#update በአፋር እና በሱማሌ ክልሎች #አዋሳኝ አካባቢዎች ምንም አይነት የፀጥታ ችግር እንዳይከሰት እንደሚሰሩ የሁለቱ ክልል ከፍተኛ ርዕሰ መሰተዳደሮች ገለፁ፡፡
የሱማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ሙስጠፋ_መሀመድ እና የአፋር ክልል ርዕሰ መሰተዳደር አቶ #አወል_አርባ ዛሬ በአዲስ አበባ በሁለቱ ክልሎች የፀጥታ ችግር መፍትሄ ዙሪያ ላይ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በሁለቱ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች አንድም ሰው እንዳይሞት እና ግጭት እንዳይከሰት የማድረግ ሰራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
የሰላም ሚኒስትር ዲኤታው አቶ #ዘይኑ_ጀማል በበኩላቸው ችግር በተፈጠረባቸው አካባቢዎች በአስቸኳይ የሀገር ሽማግሌዎች ቡድን እንዲቋቋምና ችግሩ በዘላቂነት ሊፈታ እደሚገባው ተናግረዋል፡፡ በአጠቃላይ ጉዳይ ላይም በህዝብ ለህዝብ #ውይይት ሊፈታ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ክልሎቹ #ከማንነት እና #ከወሰን ጋር ያሉ ችግሮችን ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
Via ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሱማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ሙስጠፋ_መሀመድ እና የአፋር ክልል ርዕሰ መሰተዳደር አቶ #አወል_አርባ ዛሬ በአዲስ አበባ በሁለቱ ክልሎች የፀጥታ ችግር መፍትሄ ዙሪያ ላይ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በሁለቱ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች አንድም ሰው እንዳይሞት እና ግጭት እንዳይከሰት የማድረግ ሰራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
የሰላም ሚኒስትር ዲኤታው አቶ #ዘይኑ_ጀማል በበኩላቸው ችግር በተፈጠረባቸው አካባቢዎች በአስቸኳይ የሀገር ሽማግሌዎች ቡድን እንዲቋቋምና ችግሩ በዘላቂነት ሊፈታ እደሚገባው ተናግረዋል፡፡ በአጠቃላይ ጉዳይ ላይም በህዝብ ለህዝብ #ውይይት ሊፈታ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ክልሎቹ #ከማንነት እና #ከወሰን ጋር ያሉ ችግሮችን ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
Via ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
" ጉዳዩ ሳይከር ትኩረት ይሰጠው "
በኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልሎች ወሰን አካባቢ የፀጥታ ችግር እንዳለ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ገልጸዋል።
በዚህ የፀጥታ ችግር ሳቢያ ከሀረር ወደ ጅግጅጋ የሚወስደው መንገድ ማስተጓጎል እንደተፈጠረ አመልክተዋል።
በአካባቢው የሚገኝ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ፤ በኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልል አዋሳኝ ባቢሌ ዳከተ አካባቢ ግጭት መኖሩን ጠቁሞ በዚህም መንገድ መዘጋቱን አሳውቋል።
በአካባቢው በተፈጠረው ግጭት ጉዳት መድረሱን የጠቆመው የቤተሰባችን አባል አሁንም ችግሩ እንዳለ ጠቁመዋል።
ሌላ የቤተሰባችን አባል ፤ ከአዲስ አበባ ወደ ጅግጅጋ መስመር " ባቢሌ " አካባቢ ወይም በሁለቱ ክልሎች ወሰን መንገድ ላይ በተፈጠረ ግጭት የሰው ህይወት አልፏል ብለዋል።
" ልዩ ኮሌጅ " ተብሎ የሚጠራበት ስፍራ ትናንት በፀጥታ ችግር አንድ ሰው እንደሞተ በአይናችን አይተናል ሶስት ሰው ቆስሎ ሆስፒታል ገብተዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
ዛሬ የተረጋጋ ቢሆንም አልፎ አልፎ ተኩስ ይሰማል ጉዳዩ ሳይከር የምመለከተው የፌዴራል አካል እልባት ቢሰጠው መልካም ነው ሲሉ አሳስበዋል።
በግጭቱ ምክንያት መንገድ በመዘጋቱ ከትላንት አንስቶ መንገደኞች ከፍተኛ እግልት እንደገጠማቸውም ይኸው ቤተሰባችን ገልጿል።
" በበዓል ምክንያት ከስራ ወጥተን የምመለስበት ሰዓት ላይ እንዲህ አይነት ነገር መፈጠሩ በማህበረሰቡ ላይ ትልቅ ችግር እና በባቢሌ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል " ሲሉ ገልጿል።
ሌላው የቤተሰባችን አባል ፤ ባቢሌ መውጫ እና በባንባስ መካከል በተለምዶ " ዳከታ " እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በተፈጠረ ግጭት ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል።
ሁኔታው የነዋሪዎችን ደህንነት አደጋ ላይ እንደጣለው ጠቁመዋል። ግጭቱ ዛሬም ቀጥሎ እንደዋለ ገልጸዋል።
ችግሩ በሁለቱ ክልሎች መካከል የፍተሻ ቦታ ላይ #ከወሰን ጋር በተገናኘ የተፈጠረ እንደሆነ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር ጥረት ቢያዳርግም አልተሳካም።
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልሎች ወሰን አካባቢ የፀጥታ ችግር እንዳለ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ገልጸዋል።
በዚህ የፀጥታ ችግር ሳቢያ ከሀረር ወደ ጅግጅጋ የሚወስደው መንገድ ማስተጓጎል እንደተፈጠረ አመልክተዋል።
በአካባቢው የሚገኝ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ፤ በኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልል አዋሳኝ ባቢሌ ዳከተ አካባቢ ግጭት መኖሩን ጠቁሞ በዚህም መንገድ መዘጋቱን አሳውቋል።
በአካባቢው በተፈጠረው ግጭት ጉዳት መድረሱን የጠቆመው የቤተሰባችን አባል አሁንም ችግሩ እንዳለ ጠቁመዋል።
ሌላ የቤተሰባችን አባል ፤ ከአዲስ አበባ ወደ ጅግጅጋ መስመር " ባቢሌ " አካባቢ ወይም በሁለቱ ክልሎች ወሰን መንገድ ላይ በተፈጠረ ግጭት የሰው ህይወት አልፏል ብለዋል።
" ልዩ ኮሌጅ " ተብሎ የሚጠራበት ስፍራ ትናንት በፀጥታ ችግር አንድ ሰው እንደሞተ በአይናችን አይተናል ሶስት ሰው ቆስሎ ሆስፒታል ገብተዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
ዛሬ የተረጋጋ ቢሆንም አልፎ አልፎ ተኩስ ይሰማል ጉዳዩ ሳይከር የምመለከተው የፌዴራል አካል እልባት ቢሰጠው መልካም ነው ሲሉ አሳስበዋል።
በግጭቱ ምክንያት መንገድ በመዘጋቱ ከትላንት አንስቶ መንገደኞች ከፍተኛ እግልት እንደገጠማቸውም ይኸው ቤተሰባችን ገልጿል።
" በበዓል ምክንያት ከስራ ወጥተን የምመለስበት ሰዓት ላይ እንዲህ አይነት ነገር መፈጠሩ በማህበረሰቡ ላይ ትልቅ ችግር እና በባቢሌ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል " ሲሉ ገልጿል።
ሌላው የቤተሰባችን አባል ፤ ባቢሌ መውጫ እና በባንባስ መካከል በተለምዶ " ዳከታ " እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በተፈጠረ ግጭት ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል።
ሁኔታው የነዋሪዎችን ደህንነት አደጋ ላይ እንደጣለው ጠቁመዋል። ግጭቱ ዛሬም ቀጥሎ እንደዋለ ገልጸዋል።
ችግሩ በሁለቱ ክልሎች መካከል የፍተሻ ቦታ ላይ #ከወሰን ጋር በተገናኘ የተፈጠረ እንደሆነ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር ጥረት ቢያዳርግም አልተሳካም።
@tikvahethiopia
👍592🕊106❤104😢37👎30😱22🙏16🥰13