TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
NATO ሩስያ ላይ ዛተ። የNATO ዋና ፀሀፊው ጄንስ ስቶልተንበርግ ፤ የጥምረቱ ሀገራት ለዩክሬን የጦር መሳሪያ ድጋፍ በሚያቀርቡበት መስመር ላይ ሩስያ ጥቃት እንዳትፈፅም አጥብቀው አስጠንቅቀዋል። ሩስያ ለዩክሬን የጦር መሳሪያዎች ድጋፍ በሚቀርብበት መስመር ላይ ጥቃት ከሰነዘረች ጦርነቱ በአደገኛ ሁኔታ እንደሚባባስ አስገንዝበዋል። ስቶልተንበርግ ፤ ይህን ማስጠንቀቂያ የሰጡት እሳቸው ፣ የካንዳ ጠ/ሚ…
አሜሪካ ሩስያን አስጠነቀቀች።

የአሜሪካ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ጃክ ሱሊቫን ሩስያ በNATO አባል ሀገር በሆነችው #ፖላንድ ላይ ጥቃት ከሰነዘረች NATO ምላሽ እንደሚሰጥ አስጠንቅቀዋል።

የደህንነት አማካሪው ይህን ማስጠንቀቂያ የሰጡት ዛሬ ሩስያ በፖላንድ ድንበር አቅራቢያ በሚገኝ የዩክሬን የጦር ሰፈር ላይ የአየር ድብደባ ከፈፀመች በኃላ ነው ፤ በጥቃቱ 35 ሰዎች መገደላቸው እና 134 ሰዎች መቁሰላቸው ተነግሯል።

የአሜሪካ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ጃክ ሱሊቫን ለCBS በሰጡት ቃል በNATO ግዛት ላይ አንዳች ወታደራዊ ጥቃት ቢሰነዘር አንቀፅ 5 ወደ ትግበራ እንደሚገባና የNATO ሙሉ ኃይል ምላሽ እንደሚሰጥ አስጠንቅቀዋል።

ዛሬ ሩስያ በፖላንድ ድንበር በሚገኝ የዩክሬን ጦር ሰፈር ላይ የፈፀመችው ጥቃት ምዕራባውያን ለዩክሬን የሚያደርጉትን ወታደራዊ ድጋፍ እንዲያቆሙ ካስጠነቀቀች ከአንድ ቀን በኃላ ነው።

ምንም እንኳን ሩስያ ምዕራባውያን " አርፋችሁ ቁጭ በሉ ዩክሬንን በወታደራዊ ትጥቅ አትደግፉ " ብትልም የአሜሪካ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ሱሊቫን ሀገራቸው አሜሪካ የዩክሬን ኃይሎችን በወታደራዊ እርዳታ መደገፏን እንደምትቀጥል ዛሬ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ፤ አሜሪካ እና አጋሮቿ የNATO ግዛትን እያንዳንዱን ኢንች እንደሚከላከሉ ገልፀው " ሩሲያ በአጋጣሚ ወይም ሳታስበው ጥቃት ብታደርስ እራሱ NATO ምላሽ ይሰጣል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ሱሊቫን ፥ " የምለው ነገር ቢኖር ... ሩስያ በNATO ግዛት ላይ ጥቃት ብትከፍት፣ አንዲት ጥይት ብትተኩስ የNATO ጥምረት ምላሽ ይሰጣል " ሲሉ ነው የተናገሩት።

NB : ፖላንድ የNATO አባል ሀገር ናት።

@tikvahethiopia
👎1.54K👍93856😱37👏35😢34🥰19