TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የሶማሊላንዱ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ምን አሉ ?

የሶማሊላንዱ ፕሬዝደንት በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ከኢትዮጵያ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ መፈረሙን ገልጸዋል።

በዚህም ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ ለሶማሊላንድ ሪፐብሊክ እውቅና እንደምትሰጥ ፤ ሶማሊላንድ በበኩሏ ኢትዮጵያ የባህር ኃይል እና የንግድ ባህር በር መዳረሻ እንዲኖራት ለ50 ዓመታት #በሊዝ እንደምትሰጥ ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንቱ ይህንን ጉዳይ በትላንትናው መግለጫ ወቅትም የተናገሩት ሲሆን አሁንም በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አረጋግጠዋል።

ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት በኩል እስካሁን በስምምነቱ መሰረት ለሶማሊላንድ የነፃ ሀገርነት እውቅና እንሰጣለን የሚል ቃል አልወጣም።

በሌላ በኩል ስምምነቱ ያስቆጣቸው የሶማሊያ መንግሥት የካቢኔ አባላት ዛሬ ተሰብሰበው ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሏል።

ሶማሊያ ፤ ራዝ ገዟን ሶማሊላንድ እንደ አንድ ሉኣላዊ ግዛቷ ነው የምትቆጥራት።

ለሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ቅርብ የሆኑ ምንጮች ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በይፋ ይቅርታ ካልጠየቁ እና ለሶማሊያ ልዓላዊነት ክብር ካልሰጡ ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን እንደምታቋርጥ ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ሶማሊያ ፤ በኢትዮጵያ እና በሶማሌላንድ መካከል የተደረሰውን ስምምነት በመቃወም እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል እኚሁ ለፅ/ቤቱ ቅርብ የሆኑት ምንጮች አመልክተዋል።

ተጨማሪ . . .

በኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ መካከል ከተፈረመው ስምምነት ጋር በተያያዘ ዛሬ ማክሰኞ ሁለቱ የፌደራል ፓርላማ ምክር ቤቶች አስቸኳይ የጋራ ስብሰባ እንደሚያደርጉና የሶማሊያው ፕሬዝዳንትም ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ንግግር እንደሚያደርጉ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
390😡108🙏32🕊30👏25😭16😱8😢8🥰4