TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የኢትዮጵያ ተስፋዎች🔝

#የTikvah_Ethiopia ሴት አባላት በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እና በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ሊሰሩ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ አጭር ገለፃ ተደርጎላቸዋል:: ለበርካታ ወጣት #ሴቶች አርአያ ለመሆን እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች በቀጣይ ሊሰሯቸው ባሰቧቸው ስራዎች ዙሪያም በመጪው ሳምንት #ምክክር ያደርጋሉ:: በዛሬው ውይይት ላይ የተካፈሉት #አብዛኞቹ #የStopHateSpeech አስተባባሪዎች ናቸው::

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፌስቡክ አስተያየት ሰጪዎች እነማን ናቸው

#አብዛኞቹ በተለያዩ #የፌስቡክ_ፖስቶች ላይ/በዜና ማሰራጫዎች፣ በታዋቂ ግለሰቦች ገፅ፣ በአክቲቪስቶች እንዲሁም በሌሎች.../ የስድብ ናዳ የሚያወርዱት፤ ህዝብን የሚያሸብሩት፤ ሀገሪቱ ፍፁም እልቂት ውስጥ ልትገባ እንደሆነ የሚዝቱት፤ እርስ በእርስ ፍጅት እንዲነሳ የሚቀሰቅሱት፤ በተላለፉ መረጃዎች ላይ በሙሉ ስድብ እና ጥላቻን፣ አሉባልታን የሚፅፉት አብዛኞቹ #ሀሰተኛ ገፅ ናቸው። የሰዎቹ ማንነት የማይታወቅ፣ ምስላቸው የሌለ፣ ለግጭት እንዲሁም ህዝብን ለማወናበድ የተከፈቱ ናቸውና ተጠንቀቁ። በምታነቡት አስተያየትም ተስፋ አትቁረጡ።

በሌላ በኩል...

ትክክለኛ አመለካከታቸውን #በስድብ እና በኃይል ለመግለፅ የሚሞክሩም እንዳሉ ልታውቁ ይገባል። ማስረጃን አቅርቦ ከመከራከር ይልቅ ስድብ ባህል ያደረጉ ወገኖች አሉና ከቻልን ቀርበን እናስተካክላቸው።

ኢትዮጵያ ሰላም ትሁን፤
ዜጎቿም ሰላም ወጥተው ይግቡ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia