TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች መታሰራቸው ተገለፀ። እንዚህ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ሊውሉ የቻሉት ፦ - ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣ - ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ - ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የተውጣጣ ግብረ-ኃይል ከሙስናና ሕገወጥ ተግባር ጋር በተያያዘ ክትትልና ምርመራ ሲያደርግ ከቆየ በኃላ ነው ተብሏል። ተጠርጣሪዎቹ ፤ ተገልጋዮች በመደበኛ…
#ሙስና #ICS
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ምክትል ኃላፊ የነበሩት ታምሩ ግንበቶን ጨምሮ 60 የተቋሙ ባልደረቦች 15 የሙስና ወንጀል ክስ ተመሠረተባቸው።
የተቋሙ ምክትል ዳይሬክተር ከነበሩት ታምሩ ግንበቶ በተጨማሪ የውጭ ዜጎች ቁጥጥር ቆንስላ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጅላሉ በድሩ የኬላዎች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ቦጋለም ይገኙበታል።
በፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ወንጀል ዐቃቤ ሕግ በክሱ የእያንዳንዱ ተከሳሽ የወንጀል ተሳትፎን ዘርዝሯል።
የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ታምሩ ግንበቶ ኃላፊነታቸውን በመጠቀም ፦
* ፎርቲን አቬጋ በተባለ ድርጅት የሚሠሩ 12 ግብፃዊያን ለቪዛ ቅጣት ይከፍሉ የነበረውን 24 ሺህ ዶላር በራሳቸው ትዕዛዝ 14 ሺህ ዶላሩን በመቀነስ በመመሪያው መሠረት ባልተገባ መንገድ የተቀነሰውን በዶላር መክፈል ሲገባቸው በኢትዮጵያ ብር እንዲከፍሉ በማድረግ መንግሥት ላይ ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል።
* ሀይንፊን፣ ሀድዙ የተሰኙ የቻይና ኩባንያ ድርጅት ውስጥ የሚሠሩ ብሎም ሻሎም አስመላሽ ኪዳኔ እና ነጃት ዓሊ መሐመድ ለቪዛ ቅጣት በዶላር መክፈል ከነበረባቸው 4 ሺህ ዶላር ያህል መመሪያ በመጣስ እንዳይከፍሉ በማድረግ መንግሥት ላይ ጉዳት አድርሰዋል።
* የማይገባ ጥቅምን ለማግኘት በማሰብ ተገቢ ማጣራት ሳይከናወን ነዋሪነታቸው በሶማሊ ላንድ ሐርጌሳ ለሆኑ 68 ግለሰብ የኢትዮጵያ ፓስፖርት እንዲሰጥ በማድረግ የሀገርን ደኅንነት አደጋ ላይ የሚጥል ድርጊት የፈፀሙ በመሆኑ ሥልጣንን ያለ አግባብ በመገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከስሰዋል።
1ኛው ተከሳሽ ታምሩ ግንበቶ እና 2ኛ ተካሽ ጅላሉ በድሩ በወንጀል ከሀገር እንዳይወጡ ትዕዛዝ ለተላለፈባቸው 6 ቻይናውያን መካከል ዙ ጂያን እና ዛንግፒንግል የተሰኙ ሁለቱ የተጣለባቸው እግድ ተነሥቶ የመውጫ ቪዛ በአስቸኳይ እንዲሰጣቸው በማድረጋቸው ዐቃቤ ሕግ ሁለቱንም ግለሰቦች በፈፀሙት ሥልጣንን ያለ አግባብ በመገልገል የሙስና ወንጀል ከሷቸዋል።
ዐቃቤ ሕግ የእያንዳንዱን ተከሳሽ የወንጀል ተሳትፎን በመጥቀስ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ የሙስና ወንጀል ጉዳይ ችሎት አቅርቧል።
በተከሳሾች ስም ፦
- 14,523,647.36 ብር (14 ሚሊዮን 523 ሺህ 647 ከ36 ሣንቲም)
- አክሲዮን 383,000.00 ብር (383 ሺህ)
- 8 ቤቶች ያሉ ሲሆን በፍትሕ ሚኒስቴር በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ጄኔራል በኩል ምንጩ ያልታወቀ ሀብት ማፍራት እንዲሁም በወንጀል የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ ማቅርብ ወንጀል ምርመራ እየተጣራ እና ምርመራ እየቀጠለ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።
ክሱን በንባብ ለማሰማት ፍርድ ቤቱ ለሰኞ ታኅሣሥ 8 ቀን 2016 ዓ.ም ቀጠሮ መሰጠቱን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ምክትል ኃላፊ የነበሩት ታምሩ ግንበቶን ጨምሮ 60 የተቋሙ ባልደረቦች 15 የሙስና ወንጀል ክስ ተመሠረተባቸው።
የተቋሙ ምክትል ዳይሬክተር ከነበሩት ታምሩ ግንበቶ በተጨማሪ የውጭ ዜጎች ቁጥጥር ቆንስላ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጅላሉ በድሩ የኬላዎች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ቦጋለም ይገኙበታል።
በፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ወንጀል ዐቃቤ ሕግ በክሱ የእያንዳንዱ ተከሳሽ የወንጀል ተሳትፎን ዘርዝሯል።
የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ታምሩ ግንበቶ ኃላፊነታቸውን በመጠቀም ፦
* ፎርቲን አቬጋ በተባለ ድርጅት የሚሠሩ 12 ግብፃዊያን ለቪዛ ቅጣት ይከፍሉ የነበረውን 24 ሺህ ዶላር በራሳቸው ትዕዛዝ 14 ሺህ ዶላሩን በመቀነስ በመመሪያው መሠረት ባልተገባ መንገድ የተቀነሰውን በዶላር መክፈል ሲገባቸው በኢትዮጵያ ብር እንዲከፍሉ በማድረግ መንግሥት ላይ ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል።
* ሀይንፊን፣ ሀድዙ የተሰኙ የቻይና ኩባንያ ድርጅት ውስጥ የሚሠሩ ብሎም ሻሎም አስመላሽ ኪዳኔ እና ነጃት ዓሊ መሐመድ ለቪዛ ቅጣት በዶላር መክፈል ከነበረባቸው 4 ሺህ ዶላር ያህል መመሪያ በመጣስ እንዳይከፍሉ በማድረግ መንግሥት ላይ ጉዳት አድርሰዋል።
* የማይገባ ጥቅምን ለማግኘት በማሰብ ተገቢ ማጣራት ሳይከናወን ነዋሪነታቸው በሶማሊ ላንድ ሐርጌሳ ለሆኑ 68 ግለሰብ የኢትዮጵያ ፓስፖርት እንዲሰጥ በማድረግ የሀገርን ደኅንነት አደጋ ላይ የሚጥል ድርጊት የፈፀሙ በመሆኑ ሥልጣንን ያለ አግባብ በመገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከስሰዋል።
1ኛው ተከሳሽ ታምሩ ግንበቶ እና 2ኛ ተካሽ ጅላሉ በድሩ በወንጀል ከሀገር እንዳይወጡ ትዕዛዝ ለተላለፈባቸው 6 ቻይናውያን መካከል ዙ ጂያን እና ዛንግፒንግል የተሰኙ ሁለቱ የተጣለባቸው እግድ ተነሥቶ የመውጫ ቪዛ በአስቸኳይ እንዲሰጣቸው በማድረጋቸው ዐቃቤ ሕግ ሁለቱንም ግለሰቦች በፈፀሙት ሥልጣንን ያለ አግባብ በመገልገል የሙስና ወንጀል ከሷቸዋል።
ዐቃቤ ሕግ የእያንዳንዱን ተከሳሽ የወንጀል ተሳትፎን በመጥቀስ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ የሙስና ወንጀል ጉዳይ ችሎት አቅርቧል።
በተከሳሾች ስም ፦
- 14,523,647.36 ብር (14 ሚሊዮን 523 ሺህ 647 ከ36 ሣንቲም)
- አክሲዮን 383,000.00 ብር (383 ሺህ)
- 8 ቤቶች ያሉ ሲሆን በፍትሕ ሚኒስቴር በወንጀል የተገኘ ሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ጄኔራል በኩል ምንጩ ያልታወቀ ሀብት ማፍራት እንዲሁም በወንጀል የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ ማቅርብ ወንጀል ምርመራ እየተጣራ እና ምርመራ እየቀጠለ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።
ክሱን በንባብ ለማሰማት ፍርድ ቤቱ ለሰኞ ታኅሣሥ 8 ቀን 2016 ዓ.ም ቀጠሮ መሰጠቱን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
@tikvahethiopia
👏870❤185😱61😭57🙏47🕊22😢20😡20🥰17