TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኦነግ እና ODP‼️

የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ODP) እና የኦነግ አመራሮች ዛሬ በጋራ በሰጡት መግለጫ በሁለቱ መካከል ያለውን ስምምነት በማጠናከርና ችግሮችን በመፍታት #አብረው ለመስራት #ተስማምተዋል፡፡

የODP ምክትል ሊቀመንበር አቶ #ለማ_መገርሳ ከዚህ በኋላ ከኦነግ ጋር በመደማመጥ ለአገር እድገት በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡

አቶ ለማ ከኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ጋር አብሮ ለመስራትና የኦነግ ሰራዊት የመንግስት አካል ሆኖ ተጨማሪ አቅም እንዲሆን በአስመራ ስምምነት መደረሱን ገልጸዋል፡፡

በዚህ ስምምነት መሰረት ኦነግ ወደ አገር ገብቶ ስራ መጀመሩን የገለጹት አቶ ለማ፣ አለመረጋጋት የተፈጠረው ስምምነቱ ፈርሶ ሳይሆን ካለመረዳዳት የመነጫ ነው ብለዋል፡፡

ከእንግዲህ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር ሁለቱ ፓርቲዎች መስማማታቸውን አቶ ለማ ተናግረው፣ የODP አባላትና የጸጥታ ኃይሎች ይህንን ስምምነት ተረድተው መንቀሳቀስ አለባቸው ብለዋል፡፡

ወደ ትናንትናው ላለመመለስ በጋራ ቃል ተገባብተው አብረው ለመስራት እንደተስማሙም አቶ ለማ ተናግረዋል፡፡

የኦነግ ሊቀመንበር አቶ #ዳውድ_ኢብሳ በበኩላቸው፣ በአስመራ የተደረሰውን ስምምነት በመተግበር ከODP ጋር አብሮ ለመስራት መስማማታቸውን ገልጸዋል፡፡

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከODP አብረው ለመስራት መስማማታቸውንና የኦነግ አባላትና ደጋፊዎች ለዚህ ስምምነት የበኩላቸውን አስተዋዕኦ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡

ምንጭ:- OBN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
1