TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጥቆማ #YALI2023

የማንዴላ ዋሽንግተን ፌሎ ሺፕ ፕሮግራም የ2023 (Mandela Washington Fellowship) ማመልከቻ ዛሬ ክፍት ተደርጓል።

በአህጉሪቱ ያሉ ወጣቶች ተወዳድረው #በአሜሪካ ሀገር በሚደረግ ሥልጠና ላይ እንዲሳተፉ እድሉ ተመቻችቶላቸዋል።

ከዚህ ቀደም በርካታ #ኢትዮጵያውያን ወጣቶች እድሉን ተጠቅመው ይህንን ሥልጠና ወስደዋል።

በሥልጠናው ላይ ለመሳተፍ የሚያስፈልጉትን መስፈርቶችን ለማየትና ለማመልከት ይህን ይጫኑ👇
https://www.mandelawashingtonfellowship.org/apply/

👉 Application Timeline :

• August 16, 2022 | Application opens

• September 13, 2022 | Application deadline

• November 2022 – January 2023 | Semi-finalists interviewed by local U.S. embassies and consulates

• March 2023 | Applicants are notified of their status

• May 2023 | Visa processing and Pre-Departure Orientations for Finalists

June 2023 | Fellowship begins in the United States

Via @tikvahethmagazine
👍436👎38👏16🥰11😢8😱63
ቪዲዮ ፦ ከላይ የምትመለከቱት #በአሜሪካ ሀገር ፣ ፊላደልፊያ በአንድ የ " አይፎን ስቶር " ላይ ከቀናት በፊት የተፈፀመ ዘረፋ ነው።

ነገሩ እንዲህ ነው በርካታ #ጭምብል የለበሱ እና ያለበሱ ሰዎች የአፕል ስትሮን በኃይል ሰብረው ይገባሉ።

በኃላ ውስጥ የነበሩ ለእይታ የቀረቡ #ሁሉንም አዳዲሶቹን የ " አይፎን 15 " ምርቶች እና ሌሎች የአፕል ቴክኖሎጂ ውጤቶችን " free iPhone " እያሉ እየጮሁ ይወስዳሉ።

ከአፕል ስቶር ስልኮቹን ይዘው ከወጡ በኃላ አንድ ድምፅ ይሰማሉ ፤ ስልኩ አገልግሎት እንደማይሰጥ እንዲሁም ስልኩን የያዘው ሰው ላይ ክትትል እንደሚደረግ ስልኩ ላይ በተመለኩት ፅሁፍ ይረዳሉ።

በየአፕል ስቶር ውስጥ ለማሳያ የሚቀመጡት አይፎን ስልኮች ለሽያጭ ከሚቀርቡት አይፎኖች ላይ ከሚጫነው ሶፍትዌር በተለየ ልዩ ሶፍትዌር የሚጫንባቸው ናቸው።

ይህን ሲገነዘቡ " አይፎን 15 " ስልኮቹን ጥቅም እንዳይሰጡ አድርገው ወደ መሬት እየጣሉ #ይሰባብራሉ። የውሃ መውረጃ ትቦ ውስጥም ይጨምራሉ።

ፖሊስ ደርሶ በዘረፋው ላይ የተሳተፉትን በቁጥጥር እንዳዋለ ተነግሯል። በርካታ ሰዎች መታሰራቸውን ፖሊስ አሳውቋል።

ድርጊቱ ብዙ የአሜሪካ ዜጎችን በማህበራዊ ሚዲያ እያናጋገረ እና እያወያየ ሲሆን አንዳንዶች በዘረፋ ድርጊት ፈፃሚዎች ላይ ላልቷል ያሉትን ህግ ሲተቹ ታይተዋል።

@tikvahethiopia
😁936😱323176😡116😢30🥰27🙏25🕊25