TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሰበር ዜና‼️

የጋቦን ወታደሮች የሞከሩት መፈንቅለ-መንግሥት #መክሸፉን የአገሪቱ መንግሥት አስታወቀ። የመንግሥቱ ቃል-አቀባይ ጉይ በርትራንድ ማፓንጎ የጸጥታ ኹኔታው ወደ ነበረበት መመለሱን ተናግረው "ኹኔታው በቁጥጥር ሥር ውሏል" ብለዋል። ቃል-አቀባዩ የአገሪቱን ብሔራዊ የራዲዮ ጣቢያ በቁጥጥራቸው ሥር ካዋሉ አምስት ወታደሮች አራቱ #መታሰራቸውን ለሬውተርስ ተናግረዋል።

በድንገት ወደ ብሔራዊ የራዲዮ ጣቢያ የገሰገሱ ወታደሮች የአገሪቱ ሕዝብ በመንግሥቱ ላይ እንዲነሳ ጥሪ አቅርበዋል። በዋና ከተማዋ ሊበርቪል በሚገኘው የራዲዮ ጣቢያ አቅራቢያ የተኩስ ድምፅ ተሰምቷል። በዋና ከተማዋ የጸጥታ አስከባሪዎች መሰማራታቸው እና ለመጪዎቹ ቀናት በዚያው እንደሚቆዩ የመንግሥቱ ቃል-አቀባይ ገልጸዋል።

ምንጭ፦ DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia