TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጥንቃቄ📌ይህ 5,143 ተከታዮች ያሉት የፌስቡክ ገፅ የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ የአማርኛ ገፅ #አይደለም። በዚህ ገፅ የተዛቡ መረጃዎች እየተሰራጨ በመሆኑ ጥንቃቄ አድርጉ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
1
ትዝብት📌የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች ውጤታቸውን ከ12 ሰዓት ጀምረው ማየት እንደሚችሉ በትልልቅ የመንግስት እና የግል መገናኛ ብዙሀን አሰራጭቷል። ይህ በተባለበት ሰዓት ተማሪዎች ውጤት ይታይባታል በተባለበት ድረገፅ እና የSMS ቁጥር ያለማያቋረጥ ሙከራ ቢያደርጉም ምንም ውጤት ለማየት አልቻሉም። ዝግጅት ካልተደረገበት እና ሲስተሙ በአግባቡ የማይሰራ ከሆነ ለምን ለህዝብ ይፋ ተረገ?? ይህን መሰሉ አሰራር የተቋሙን ታማኝነት ያሳጣዋል። በሌላ በኩል ተቋሙ ውጤት ማይታይበት ችግሩ ምን እንደሆነና ለምን እንዲህ ሊሆን እንደቻለ በመግለፅ ህዝቡን ይቅርታ ሊጠየቅ ይገባው ነበር። ብዙ ተማሪዎችን እና ወላጆችን በአሰራር ክፍተት #ማስጨነቅ ፍፁም ተገቢ #አይደለም። ሊታረም ሊስተካከል ይገባዋል።

ህዝብ ይከበር!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀጫሉ ሁንዴሳ...

“•••እነኚህ ሰዎች ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ሰርተው #ያስደመሙኝ ነገር አለ። ከዚህ በፊት ኦሮሞ እንደ አገር አፍራሽ ተደርጎ ብዙ ተሰርቶበታል። አሁን ግን ኦሮሞ አገር አፍራሽ እንዳልሆነ፣ ትልቅ ሃሳብ ያለው እንጂ የሚያሳስብ እንዳልሆነ፣ ያገሪቱ ጋሻ እንደሆነ ባለም ላይ አስመስክረዋል። በእርግጥ ሁሉም ነገር ተሟልቶ ተጠናቋል ማለት አይደለም#ለዘመናት የተተበተበብንን ትብታብ በጣጥሶ ነገሮችን ለማስተካከል #አይደለም ስምንት ወር #ስምንት አመትም አይበቃም። አሁን የታሰርንበትን እስራቶችን (ቋጠሮዎችን) በመፍታት ደረጃ ላይ ነው ያሉት። ደግሞም #ሁሉንም ነገር ከነሱ ብቻ መጠበቅ የለብንም። #እኛም እጅ ለእጅ ተያይዘን የምንሰራቸው ነገሮች አሉ።”

ሀጫሉ ሁንዴሳ ከOBN ቴሌቪዝን ጋር በነበረው ቆይታ የተናገረው!

©Daniel Ragassa
@tsegabwolde @tikvahethiopia
fake page🔝

ከላይ ያለው የፌስቡክ ገፅ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ #አይደለም

#ቲክቫህኢትዮጵያ #TIKVAHETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ይህ በEBS ስም የተከፈተና ከ46,000 በላይ ተከታዮች ያሉት የቴሌግራም ቻናል የEBS ቴሌቪዥን #አይደለም

ከዚህ ቀደም "አዲስ ነገር" EBS በሚል በቴሌግራም ላይ የተከፈተ ገፅ ትክክለኛ እንዳልሆነ ከEBS ሰዎች የደረሰንን መልዕክት ማጋራታችን አይዘነጋም።

@tsegabwolde @tikvahethiopia