ግለሰብ (ጾታ-ሴት) ከንግድ ባንክ ዋና መ/ቤት እንደደወለች በማስመሰል ፦ ደንበኞች የሞባይል ባንኪንግ ሲጠቀሙ ኔትዎርኩ please try again ፣ connection problem ፣ error ፣ service not available " የሚል ችግር እየገጠማቸው እንደሆነ ትገልጸለች።

በዚህ ምክንያት ባንኩ ከብዙ ደንበኞቹ ቅሬታ በመምጣቱ ፤ " ችግሩን በዋናው የንግድ ባንክ መ/ ቤት #ሲስተም ላይ ለማስተከል ነው " በማለት የደንበኛውን የግል መረጃዎች በመቀበልና በማታለል ዝርፊያ ለመፈፀም ሞክራለች።

አሁን ላይ እንዲህ ያሉት አጭበርባሪዎች ተበራክተዋል ተጠንቀቁ።

ለማንኛውም #የማታውቁት ስልክ የባንክ መረጃችሁን እንዳትሰጡ።

@tikvahethiopia
🤔810🙏391225😱72😡59👏49😢44🥰34🕊25😭22