#update የአሜሪካ ኤምባሲ⬇️
ረቡዕ መስከረም 9 ቀን 2011 ዓ.ም. ‹‹በአዲስ አበባ ከተማ ታላቅ ሕዝባዊ ሠልፍ እንደሚኖር ተገምቷል፤›› ብሎ የኤምባሲው ሠራተኞች ከቤታቸው እንዳይወጡ፣ በተጠቀሰው ቀንም ኤምባሲው ሥራ እንደማይኖረው ገልጾ የአሜሪካ ኤምባሲ ያወጣው ማሳሰቢያ በርካቶችን ግር አሰኝቷል፡፡ ኤምባሲው ከአስተማማኝ መረጃ አረጋግጫለሁ ያለለት ሠልፍም #አልተካሄደም፡፡
ኤምባሲው በድረ ገጹ ሁሉም የቪዛ አገልግቶችና የአሜሪካ ዜጎች አገልግሎት ቀጠሮዎች ሙሉ በሙሉ መሰረዛቸውንና አሜሪካዊ ዜግነት ያላቸው ሰዎች በድረ ገጹ አማካይነት ሌላ ቀጠሮ እንዲይዙ ገልጿል፡፡ የኢሚግሬሽን ቪዛ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ሌላ ቀጠሮ ተዘጋጅቶ እንደሚጠሩና ከዚህ ውጪ ያሉ የቪዛ አገልግሎት የሚጠይቁ ሰዎች በኤምባሲው ድረ ገጽ ቀጠሮ እንዲያሲዙ አሳስቦ ነበር፡፡
ኤምባሲው ይህን ካለ በኋላ በሠልፉ የሚሳተፉ ዜጎች ሰላማዊ በሆነ መንገድ መልዕክታቸውን እንዲገልጹ እንደሚያበረታታም አስታውቋል፡፡
ይሁን እንጂ የአሜሪካ ኤምባሲ ያወጣውን መግለጫ ያየው የእንግሊዝ ኤምባሲ፣ ‹‹የአሜሪካ ኤምባሲና የኢንተርናሽናል ኮሙዩኒቲ ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን እናውቃለን፡፡ ነገር ግን የእግሊዝ ኤምባሲ ሌላ ማሳሰቢያ እስካልወጣ ድረስ መደበኛ ሥራውን ያከናውናል፤›› ሲል በትዊተር ገጹ ላይ አስታውቋል፡፡ የኤምባሲው መረጃ የደረሳቸው ዓለም አቀፍ ተቋማትም ሠራተኞቻቸው ሥራ እንዳይገቡ ያደረጉ ሲሆን፣ ሌሎች ከኤምባሲው ጋር ግንኙነት ያላቸው የአገር ውስጥ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሠራተኞችም በተመሳሳይ ሥራ እንዳልገቡ ሪፖርተር ማረጋገጥ ችሏል፡፡
አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ቃል አቀባይ ኒክ ባርኔት ከሪፖርተር ጋር በነበራቸው የስልክ ቆይታ፣ በተጠቀሰው ቀን ሠልፍ እንደሚኖር አስተማማኝ መረጃ እንደደረሳቸውና በዚህ መረጃ መሠረት ኤምባሲው እንደወሰነ ገልጸው፣ ይኼንን ዓይነት ውሳኔ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ ኤምባሲው #በሕግ ስለሚገደድ በይፋ እንዳጋራው ተናግረዋል፡፡
ነገር ግን ሰዎች ኤምባሲው #ድብቅ አጀንዳ እንዳለው አድርገው እንደተመለከቷቸውና ይህ ማሳሰቢያ የዜጎችን ደኅንነት ከማስጠበቅ የዘለለ ሌላ ሚና እንደሌለው ተናግረዋል፡፡
‹‹ሠልፉ #ሰላማዊ ቢሆን እንኳን ተፅዕኖ ሊኖረው ይችላል፡፡ ሰዎች ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ላይችሉና በቤታቸውና በመሥሪያ ቤታቸው መካከል ሆነው መንቀሳቀስ ሊሳናቸው ይችላል፡፡ እኛም አገልግሎቶችን ለመስጠት እንቸገራለን፤›› ሲሉ ባርኔት አስታውቀዋል፡፡ ስለዚህ አስተማማኙ ውሳኔ ሠራተኞቻችን ቤት እንዲቆዩ መምከር ነው ብለዋል፡፡
ይሁንና በአዲስ አበባ ምንም ዓይነት ሠልፍ በሌለበት ጊዜ ኤምባሲው ይኼንን መግለጫ በማውጣቱ በርካቶች በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ሲተቹና የሐሰት መረጃ አሠራጭ ሲሉ ወቅሰዋል፡፡
ይሁን እንጂ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በአዲስ አበባ ለረቡዕ መስከረም 9 ቀን 2010 ዓ.ም. የተጠራ ምንም ዓይነት ሠልፍ አለመኖሩን አስታውቋል። መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተቋማት በአዲስ አበባ የተጠራ ሠልፍ አለ በማለት ያወጡት መረጃ ሙሉ በሙሉ #የተሳሳተም ነው ብሏል።
©ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ረቡዕ መስከረም 9 ቀን 2011 ዓ.ም. ‹‹በአዲስ አበባ ከተማ ታላቅ ሕዝባዊ ሠልፍ እንደሚኖር ተገምቷል፤›› ብሎ የኤምባሲው ሠራተኞች ከቤታቸው እንዳይወጡ፣ በተጠቀሰው ቀንም ኤምባሲው ሥራ እንደማይኖረው ገልጾ የአሜሪካ ኤምባሲ ያወጣው ማሳሰቢያ በርካቶችን ግር አሰኝቷል፡፡ ኤምባሲው ከአስተማማኝ መረጃ አረጋግጫለሁ ያለለት ሠልፍም #አልተካሄደም፡፡
ኤምባሲው በድረ ገጹ ሁሉም የቪዛ አገልግቶችና የአሜሪካ ዜጎች አገልግሎት ቀጠሮዎች ሙሉ በሙሉ መሰረዛቸውንና አሜሪካዊ ዜግነት ያላቸው ሰዎች በድረ ገጹ አማካይነት ሌላ ቀጠሮ እንዲይዙ ገልጿል፡፡ የኢሚግሬሽን ቪዛ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ሌላ ቀጠሮ ተዘጋጅቶ እንደሚጠሩና ከዚህ ውጪ ያሉ የቪዛ አገልግሎት የሚጠይቁ ሰዎች በኤምባሲው ድረ ገጽ ቀጠሮ እንዲያሲዙ አሳስቦ ነበር፡፡
ኤምባሲው ይህን ካለ በኋላ በሠልፉ የሚሳተፉ ዜጎች ሰላማዊ በሆነ መንገድ መልዕክታቸውን እንዲገልጹ እንደሚያበረታታም አስታውቋል፡፡
ይሁን እንጂ የአሜሪካ ኤምባሲ ያወጣውን መግለጫ ያየው የእንግሊዝ ኤምባሲ፣ ‹‹የአሜሪካ ኤምባሲና የኢንተርናሽናል ኮሙዩኒቲ ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን እናውቃለን፡፡ ነገር ግን የእግሊዝ ኤምባሲ ሌላ ማሳሰቢያ እስካልወጣ ድረስ መደበኛ ሥራውን ያከናውናል፤›› ሲል በትዊተር ገጹ ላይ አስታውቋል፡፡ የኤምባሲው መረጃ የደረሳቸው ዓለም አቀፍ ተቋማትም ሠራተኞቻቸው ሥራ እንዳይገቡ ያደረጉ ሲሆን፣ ሌሎች ከኤምባሲው ጋር ግንኙነት ያላቸው የአገር ውስጥ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሠራተኞችም በተመሳሳይ ሥራ እንዳልገቡ ሪፖርተር ማረጋገጥ ችሏል፡፡
አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ቃል አቀባይ ኒክ ባርኔት ከሪፖርተር ጋር በነበራቸው የስልክ ቆይታ፣ በተጠቀሰው ቀን ሠልፍ እንደሚኖር አስተማማኝ መረጃ እንደደረሳቸውና በዚህ መረጃ መሠረት ኤምባሲው እንደወሰነ ገልጸው፣ ይኼንን ዓይነት ውሳኔ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ ኤምባሲው #በሕግ ስለሚገደድ በይፋ እንዳጋራው ተናግረዋል፡፡
ነገር ግን ሰዎች ኤምባሲው #ድብቅ አጀንዳ እንዳለው አድርገው እንደተመለከቷቸውና ይህ ማሳሰቢያ የዜጎችን ደኅንነት ከማስጠበቅ የዘለለ ሌላ ሚና እንደሌለው ተናግረዋል፡፡
‹‹ሠልፉ #ሰላማዊ ቢሆን እንኳን ተፅዕኖ ሊኖረው ይችላል፡፡ ሰዎች ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ላይችሉና በቤታቸውና በመሥሪያ ቤታቸው መካከል ሆነው መንቀሳቀስ ሊሳናቸው ይችላል፡፡ እኛም አገልግሎቶችን ለመስጠት እንቸገራለን፤›› ሲሉ ባርኔት አስታውቀዋል፡፡ ስለዚህ አስተማማኙ ውሳኔ ሠራተኞቻችን ቤት እንዲቆዩ መምከር ነው ብለዋል፡፡
ይሁንና በአዲስ አበባ ምንም ዓይነት ሠልፍ በሌለበት ጊዜ ኤምባሲው ይኼንን መግለጫ በማውጣቱ በርካቶች በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ሲተቹና የሐሰት መረጃ አሠራጭ ሲሉ ወቅሰዋል፡፡
ይሁን እንጂ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በአዲስ አበባ ለረቡዕ መስከረም 9 ቀን 2010 ዓ.ም. የተጠራ ምንም ዓይነት ሠልፍ አለመኖሩን አስታውቋል። መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተቋማት በአዲስ አበባ የተጠራ ሠልፍ አለ በማለት ያወጡት መረጃ ሙሉ በሙሉ #የተሳሳተም ነው ብሏል።
©ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጥረት‼️
• በየዓመቱ 100 ሚሊዮን ብር ሲከስር ነበር፡፡
• የባንክ ዕዳውም 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡
በቀድሞው ኢህዴን (አዴፓ) በዘላቂ በጎ አድራጎት ወይም ኢንዶውመንት ቁመና ይዞ የተመሠረተው ጥረት ኮርፖሬት 20 ኩባንያዎች አሉት። ከእነዚህ ውስጥ ከሰባቱ በየዓመቱ 100 ሚሊየን ብር አካባቢ ይከስራል።
የጥረት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አምላኩ አስረስ እንደሚሉት በቀደመው አመራር ጥረት 11 ቢሊዮን ብር ጥሬ ሀብት አለው ተብሎ ሪፖርት የተደረገውም ስህተት ነው። የጥረት በአሁኑ ወቅት ያለው ጥሬ ሀብት 5 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ሲሆን 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን አካባቢ የባንክ ዕዳ አለበት። ከዚህም በተጨማሪ ካሉት 20 ኩባንያዎች በሰባት ኩባንያዎች በየዓመቱ 100 ሚሊዮን ብር ይከስራል።
ጥረት በትራንስፖርት ዘርፉ የተሠማሩ 500 ተሽከርካሪዎች አሉት እየተባለ ሪፖርት ሲደረግ ቢቆይም በተግባር ያሉት ተሸከርካሪዎች ግን 348 ናቸው። ከዚህ ውስጥ 48ቱ ብቻ ዓመት እስከ ዓመት ይሠራሉ፤ ሌሎቹ የተበላሹ ናቸው። ጥረት ከኪሳራው ለመውጣት አዲስ ፍኖተ ካርታ እያዘጋጀ ሲሆን የመዋቅር እና የአመራር ለውጥም እያደረገ እንደሆነ ዶክተር አምላኩ አስረድተዋል። አጥፊዎችም #በሕግ የሚጠየቁ ይሆናል ብለዋል።
ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
• በየዓመቱ 100 ሚሊዮን ብር ሲከስር ነበር፡፡
• የባንክ ዕዳውም 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡
በቀድሞው ኢህዴን (አዴፓ) በዘላቂ በጎ አድራጎት ወይም ኢንዶውመንት ቁመና ይዞ የተመሠረተው ጥረት ኮርፖሬት 20 ኩባንያዎች አሉት። ከእነዚህ ውስጥ ከሰባቱ በየዓመቱ 100 ሚሊየን ብር አካባቢ ይከስራል።
የጥረት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አምላኩ አስረስ እንደሚሉት በቀደመው አመራር ጥረት 11 ቢሊዮን ብር ጥሬ ሀብት አለው ተብሎ ሪፖርት የተደረገውም ስህተት ነው። የጥረት በአሁኑ ወቅት ያለው ጥሬ ሀብት 5 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ሲሆን 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን አካባቢ የባንክ ዕዳ አለበት። ከዚህም በተጨማሪ ካሉት 20 ኩባንያዎች በሰባት ኩባንያዎች በየዓመቱ 100 ሚሊዮን ብር ይከስራል።
ጥረት በትራንስፖርት ዘርፉ የተሠማሩ 500 ተሽከርካሪዎች አሉት እየተባለ ሪፖርት ሲደረግ ቢቆይም በተግባር ያሉት ተሸከርካሪዎች ግን 348 ናቸው። ከዚህ ውስጥ 48ቱ ብቻ ዓመት እስከ ዓመት ይሠራሉ፤ ሌሎቹ የተበላሹ ናቸው። ጥረት ከኪሳራው ለመውጣት አዲስ ፍኖተ ካርታ እያዘጋጀ ሲሆን የመዋቅር እና የአመራር ለውጥም እያደረገ እንደሆነ ዶክተር አምላኩ አስረድተዋል። አጥፊዎችም #በሕግ የሚጠየቁ ይሆናል ብለዋል።
ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢሶዲፓ🔝ኢህአዴግ በሕገወጥነትና በአምባገነናዊነት ያዋቀራቸው የመስተዳደር #አከላለሎች ዛሬ ለተፈጠረው የመለያየት ስሜት እና ግጭቶች ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው ሲሉ የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ ከሰሰ፡፡ መንግሥት ለዚህ ችግር አፋጣኝ መፍትሄ እንደሚፈልግም አሳስቧል፡፡ ሕዝቡ በበኩሉ ለተፈጠሩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ #በትግስትና #በሕግ አግባብ እንዲታገል ጥሪ አቅርቧል፡፡
©VOA የአማርኛው አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
©VOA የአማርኛው አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia