TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ቴዎድሮስ በእስር ላይ ይገኛል‼️

#ቴዎድሮስ_አዲሱ(ቴዲ ማንጁስ) በ80 ሺህ ብር ዋስ ቢፈቀድለትም #በሙስና_ወንጀል ተጠርጥሮ በእስር ላይ ይገኛል፡፡

ቴዎድሮስ አዲሱ ከሀምሌ 28-30 ቀን 2010ዓ.ም በጀጅጋ እና አካባቢው ተከስቶ በነበረው ሁከትና ብጥብጥ ተጠርጥሮ በተደጋጋሚ ፍርድ ቤት ቢቀርብም ዐቃቤ ህግ በጉዳዩ ላይ ምርመራውን ስላላጠናቀቀ እና በተደጋጋሚ የጊዜ ቀጠሮ መጠየቁ #ፍትሃዊ አለመሆኑንና የግለሰቡን ፍትህ የማግኘት መብት የሚጎዳ መሆኑን በማመን መዝገቡ እንዲዘጋ የጠየቀ ሲሆን ፍርድ ቤቱም በ80 ሺህ ብር ዋስ #እንዲወጣ ፈቅዶ ነበር፡፡

ሆኖም ግን ግለሰቡ በሌላ ወንጀል ከቀድሞው የሱማሌ ክልል ምክትል የትምህርት ቢሮ ኃላፊና ከኒያላ ኢንሹራንስ የጅጅጋ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ጋር በመመሳጠር #በተጭበረበረ የኢንሹራንስ ዋስትና አፈጻጸም የቅድመ ክፍያ ቦንድ ከኢንሹራንስ እንዲጻፍ በማድረግ በውሉ ላይ ከተጠቀሰው ቅድመ ከፍያ ላይ ብር 15,306,303.3 ከክልሉ ትምህርት ቢሮ ወጪ በማድረግ የወሰደ በመሆኑ ለትምህርት ቤቱ መፀሐፍቱን ሳያቀርብ ገንዘቡን ከጥቅም ተጋሪዎች ጋር በመከፋፈል ለግል ጥቅማቸው አውለዋል በሚል በሙስና ወንጀል ተጠርጥሮ ምርመራ እየተካሄደበት ይገኛል፡፡

መርማሪ ፖሊስ በቴዎድሮስ አዲሱ ላይ #በከባድ የሙስና ወንጀል የጀመረውን ምርመራው ለማከናወን የ14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደለት ተጠርጣሪው በእስር ቤት እንዲቆይ እና ለየካቲት 5 ቀን 2011 እንዲቀርብ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ምንጭ፦ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"...በመጠለያው ውስጥ የሚገኙት ወገኖች እንኳን ለራሳቸው ለሌላው የሚተርፉ አርሶ አድሮች ነበሩ " - አቶ መላኩ አለበል

ዛሬ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማቱ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማንዱራ ወረዳ እና አካባቢው ተፈናቅለው በቻግኒ ከተማ ለሚገኙ ወገኖች በቦታው በመገኘት ድጋፍ አደረጉ።

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በቻግኒ ከተማ ተጠልለው ለሚገኙ ከ40 ሺህ በላይ ለሆኑ ተፈናቃዮች የሚውል 2800 ኩንታል ስንዴ አስረክበዋል።

አቶ መለኩ አለበል ፥ "በመጠለያው ውስጥ የሚገኙት ወገኖች እንኳን ለራሳቸው ለሌላው የሚተርፉ የነበሩ አርሶ አድሮች ናቸው፤ ነገር ግን የነሱ ባልሆነ ጅንዳ የተለያየ ፍላጎት ባላቸው ሃይሎች የተሳሳተ ስሌት ለችግር ተጋልጠዋል" ብለዋል።

መንግስት ተፈናቃዮችን ወደቀያቸው ለመመለስ የተጠናከረ ሥራ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

በመጠለያው ውስጥ ለሚገኙት ዜጎች ከተለያዩ ወገኖች የሚመጣውን ርዳታ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት #ፍትሃዊ በሆነ መልኩ በፍጥነት እንዲያከፋፍሉ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።

አቶ መላኩ አለበል በመጠለያ ውስጥ የሚገኙ ተፈናቃዮችን ተዟዙረው ተመልክተዋል፤ አሉብን ያሏቸውን ችግሮችም ጠይቀው መረዳታቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በድረገፁ አስነብባል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia